ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.2K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
"ጎንደር ላይ ምሽጉ እንደ ገል ሲሰበር፡
ባንዳ ሲነፋረቅ  ጀግና ይስቅ ነበር"

በደብረታቦር ከተማ መኃል ለመኃል ሰንጥቆ የገባው ጀግናው የአፋብን ሰራዊት፣ በርካታ የጠላት ምሽጎችን ደረማምሶ ብልፅግና የተባለ ጉድፍን ከደብረታቦር አፅድቷል።

ብልፅግና የሚሉት በንፁኋን ደም የጨቀየ፣ በደሃ እምባ የረሰረሰ ሀገር አፍራሽ ቡድን ጎንደር ላይ ግብዓተ መሬቱ እየተፈፀመ ነው።

1፦ደብረታቦር፣
2፦ እብናት
3፦ አለም በር
4፦ስማዳ
5፦ እስቴ/እንዳቤት
6፦ ንፋስ መውጫ-ጋይንት
7፦ አርብ ገበያ
8፦ ሀሙሲት
9፦ ደጎማ
10 ፦አርባያ
11፦ ስላሬ
12፦ ሚካኤል ደብር
13፦ ማሰሮ ደንብ
14፦ ሰዴሙጃ
15፦ ማህደረ-ማሪያም
16፦ ገላውዴዎስ
17፦ ልጫ

እና ሌሎች አከባቢዎች በፋኖ ቁጥጥር ስር መግባታቸው የመረብ ሚዲያ የግንባር ዘጋቢዎች ለማረጋገጥ ችለዋል።
8👍2🙏1
ሰበር!...ባሕርዳር መኮድ ካምፕ!
የሰሜን ምዕራብ ዕዝን ጨምሮ የአገዛዙ ወታደራዊ ኃይል ዋና ማዘዣ ጣቢያ በሆነው መኮድ ካምፕ ውስጥ በተቀሰቀሰ ግጭት በርካታ ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ ተደረጉ!

የግጭቱ መነሻ ዛሬ የካቲት 04/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በተካሄደ ወታደራዊ የግምገማ መድረክ "በፋኖ ቁጥጥር ስር እየገቡ በሚገኙ አከባቢዎች ላይ ንፁኋንን ያነጣጠረ የድሮን ጥቃት እንዲፈፀምና በዚህም ሕዝቡ አስመታችሁን በሚል ፋኖን እንዲቃዎም ማስደረግ" የሚል መመሪያ የወረደ ሲሆን፡ "የገጠምነው ከፋኖ ጋር እንጂ ንፁኋኖች ምን አደረጉን?" በሚል መመሪያውን የተቃዎሙ የአማራ ተወላጅ የሆኑ የጦር መኮነኖች ከግምገማ መድረኩ በኋላ መረሸናቸውን የመረብ ሚዲያ ወታደራዊ ምንጮች ተናግረዋል።

ይሄንን ተከትሎ በካምፑ ውስጥ በሚገኘው ሰራዊት መካከል ከባድ የሆነ የእርስ በእርስ ውጊያ ተቀስቅሶ በርካታ ወታደሮች መገደላቸው ተሰምቷል።

በአሁን ሰዓት በካምፑ ውስጥ የአማራ ተወላጅ የሰራዊት አባላትና የጦር መኮነኖች እየተመረጡ ትጥቅ እንዲያወርዱ ተደርገው እየታሰሩ ነው።

ከዚህ በተጨማሪ ፋኖ ወደ ከተማዋ መጠጋቱን ተከትሎ ሊከዱ ይችላሉ በሚል የሚጠረጠሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን በስውር እያፈነ የሚገድል ስኳድ ቡድን በካምፑ ውስጥ ተዋቅሮ ወደ ስራ ገብቷል።

በካምፑ ውስጥ የተቀሰቀሰቀሰው የእርስ በእርስ ውጊያም ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት 8:20 ሰዓት ድረስ ተባብሶ ቀጥሏል።

"አማራዋ እናቴ ላይ የድሮን እሳት ሲዘንብ ከጠላቴ ጋር ተባባሪ አልሆንም" ያሉ በርካታ ወታደሮችም ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ለሊቱን ከወታደራዊ ካምፑ ወጥተው ጠፍተዋል።

መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!

