ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.2K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
ምኒልክ ዕዝ ንጉስ ሚካኤል አሊ ኮር መብረቅ ክፍለ ጦር ጋር የተፋለሙት 11ኛ ዕዝ እና የአየር ወለድ ኮማንዶ ዕዝ አባላት ድባቅ ተመቱ!

በምዕራብ ወሎ ግንባር ወግድ ወረዳ ውስጥ በ2 ጄኔራሎች የተመራ ለተከታታይ ሁለት ቀናት የዘለቀ ከባድ ውጊያ የተካሄደ ሲሆን በዚህ ውጊያ በርካታ የጠላት ኃይል ተደምስሷል::

2 መድፍ፣ 2 ሞርተር 120፣ 4 ዙ-23 እና ከ60 በላይ በሚሆን ተሽከርካሪ የተጫነ እግረኛ ሰራዊትን በመያዝ የ11ኛ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜ/ጄኔራል ዘውዱ ሰጣርጌ እንድሁም የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ኮር 2 አዛዥ ብ/ጄኔራል ሞሲሳ ቶሎሳ በምዕራብ ወሎ ግንባር ወግድ ወረዳ ውስጥ በርካታ ቀጠናዎችን የሸፈነ ውጊያ ቢከፍቱም የአፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር መብረቅ ክፍለ ጦር ሰራዊት ባካሄደው የመልሶ ማጥቃት ውጊያ የወገን ኃይል ድል ቀንቶታል::

በማከፍታ ቀጠና ሰኮሩ ታዳጊ ከተማ አቅራቢያ የሚገኘውና ታሪካዊው የበላይ ዘለቀ ምሽግ የሚገኝበት ቦታ ላይ ጭምር ከፍተኛ ተጋድሎ የተደረገ ሲሆን የጠላት ኃይል ላይ መጠነ ሰፊ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሷል:: ከበላይ ዘለቀ ምሽግ በተጨማሪ በጎረንጅ፣ ጎለሌ፣ ሸመኔ እና ሌሎች አካባቢዎች ውጊያ ሲካሄድ ውሎ አድሯል::

ወግድ ወረዳ ውስጥ እየተካሄደ ባለው ውጊያ መሃል ከባድ ሽንፈት የገጠመው አገዛዙ ለፋኖ መረጃ ሰጥታችኃል የተባሉ ሁለት የብልፅግና አመራሮች እና ንፁሓን መታሰራቸውንም ለማረጋገጥ ችለናል::

በዚህም መሰረት:-

1ኛ. አብይ አያሌው የወረዳው ብልጽግና የፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊ
2ኛ. እንዳልካቸው አቢ የወረዳቅ ኦድት ኮሚሽን ኃላፊ

3ኛ. አረቡ ቀዮ የተባለ ባለሀብት

4ኛ. ተሰፋዬ ጀማል የተባለ የቡና ባንክ ጥበቃ እና ሌሎች ንፁሓን በዛሬው ዕለት ታፍነው ታስረዋል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ምኒልክ ዕዝ
ጥር 27/2018 ዓ.ም
3🙏1
በስቦ መምታት የውጊያ ታክቲክ የጠላት ብልፅግና ወታደርን ወሽመጥ በመቁረጥ ውጤታማ ድል ተመዘገበ!

በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ምስራቅ አማራ ኮር 1 ባለሽርጡ ክፍለጦር ላይ ጥቅታ ለማድረስ ከጉቢሳ ወደ ኮለቦ፣ ከጭሰ አባሊማ ወደ ሲልኮ፣ከጊራና ወደ ጉባ ፣ከመርሳ ወደ ሀብሩና ፋጂ የተንቀሳቀሰው የጠላትን ሀይል በቀን 26/05/2018 ከኮለቦና ሩጋ ያለውን የጠላት ሀይል ስቦ በማስገባት መነዮ ቀሊና ላይ ምሽት 1:30 ላይ የጠላትን ሀይል ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ተጎናፀፈ።

