ይህ ትግል በአሸናፊነት የሚደመደመው በመሣሪያ ብዛት ብቻ ሳይሆን፣ በያዝነው የሞራልና የሰብአዊነት የበላይነት ነው።
የፍቅር ጥይት፤ ለአገዛዙ ወንበር የመጣኸው ወታደር ሆይ፣ በሕዝብ እቅፍ ውስጥ መሆንህን ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።
በነፃነትና በሕልውና ትግል ግንባሮች ላይ የምናየው ትዕይንት፣ ዓለምን የሚያስደንቅና የትግላችንን መንፈሳዊ ልዕልና የሚያሳይ ነው። አንተ! ወደህም ይሁን ተገደህ የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም፣ ሕዝብን በድሮንና በከባድ መሣሪያ እንድትጨፈጭፍ ታጥቀህ የመጣህ ወታደር ዙፋን ጠባቂ ወታደር ነበርህ።
ነገር ግን፤ የተማረክህ ዕለት የገጠመህ ሞት ሳይሆን ሕይወት ነው፤ በጥላቻ የታወረ አፈሙዝ ሳይሆን በፍቅር የተዘረጋ የሕዝብ እጅ ነው። አንተ! ልትገድለው፣ ቤቱን ልታፈርስና ልጆቹን ልታሳጣ የመጣኸው ይኽ "ጠላት" ያልከው ሕዝብ፤ ዛሬ የቆሰለ አካልህን በጨርቅ እየጠቀለለ ያክምሃል። ጥይት ልታጎርሰው የመጣኸው ሕዝብ፣ ካለው ጥቂት ጉርሻ አከፋፍሎ አብልቶሃል።
ይህ ተግባር ትግላችን ከወንበርና ከጥቅም በላይ መሆኑን የሚያሳይ ከፕሮፖጋንዳ ያለፈ ድንቅ ተግባር ነው። እኛ የምንዋጋው የሥርዓቱን ግፍ እንጂ የአንተን ማንነት አይደለም። ደጋግመን እንደተናገርነው፣ ትግላችን የጥላቻ ሳይሆን የነፃነት፣ የፍትሕና የእኩልነት ነው። ዓላማችን፤;እኩልነት የጠፋባትን፣ ፍትሕ የራቃትንና በንጹሐን ደም የምትታጠበውን ሀገር ነፃ ማውጣት ነው። አገዛዙ አንተን ለሥልጣኑ "መሣሪያ" አድርጎ ሲጠቀምብህ፣ እኛ ግን እንደ "ሰው" እናከብርሃለን። አንተን መግደል ሳይሆን አንተ ጋር የተሸረበውን የባርነት ሰንሰለት መበጠስ የትግላችን አካል ነው።
እንደወትሮው ሁሉ ዛሬም የምናስተላልፈው መልዕክት! በየግንባሩ ያላችሁና ለአገዛዙ ጥላቻ ተሰልፋችሁ የምትገኙ ወታደሮች ሆይ፤ አስተውሉ! ጠላታችሁ ማን ነው? ጠላታችሁ የተራባችሁ ዕለት የሚያበላችሁ፣ የተጠማችሁ ዕለት ውኃ የሚያጠጣችሁ ይህ የዋህና ጀግና ሕዝብ ነውን? በገዛ ወገኑ ላይ ድሮን የሚያዘንብ አገዛዝ ወይስ የቆሰለ ምርኮኛን የሚያክም ሕዝብ የትኛው ነው ለሀገር የሚቆረቆረው?
ለአገዛዙ ሰራዊት የቀረበ የሕሊና ጥያቄ፤ ወታደር ሆይ! ይህን ፎቶ በጥልቀት ተመልከተው፤ የታጠቀው ማን ነው? አንተ የጥፋት መሣሪያ ታጥቀህ መጣህ፤ አርሶ አደሩ ግን የሕይወት መሣሪያ የሆነውን "እንጀራ" ይዞ ቀረበልህ። ጠላትህ ማን ነው? አዛዦችህ "ሽፍታና ጽንፈኛ" ብለው ሊያስገድሉህ የላኩህ ሕዝብ፣ ዛሬ በረሃብ እንዳትዝል የላብ እህሉን እያቀረበልህ ነው። ለማን ትሞታለህ? አንተ ቆስለህ ስትማረክ ጀርባውን የሰጠህ አገዛዝ ወይስ የቆሰለ አካልህን አክሞ ያበላህ ሕዝብ የትኛው ነው ለክብርህ የሚመጥነው?
ይህ ትግል በአሸናፊነት የሚደመደመው በመሣሪያ ብዛት ብቻ ሳይሆን፣ በያዝነው የሞራልና የሰብአዊነት የበላይነት ነው። አፈሙዝ ታጥቀህ ልትገድለው ብትመጣም፣ ሕዝባችን በፍቅርና በሰብአዊነት ይዞሃል። ይህ ፍቅር ነገ ለምትፈጠረው አዲስና ፍትሐዊት ኢትዮጵያ መሠረት ነው።
ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ማውቅ ያለበት ዋና ነገር፤ ይህ ትግል የሁለት ታጣቂዎች ሽኩቻ አይደለም። ይህ ትግል በግፈኛ አምባገነንነት እና በሰብአዊነት መካከል ያለ ግብግብ ነው። አገዛዙ በንጹሐን ላይ ድሮን ሲያዘንብ፣ የነፃነት ኃይሎችና ሕዝቡ ግን ለምርኮኞች የጄኔቫን ስምምነት (Geneva Convention) በላቀ ሁኔታ በተግባር እየተረጎሙት ይገኛሉ።
ዓለም ሊያውቀው የሚገባው ሀቅ ቢኖር፣ በኢትዮጵያ ምድር ፍትሕንና ሰላምን ሊያመጣ የሚችለው አፈሙዙን ለሰው ልጅ ክብር ዝቅ የሚያደርገው በፋኖ ኃይል እንጂ፣ ሕዝቡን እንደ ጠላት ፈርጆ የሚጨፈጭፈው አምባገነን ሥርዓት አለመሆኑን ነው።
ጥላቻን በፍቅር እናሸንፋለን!
ትግላችን ለፍትሕ፣ ለእኩልነትና ለነፃነት ነው!