የቴሌግራም ገፃችን👉https://t.me/MerebMedia24
4🙏1
ከየካቲት 02/06/2018 እሰከ 04/06/2018 ለተከታታይ 3ቀናት ጣና ገላውዲዎስ ከአንበሳሜ እሰከ ሐሙሲት ከተማ አድማሱን አስፍቶ በተደረገ ተጋድሎ በጠላት ከፍተኛ ኪሳራ ደርሳል የተገኘ ምርኮ
ድሽቃ 02
ብሬን 02
ክላሽ 167
አብራረው 32
አንድ ኦባ አይሱዙ ሙሉ የድሽቃ ተተካሽ
ወታደራዊ ተሽከርካሪ 6 ፖትሮል የተማረከ
የሞተ ሚኒሻ እና አድማ 45
ምርኮኛ 13
ሚኒሻ 4
ሲሆን አሁን ላይም ውጊያው ከመከላከያ ጋር እንደቀጠለ ነው።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን

አፋብን ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር ጣና ገላውዲዎስ ክ/ጦር
ህ/ግ ፋኖ ፍቅሩ ባየ
5🙏1
አንድነት በተግባር የተገለጠበት የዓምሐራ ፋኖ በደብረ ታቦር ከተማ
[የካቲት 04/2018ዓ.ም]

01 👉👉👉 13:00 ሠዓታትን የፈጀ አውደ ውጊያ በደብረ ታቦር ከተማ

የአገዛዙ አራዊት ሰራዊትን ለማምበርከክ የአፋብን ሰ/አ/ቀ በላይ ዕዝ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ለየካቲት 04/2018ዓ.ም የተጠና ዕቅድ ሲያዘጋጅ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር እና የጉና ክ/ጦር ገ/መሥቀል ብርጌድ አካል የሆነችው ጣይቱ ሻለቃ በጋራ የውጊያው ዋዜማ ከ04:00 ጀምሮ ሌሊቱን የደብረ ታቦር ከተማ ቁልፍ ቁልፍ ቦታዎችን ተቆጣጥረው ያለ ተኩሥ የአገዛዙ ወታደሮችን ሲያፈራርሥ አድሯል። ውጊያውንም ከማለዳ እሥከ ጠዋቱ 3:20 ደብረ ታቦር የከተመውን የአገዛዙ ታጣቂ በአባታቸው ውባንታዊ ሰይፍ ሲያናፍጡት አርፍደዋል። ከጠዋቱ 03:20 በኋላ የበላይ ዕዙ ግዙፍ ጉና ክፍለ ጦር እና የጠቅላይ ግዛቱ ክፍለ ጦሮች በመናበብና የውጊያ ቀጠናዎችን በመከፋፈል ጠላትን ሲያምበረክኩ ውለዋል። ከቀኑ 6:30 ገደማ ጀምሮ የ5ኛ ኮር ሰራዊት በአርበኛ ሻምበል ሙሉሰውና አርበኛ ግዛቸው አሌ የውጊያው አካል ሆኗል።

በውጊያው ተሳታፊ የሆኑ የአፋብን ሰ/አ/ቀ በላይ ዕዝ እና ጎንደር/ጠ/ግ/ዕዝ ክፍለ ጦሮች፦
👊ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክ/ጦር
👊ግዙፉ ጉና ክፍለ ጦር 05ቱም ብርጌዶች
👊የዕቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር የተውጣጣ ሰራዊት
👊የጀነራል ፋንታ በላይ ክፍለጦር የተውጣጣ ሰራዊት
👊የተራራው ራሥ ጉና ክፍለ ጦር የተውጣጣ ሰራዊት
👊የአፄ ኢያሱ ክፍለ ጦር የተውጣጣ ሰራዊት
👊የዞዝ አምባ ንጉሱ ክፍለ ጦር የተውጣጣ ሰራዊት እና
👊የጋፋት ክ/ጦር 01 ሻለቃ
👊ታሪኳን በወርቅ የደም ቀለም የጻፈችው የነበልባሉ ፎገራ ክ/ጦር አካል የሆነችው ክርሥትያን ታደለ ብርጌድ እና ከነበልባሉ ክፍለ ጦር የተውጣጡ አካላት ከወረታ እሥከ ዓለም ሣጋ የሸፈኑ