የባለሽርጡ ክፍለጦርን ሊያጠቃና የክፍለጦሩን ነባር ይዞታዎች ሊወር የመጣው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት በአምስት አቅጣጫ ለማፈን ቢሞክርም የጠላትን የጥፋት እቅድ ቅዠት በማድረግ 50 ሙትና 78 ቁስለኛ በማድረግ ከትላንት ከጥዋቱ 12:30 እስከ ዛሬ 27/05/2018 ዓ.ም በቆየ አውደ ውጊያ የጠላትን ከበባ ያለምንም መስዋዕትነት በአርበኛ እንድሪስ ጉደሌና በሌሎች በሳል የክፍለጦሩ ወታደራዊ ጠበብቶች በመስበር በጥላት ላይ ከፍተኛ ስብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረስ ተችሏል።

በዚህ አውደ ውጊያ የተበሳጨው የጠላት ሀይል በደቡብ ወሎ ዞን ተወለደሬ ወረዳ ሲልኮ እየተባለ በሚጠራው ቦታ 450 የሚደርሱ ወጣቶችን፣ አርሶ አደሮችን እና የቀን ሰራተኛዎችን በማፈን ስልጠና ሰልጥናችሁ አገራችሁን ትጠብቃላችሁ በሚል ሰበብ ወደ ማጓሪያ ቀጠና አስገብቶ ፋኖን ማረኩ በሚል የሀሰት ዶክመንተሪ ዝግጂት ላይ ይገኛል።
በተያያዘም በሀይል ላፈናቸው ንፁሀን በየቤቱ እየገባ የግል ታጣቂ ግለሰቦችን መሳሪያ ለማስወረድ ድንገተኛ ፍተሻና ድብደባ እያካሄደ ይገኛል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበር ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ምኒልክ ዕዝ
ጥር 28/2018 ዓ.ም
3🙏2
አፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ አሳምነዉ ኮር እሸት ክፍለ ጦር ከአዉደ ዉጊያ ጎን ለጎን ጥልቅ ተሐድሶ አደረገ!!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)  ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ በግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ስር የሚገኘው እሸት ክፍለ ጦር ለተከታታይ ሶሰት ቀናት በጥልቀት ከገመገመ በኋላ ሁሉን አቀፍ ተሐድሶ ካደረገ በኃላ የአመራር ሪፎርም ስራ ሰርቷል ።

በተሐድሶው ላይ የተገኙት የምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ም/ወታደራዊ አዛዥ እና የላስታ አሳምነዉ ኮር ሰብሳቢ አርበኛ ወንድሙ ማሩ ፣የላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ስትራቴጅክ ጉዳዮች ኃላፊ አርበኛ ተመቸ ቢራራ እና ሌሎች የኮር አመራሮች ተገኝተዉ ለሰራዊቱ አቅም ግንባታና ማበረታቻ የሰጡ ሲሆን ሰራዊቱም የነበሩባቸውን ጥቃቅን ክፍተቶች እንደሞሉበት ታውቋል።

እሸት ክፍለ ጦር ወቅቱን የዋጄ በግዳጅ አፈፃፀም የላቀ ሰራዊት እየገነባ ያለ ክፍለ ጦር ሲሆን ከተራ ተዋጊ አባል እስከ ክፍለ ጦር መሪ ቅልቅልና አዲስ አደረጃጀት በመስራት ለቀጣይ ግዳጅ በወትሮ ዝግጁነታቸው እንደሚገኙ አስታውቀዋል።

በመጨረሻም የተመደቡት አመራሮች ይህን የተጣለብነን አደራ በአግባቡ ተወጥተን የአማራን ህዝብ የተደቀነበትን የህልዉና አደጋና ዘርፈ ቡዙ ችግሮች አላቀን አማራ በማንነቱ እማይሸማቀቅበት እና ሁሉን አካታች ይምትሆን ሀገረ መንግስት እንደምንገነባ ቃል እንገነባለን ሲሉ ቃለ መሃላ ፈፅመዋል።

