ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.21K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
ሰበር መረጃ - የወልድያ ዙሪያ ትንቅንቅ | ደረሳዎች ላይ ያነጣጠረው የውጫሌው አፈሳ | የደብረብርሃንና ጎንደር ዙሪያ አውደውጊያ
🙏1
ካላኮርማ ክፍለ ጦር ጉባላፍቶ እና ራያ ቆቦ ወረዳ በሁለት ግንባር ከባድ ውጊያ በማካሄድ ድል አስመዘገቡ::

ምስራቅ አማራ ኮር 2 ካላኮርማ ክፍለ ጥር 5/2018 ዓ.ም ጦር ጉባላፍቶ ወረዳ በቅሎ ማነቂያ እና ራያ ቆቦ ሮቢት ከተማ በሁለት ግንባሮች ከባድ ውጊያ በማካሄድ በርካታ ጥምር ዙፋን ጠባቂ አገር አፍራሽ የጠላት ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል አስመዝግበዋል::

ካላኮርማ ክፍለ ጦር 2ኛ እና 3ኛ ሻለቃ ከእንጃፋት ወንዳች ኩልመስክና ድልብ የመጣንና በቅሎ ማነቂያን ይዞ ወደ ቃሊም ማጥቃት ያደረገን ጠላት ባግባቡ መክተው በመዋልና በርካታ ሰራዊቱን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ብሎም ምሽግ ያደረገውን በቅሎ ማነቂያ ከተማና ዙሪያውን በማስለቀቅ ወታደራዊ ገዥ መሬት መቆናጠጥም ችለዋል::

በሌላኛው ግንባር ካላኮርማ ክፍለ ጦር 1ኛ እና 4ኛ ሻለቃ እንዲሁም የ5ኛ ሻለቃ ቃኝ ጥር 5/2018 ዓ.ም ቀትር አካባቢ ጀምሮ ራያ ቆቦ ሮቢት ከተማ ድረስ ዘልቀው በመግባት በርካታ የፋሽስቱ አገዛዝ ጥምር ሰራዊት ላይ ከባድ ጥቃት በማድረስ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ጀብድ ፈፅመው ድል አስመዝግበዋል::

በዚህም የምስራቅ አማራ ኮር ሁለቱ ካላኮርማ ክፍለ ጦር በሁለት ግንባሮች ከባድ ተጋድሎ በማድረግ ቃሊምና ወልድያ ዙሪያ ከባድ ትንቅንቅና ተጋድሎ ካደረጉት ከምስራቅ አማራ ኮር አንድ አሃዶች ጋር የተናበበና የተቀናጀ ሚዛን ጠባቂ ግዳጅ በመፈፀም አመርቂ ድል አስመዝቧል::

የፋኖን ክንድ መቋቋም ያቃተው የፋሽስቱ ብልፅግና አገዛዝ ጥምር ሰራዊት ራያ ቆቦ ሮቢት ከተማ ያልታጠቁ ንፁሃን አማራዎችን በግፍ ረሽኗል:: መረጃውን በዝርዝር ለህዝብ ይፋ የምናደርግ ይሆናል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 5/2018 ዓ.ም
👍2
ሐውጃኖ ክፍለ ጦር ወልድያ ዙሪያ እና ቃሊም በመካናይዝድና በድሮን የታገዘ የጠላት ሃይል ጋር ተጋድሎ በማድረግ ታላቅ ድል አስመዘገቡ::

​የሐውጃኖ ክፍለ ጦር ጥር 5/2018 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ ከአሳምነው ክፍለ ጦር ጋር በመጣመር ከባድ ትንቅንቅና ተጋድሎ በማድረግ በጠላት ላይ የተለመደውን ገድላቸውን በመፈፀም ታላቅ ድል ተቀዳጅተዋል::

የአብይ አህመድ የዙፋን ጠባቂ ሰራዊት በድሮን፣ በመድፍ፣ በታንክና በሞርታር ታግዞ የከፈተውን መጠነ ሰፊ ጥቃት የሐውጃኖ አንበሶች በላቀ ወታደራዊ ጥበብ መክተው በማክሸፍና ከባድ መልሶ ማጥቃት በማድረግ ጠላትን አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::