የጠላት አሰላለፍ
የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ቅጥረኞች ከ13 ወረዳ የነበረው የአድማ ብተና፣ ሚሊሻ፣ ፖሊሥና ከሁሉም ወረዳ የተሰባሰበው ከሃዲ ወዶ ገብ ነው። ከቀኑ 5:30 ጀምሮ ደግሞ
በመጀመሪያው ዙር ከባሕር ዳር የመጣ 250+ መከላከያ፣ 200+ አድማ ብተና እና 60+ ወዶ ገብ ከሐዲ የጸዳሉ አጃቢዎች ከ02 ዙ-23፣ 02 ዲሽቃ፣ 120 ሞርታር ይዞ የመጣውን
በመቀጠል ከባሕር ዳር የመጣው 54 ተሽከርካሪ መከላከያ 03 መድፍ፣ 02 ታንክ፣ ከ17 ዲሽቃዎች
3ኛ ዙር ከአርኖ ጋርኖ በ10 ተሺከርካሪ የመጣውን መከላከያ
4ኛ ዙር ከአዲሥ ዘመን የመጣውን አድማ ብተና

አፋብን ሰ/አ/ቀ በላይ ዕዝ እና ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ በጋራ በሥፋት የመጣውን የአገዛዙ አራዊት ሰራዊት መደበኛ ውጊያ ገጥመውት ውለዋል። አገዛዙ የሰራቸው የኮንክሪት ምሽጎች ተሰባብረዋል።

ተሥፋ የቆረጠው የአቢይ አሕመድ ፋሽሥት አገዛዝ ለደብረ ታቦር ከተማ 07 ድሮኖችን መድቦ ውሏል። 14 የድሮን ጥቃቶችን በደብረ ታቦር ከተማና ታቦር ዙሪያ ቦታዎች ጥሏል። ሞርታር ክርሥትያን ታደለ ብርጌድ ላይ ብቻ 23 ጊዜ ጥሏል፤ ነገር ግን የሲቪል መኖሪያ ቤቶችንና የመንግሥት ትምሕርት ቤቶች ነው ያወደመው። ነገር ግን በዚህ የድሮን ጥቃት በጅምላ የተመቱት አገር አማን ብለው የተቀመጡ የማሕበረሰቡ አካላት ናቸው። ማሰቢያውን የተቀማው የአገዛዙ አራዊት ሰራዊት ከወጂ እሥከ ደብረ ታቦር ከተማ ድረሥ 02 ዙ-23፣ ቁጥሩ ያልታወቀ ሞርታር፣ ከ17 በላይ ዲሽቃ፣ 03 መድፍ፣ 02 ታንክ እና መሰል የቡድን መሳሪያዎችን ቢይዝም ጥበበኛው የአማራ ፋኖ በክንዱ ሲያደቅቀው ውሏል።

ከ11:30 በኋላ የፀዳሉ ደሴን ወደ ዓለም በር መምጣት መረጃው የደረሳቸው የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር በፍጥነት ወደ ቦታው አምርተው ከበባ ፈጽመዋል። ፀዳሉ ደሴን መከላከያው ወደ ባሕርዳር እንዲያመልጥ ሲያደርጉ ራሳቸው ዋጋ ከፍለዋል። ምሽት 01:00 ፀዳሉ ደሴ ከመማረክ ያመለጠበት መዳኛ ሠዓቱ ሆኖ ተመዝግቧል።

ሙሉ ቀናትን በተደረገው አውደ ውጊያ ከሁሉም ሰራዊት የተማረከውን ቅጥረኛ፣ መሣሪያ፣ ተተኳሽና ቁሥ በነገው ዕለት በቪዲዮ እና በማሥረጃ የምናቀርብ ይሆናል።