በዚህ ጥልቅ ተሐድሶ የክፍለ ጦሩ አመራሮች እንደሚከተለዉ ተዘርዝረዋል።

1.የክ/ጦር አዛዥ..... መቶ አለቃ በሪሁን ደምሌ
2. የክ/ም/አዛዥ ..... አርበኛ ፍቃድ አበባዉ
3. የክ/ጦር ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ.......አርበኛ ደሰላ ወንዴ
4. የክ/ጦር ወታደራዊ አስተዳደር ኃላፊ.........10 አለቃ አንደበት ወንድምነዉ
5. ዘመቻ ኃላፊ.............አርበኛ ኮስትር አሸነፍ
6 . ሕ/ግንኙነት ኃላፊ......... መቶ አለቃ ደስታዉ አንባዉ
7. ፋይናስ አርበኛ ዮሐንስ አዱኛዉ (ጆን)
8. የሰዉ ሃይል አርበኛ ቡግሳ ተስፋ
9. ስልጠና ክፍል ኃላፊ ......አርበኛ ጌትነት አለምነዉ
10. ሎጀስቲክ ኃላፊ.......አርበኛ እያያዉ ደረሰ
11. ህግ ክፍል ኃላፊ.........አርበኛ ጌታሁን ወዳይ
12. ጤና መምሪያ ኃላፊ......አርበኛ አበበ ሞላ
13. መረጃና ደህንነት         .............. አርበኛ XXXX

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒሊክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ደረበ መኮንን!!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 29/2018 ዓ.ም
👍4
ሰበር የድል ዜና!!!

የአገዛዙ ወንበር አስጠባቂ ጥምር ሰራዊት በቋራ ምድር ተደመሰሰ

የመይሳው ካሳ 2ኛ ኮር 4ኛ ቀኑን ያስቆጠረ እልህ አስጨራሽ አውደ ውጊያዎችን በቀጠናው እየተፋለመ ከፍተኛ ድል እያስመዘገበ ይገኛል። በትናንትናው እለት ጥር 28/2018 ከሌሊቱ 8:00 ስአት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ስአት ቋራ ወረዳ አባድግሱ ከምትባል ቦታ የተሰራው ጀብድ በአገዛዙ ግብስብስ ሀይል ላይ ከፍተኛ ሽንፈትን እንዲያስተናግድ አድርጓል።በመይሳው ካሳ 2ኛ ኮር ሰብሳቢ አርበኛ ማንዴላ እያዩና በኮሩ ከፍተኛ አመራሮች የተመራው ይህ አውደ ውጊያ ጠላትን ከበባ ውስጥ በማስገባት ክፉኛ ሲርበተበት ውሎ ያመሸ ሲሆን የፋኖ ሰራዊት አሰላለፍ: አድዋ ክ/ጦ ከጀርባ በስተምዕራብ ፣ የኮሩ ተወርዋሪ ከፊታውራሪ ገበየሁ ክ/ጦ ከተውጣጡ ሰራዊቶች ጋር በመሆን በቀኝ በኩል ፣ ኦሜድላ ክ/ጦ ነብሮ ብርጌድ በግራ በኩል እና ካራማራ ክ/ጦ አሳምነው ብርጌድ ከጠላት ፊት ለፊት ሆነው የተሰለፉ ሲሆን ፤ ይህ የፋኖ አሰላለፍ ያስደነገጠው የአገዛዙ የብርሀኑ ጁላ ደም መጣጭ ሰራዊት በጭንቀት መውጫ መግቢያ ሲያጣ በአንድ በኩል ከፊት ለፊት ለመውጣት ሙከራ ቢያደርግም የበረሀው ፈርጦች የአሳምነው ልጆች ወይ ፍንክች በማለት ትንቅንቁን አፏፉመውት የጠላት ሀይል ነብስ ውጭ ነብስ ግቢ ሆኖበት አዳሩን በእሳት አለንጋ ሲለበለብ አድሮ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ያልቻለውን በየቦታው እያዝረከረከ በየቦታው የድረሱልኝ ጥሪውን እየቀባጠረ ወደ መጣበት ወደ ፋርሽዋ ሊመለስ ችሏል።

በዚህ አውደ ውጊያ የአገዛዙ ከፍተኛ አመራሮች 50 አለቃ ማዕረግ ያለው እስከ ወዲያኛው የተሸኘ ሲሆን በየቦታው ያዝረከረከውን አስክሬን የፋኖ ሰራዊት የአካባቢውን ማህበረሰብ በማስተባበር ሊቀብር ችሏል።

በዚህ ልዩ ኦፕሬሽን የተገኘ ድል:
ሙት = 36
ቁስለኛ = 45
የተማረከ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ = 12
1የዲሽቃ አፈሙዝ
ተተኳሽ = 650 የክላሽ