ክብር ለሰብአዊነት ዘብ ለቆመው ሕዝባችን!
አዲስትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ!
ታህሳስ 28/2018ዓ.ም
የፍቅር ጥይት፤ ለአገዛዙ ወንበር የመጣኸው ወታደር ሆይ፣ በሕዝብ እቅፍ ውስጥ መሆንህን ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።
በነፃነትና በሕልውና ትግል ግንባሮች ላይ የምናየው ትዕይንት፣ ዓለምን የሚያስደንቅና የትግላችንን መንፈሳዊ ልዕልና የሚያሳይ ነው። አንተ! ወደህም ይሁን ተገደህ የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም፣ ሕዝብን በድሮንና በከባድ መሣሪያ እንድትጨፈጭፍ ታጥቀህ የመጣህ ወታደር ዙፋን ጠባቂ ወታደር ነበርህ።
ነገር ግን፤ የተማረክህ ዕለት የገጠመህ ሞት ሳይሆን ሕይወት ነው፤ በጥላቻ የታወረ አፈሙዝ ሳይሆን በፍቅር የተዘረጋ የሕዝብ እጅ ነው። አንተ! ልትገድለው፣ ቤቱን ልታፈርስና ልጆቹን ልታሳጣ የመጣኸው ይኽ "ጠላት" ያልከው ሕዝብ፤ ዛሬ የቆሰለ አካልህን በጨርቅ እየጠቀለለ ያክምሃል። ጥይት ልታጎርሰው የመጣኸው ሕዝብ፣ ካለው ጥቂት ጉርሻ አከፋፍሎ አብልቶሃል።
ይህ ተግባር ትግላችን ከወንበርና ከጥቅም በላይ መሆኑን የሚያሳይ ከፕሮፖጋንዳ ያለፈ ድንቅ ተግባር ነው። እኛ የምንዋጋው የሥርዓቱን ግፍ እንጂ የአንተን ማንነት አይደለም። ደጋግመን እንደተናገርነው፣ ትግላችን የጥላቻ ሳይሆን የነፃነት፣ የፍትሕና የእኩልነት ነው። ዓላማችን፤;እኩልነት የጠፋባትን፣ ፍትሕ የራቃትንና በንጹሐን ደም የምትታጠበውን ሀገር ነፃ ማውጣት ነው። አገዛዙ አንተን ለሥልጣኑ "መሣሪያ" አድርጎ ሲጠቀምብህ፣ እኛ ግን እንደ "ሰው" እናከብርሃለን። አንተን መግደል ሳይሆን አንተ ጋር የተሸረበውን የባርነት ሰንሰለት መበጠስ የትግላችን አካል ነው።
እንደወትሮው ሁሉ ዛሬም የምናስተላልፈው መልዕክት! በየግንባሩ ያላችሁና ለአገዛዙ ጥላቻ ተሰልፋችሁ የምትገኙ ወታደሮች ሆይ፤ አስተውሉ! ጠላታችሁ ማን ነው? ጠላታችሁ የተራባችሁ ዕለት የሚያበላችሁ፣ የተጠማችሁ ዕለት ውኃ የሚያጠጣችሁ ይህ የዋህና ጀግና ሕዝብ ነውን? በገዛ ወገኑ ላይ ድሮን የሚያዘንብ አገዛዝ ወይስ የቆሰለ ምርኮኛን የሚያክም ሕዝብ የትኛው ነው ለሀገር የሚቆረቆረው?
ለአገዛዙ ሰራዊት የቀረበ የሕሊና ጥያቄ፤ ወታደር ሆይ! ይህን ፎቶ በጥልቀት ተመልከተው፤ የታጠቀው ማን ነው? አንተ የጥፋት መሣሪያ ታጥቀህ መጣህ፤ አርሶ አደሩ ግን የሕይወት መሣሪያ የሆነውን "እንጀራ" ይዞ ቀረበልህ። ጠላትህ ማን ነው? አዛዦችህ "ሽፍታና ጽንፈኛ" ብለው ሊያስገድሉህ የላኩህ ሕዝብ፣ ዛሬ በረሃብ እንዳትዝል የላብ እህሉን እያቀረበልህ ነው። ለማን ትሞታለህ? አንተ ቆስለህ ስትማረክ ጀርባውን የሰጠህ አገዛዝ ወይስ የቆሰለ አካልህን አክሞ ያበላህ ሕዝብ የትኛው ነው ለክብርህ የሚመጥነው?
ይህ ትግል በአሸናፊነት የሚደመደመው በመሣሪያ ብዛት ብቻ ሳይሆን፣ በያዝነው የሞራልና የሰብአዊነት የበላይነት ነው። አፈሙዝ ታጥቀህ ልትገድለው ብትመጣም፣ ሕዝባችን በፍቅርና በሰብአዊነት ይዞሃል። ይህ ፍቅር ነገ ለምትፈጠረው አዲስና ፍትሐዊት ኢትዮጵያ መሠረት ነው።
ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ማውቅ ያለበት ዋና ነገር፤ ይህ ትግል የሁለት ታጣቂዎች ሽኩቻ አይደለም። ይህ ትግል በግፈኛ አምባገነንነት እና በሰብአዊነት መካከል ያለ ግብግብ ነው። አገዛዙ በንጹሐን ላይ ድሮን ሲያዘንብ፣ የነፃነት ኃይሎችና ሕዝቡ ግን ለምርኮኞች የጄኔቫን ስምምነት (Geneva Convention) በላቀ ሁኔታ በተግባር እየተረጎሙት ይገኛሉ።
ዓለም ሊያውቀው የሚገባው ሀቅ ቢኖር፣ በኢትዮጵያ ምድር ፍትሕንና ሰላምን ሊያመጣ የሚችለው አፈሙዙን ለሰው ልጅ ክብር ዝቅ የሚያደርገው በፋኖ ኃይል እንጂ፣ ሕዝቡን እንደ ጠላት ፈርጆ የሚጨፈጭፈው አምባገነን ሥርዓት አለመሆኑን ነው።
ጥላቻን በፍቅር እናሸንፋለን!
ትግላችን ለፍትሕ፣ ለእኩልነትና ለነፃነት ነው!
ክብር ለሰብአዊነት ዘብ ለቆመው ሕዝባችን!
አዲስትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ!