​ጥር 5/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 የተጀመረውና እስከ ምሽቱ 3:00 ሰዓት ድረስ ለ13 ሰዓታት ያህል ያለማቋረጥ ሲካሄድ የዋለውና ጠላት በመቶዎች ሙትና ቁስለኛ እንዲሁም ምርኮኛ በሆነበት እጅግ ከባድ ፍልሚያ በሐውጃኖ ክፍለ ጦር ሙሉ የበላይነት ተጠናቋል።

በታሪካዊው የአውደ ውጊያ ግንባር ጀግናው የሐውጃኖ ክፍለ ጦር በአርበኛ ካሳ አበበ እና በምክትሉ አርበኛ ደሳለኝ መራጊያው እየተመራ ከምስራቅ አማራ ኮር አንዱ መንትያው አሳምነው ክፍለ ጦር ጋር ጎን ለጎን ተሰልፎ በቃሊም ሚጦ በኩል ባደረገው ከባድ ማጥቃት፣ በከፍተኛ ዘመናዊ ትጥቅ የታገዘውን የጠላት ኃይል በከበባ ውስጥ አስገብቶ እንደ ቅጠል አርግፎት ውሏል::

​በዚህ ታሪካዊ ፍልሚያ የተገኙ ድሎች፦
👉​የሰው ኃይል ኪሳራ፦ በጠላት ወገን ላይ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሙትና ቁስለኛ ተመዝግቧል። በሐውጃኖ ክፍለ ጦር እና አሳምነው ክፍለ ጦር ጥምረት በመቶዎች የሚቆጠር ጠላት ሙትና ቁስለኛ ብሎም ምርኮኛ ሆኗል::

​የተማረኩ ትጥቆች፦
👉​ 8 ክላሽ
👉​1100 የሚደርስ የተለያየ አይነት ተተኳሽ
👉20 የክላሽ ካዝና
👉5 የሞርተር ቁንቡላ
👉የሰው ሃይል ሙሉ ዶክሜንት

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 5/2018 ዓ.ም
1🙏1
የራያ ቆቦ ወርቄ የአገዛዙ ሚሊሻዎች በራያ ሮቢት ሶስት በመግደልና አምስት በማቁሰል ስምንት ጦር መሳሪያ ያልታጠቁ ንፁሃን አማራዎችን በግፍ ጨፈጨፉ::

የፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና አገዛዝ ጋር በመወገን የአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየፈፀሙ ያሉት የራያ ወርቄ ሚሊሻዎች በትናትናው ዕለት ጥር 5/2018 ዓ.ም ከብልፅግና መከላከያ ጋር ሆነው ካላኮርማ ክፍለ ጦር ጋር ባደረጉት ውጊያ በደረሰባቸው ከባድ ሽንፈት ሸሽተው ወደ ሮቢት ከተማ በመግባት ስምንት ያልታጠቁ ንፁሃን አማራዎችን በጥይት ጨፍጭፈዋል::

በነፃነት ታጋዩ ፋኖ ሲሸነፉ ፈሪ ሁሌም አህያውን ትቶ ዳውላውን ነውና እነዚህ ህዝቡ በአደባባይ የሚያውቃቸውና ነገን በተስፋ እየጠበቀ በፍፁም ትግስት የያዛቸው ህዝብን ከህዝብ የማፋጀት አላማ ያነገቡ የወርቄ ታጣቂዎች ራያ ቆቦ ሮቢት ከተማ ገብተው ንፁሃንን በግፍ ሲጨፈጭፉ አገዛዙም የሚፈልገው ድርጊት በመሆኑ በዝምታ ማየትን መርጧል::