02.👉👉👉ደራ ሐሙሲት
ከአገዛዙ አራዊት ሰራዊት በትናንትናው ዕለት 01 ዲሽቃ፣ ከ115+ ክላሽና አንድ ኦባማ ሙሉ የክላሽና የዲሽቃ ተተኳሽ መማረካቸው ይታወሳል። በተመሣሣይ ከትናንት የተረፈውን 01 ክላሽ በጠዋቱ ሐሙሲት ከተማ ላይ ማርከውታል።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ዝንተዓለም ዓምሐራ Forever AMHARA👊
አፋብን ሰ/አ/ቀ በላይ ዕዝ
ሜጀር ጀነራል ውባንተ ፩ኛ ኮር ሕ/ግ ክፍል
ፋኖ ኃቅአለው ፀጋ አለባቸው
2🙏1
ጀምበር የጠለቀችበትና ጣዕረ ሞት ላይ ያለው ብልፅግና የመጨረሻ ያለውን እርምጃ እየወሰደ ንፁሃንን እየጨፈጨፈ ንብረትም እያወደመ ነው።

ሽንፈቱን በተግባር የተረዳው ተረኛ ስብስብ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ነውና የቻልኩትንና ያገኘሁትን የአማራ እና አማራ አጥፍቸ ነው በማለት ሲጠፋ አመታቶች አስቆጥሯል።ዛሬ ግብዓተ መሬቱ ሲቃረብ ደግሞ በክፋትላይ ክፋት በጭካኔ ላይ አረመኔዊነቱን በንፁሀን ላይ እያሳየን ይገኛል።በዛሬው እለት ደቡብ ወሎ ወረኢሉ ወረዳ ላይ የሶስት አርሶ አደሮች ቤት ከነሙሉ ንብረቱ ቤንዚን አርከፍክፎ ያቃጠለ ሲሆን ቤት ንብረታቸው የተቃጠለባቸው አርሶደሮች ፦

1. አቶ አያሌው አህመድ ሁለት ቆርቆሮ ቤት
2. አቶ አሊ ይማም ሶስት ቆርቆሮ ቤት
3. አቶ ከበደ ማህሙድ ሁለት ቆርቆሮ ቤት

የሶስቱም አርሶደሮች ከነሙሉ ንብረቱ በሀገር አፍራሹ የብልፅግና ራሱን ጥምር ጦር ብሎ የሰየመ የአብይና ሽመልስ አማራን የማጥፋት፣የማቆርቆዝና የማዳከም ልዩ ተልኮ የተሰጠው ተላላኪ ቡድን አማራ መቸም የማይረሳውና ይቅር የማይለው ነውር እየፈፀመ ይገኛል።

በመጨረሻም ከፋሽስቱ ብልፅግና አገዛዝ ጋር ሆናችሁ ወገናችሁ የአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየፈፀማችሁና ቤት ንብረት እያወደማች ያላችሁ ሃይሎች ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በመረዳት ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡና ከህዝብ ጎን እንድትቆሙ ስንል መልክታችንን እናስተላልፋለን!

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምኒልክ ዕዝ ልጅ እያሱ ኮር የጎፍ ክፍለ ጦር
የካቲት 4/2018 ዓ.ም
3💔1
ኑ ጠላትን በጋራ ታግለን የአማራን ህዝብ ሕልውና እናረጋግጥ!
የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተላለፈ የምህረት አዋጅ
ሀ) መግቢያ:
አረመኔው የብልፅግና አገዛዝ የአማራን ህዝብ ህልውና አደጋ ላይ ለመጣል የጀመረውን ጦርነት ለማሳካት ይችል ዘንድ በርካታ አረመኔያዊ ተግባራትን ሲፈፅም መቆየቱ ይታወቃል።
የአማራን ህዝብ ያለ ልዩነት ለመፍጀት አቅሙ የፈቀደውን ሁሉ እየተጠቀመ ያለው አገዛዝ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ጂኦ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎቶችን በማገልገል በፈጠረው የማውደም አቅም ተማምኖ በከፈተው ጦርነት ራሱ እየተለበለበበት ይገኛል።