ታህሳስ 28/2018ዓ.ም
❤2👍1
የአደረጃጀት ዜና፤
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር ትግሉ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ የትግሉ ሂደት ምን ይመስል እንደነበር ጥልቅ ግምገማ እና ምክክር ካደረገና የወደፊት የትግል አቅጣጫዎችን በመለየት ለቀጣይ ትግሉን ወደተሻለ ምዕራፍ ያሸጋግራሉ ያላቸውን አርበኞች ወደፊት ለማምጣት ያስቻለ የአደረጃጀት ሪፎርም ከትንናንት በስቲያ ማለትም ታህሳስ 26 ቀን 2018 ዓ/ም አድርጓል።
በዚህም መሰረት ስማቸው ከስር የተጠቀሱት አርበኞች ኮሩን እንድመሩ ተሰይመዋል፤
1. የንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር ሰብሳቢ - አርበኛ አብነው ታደሰ
1.1. ምክትል ሰብሳቢ እና ወታደራዊ አዛዥ - አርበኛ እንድሪስ ይማም
1.2. ምክትል ወታደራዊ አዛዥ - አርበኛ አበበ መኩሪያ
1.3. ምክትል ሰብሳቢ እና የፓለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ - አርበኛ ብሩክ ሞገስ
1.4. የፓለቲካ ጉዳዮች ም/ኃላፊ - አርበኛ ተመቸው ጀንበሩ
2. ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ - አርበኛ ጌትነት አበበ
2.1. ዘመቻ መምሪያ ም/ኃላፊ - አርበኛ ጎሹ ታረቀኝ
3. የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ ቃለአብ ወርቅዬ
3.1. የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ አርበኛ ሙሉጌታ አረጋው
4. የመዝናኛ እና ኪነጥበብ ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ ካሣሁን ታደሰ
4.1. የመዝናኛ እና ኪነት ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ አባተ አብነው
5. አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ - ኦንጅነር ተመስገን ለማ
5.1. አስተዳደር ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ ሼህ ይማም ሙሀመድ
6. የሎጅስቲክስ አቅርቦትና ስርጭት ኃላፊ - አርበኛ አያሌው አሰፋ
6.1. የሎጅስቲክስ አቅርቦትና ስርጭት ም/ኃላፊ - አርበኛ ኤሊያስ በለጠ
7. የፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ አህመድ ሁሴን
7.1. የፋይናንስ ዘርፍ ም/ ኃላፊ - አርበኛ አበበ ነጋ
8. ኦድተር - አርበኛ መከተ ካሳው
9. ኦርድናንስ- አርበኛ በፍቃዱ ገንብር
9.1. ምክትል ኦርድናንስ- አርበኛ አላምረው ደስታ
10. የወታደራዊ ስልጠና ዘርፍ ኃላፊ - መቶ አለቃ በላይ መከተ
10.1. የወታደራዊ ስልጠና ዘርፍ ም/ኃላፊ - ኮማንዶ ኡመር ምሳው
11. የመረጃ እና ደህንነት ኃላፊ - አርበኛ ××××××××××
11.1. የመረጃ እና ደህንነት ም/ ኃላፊ - አርበኛ ×××××××
12. የጤና ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ መርከብ አበራ
12.1. የጤና ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ ሚካኤል ጋሻው
13. የሰው ሀይል ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ ተፈራ ብሩ
13.1. የሰው ሀይል ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ ታደሰ መሰረት
14. የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ ሳራ ካሳዬ
14.1. የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ ሀይማኖት ጎቼ
15. የህግ አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ ታምራት በሽር
15.1. የህግ አገልግሎት ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ ሰይድ ካሳ
የንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር የአደረጃጀት ሪፎርም በሰራ በማግስቱ የውጊያ እቅድ በማውጣት በስሩ ላሉት አምስቱም ክፍለ ጦሮች ስምሪት ሰጥቶ በምዕራብ ወሎ ግንባር በዛሬው እለት ከፍተኛ የጦር ሜዳ ጀብዱ ተፈፅሟል። ዝርዝሩ በምሽት ጥቅል የውሎ ዘገባችን የሚካተት ይሆናል ሲል የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ፋኖ ቃለአብ ወርቅዬ ለምኒልክ ዕዝ በላከው ሪፓርት አስታውቋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር ትግሉ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ የትግሉ ሂደት ምን ይመስል እንደነበር ጥልቅ ግምገማ እና ምክክር ካደረገና የወደፊት የትግል አቅጣጫዎችን በመለየት ለቀጣይ ትግሉን ወደተሻለ ምዕራፍ ያሸጋግራሉ ያላቸውን አርበኞች ወደፊት ለማምጣት ያስቻለ የአደረጃጀት ሪፎርም ከትንናንት በስቲያ ማለትም ታህሳስ 26 ቀን 2018 ዓ/ም አድርጓል።
በዚህም መሰረት ስማቸው ከስር የተጠቀሱት አርበኞች ኮሩን እንድመሩ ተሰይመዋል፤
1. የንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር ሰብሳቢ - አርበኛ አብነው ታደሰ
1.1. ምክትል ሰብሳቢ እና ወታደራዊ አዛዥ - አርበኛ እንድሪስ ይማም
1.2. ምክትል ወታደራዊ አዛዥ - አርበኛ አበበ መኩሪያ
1.3. ምክትል ሰብሳቢ እና የፓለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ - አርበኛ ብሩክ ሞገስ
1.4. የፓለቲካ ጉዳዮች ም/ኃላፊ - አርበኛ ተመቸው ጀንበሩ
2. ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ - አርበኛ ጌትነት አበበ
2.1. ዘመቻ መምሪያ ም/ኃላፊ - አርበኛ ጎሹ ታረቀኝ
3. የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ ቃለአብ ወርቅዬ