እነዚህ ፀረ-አማራ ታጣቂዎች ስራቸው የሚመዘዘው ከኦህዴድ ብልፅግና ሲሆን የተሰጣቸውን ሃይማኖትን መሰረት አድርጎ ህዝብን ከህዝብ የማጋጨት አላማ አንግበው ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ንፁሃን ያልታጠቁ አማራዎችን በግፍ እየጨፈጨፉ ቀጥለዋል::

በዚህም በትናትናው ዕለት ጥር 5/2018 ዓ.ም ራያ ቆቦ ሮቢት አቶ ሽመልስ ሲሳይ የተባለ ጋሪ እየገፋ በቀን ስራ የሚተዳደር ግለሰብ እና ሁለት ወንድና ሴት (ትግስት እና አያሌው መለሰ) የተባሉ የሆቴል አስተናጋጆችን በጥይት ደብድበው ሲገድሉ አምስት ተጨማሪ በማቁሰል ባጠቃላይ ስምንት ንፁሃን ያልታጠቁ አማራዎች ላይ ጥቃት ፈፅመዋል::

ከዚህ ግፍ በተጫማሪም ፀረ-አማራ ሚሊሻዎቹ ሮቢት ከተማ የተለያዩ ሱቆችንና የንግድ ቦታዎችን ንብረት ዘርፈው መሄዳቸውን ከከተማው ነዋሪዎች ለማረጋገጥ ችለናል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 6/2018 ዓ.ም
🙏1
በመካነሰላም ግንባር የ45ተኛ ክፍለ ጦር አንድ ቲም የሚሆኑ አባላት ተደመሰሱ!!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር ኢንጅነር ደሳለኝ አሰፋ ክፍለ ጦር ሰራዊት ሰሞኑን ለተከታታይ ቀናት በተደረገ ግምገማ መሰረት የአመራር ሪፎርም ከተደረገለት በኃላ በትናንትናው እለት በመካነሰላም ግንባር ድል ቀንቶታል:: ከመካነሰላም ከተማ በመነሳት ወደ ሰኞ ገበያ አቅጣጫ ተንቀሳቅሶ በወገን ኃይል ላይ ጉዳት ለማድረስ ተኩስ የከፈተውን ጠላት በመልሶ ማጥቃት ጉዳት ያደረሱበት የኢንጅነር ደሳለኝ አሰፋ ክፍለ ጦር 1ኛ ጥላሁን ፈንታው ሻለቃ እና 2ተኛ ጌታሰው አስረስ ሻለቃ ፋኖዎች አንድ ቲም የሚሆኑ ወታደሮችን ሲደመስሱ 3 አቁስለዋል::

ኢንጅነር ደሳለኝ አሰፋ ክፍለ ጦር አዛዥ አርበኛ ስንደው ገዜ እና የክፍለ ጦሩ ወታደራዊ ስልጠና ዘርፍ ኃላፊ ኮማንዶ ጀንበሩ ጌታቸው በመሩት በትናንቱ ኦፕሬሽን ያልታሰበ ጉዳት የደረሰበት የጠላት ኃይል በከፍተኛ ሁኔታ ተደናግጦ ስለነበር የወረዳው ካቢኔ አባላት ጭምር ከተማይቱን ለቀው ሜዳ ላይ ማደራቸው ተርጋግጧል:: የተደመሰሱ አባላቱን አስከሬን በ3 አምቡላንስ ጭኖ መካነሰላም ከተማ ወደሚገኘው ጁኒየር ትምህርት ቤት የወሰደው ጠላት ጁኒየር ትምህርት ቤትን ካምፕ አድርጎት መክረሙ አንሶት እንደ መካነ-መቃብር እየተጠቀመው መሆኑ ይታወቃል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም
1🙏1
በአውደ ውጊያ በፋኖ የተሸነፈው ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ ቃሊም ዙሪያ የድሮን ጥቃት በመፈፀም ጦር መሳሪያ ያልታጠቁ ንፁሃን አማራዎችን ጨፈጨፈ::