በዚህ አንድ ሳምንት ከአገዛዙ ጥምር ሰራዊት ጋር በሚደረገው እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ አገዛዙ ከሽንፈት የማያድነውን የኔት ወርክ መዝጋት ዘመቻ እንደ አንድ አማራጭ በማድረጉ በግንኙነት ማነስ ከህዝብ ጀሮ ያላደረስናቸው አውደ ውጊያዎች የሚከተሉት ናቸው:

1.ጥር 26_27/2018 የአድዋ ክ/ጦ በጋዝጌ ቀጠና ሮብ ገበያ እና ኤረፍት በተደረገው የሁለት ቀን አውደ ውጊያ የአገዛዙ የመከላከያ ሰራዊት ተብየው እና ጋሻአጃግሬው ሚኒሻ ክፉኛ ሽንፈትን አስተናግዷል።

በዚህ አውደ ውጊያ የአገዛዙ ጥምር ሰራዊት መነሻውን ሰሜን አቸፈር ሊበን ተነስቶ ወደ ጋዝጌ ቀጠና አርሶአደሩን ትጥቅ ለማስፈታት እና ሁለንተናዊ ጀኖሳይድ ለመፈፀም አስቦ ቢንቀሳቀስም የመይሳው ካሳ ፪ኛ ኮር አድዋ ክ/ጦ በተደረገው እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ ከፍተኛ ኪሳራን ከማስተናገዱ ባሻገር ከበባ ውስጥ ገብቶ እጅ መስጠት ሲጀምር በሁለት አቅጣጫ ከጃዊ ጃይማላ እና ከአለፋ ሻሁራ ተጨማሪ ሀይል ደርሶ ሊያስለቅቀው ችሏል።

በሁለት ቀን አውደ ውጊያ የተገኘ ድል: ከ20በላይ የታሰሩ ንፁሀን አርሶአደር መሳሪያ አላችሁ አስረክቡ በማለት በግፍ የታሰሩትን ማስፈታት ተችሏል። ከዚህ በተጨማሪ የአገዛዙ ሰራዊት ሙት እና ቁስለኛ እንደሚከተለው ይሆናል።
ሙት = 30
ቁስለኛ =ከ38 በላይ
5 ምርኮኛ ሰራዊት
የነፍስ ወከፍ መሳሪያ = 10
ከ3000በላይ ተተኳሽ
የአንድ ሬጅመንት ሙሉ የእጅ ስልክ


2.ስቦ በመምታት ኦፕሬሽን ከአድዋ ክ/ጦ ፣ ከፊውታራሪ ገበየሁ ክ/ጦ እና ከኮሩ ተወርዋሪ በተውጣጡ የፋኖ ሀይሎች የአገዛዙ ሰራዊት ከአባድግሱ ወደ ባርባስ ወደ ምትባል ገዥ ቦታ ለኩሶ ወደ ኃላ በመውጣት የሙት ወረዳ ላይ/ባርባስ ጥር 26/2018 ከቀኑ 9:00 ስአት ጀምሮ ለ2ስአት ያህል በተደረገው አውደ ወጊያ የጠላት ሀይል ኩምሽሽ ብሎ ሙት እና ቁስለኛ በመሆን እንደ ገና ወደ ኃላ አባድግሱ ወደ ምትባል ቦታ ሊመለስ ችሏል።

በዚህ አውደውጊያ የተገኘ ድል:
ሙት = 5
ቁስለኛ = 12

3.በአዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ ነጋዴ ባህር ከተማ አቸራበር በፊታውራሪ ገበየሁ ክ/ጦ ታጠቅ ብርጌድ 2ኛ ሻለቃ ቃኝ በሆነችው ሻንበል1 አንድ አስደማሚ ኦፕሬሽን ተደርጓል።

ለአገዛዙ ሰራዊት አጋር የሆነው ሆድ አደር ሚኒሻ መነሻውን ከጭልጋ ወረዳ ወደ ነጋዴ ባህር ሲንቀሳቀስ ቀድመው መረጃን በማፈንፈን የሻለቃዋ ቃኝ በፍጥነት ደፈጣ በመያዝ በሚኒሻው ላይ መብረቃዊ ጥቃት በማድረስ ከቦታው መሰወር ችላለች።

በዚህ ልዩ ኦፕሬሽን የተገኘ ድል:
ሙት = 5
ቁስለኛ = 8
5 የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እስከ መሉ ትጥቁ