3.1. የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ አርበኛ ሙሉጌታ አረጋው
4. የመዝናኛ እና ኪነጥበብ ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ ካሣሁን ታደሰ
4.1. የመዝናኛ እና ኪነት ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ አባተ አብነው
5. አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ - ኦንጅነር ተመስገን ለማ
5.1. አስተዳደር ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ ሼህ ይማም ሙሀመድ
6. የሎጅስቲክስ አቅርቦትና ስርጭት ኃላፊ - አርበኛ አያሌው አሰፋ
6.1. የሎጅስቲክስ አቅርቦትና ስርጭት ም/ኃላፊ - አርበኛ ኤሊያስ በለጠ
7. የፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ አህመድ ሁሴን
7.1. የፋይናንስ ዘርፍ ም/ ኃላፊ - አርበኛ አበበ ነጋ
8. ኦድተር - አርበኛ መከተ ካሳው
9. ኦርድናንስ- አርበኛ በፍቃዱ ገንብር
9.1. ምክትል ኦርድናንስ- አርበኛ አላምረው ደስታ
10. የወታደራዊ ስልጠና ዘርፍ ኃላፊ - መቶ አለቃ በላይ መከተ
10.1. የወታደራዊ ስልጠና ዘርፍ ም/ኃላፊ - ኮማንዶ ኡመር ምሳው
11. የመረጃ እና ደህንነት ኃላፊ - አርበኛ ××××××××××
11.1. የመረጃ እና ደህንነት ም/ ኃላፊ - አርበኛ ×××××××
12. የጤና ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ መርከብ አበራ
12.1. የጤና ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ ሚካኤል ጋሻው
13. የሰው ሀይል ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ ተፈራ ብሩ
13.1. የሰው ሀይል ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ ታደሰ መሰረት
14. የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ ሳራ ካሳዬ
14.1. የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ ሀይማኖት ጎቼ
15. የህግ አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ - አርበኛ ታምራት በሽር
15.1. የህግ አገልግሎት ዘርፍ ም/ኃላፊ - አርበኛ ሰይድ ካሳ
የንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር የአደረጃጀት ሪፎርም በሰራ በማግስቱ የውጊያ እቅድ በማውጣት በስሩ ላሉት አምስቱም ክፍለ ጦሮች ስምሪት ሰጥቶ በምዕራብ ወሎ ግንባር በዛሬው እለት ከፍተኛ የጦር ሜዳ ጀብዱ ተፈፅሟል። ዝርዝሩ በምሽት ጥቅል የውሎ ዘገባችን የሚካተት ይሆናል ሲል የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ፋኖ ቃለአብ ወርቅዬ ለምኒልክ ዕዝ በላከው ሪፓርት አስታውቋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም
👍2❤1
አፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክ/ጦር በጠላት ላይ የተጠና የሌሊት ኦፕሬሽን ሰራ !
የጠላትን ቅስም በመስበር የሚታወቀው የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር በባልጪ ከተማ በመሸገው የአብይ አህመድ ሰራዊት ላይ አስደማሚ የሌሊት ኦፕሬሽን ሰርቷል ።
ኦፕሬሽኑ የተሰራው የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክ/ጦር በኃይሉ እና መቶ አለቃ አበባው ብርጌድ ሸማቂ የፋኖ አባላቶችና አመራሮች ተናበው በወሰዱት የቅንጅት እርምጃ ነው ።
በህዝብ ቅቡልነው ያጣው አራጁ የአብይ አህመድ ዙፋን አስጠባቂ ሰራዊት በየጊዜው የሚደርስበትን ከባድ የፋኖ ምት በሚዲያ ፕሮፖጋንዳ ለመቀልበስ በማቀድ የፋኖ አባላቶች እና አመራሮች የሚገኙበትን ቦታ በሌሊት ለመክበብ ያሰላውን ዕቅድ ተከትሎ ነው ፋኖ የሌሊት ኦፕሬሽን የሰራበት ።
ታህሳስ 26/2018 ዓ ም የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኅይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር የነበልባል ክ/ጦር ለማፈን እየተንቀሳቀሰ በነበረው የአብይ አህመፍ ዙፋን አስጠባቂ ሰራዊት ከምሽቱ 4:35 ላይ ሁለቱ ብርጌዶች ተናበው በወሰዱት የሌሊት ኦፕሬሽን በርካታ ምልምል ስራዊቱ ሙትና ቁስለኛ መሆኑ መዘገባችን ይታወሳል ።
የፋኖን የቦንብ እና የጥይት ናዳ መቋቋም ያቃተው የብረሃኑ ጁላ ግትልትል ሰራዊት ሙትና ቁስለኛውን እንኳን መሰብሰብ ሳይችል እግሩ በመራው ተበታትኖ አድሯል ።
በልዩ ጥበብ ኦፕሬሽናቸውን ያሳኩት የነበልባል ክ/ጦር የኃይሉ እና መቶ አለቃ አበባው ብርጌድ ሸማቂ የፋኖ አባላቶችና አመራሮች ስራቸውን እንደጨረሱ በሰላም ወደ ምሽጋቸው ተመልሰዋል ።
የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ ኮር የህዝብ ግንኘነት ኃላፊ አርበኛ ይታገስ ጌታሁን መረጃውን አድርሶናል ።
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"
@አፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ዜና ክፍል።
የጠላትን ቅስም በመስበር የሚታወቀው የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር በባልጪ ከተማ በመሸገው የአብይ አህመድ ሰራዊት ላይ አስደማሚ የሌሊት ኦፕሬሽን ሰርቷል ።
ኦፕሬሽኑ የተሰራው የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክ/ጦር በኃይሉ እና መቶ አለቃ አበባው ብርጌድ ሸማቂ የፋኖ አባላቶችና አመራሮች ተናበው በወሰዱት የቅንጅት እርምጃ ነው ።
