ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.35K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.19K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
ሰበር ዜና

በአፋብኃ በላይ ዘለቀ እዝ 3ኛ ኮር አያሌው ብሩ ክፍለጦር በአገዛዙ ሃይል ላይ በወሰደው ርምጃ ከፍተኛ ድል ተቀዳጀ::

አያሌው ብሩ ክፍለጦሩ ከሌሎች ክፍለጦሮች ጋር በመሆን ትልቅ ተጋድሎ በማድረግ ድል ሲቀናው ያገዛዙ ዘራፊ ሃይል በንፁሃን ላይ ዝርፊያ : ግድያና እገታ ፈፅሟል::

የኮሩ ፅህፈት ቤት መምሪያ ሃላፊ አርበኛ መምህር አብርሃም እያሱ በቀጠናው የተደረገውን አጠቃላይ አውደውግያና የተገኙ ድሎችን አስመልክቶ ላለማቀፍ ፋኖ ሚዲያ መረጃውን አጋርቶናል::

ዝርዝሩን በማታ የዜና እወጃችን በዩቱዩብ ቻናላችን Global Fano Media ይከታተሉ
1👍1
የጠላትን ተልዕኮ ተቀብሎ ሲንቀሳቀስ በነበረው የሰራዊት አባል ላይ እርምጃ መውሰረዱን 206ኛ ኮር አስታወቀ።

ህዳር 29/2018 ዓ.ም

በመልሶ ማደራጀት ትግበራው ሰራዊቱን በተቀናጀ መልኩ እያደራጀ የሚገኘው 206ኛ ኮር በሰራዊቱ መካከል የተሰገሰጉ የጠላት እጆችን እየቆረጠ ሲሆን በ14ኛ ክ/ጦር ጅበላ ሙተራ ሻለቃ አባል በነበረው አንተነህ ናዴ ላይ ክትትልና ምርመራ ከተደረገበት በኋላ ወንጀለኛ ሁኖ በመገኘቱ የድርጅቱን መመሪያና ደንብ መሰረት በማድረግ  ኮሩ እርምጃ ወስዶበታል።

ከጠላት ዋና አጀንዳዎች መካከል ሰራዊቱን እርስ በእርስ ማጋጨትና ማስከዳት ፣በፋኖ ስም ፀያፍ ተግባራትን መስራት በዋናነት የተቀበለው አንተነህ ናዴ ፦

1ኛ .የጅበላ ሙተራን ሻለቃ ሰራዊትን በማጋጨት
2ኛ .በአስገድዶ መድፈር
3ኛ . አባላትን በማስከዳት
4ኛ.ወታደራዊ ሚስጢሮችን ለጠላት አሳልፎ በመስጠት
5ኛ. ከማህበረሰቡ በማስገደድ ገንዘብ በመቀበልና በመዝረፍ
6ኛ. ከጠላት ኃይል አመራሮችና ቡድኖች ጋር ግንኙነት በመፍጠር ተልዕኮውን ጨርሶ በፋኖ አመራሮች ላይ ግድያ ፈፅሞ ወደ ጠላት ለመቀላቀል ሲነጋገር በተገኘ የስልክ ልውውጥ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ከላይ የተዘረዘሩ ወንጀሎችን ፈፅሞ በመገኘቱ ኮሩ አስተማሪ የሆነ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል።

የሰራዊቱን የውስጥ አንድነትና የትግሉን ህልውና ለማስቀጠል በትኩረት እየሰራ የሚገኘው 206ኛ ኮር በጅበላ ሙተራ ሻለቃ ተፈጥሮ የነበረውን ችግር በመፍታት ሰራዊቱ  አንድነቱን በማፅናት ማንኛውንም ግዳጅ መወጣት በሚያስችልበት ቁመና ላይ መገኘቱንም ኮሩ አክሎ ገልጿል።