ይህ በእንዲህ እንዳለ ፈርጣጩ የአብይ ወንበር አስጠባቂ ጥምር ሰራዊት በማፊያ አመራሮች እየተመራ ፋኖን እናፅዳ እያለ እራሱ እየፀዳ የሀገሪቱን ወጣት በስሜት በሀገር መከላከያ ስም እየነገደ አማራ ላይ የተሰጠውን የአውሬውን ተልእኮ ለመፈፀም ቢሞክርም ከመጥፋት ግን አላዳነውም፤ የሀገሪቱን እንቁ ሀብት እያግበሰበሰ የወጣቱን ደም እየለገሰ በስልጣን መቆየት እንደማይቻል ክንደ ብርቱው የፋኖ ሰራዊት የሚያስመዘግበው ውጤት ማሳያ ነው።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
አፋብን ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ ፪ኛ ኮር
ጥር 29/2018
🙏61
ከአዉደ ዉጊያ ጎን ለጎን የሜጀር ጄኔራል ውባንተ አባተ ክፍለ ጦር በመቄት ጥልቅ ተሐድሶ አደረገ!!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ በግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ስር የሚገኘው ሜጀር ጄኔራል ውባንተ አባተ ክፍለ ጦር በመቄት ከጥር:-26 ጥር:- 28/05/2018 ዓ/ም ለተከታታይ ሶሰት ቀናት በጥልቀት በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል ።

በተሐድሶው ላይ የተገኙት የሜጀር ጄኔራል ውባንተ አባተ ክፍለጦር ዋና አዛዥ አርበኛ ኮማንዶ አማን ጎበዜ ፣ምክትል አዛዥ አርበኛ ሸጋው ወርቄ ጉድለቶቻችን በማረም ቀጣይ ግዳጆችን በብቃት መፈፀም አለብን ብለዋል።
የወረዳው ጊዚያዊ ህዝብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ ፋኖ መምህር በሪሁን ደምሌ በበኩሉ ወታደሩ በየወቅቱ አቅሙን እያሳደገ አቅዶ ጠላትን መምታት እንዳለበት ገልፆ የህዝብ ጉዳይን የህዝብ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ቀጣይም አቅሙን አጠናክሮ ህዝብን በቅን ልቦና ያገለግላል ብሏል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 29/2018 ዓ.ም
🙏3
ባለሽርጡ ክፍለ ጦር የሃብሩ ወረዳ ካድሬዎችን ያጀበ የፋሽስቱ ብልፅግና አገዛዝ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ጋር ተጋድሎ በማድረግ ድል አስመዘገቡ::

የአገዛዙ ካድሬዎች ህዝብን በስብሰባ ለማደናገርና የሃሰት ቅስቀሳ ለማድረግ ብሎም ፀረ-ህዝብና አገር አፍራሽ ተልዕኳቸውን ለማስፈፀም ወደ ሰሜን ወሎ ዞን ሃብሩ ወረዳ ልዩ ስሙ 032 ቀበሌ ኮሎቦ በብልፅግና መከላከያ ታጅበው ህዝብ ሊሰበስቡ ባሰቡበት ሁኔታ ከባለሽርጡ ክፍለ ጦር በደረሰባቸው ያላሰቡት ድንገተኛ ጥቃት ብትንትናቸው ወጥቶ ወደ መርሳ ከተማ ተመልሰዋል::