በህዝብ ቅቡልነው ያጣው አራጁ የአብይ አህመድ ዙፋን አስጠባቂ ሰራዊት በየጊዜው የሚደርስበትን ከባድ የፋኖ ምት በሚዲያ ፕሮፖጋንዳ ለመቀልበስ በማቀድ የፋኖ አባላቶች እና አመራሮች የሚገኙበትን ቦታ በሌሊት ለመክበብ ያሰላውን ዕቅድ ተከትሎ ነው ፋኖ የሌሊት ኦፕሬሽን የሰራበት ።
ታህሳስ 26/2018 ዓ ም የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኅይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር የነበልባል ክ/ጦር ለማፈን እየተንቀሳቀሰ በነበረው የአብይ አህመፍ ዙፋን አስጠባቂ ሰራዊት ከምሽቱ 4:35 ላይ ሁለቱ ብርጌዶች ተናበው በወሰዱት የሌሊት ኦፕሬሽን በርካታ ምልምል ስራዊቱ ሙትና ቁስለኛ መሆኑ መዘገባችን ይታወሳል ።
የፋኖን የቦንብ እና የጥይት ናዳ መቋቋም ያቃተው የብረሃኑ ጁላ ግትልትል ሰራዊት ሙትና ቁስለኛውን እንኳን መሰብሰብ ሳይችል እግሩ በመራው ተበታትኖ አድሯል ።
በልዩ ጥበብ ኦፕሬሽናቸውን ያሳኩት የነበልባል ክ/ጦር የኃይሉ እና መቶ አለቃ አበባው ብርጌድ ሸማቂ የፋኖ አባላቶችና አመራሮች ስራቸውን እንደጨረሱ በሰላም ወደ ምሽጋቸው ተመልሰዋል ።
የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ ኮር የህዝብ ግንኘነት ኃላፊ አርበኛ ይታገስ ጌታሁን መረጃውን አድርሶናል ።
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"
@አፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ዜና ክፍል።
❤4👍1
ዘመቻ መሪው እና ብሬን እረዳቱ በአገዛዙን ሰራዊት ላይ በመታኮስ 64ኛ ክፍለ ጦር ተቀላቀሉ።
10 አለቃ አሰግድ አስጠራው የክፍለ ጦር ቀኝ እና ምሃንዲስ ዘመቻ መሪ እና አክሊሉ ባይነስ ብሬን እረዳት ቢቸና ከተማ ከሚገኘው 6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር 75ኛ ክፍለ ጦር ቀኝ እና መሃንዲስ ብሬን እረዳት ሲሆኑ ቢቸና ከተማ ከምሽቱ 4:00 ሰዓት አካባቢ አብረውት የነበሩ ጓዶቹን ክላሽ ነጥቆ በመታኮስ በጠላት ኃይል ላይ ጉዳት በማድረስ የአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር #64ኛ_ክፍለ_ጦር ተቀላቅለዋለ ።
#ሚሊሻ_ደረሰ_ዋለ
ሸበል በረንታ ወረዳ ሌዲና አካባቢው ቀበሌ ተወላጅ ሲሆን በሸበል በረንታ ወረዳ መርገጭ 01 ቀበሌ የሚገኘው የአገዛዙን ቅጥረኛ ሚሊሻ በካባቢው ማህበረሰቡ ላይ የሚፈፅመውን #ዝርፊ በመቃወም ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቅሏል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስተ ተስፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ!
@አፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 64ኛ ክፍለ ጦር ሕዝብ ግንኙነት
10 አለቃ አሰግድ አስጠራው የክፍለ ጦር ቀኝ እና ምሃንዲስ ዘመቻ መሪ እና አክሊሉ ባይነስ ብሬን እረዳት ቢቸና ከተማ ከሚገኘው 6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር 75ኛ ክፍለ ጦር ቀኝ እና መሃንዲስ ብሬን እረዳት ሲሆኑ ቢቸና ከተማ ከምሽቱ 4:00 ሰዓት አካባቢ አብረውት የነበሩ ጓዶቹን ክላሽ ነጥቆ በመታኮስ በጠላት ኃይል ላይ ጉዳት በማድረስ የአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር #64ኛ_ክፍለ_ጦር ተቀላቅለዋለ ።
#ሚሊሻ_ደረሰ_ዋለ
ሸበል በረንታ ወረዳ ሌዲና አካባቢው ቀበሌ ተወላጅ ሲሆን በሸበል በረንታ ወረዳ መርገጭ 01 ቀበሌ የሚገኘው የአገዛዙን ቅጥረኛ ሚሊሻ በካባቢው ማህበረሰቡ ላይ የሚፈፅመውን #ዝርፊ በመቃወም ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቅሏል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስተ ተስፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ!
@አፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 64ኛ ክፍለ ጦር ሕዝብ ግንኙነት
👍2
ሰበር ዜና‼️
ኦራሉ ልክ እንደ ደመራ እንጨት በእሳት ነዷል!
መቅደላ ወረዳ ልዩ ስሙ ገናቲት በተባለ አከባቢ አንድ የአገዛዙ ወታደራዊ ኦራል ከነ ጫነው ሰራዊቱ ሙሉ በሙሉ በቦምብ ጋይቶ ወድሟል።
ዛሬ ታህሳስ 28/2018 ዓ/ም ከንጋት ጀምሮ በምስራቅ አማራ ቀጠና ምዕራብ ወረዳዎች ላይ ከባድ ተጋድሎ እየተደረገ ነው።
ተጨማሪ ዝርዝር መረጃውን ይዘን የምንመለስ ይሆናል....
@መረብ
ኦራሉ ልክ እንደ ደመራ እንጨት በእሳት ነዷል!
መቅደላ ወረዳ ልዩ ስሙ ገናቲት በተባለ አከባቢ አንድ የአገዛዙ ወታደራዊ ኦራል ከነ ጫነው ሰራዊቱ ሙሉ በሙሉ በቦምብ ጋይቶ ወድሟል።
ዛሬ ታህሳስ 28/2018 ዓ/ም ከንጋት ጀምሮ በምስራቅ አማራ ቀጠና ምዕራብ ወረዳዎች ላይ ከባድ ተጋድሎ እየተደረገ ነው።
ተጨማሪ ዝርዝር መረጃውን ይዘን የምንመለስ ይሆናል....
@መረብ
❤4
"ከህዝባችን ጋር ሁነን ትንኞች ሸልከዉ ሊያልፉበት የማይቻላቸዉ አስተማማኝ የደህንነት መረብ ዘርግተናል" የአፋብኃ ቴዎድሮስ እዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክ/ጦር ሰብሳቢ ፋኖ አንሙትጌታሁን
መገናኛ እና ጂፒኤስ ይዞ በስቢል አለባበስ ሲንቀሳቀስ የነበረ የፋሽቱ አብይ አህመድ መታደራዊ መረጃ ዛሬ ታህሳስ 28/2018 ዓ/ም በጀግኖቹ የ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ሻለቃ ልጆች ቁጥጥር ስር ዉሏል።
ይህ የ304ኛ ኮር 99ኛ ክ/ጦር 5ኛ ሻለቃ መገናኛ ባለሙያ እንደሆነ የተናገረዉ ደመቀ ታረቀኝ የተባለ የጠላት ደህንነት በምርመራ ወቅት እንዳስረዳዉ ከሆነ ወደ ፋግታ የገባዉ የጠላት ጦር በማህበረሰቡ ላይ ሊፈፅም ያሰበዉን ፀረ አማራነት ተግባር ጨምሮ ብዙ ጉዳዮችን አጋልጧል።
ከሰዉ እስከ ትንኝ ሁሉም ነገር በፋኖ የደህንነት እይታ ስር ነዉ!!