ጥር 5/2018 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ 13 ሰዓት በፈጀ ከባድ ውጊያ በርካታ እግረኛ ሰራዊቱ በከበባ የተመታበት ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ ከወልድያ ከተማ በቅርብ ርቀት የምትገኘው ቃሊም ከተማ ዙሪያ ስድስት ጊዜ የድሮን ጥቃት በመፈፀም ንፁሃን ጦር መሳሪያ ያልታጠቁ አማራዎችን ህይወት ቀጥፏል:: የተወሰኑትም ቀላልና ከባድ ቁስለኛ ሲሆኑ በእንስሳቶች እንዲሁም ቤትና ንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል::

በድሮን ጥቃቱ አንድ የቤተክርስቲያን ጠባቂ አባትን ጨምሮ የሌሎችም ህይወት ሲያልፍ ቀላልና ከባድ ቁስለኞችም መኖራቸውን ለማረጋገጥ ችለናል:: ሌሎች ንፁሃኖችም ከወልድያ ከተማ በሚወነጨፍ መድፍ ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ቀላልና ከባድ ቁስለኛ የሆኑም አሉ:: መድፉ በእንስሳቶችና በቤት ንብረት ላይም ከባድ ጉዳት አድርሷል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 6/2018 ዓ.ም
👍1🙏1
64ኛ ክፍለ ጦር ሶስት ቀን የፈጄ የስራ ስምሪት ግምገማ አካሔደ።

የአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች እና የእነማይ ወረዳ እና የሸበል በረንታ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች የክፍለ ጦሩ የአንድ ወር የስራ ስምሪት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አድረጓል።

የውይይት መድርኩን የመሩት የአፋብኃ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የቴዎድሮስ ዕዝ ም/ል ሰብሳቢ እና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አርበኛ አስረስ ማር ዳምጤ፣ አርበኛ ጥላሁን አበጄ እንዲሁም የክ/ጦሩ ዋና ሰብሳቢ ፋኖ ጥላሁን ሽፈራው ሲሆኑ በክፍለ ጦሩ የአንድ ወር የስራ ቸክ ሊስት የተሰጡ ስራዎችን በማገማገም ለአመራሩ ወታደራዊ እና ፓለቲካዊ ግንዛቤዎች በሰፊው ተሰጥተዋል።

በስራ ቸክ ሊስቱ በወታደራዊ ፕወዛ፣ ወታደራዊ ስራዎች፣ በፋይናስ አሰባሰብ፣ በፍትህ አሰጣጥ፣ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና መሰረተ ልማት፣ በህዝብ ንቅናቄ የውይይት መድርኮች፣ በአስተዳደር ፀጥታ እና ተተኪ አመራር የማብቃት ስራዎች ላይ የክፍለ ጦሩ እና የወረዳው ጊ/መንግስት አመራር በሰፊው በመወያየት ድርጅቱ በእየ ዘርፉ የሰጠውን የስራ ሐላፊነት ገምግመዋል።

አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
            
@አፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክፍለ ጦር ሕዝብ ግንኙነት
🙏31
በድሮን ጥቃት ከ105 በላይ የአገዛዙ ሚሊሻዎችና ንፁሃን ወገኖች በበለሳ ተገደሉ!!  

     በቅርቡ በዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ጥር 01/2018 ዓ.ም  ከባድ ድምሰሳ ሽንፈት የተጎነጨው የአብይ ሰራዊት የሞራል ማካካሻ የአየር ጥቃት ለማድረስ በማቀድ ከሰሞኑ በሳህላ እና በበለሳ ቀጠና ተደጋጋሚ የአየር ቅኝት እያደረገ የሰነበተ ሲሆን በዛሬው ዕለት ጥር 07/2018 ዓ.ም ረፋድ ዋግ ህምራ ዞን ሳህላ ወረዳ ሰየም ድልድይ የተባለ ቦታ በርካታ የራሱ የአገዛዙ ቅጥረኛ የሚሊሻ ዓባላትና ተገደው የተሰበሰቡ ንፁሃን ወገኖቻችንን የሰው አልባ አይሮፕላን (ድሮን) ጥቃት አድርሶባቸዋል።