የአማራን ህዝብ ለማጥፋት ከሚጠቀምባቸው ስልቶች መካከል ነባሩን የብአዴን መዋቅር በመጠቀም ባሰባሰበው የምሊሻ እና የአድማ ብተና ኃይል ከፋኖ ጋር እንዲዋጋ እና ህዝባችን በሁለት ጎራ ተሰልፎ እንዲጠፋፋ የሞከረበት መንገድ አንደኛው ነው።
በአንድ ህዝብ መካከል እና በኢትዮጵያዊያን መካከል እንዲሁም ቀጠናዊ ጦርነቶችን በማስነሳት ለአፍሪካ ቀንድ የቀውስ ዘበኛ የሆነውን አገዛዝ በወንድማማችነት እና በጥበብ በማስወገድ የጋራ መንግስት መመስረት እንደሚገባን በተደጋጋሚ ጥሪወች ስናስተላልፍ የቆዬን መሆኑ ይታወቃል።
በተለይም ከሰሞኑ ደግሞ ጠላት በአንድ በኩል የህዝብ መገናኛ መስመሮችን በመዝጋት ንፁሃን ላይ ጭፍጨፋ እያደረገ በሌላ በኩል ደግሞ ብሔራዊ አጀንዳ ያለው እና ለሀገር ብሔራዊ ተልዕኮ የተሰለፈ በመምሰል የሚያደርገውን የማደናገሪያ ስልት በንቃት በመከታተል የፋኖ ሰራዊት በወሰዳቸው እርምጃወች ወራሪው የብልፅግና ኃይል ከፍተኛ ትርምስ ውስጥ ገብቷል።
የድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ መወለድ ያስገኘው የአንድነት መንፈስ ለተገኙ ወታደራዊ ድሎች ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። የድላችን ምስጢር ያለው አንድነታችን ላይ መሆኑም በተግባር ተረጋግጧል። ድርጅታዊ አንድነታችንን በጠበቀ መልኩ ከኢትዮጵያዊያን እና ከቀጠናው ኃይሎች ጋር የሚደረግ ትብብር አገዛዙን ሙሉ በሙሉ ለማስወገድ ወሳኝ ሂደት መሆኑ ግልፅ ነው። ህዝባዊ ዓላማችንን የተጋራን ጋር በመርህ የምናደርገው ትብብር እና አንድነት የአረመኔውን አገዛዝ እድሜ ለማሳጠር ትልቅ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው።
ይህንን ተከትሎ ባቀረብነው ወገናዊ ጥሪ በርካታ የአገዛዙ አገልጋይ የነበረ ምሊሻ፣ አድማ ብተና እና የመከላከያ ኃይል የወገንን ኃይል እየተቀላቀለ ይገኛል።
ስለሆነም ዛሬም አገዛዙን በማገልገል ላይ ለምትገኙ የምሊሻ፣ የአድማ ብተና፣ የመደበኛ ፖሊስ፣ መከላከያ እና በሌሎች የአገዛዙ ታጣቂ አደረጃጀቶች ውስጥ ላላችሁ ተመሳሳይ ጥሪወችን እናስተላልፋለን።
ይህንን ጥሪ ያስተላለፈው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ስራ አመራር በጉዳዩ ላይ በዝርዝር ተወያይቶ ጥሪዉን በመቀበል ወገናቸውን ለመካስ ለሚፈልጉ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት እና የካድሬ መዋቅር የምህረት አዋጅ አውጇል።
ለ) የምህረት አዋጁ የተላለፈላቸው የአገዛዙ መዋቅር አካላት:-
፩) በየደረጃው የሚገኙ የብልፅግና አመራር አባላት
፪) ምሊሻ፣ ሰላም አስከባሪ እና በሌላም ስያሜ ብልፅግና ያደራጃቸው ታጣቂወች
፫) የክልል አድማ ብተና እና መደበኛ ፖሊስ አባላት
፬) በሀገር መከላከያ ሰራዊት ስም በየቀጠናው የተሰማሩ እግረኞች እና የአገዛዙ መኮንኖች