አዲስ ትዉልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!!!
መገናኛ እና ጂፒኤስ ይዞ በስቢል አለባበስ ሲንቀሳቀስ የነበረ የፋሽቱ አብይ አህመድ መታደራዊ መረጃ ዛሬ ታህሳስ 28/2018 ዓ/ም በጀግኖቹ የ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ሻለቃ ልጆች ቁጥጥር ስር ዉሏል።
ይህ የ304ኛ ኮር 99ኛ ክ/ጦር 5ኛ ሻለቃ መገናኛ ባለሙያ እንደሆነ የተናገረዉ ደመቀ ታረቀኝ የተባለ የጠላት ደህንነት በምርመራ ወቅት እንዳስረዳዉ ከሆነ ወደ ፋግታ የገባዉ የጠላት ጦር በማህበረሰቡ ላይ ሊፈፅም ያሰበዉን ፀረ አማራነት ተግባር ጨምሮ ብዙ ጉዳዮችን አጋልጧል።
ከሰዉ እስከ ትንኝ ሁሉም ነገር በፋኖ የደህንነት እይታ ስር ነዉ!!
አዲስ ትዉልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!!!
❤1
ሰበር ዜና!
የአፋብኃ ምኒልክ ዕዝ አሃዶች እና ከአፋህድ የተለያዩ አሃዶች በጥምረት የወረዳ ከተሞችን ጨምሮ የፋሽስቱ አገዛዝ የጦር ተሽከርካሪዎችን : በርካታ ተተኳሽ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እንዲሁም በርካታ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊቶችን በመማረክ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::
አፋብኃ ምኒልክ ዕዝ በሶስት ኮሮች ማለትም ንጉስ ሚካኤል አሊ ኮር፣ ልጅ እያሱ ኮር እና የደጋው መብረቅ ኮር፣ እንዲሁም የዕዙ ልዩ ዘመቻ አሃድ በሆነችው በላጎ ተወርዋሪ ሻለቃ እና ከአፋህድ የተለያዩ አሃዶች በጥምረት ደቡብና ምዕራብ ወሎ ቤተ-አማራ ቀጠናዎች ላይ ዛሬ ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም ማለዳ ጀምሮ በተመሳሳይ ሰዓት በተጀመረው ማጥቃት በርካታ ወታደራዊ ፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ድሎችን ተጎናጽፏል::
በአፋብኃ ምኒልክ ዕዝ አሃዶች እና አፋህድ የተለያዩ አሃዶች ጥምረት ነፃ የወጡ የቤተ-አማራ የወረዳ እና ታዳጊ ከተሞች፦
•ጃማ ከለላና ልጓማ እንዲሁም ደብረዘይት ከተሞች በአፋህድ አሃዶች እና አፋብኃ ንጉስ ሚካኤል ኮር ጥምረት
•ለገሂዳ ገነቴ እና ሳይንት ደንሳ ከተማ ንጉስ ሚካኤል ኮር
•ተንታ አጅባር ልጅ እያሱ ኮር እና የደጋው መብረቅ ኮር እንዲሁም ልዩ ዘመቻ በላጎ ሻለቃ ነፃ ወተዋል::
በዚህም የምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጥምረት ባደረጉት ከባድ ማጥቃት የወረዳ ከተሞችን ጨምሮ በርካታ የፋሽስቱ አገዛዝ ሰራዊት ተሽከርካሪዎች ከተተኳሽ ጋር እና የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች ተማርከዋል::
በተጋድሎው የተገኙ ድሎች፦
*ልጅ እያሱ ኮር : በ24ኛ ክፍለ ጦር የተገኙ ድሎች
- 1 ብሬን
- 30 ክላሽ
- 1000 የብሬን ተተኮሽ
- 1500 የክላሽ ተተኳሽ
- 10 ምርኮኛ
•በ23ኛ ክፍለ ጦር የተገኙ ድሎች
- 1 ብሬን
- 1 ስናይፐር
- 1ኦራል ወታደራዊ ቁሳቁስ የጫነ
- 1 ካሶኒ ስንቅ የጫነ
- 40 ክላሽ
- 2000 የክላሽ ተተኳሽ
- 1500 የብሬን ተተኳሽ
- 25 ምርኮኛ (መቶ አለቃ ማዕረግተኛን ጨምሮ)
•ልዩ ዘመቻ በላጎ ተወርዋሪ ሻለቃ ከልጅ እያሱ ኮር ክፍለጦሮች ጋር በጥምረት በመሰለፍ ድሎቹን ሰርታለች::
*ደጋው መብረቅ ኮር
- 2 ብሬን
- 75 ክላሽ
- 1 ኦራል ተተኳሽ : የእጅ ቦምብን ጨምሮ (ከሌሎች የምኒልክ ዕዝ አሃዶች ጋር)
- 51 መከላከያ 35 ሚሊሻ 20 ፖሊስ በአጠቃላይ 106 ምርኮኛ
•የንጉስ ሚካኤል አሊ ኮር የተገኙ ድሎችና ቁጥራዊ መረጃዎች ተሟልተው እንደደረሱን ይፋ የምናደርግ ይሆናል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
@አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
የአፋብኃ ምኒልክ ዕዝ አሃዶች እና ከአፋህድ የተለያዩ አሃዶች በጥምረት የወረዳ ከተሞችን ጨምሮ የፋሽስቱ አገዛዝ የጦር ተሽከርካሪዎችን : በርካታ ተተኳሽ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እንዲሁም በርካታ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊቶችን በመማረክ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::
አፋብኃ ምኒልክ ዕዝ በሶስት ኮሮች ማለትም ንጉስ ሚካኤል አሊ ኮር፣ ልጅ እያሱ ኮር እና የደጋው መብረቅ ኮር፣ እንዲሁም የዕዙ ልዩ ዘመቻ አሃድ በሆነችው በላጎ ተወርዋሪ ሻለቃ እና ከአፋህድ የተለያዩ አሃዶች በጥምረት ደቡብና ምዕራብ ወሎ ቤተ-አማራ ቀጠናዎች ላይ ዛሬ ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም ማለዳ ጀምሮ በተመሳሳይ ሰዓት በተጀመረው ማጥቃት በርካታ ወታደራዊ ፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ድሎችን ተጎናጽፏል::
በአፋብኃ ምኒልክ ዕዝ አሃዶች እና አፋህድ የተለያዩ አሃዶች ጥምረት ነፃ የወጡ የቤተ-አማራ የወረዳ እና ታዳጊ ከተሞች፦
•ጃማ ከለላና ልጓማ እንዲሁም ደብረዘይት ከተሞች በአፋህድ አሃዶች እና አፋብኃ ንጉስ ሚካኤል ኮር ጥምረት
•ለገሂዳ ገነቴ እና ሳይንት ደንሳ ከተማ ንጉስ ሚካኤል ኮር