ባለሽርጡ ክፍለ ጦር ቀጠናውን በመቆጣጠር የህዝብ አስተዳደር መዋቅር ዘርግተው እያስተዳደሩት ያለ ሲሆን አገዛዙ ብልፅግና ምንም አይነት መፈናፈኛ እንዳያገኝ በማድረግና በተደጋጋሚ ጊዜ ክንዳቸውን በማቅመስ ዛሬም ድላቸውን አስቀጥለዋል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ትግላችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 29/ 2018 ዓ.ም
🙏3
የሚኒሻ አባሉ ፋኖን ተቀላቀሉ አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ የማደርሰውን ግፍ አይተናል ከዚህ በኋላ የዚህ ስርዓት ተባባሪ ሁነን ህዝባችን ላይ በደል ማድረስ የለብነም በማለት ትናት የበደልነውን ህዝብ ፋኖን በመቀላቀል አሰከፊውን ስርዓት ለማስወገድ በአቅራባችን ያለውን ጣና ብርጌድ በመቀላቀል ህዝባችን
እክሳለን ብለዋል ።
1ኛ መሀበው ማራለም ከአንበሳሜ ከተማ ሚኒሻ የነበረ
2ኛ ሰውመሆን ካሳሁን ሐሙሲት ከተማ ሚኒሻ
የያዙት የትጥቅ ዓይነት
1ክላሽ
1 አብራረው ይዘው በመውጣት ፋኖን ተቀላቅለዋል
አፋብን ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር ጣና ገላውዲዎስ ክ/ጦር ህ/ግ ፍቅሩ ባየ
🙏63
አፋብን ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር ጣና ገላውዲዎስ ክ/ጦር አሀድ የሆነችው ጣና ብርጌድ ሻለቃ አንድ ናሁ ሰነይ ሻለቃ ለወራት በአድማ ብተና ተይዞ የነበረውን የገጠር ከተማ የሆነችውን ጉማራ ላይ ጥር 30/05/2018 ከምሽቱ 1:00ሰዓት እሰከ 3:00 ሰዓት በተደረገ እልህ አስጨራሽ ውጊያ ምሽጉን ለቆ ወደ ሐሙሲት ከተማ ሲፈረጥጥ በጣላት ላይ ከባድ ጉዳት ማድረስ ተችላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን

አፋብን ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ1ኛ ኮር ጣና ገላውዲዎስ ክ/ጦር ህ/ግ
ፍቅሩ ባየ
🙏3
የደጋው መብረቅ ኮር ቀኛዝማች ተበጀ ወርቁ ክፍለ ጦር ለሶስተኛ ዙር በርካታ እግረኛ ፋኖዎችን በደማቅ ሁኔታ አስመረቁ::

አፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የደጋው መብረቅ ኮር ቀኝአዝማች ተበጀ ወርቁ ክፍለ ጦር ለበርካታ ወራቶች ሲያሰለጥናቸው የነበሩትን ፋኖዎች የካቲት 1/2018 ዓ/ም የኮሩ አመራሮች በተገኙበት መድረክ ላይ አስመርቋል!

ቀኝአዝማች ተበጀ ወርቁ ክፍለ ጦር በርካታ እግረኛ ፋኖዎችን ለሶስተኛ ዙር ያስመረቀ ሲሆን በዚህ የምርቃት ስነ-ስርዓት ላይ የደጋው መብረቅ ኮር የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አርበኛ ብርሃን አረጋ በመክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ የእንኳን ደሳላችሁ መልክት ያስተላለፉ ሲሆን "የአማራ ህዝብ የብረት አጥር ናችሁ!! የአማራን ህዝብ ጥላት የሚያጠቃው በእናተ አስከሬን ላይ ተረማምዶ ነው። ስለዚህ እናተ የአማራ ህዝብ መታፈሪያና መከበሪያ የብረት አጥር ናችሁ!" በማለት ለተመራቂዎች መልክት ያስተላለፈ ሲሆን::

የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አርበኛ መኩሪያ አጋዡ(መምህሩ) "እናተ አማራ ናችሁ! በአማራዊ የሞራል ልዕልና ቁማችሁ የተገኛችሁ!" በማለት ለተመራቂዎች መልክት አስተላልፈዋል።

የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ አርበኛ በለጠ መኩሪያው በበኩላቸው ለተመራቂ ፋኖዎች የአማራን ህዝብ ነፃ የማውጣት ሀላፊነት የዚህ ተመራቂ ጭምር ነው ሲሉ ለተመራቂዎች አሳስበዋል።

በዚሁ የምርቃት ስነ ስርዓት ላይ የአሰልጣኞች ምስጋናና እየፈፀሙት ላለው ህያው ገድል የሽልማት ፕሮግራም የተበረከተ ሲሆን፤ይህ የአሰልጣኞች ማነሻሻ የምስጋና እውቅና ለቀጣይ የተልዕኮ መሰላል ይኖን ዘንድ ታስቦም የተደረገ ነው።

እየተዋጋን እንሰለጥናለን እየሰለጠን እንዋጋለን!

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ምኒልክ እዝ
የካቲት 1/2018 ዓ.ም
🙏3