  እስከ አሁን በደረሰን መረጃ ከ65 በላይ የሚሊሻ ዓባላት የሞቱ ሲሆን ከ40 በላይ ንፁሃን ወገኖች በአየር ጥቃቱ የህይወት መስዕዋትነት እንደከፈሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ቁጥራቸው ያልተረጋገጠ  ቁስለኛ መሆናቸውም ታውቋል።

      የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል በላይ ዕዝ የሰራዊት ዓባላትን ለማጥቃት ሲቃጥት የሰነበተው አገዛዙ በዛሬው ዕለት የአካባቢውን ሚሊሻና ንፁሃን ወገኖችን እጅግ አሳዛኝ በሆነ ሁኔታ በጅምላ ጨፍጭፏቸዋል።

    በቀጣይ መረጃዎችን ለህዝባችን በይፋ እየተከታተልን የምናሳውቅ ሁኖ የንፁሃን ወገኖቻችንን ዘግናኝ ጭፍጨፋ በአገዛዙ ላይ በማነጣጠር የአፀፋ ምላሽ እንደምንሰጥ እያሳወቅን በጅምላ የአየር ጥቃት ህይወታቸው ላለፈ ወገኖቻችን በላይ ዕዝና ጎንደር ጠ/ግዛት ዕዝ በሚንቀሳቀሱበት የሰሜን አማራ ቀጠና (ጎንደር) በቀጣይ ቀናት ለሰማዓት ወገኖቻችን የሚመጥኑ ህዝባዊ የሀዘን አዋጅ ሊታወጅ እንደሚችል እናሳውቃለን።

       ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
@አፋብኃ በላይ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ
2
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒልክ ዕዝ ም/ወታደራዊ አዛዥ እና የላስታ አሳምነዉ ኮር ሰብሳቢ አርበኛ ወንድሙ ማሩ በወቅታዊ ጉዳይ አጠር ያለ መግለጫ!

የምኒልክ ዕዝን ክንድ መቋቋም ያቃተው ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ ከተግባር ይልቅ "ውሸት"ን ትልቅ የአውደ ውጊያ ግንባር ካደረገው አመታቶች የተቆጠሩ ሲሆን ዛሬም አጠናክሮ ቀጥሎበት በአፋብኃ ምኒልክ ዕዝ ስም የሃሰት መግለጫ እያወጣ ይገኛል::

በመሆኑም እኔን እና የአሳመነዉ ኮር ም/አዛዥ የሆነዉን ኮማንዶ ፍቅሩ ሙልዬን ከአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ከሚኒልክ ዕዝ በድርጅቱ ትዕዛዝ እንደታገድን አድርገዉ ምላሱ ብቻ የቀረዉ የብልፅግናዉ አገዛዝ በትላንታናዉ ዕለት የማስመሰል መግላጫ አዉጥቷል።

እንኳን በወሬ ልንፈታ እና ልንደነግጥ ቀርቶ ድሮኑን እና ታንኩንም አልፈራንም እናም በመላዉ ዓለም ለምትገኙ አማራዊያን እና የትግላችን ደጋፊዎች ይህ የአገዛዙ የዉሸት መግለጫ መሆኑን እንድታዉቁ እና አሁን ላይ እኔም ሆንኩ ኮማንዶ ፍቅሩ ሙልዬ የተጣለብንን ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጣን እንገኛለን።

እናንተም በውሸታችሁ ቀጥሉ እኛም በሐቀኛ ተግባራችን! በያዝናቸው አመርቂ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ድሎቻችን ታጅበን ለመጨረሻው ግብ ድልና ነፃነታችን እየታገልን እንገኛለን::

ግፈኞች ሆይ ጦራችሁም ወሬያችሁም አይፈታንም:: አላማችንንም ላፍታም ቢሆን አያደናቅፈውም!

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒልክ ዕዝ ም/ወታደራዊ አዛዥ እና የላስታ አሳምነዉ ኮር ሰብሳቢ አርበኛ ወንድሙ ማሩ!!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥር 7/2018 ዓ.ም