ሐ) የምህረት አዋጁን ማውጣት ያስፈለገበት ምክንያት
ሶስት ዓመታትን ሊደፍን ጥቂት ጊዜ በቀረው የጦርነት ሂደት በግልፅ መገንዘብ እንደሚቻለው የብልፅግና መዋቅር በአማራ ህዝብ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ድቀት ላይ ስልጣኑን ከማራዘም ያለፈ ለአማራ ህዝብ የሚጠቅም አንድም አጀንዳ የሌለው በመሆኑ የአማራ ህዝብ እንደ ህዝብ በተለያዬ ጎራ የተሰለፍን የአማራ ልጆችም እንደ የአንድ እናት ልጆች በመቀናጀት የህዝባችንን ህልዉና ማስጠበቅ ከእኛ የሚጠበቅ ተግባር ነው። በመሆኑም:-
፩) ለአማራ ህዝብ ሁለንተናዊ መብት እና ነፃነት እንጅ ለአብይ አህመድ ወንበር መፅናት የሚወድቅ የአማራ ወጣት መኖር ስለሌለበት፤
፪) ህዝባችንን በጅምላ ለሚጨፈጭፍ አገዛዝ በማገልገል የዘቀጠ ታሪክ ውስጥ ራስን ከማግኘት ይልቅ ለነፃነቱ የሚዋደቅን ኃይል በመቀላቀል ደማቅ ታሪክ መፃፍ ታሪክ የጣለብን ግዴታ በመሆኑ፤
፫) ህዝብን ታግሎ ያሸነፈ አገዛዝ እንደሌለው ሁሉ አብይ አህመድም የአማራን ህዝብ ማሸነፍ ስለማይችል እና በተሸናፊነት ለሚያጠናቅቀው ብልፅግና በመላላክ እና በራስ ወገን ላይ በመተኮስ የታሪክ፣ የህሊና እና የፍትህ ተጠያቂነትን ከማስተናገድ ለመዳን ሲባል፤
፬) አገዛዙን በጋራ ታግለን በማሸነፍ ለህዝባችን ሰላም ማምጣት የትውልዱ ግዴታ በመሆኑ፤
፭) እንዲሁም የምንታገለው ለአማራ ህዝብ ህልውናና መዳን እንደመሆኑ መጠን የፋኖ ትግልም የአማራ ህዝብ ትግል ስለሆነ በሁሉም ጎራ ላሉ አማራዊ ወንድሞች ጥሪ ማድረግ እና ማታገል የድርጅታችን ተልዕኮ በመሆኑ፤
ይህንን የምህረት አዋጅ በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ስራ አመራር ውሳኔ መሰረት ለህዝብ ይፋ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
መ) የምህረት አዋጁ አተገባበር
፩) የምህረት አዋጁ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ካላይ በተራ ቁጥር "ለ" ስር የተዘረዘሩት የምሊሻ፣ አድማ ብተና፣ መከላከያ እና ሌሎች የታጠቁ የብልፅግና ኃይሎች እንዲሁም በየደረጃው ያሉ አመራሮች በየአካባቢያቸው ላለው የድርጅታችን መዋቅር እና ለዚህ ጉዳይ በተቋቋመው ግዜያዊ ግብረ ኃይል በአካል ቀርበው ሪፖርት ያደርጋሉ።
፪) ምህረት ጠይቀው ወገናቸውን ለመካስ የሚመጡ ግለሰቦች የአካል ደህንነት ዋስትና ይሰጣቸዋል። በተዘጋጀላቸው ማረፊያ የተሃድሶ ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋል።
፫) ለትግል አገልግሎት ከሚዉል የጦር መሳሪያን ጨምሮ ማንኛውም የምህረት ጠያቂወች ንብረት በባለቤቶች እጅ ይቆያል።
፬) ምህረት የተደረገላቸው ግለሰቦች ድርጅቱ ባዘጋጀው ፎርም መሠረት ለአማራ ህዝብ ነፃነት ሊሰሩ ካልተቻለም ከጠላት ወገን ላይሰለፉ ቃለ-መሃላ ይፈፅማሉ።