•ተንታ አጅባር ልጅ እያሱ ኮር እና የደጋው መብረቅ ኮር እንዲሁም ልዩ ዘመቻ በላጎ ሻለቃ ነፃ ወተዋል::
በዚህም የምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጥምረት ባደረጉት ከባድ ማጥቃት የወረዳ ከተሞችን ጨምሮ በርካታ የፋሽስቱ አገዛዝ ሰራዊት ተሽከርካሪዎች ከተተኳሽ ጋር እና የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች ተማርከዋል::
በተጋድሎው የተገኙ ድሎች፦
*ልጅ እያሱ ኮር : በ24ኛ ክፍለ ጦር የተገኙ ድሎች
- 1 ብሬን
- 30 ክላሽ
- 1000 የብሬን ተተኮሽ
- 1500 የክላሽ ተተኳሽ
- 10 ምርኮኛ
•በ23ኛ ክፍለ ጦር የተገኙ ድሎች
- 1 ብሬን
- 1 ስናይፐር
- 1ኦራል ወታደራዊ ቁሳቁስ የጫነ
- 1 ካሶኒ ስንቅ የጫነ
- 40 ክላሽ
- 2000 የክላሽ ተተኳሽ
- 1500 የብሬን ተተኳሽ
- 25 ምርኮኛ (መቶ አለቃ ማዕረግተኛን ጨምሮ)
•ልዩ ዘመቻ በላጎ ተወርዋሪ ሻለቃ ከልጅ እያሱ ኮር ክፍለጦሮች ጋር በጥምረት በመሰለፍ ድሎቹን ሰርታለች::
*ደጋው መብረቅ ኮር
- 2 ብሬን
- 75 ክላሽ
- 1 ኦራል ተተኳሽ : የእጅ ቦምብን ጨምሮ (ከሌሎች የምኒልክ ዕዝ አሃዶች ጋር)
- 51 መከላከያ 35 ሚሊሻ 20 ፖሊስ በአጠቃላይ 106 ምርኮኛ
•የንጉስ ሚካኤል አሊ ኮር የተገኙ ድሎችና ቁጥራዊ መረጃዎች ተሟልተው እንደደረሱን ይፋ የምናደርግ ይሆናል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
@አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
❤7
"ሰሞኑን የምናበስረሰው የአንድነት እና የፍቅር የምስራች ይኖረናል። መላው የኢትዮጰያ ህዝብ ይጠብቀን።"
ከአፋህድ ሸዋ ጠቃይ ግዛት እዝ የተሰጠ መግለጫ
መልካም ገና!!! --- በገና ዋዜማ አፋህድ እና አፋብኃ በወሎ ቤተ አማራ በጋራ ታላቅ ድል ተቀዳጁ!!!
ከሁሉ አስቀድሞ---
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ሁሉ፣ እንኳን ለመድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ 2018ኛ የልደት በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ !!!
ዛሬ ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከንጋቱ 11:00 ጀምሮ በወሎ ቤተ አምሓራ በርካታ ወረዳዎች ታላቅ ተጋድሎ ሲደረግ ውሏል።
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ እና ከአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት(አፋሕድ) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ፣ ወሎ ቤተ አምሐራ ጠቅላይ ግዛት እዝ እና ከአፋህድ ጎጃም ጠቅላይ ግዛት እዝ የተወጣጡ ውስን ሻለቆች፣ እንዲሁም፣ የክፍለጦር፣ የኮር እና የዕዝ ቃኝዎች ተቀናጅተው "ዘመቻ ስንታየሁ ማሞ(ራንቦ)" ብለው የሰየሙትን የአንድነት ማብሰሪያ የተጠና ኦፐሬሽን አድርገው በጠላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል።
በከላላ ወረዳ፣ በጢርጢራ፣ በጃማ ደጎሎ፣ በተንታ አጅባር፣ በመቅደላ፣ በወግዲ፣ በልጓማ፣ በውጫሌ፣ በለገ ሂዳ፣ ለጋንቦ፣ በሀይቅ ዙሪያ እና በሌሎችም ተጨማሪ የወሎ ቤተ አማራ ቀጠናዎች በተደረጉ ውጊያዎች በርካታ ቁጥር ያለው የአገዛዙ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ እና ምርኮኛ የሆነ ሲሆን፣ የጠላት ካምፖችም ተደምስሰዋል። በተጨማሪም፣ መቅደላን ጨምሮ ሌሎች የወረዳ ከተሞችን በጥምር የፋኖ ኃይሉ ተይዘዋል።
ዝርዝር መረጃዎችን ከዓመት በዓሉ ማግስት ይዘን እንመለሳለን።
በመጨረሻም፣ ግን ከሁሉም በላይ፣ በመላ ዓለም ያላችኹ የክርስትና እምነት ተከታዮች ሁሉ፣ እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችኹ እንላለን።
በክርስትና እምነት አስተምሮ፣ ዘመን የማይቆጠርለት አምላክ ሰውን ለማዳን ሰው ሆኖ ዘመን ተቆጥሮለት ከድንግል ማርያም በመወለዱ የማይታየው ታየ፣ የማይመረመረው ርቃቄ ተገልጦ ሰው እና መላእክት በአንድ ጋር በደስታ ዘመሩ፣ በድቅድቅ ጨለማ የነበረው ዓለም ወደሚደነቅ ብርሃን ወጣ።
በክርስትና አስተምሮ፣ ከአብ እና ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ፣ ከሦስትነቱ ሳይጎድል፣ ከአምላክነት ክብሩ ሳይቀነስ፣ በፍፁም ትህትና በበረት መወለዱ እና መተኛቱ፣ ከዚያም በገዛ ፈቃዱ ለሰው ልጅ ፍቅር ብሎ የሞት ፅዋን መቅመሱ፣ በእኛ ዘመን ለሰው ልጆች ፍቅር ብለው መስዋዕትነት ከከፈሉት መካከል ለብዙዎቹ ዋነኛው ምሳሌ እና አርአያ ነው። ምሳሌነቱም ለሁሉም ፍጥረታት ዘላለማዊ ነው።
ስለዚህም፣ የትግላችን ሰማዕታት እያሰብን በዓሉ የፋኖ አንድነት እና የህዝብ ፍቅርን ለዓለም በተጨባጭ የምንገልጥበት ዋዜማ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ መግለፅ እንወዳለን።
ሰሞኑን የምናበስረሰው የአንድነት እና የፍቅር የምስራች ይኖረናል። መላው የኢትዮጰያ ህዝብ ይጠብቀን። ይህን የምለው በተቀደሰው የገና ዕለት መሆኑን በታላቅ ታላቅ ደስታ ነው።
ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!!!
ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!!
ድል ለኢትዮጰያ ህዝብ!!!
/
ታህሳስ 28፣ 2018 ዓ.ም።
ከአፋህድ ሸዋ ጠቃይ ግዛት እዝ የተሰጠ መግለጫ
መልካም ገና!!! --- በገና ዋዜማ አፋህድ እና አፋብኃ በወሎ ቤተ አማራ በጋራ ታላቅ ድል ተቀዳጁ!!!
ከሁሉ አስቀድሞ---
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ሁሉ፣ እንኳን ለመድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ 2018ኛ የልደት በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ !!!
ዛሬ ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከንጋቱ 11:00 ጀምሮ በወሎ ቤተ አምሓራ በርካታ ወረዳዎች ታላቅ ተጋድሎ ሲደረግ ውሏል።
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ እና ከአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት(አፋሕድ) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ፣ ወሎ ቤተ አምሐራ ጠቅላይ ግዛት እዝ እና ከአፋህድ ጎጃም ጠቅላይ ግዛት እዝ የተወጣጡ ውስን ሻለቆች፣ እንዲሁም፣ የክፍለጦር፣ የኮር እና የዕዝ ቃኝዎች ተቀናጅተው "ዘመቻ ስንታየሁ ማሞ(ራንቦ)" ብለው የሰየሙትን የአንድነት ማብሰሪያ የተጠና ኦፐሬሽን አድርገው በጠላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል።
በከላላ ወረዳ፣ በጢርጢራ፣ በጃማ ደጎሎ፣ በተንታ አጅባር፣ በመቅደላ፣ በወግዲ፣ በልጓማ፣ በውጫሌ፣ በለገ ሂዳ፣ ለጋንቦ፣ በሀይቅ ዙሪያ እና በሌሎችም ተጨማሪ የወሎ ቤተ አማራ ቀጠናዎች በተደረጉ ውጊያዎች በርካታ ቁጥር ያለው የአገዛዙ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ እና ምርኮኛ የሆነ ሲሆን፣ የጠላት ካምፖችም ተደምስሰዋል። በተጨማሪም፣ መቅደላን ጨምሮ ሌሎች የወረዳ ከተሞችን በጥምር የፋኖ ኃይሉ ተይዘዋል።
ዝርዝር መረጃዎችን ከዓመት በዓሉ ማግስት ይዘን እንመለሳለን።
በመጨረሻም፣ ግን ከሁሉም በላይ፣ በመላ ዓለም ያላችኹ የክርስትና እምነት ተከታዮች ሁሉ፣ እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችኹ እንላለን።
በክርስትና እምነት አስተምሮ፣ ዘመን የማይቆጠርለት አምላክ ሰውን ለማዳን ሰው ሆኖ ዘመን ተቆጥሮለት ከድንግል ማርያም በመወለዱ የማይታየው ታየ፣ የማይመረመረው ርቃቄ ተገልጦ ሰው እና መላእክት በአንድ ጋር በደስታ ዘመሩ፣ በድቅድቅ ጨለማ የነበረው ዓለም ወደሚደነቅ ብርሃን ወጣ።
በክርስትና አስተምሮ፣ ከአብ እና ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ፣ ከሦስትነቱ ሳይጎድል፣ ከአምላክነት ክብሩ ሳይቀነስ፣ በፍፁም ትህትና በበረት መወለዱ እና መተኛቱ፣ ከዚያም በገዛ ፈቃዱ ለሰው ልጅ ፍቅር ብሎ የሞት ፅዋን መቅመሱ፣ በእኛ ዘመን ለሰው ልጆች ፍቅር ብለው መስዋዕትነት ከከፈሉት መካከል ለብዙዎቹ ዋነኛው ምሳሌ እና አርአያ ነው። ምሳሌነቱም ለሁሉም ፍጥረታት ዘላለማዊ ነው።
ስለዚህም፣ የትግላችን ሰማዕታት እያሰብን በዓሉ የፋኖ አንድነት እና የህዝብ ፍቅርን ለዓለም በተጨባጭ የምንገልጥበት ዋዜማ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ መግለፅ እንወዳለን።
ሰሞኑን የምናበስረሰው የአንድነት እና የፍቅር የምስራች ይኖረናል። መላው የኢትዮጰያ ህዝብ ይጠብቀን። ይህን የምለው በተቀደሰው የገና ዕለት መሆኑን በታላቅ ታላቅ ደስታ ነው።
ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!!!
ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!!
ድል ለኢትዮጰያ ህዝብ!!!
/
ታህሳስ 28፣ 2018 ዓ.ም።
❤2👎1