፭) አቅሙ እና ፍላጎቱ ያላቸው የምህረት ተጠቃሚወች የወገንን ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር ተቀላቅለው ለህልዉና ተጋድሎው የበኩላቸውን ድርሻ ይወጡ ዘንድ በሌላ ማናቸውም ለህዝብ ጠቃሚ በሚሆኑ ተልዕኮወች ላይ ይሰማሩ ዘንድ ድርጅቱ ሁኔታወችን ያመቻቻል።
፮) ይህ የምህረት አዋጅ ከዛሬ የካቲት 04 ቀ 2018 ዓ.ም ላሉት ተከታታይ 15(አስራ አምስት ቀናት) ብቻ ተፈፃሚ ይሆናል።
ሠ) የምህረት አዋጁን በማስፈፀም የሰራዊታችን እና የድርጅታችን አመራር ግዴታ
፩) የምህረት አዋጁን አፈፃፀም ለመከታተል በማዕከል የተቋቋመው ግብረ ኃይል የመመሪያዉን አተገባበር ይከታተላል፤ መረጃወችን ይሰጣል፤ መፍትሔ ያስቀምጣል።
፪) የድርጅቱ መዋቅር አመራር እና ሰራዊቱ ለምህረት ጠያቂወቹ የአካል ዋስትና መስጠትን ጨምሮ በእንክብካቤ በማስተናገድ በፍፁም ጨዋነት አዋጁን ይተገብራል።
፫)በአፈፃፀም ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ወዲያውኑ ለግብረኃይይሉ ያሳውቃል፣ የተሰጠዉን የመፍትሔ አቅጣጫ ይተገብራል።
፬ በግል ቂም ቁርሾ ወይም በሌላ ግላዊ እና ቡድናዊ ፍላጎቶች ምክንያት ከዚህ አዋጅ በተቃረነ መንገድ በማንኛውም ምህረት ጠያቂ ላይ አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ማድረስ ወይም ንብረት መቀማት ፍፁም የተከለከለ ተግባር ነው።
🙏1
፭) የዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌወችን እና መርሆወችን እንዲሁም ዓለም አቀፍ የጦር ህግጋትን የተከተለ አሰራር ይተገበራል።
፮) ይህንን አዋጅ ጥሶ የተገኘ ማንኛውም የድርጅቱ አመራር እና አባል ወይም ሌላ አካል ከባድ ቅጣት ይጠብቀዋል።
ረ) የሕዝቡ፣ የሀገር ሽማግሌወች እና የኃይማኖት አባቶች ሚና
በየቀጠናው ያለው ህዝብ፣ የሀገር ሽማግሌወች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ ምሁራን እና ሌሎች ተሰሚነት ያላቸው ግለሰቦች በጠላት የፀጥታ እና የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ያሉ ግለሰቦች በዚህ አዋጅ መሰረት አፈሙዛቸውን ወደ ዋናው ጠላት እንዲያዞሩ ካልሆነም ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲኖሩ እና የአማራው ኃይል ፍፁም ህብረት እንዲኖር የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ይጠበቃል።
በመጨረሻም የአማራ ልጆች በጋራ ተባብረን ህዝባችንን ሊያጠፋ የተነሳውን ጠላት እናስወግድ ዘንድ አንድነት እና ህብረት ያስፈልገናል እና ወደ አማራ የምንተኩሰው ጥይት እንዳይኖር እና አንድ ጠላት ላይ ብቻ አነጣጥረን እናሸንፍ ዘንድ ኑ እንላለን።

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ
👍2🙏1
ፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና ከየ አቅጣጫው ወደ ጦርነት ሊገባ መሆኑን የተገነዘበው ሰራዊቱ እየፈረሰ ፋኖን እየተቀላቀለ ይገኛል::

ከዚህ ጋር ተያይዞም የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 49ኛ ክፍለ ጦር የሆኑ አምስት አባላት ከኦህዴድ ብልፅግና ጋር ሆነን ወገናችንን አንወጋም በማለት ምስራቅ አማራ ኮር 1 አሳምነው ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል:: ክፍለ ጦሩም አቀባበል አድርጎላቸዋል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ትግላችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
የካቲት 5/2018 ዓ.ም
3🙏1
የህዝብ ሃብት የሆኑ መሬቶች በብልፅግናው አገዛዝ ባደባባይ እየተዘረፉ መሆኑን ነዋሪዎች በማስረጃ እያጋለጡ ቀጥለዋል::

ጀምበር የጠለቀችበትና ተስፋ የቆረጠው ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ የህዝብ ሃብት መዝረፉን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን የሰሜን ወሎ ዞን ወልድያና ቆቦ ከተማ ካድሬዎችም የከተሞቹን የህዝብ ሃብት ባደባባይ እየዘረፉ መሆኑን ነዋሪዎች በማስረጃ እያጋለጡ ይገኛሉ::

ከዚህ ጋር ተያይዞም ባለፈው ጊዜ ቆቦ ከተማ ሁለገብ አዳራሽን ሸጠው የተከፋፈሉ ሆድ አደርና አገር አፍራሽ የዞንና የወረዳ ካድሬዎች እንዲሁም የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት አመራሮች በማስረጃ የተጋለጡ መሆኑ ይታወሳል:: ጉዳዩም በፍርድ ቤት ተይዞ የህዝብ ሃብት የሆነው ቆቦ ሁለገብ አዳራሽ ተመላሽ እንዲሆን ተወስኖ እንደነበር ከፍርድ ቤት ያገኘነው ማስረጃ ይናገራል::

ስለሆነም አሁንም ዘረፋው ተጠናክሮ ቀጥሎ ከዚህ በታች በማስረጃ የተዘረዘሩት የወልድያ ከተማ እና የቆቦ ከተማ መሬቶች ለጦርነት አላማ ሊውሉ ጥርና የካቲት/2018 ዓ.ም በወጣ የጨረታ ማስታወቂያ ለሽያጭ መቅረባቸውን የከተሞቹ ህዝብ ባደረሰን ማስረጃ አረጋግጠናል::

ወልድያ ከተማ በክልሉ ከፍተኛ የህዝብ ሃብት የሆኑ መሬቶች የሚዘረፉበት ከተማ ሲሆን ባለፉት ሶስት አመታት ድሃ የቀበሌ ነዋሪዎችን በማፈናቀል የአገዛዙ ሹማምንቶች እንደተከፋፈሉትና ዛሬም ተጠናክረው እንደቀጠሉበት ከህዝብ የደረሰን ማስረጃ ያሳያል::

ቆቦ ሁለገብ አዳራሽ ባለፈው ጊዜ ሰማኒያ ሚሊየን ብር እና ከዛ በላይ ተሽጦ ገንዘብ ሲካፈሉ ተጣልተው በፍርድ ቤት ትዛዝ ገንዘቡ ለገዥ ተመላሽ ከሆነ በኋላ እንደገና ለጨረታ የቀረበ ሲሆን እነዚህና ሌሎች ለጊዜው በስም ያልተጠቀሱ የህዝብ ሃብት የሆኑ መሬቶች የአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየፈፀመ ላለው የብልፅግና አገዛዝ ለጦርነቱ አላማ ለማዋል እየተዘረፉ በህገወጥ ጨረታ ለገበያ መቅረባቸውን ነዋሪዎች በማስረጃ አስደግፈው አድርሰውናል::

በመጨረሻም ለመላው ህዝባችን ምኒልክ ዕዝ ከሚያዚያ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ ያፀደቀውን መመሪያውን መሰረት በማድረግ የህዝብ ሃብት ጊዜውን ጠብቆ ለህዝብ መሆኑና መመለሱ አይቀርምና ተስፋ የቆረጠው አገዛዝ ካድሬዎች የጦር መሪዎች ስግብግብ ነጋዴዎችና ህገወጥ ደላላዎች ተቀናጅተው ከሚሰሩት የመሬት ወረራና ዘረፋ ባለመሳተፍ ሃብታችሁን እንድትጠብቁ ብሎም ከህልውና ትግሉ ጎንም እንድትቆሙ ስንል ዛሬም እንደ ትላንቱ መልክታችንን እናስተላልፋለን!

*ማስታወሻ፦ ምኒልክ ዕዝ በሁሉም የወሎ ቤተ-አማራ አካባቢዎች በአገዛዙ እየተዘረፉ ያሉ የህዝብ ሃብቶችን የሚከታተልና ማስረጃ የሚይዝ ህቡዕ (ስውር) አደረጃጀት እንዳለው ለህዝብ ማሳወቃችን የሚታወስ ነው::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምኒልክ ዕዝ
የካቲት 5/2018 ዓ.ም
2🔥2