በቀጠናው እረጅም እጆቹን አስገብቶ ሲንቀሳቀስ የነበረው ጠላት መሰል እርምጃዎችን ለማደናቀፍ የተንቀሳቀሰ ሲሆን አንተነህ ናዴ ላይ እርምጃ ከተወሰደ በኋላ ወደ ቸርተከል ከተማ የተንቀሳቀሰውን ጠላት የጅበላ ሙተራ ሻለቃ ወደ ኋላ መመለሷም በመረጃው ተመላክቷል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ የትግሉን ህልውና ለማስቀጠል የሰራዊቱን አንድነትና ደህንነት ማስጠበቅን የቅድሚያ ቅድሚያ አድርጎ እየሰራ የሚገኘው 206ኛ ኮር አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ በወንጀለኞች ላይ ድርጅታዊ እርምጃ መወሰዱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጧል።

የሰራዊታችን ደህንነት ለማይቋረጠው ትግላችን!

አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
3👍2
በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር 06/ ቆቦ ቀበሌ ላይ የጨፍጫፊው አገዛዝ የአማራ ህዝብ መኖሪያ ቤቶችን በሞርተር አውድሟል፣ ንፁሃኖችን ረሽኗል!!

ፀረ-አማራው የብልፅግና ስርዓት ወንበር አስጠባቂው ሀይል ትናንት ህዳር 28/2018 ዓ.ም የ103ተኛ አየርወለድ ኮማንዶ መነሻውን ከሸዋ ሮቢት ከተማ በማድረግ ወደ ቆቦ በማቅናት ለዘረፋና ለጥቃት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በአፋህድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ አምደፅዮን ኮር በራንቦና በ7ለ70 ክፍለጦር ሻለቆች እንዲሁም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ በራሳ አርበኛ ፋኖ ጦርና በቆቦና ተሬ ቀጠና አርበኞች ጦር ቅንጅት ለዘረፋ ወደ ቆቦ የተንቀሳቀሰው የጠላት ሀይል ትልቅ ኪሳራ ደርሶበታል።

በጀግኖቹ የተቀናጀ የማጥቃት ውጊያ የተመታው ዘራፊው የጠላት አየርወለድ በብስጭት በዙ 23 እና በሞርታር ተኩስ የማህበረሰቡን ቤት ኢላማ በማድረግ ቆቦ ላይ የመኖሪያ ቤቶችን ሲያወድም  በንግድና በግብርና ስራ የሚተዳደሩ ንፁሀኖች ተገድለዋል የንፁሃን አማሮች ሃብት ንብረት በጨፋጫፊው ሰራዊት ተዘርፏል !!

ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት !!
ድል አማራ ፋኖ !!
ድል ለአማራ ህዝብ !!

   @ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ !!
💔3
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር!

ህዳር 29/2018 ዓ.ም

ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር በአገዛዙ ሰራዊት ላይ የደፈጣ ጥቃት ፈፀመ!

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ላስታ ጄኔራል አሳምነዉ ፅጌ ኮር ጄኔራል ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር ህዳር 29/2018 ዓ/ም ከጧቱ 12:00 ሰዓት እስከ ቀትር 6:30 ሰዓት ድረስ በወሰደው የደፈጣ ጥቃት አይና ቡግና ከአይና ቅዱስ ሐርቤ መውጫ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የአገዛዙ ተላላኪ የሆነውን መከላከያን እና ሚሊሻን በደፈጣ ሶራ ሜዳ ላይ ሲያራግፉት ውለዋል።

በዚህ የደፈጣ ጥቃት የክፍለ ጦሩ 2ኛ ሻለቃ፣4ኛ ሻለቃ እና 3ኛ ሻለቃ አንድ ሻምበል በመናበብ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም ጠላት አንድ የፖሊስ መኪናና አምቡላንስ ቁስለኛ ይዞ ሲመለስ ከ12 በላይ ሲደመሰስ እዲሁም ሰባት ጥቁር ክላሽ 836 የብሬን ተተኳሽ እና 659 የክላሽ ተተኳሽ ተማርኳል።

የፋኖን ምት መቋቋም ያቃተው የአገዛዙ ሰራዊት በቡግና ወረዳ 03 መሰቀለ ክርሥቶስ ቀበሌ እየተባለ ከሚጠራው ቦታ ላይ የከብት ሳር ወይም መኖ እየተሸከመ ያገኘውን የ16 አመት ህፃን ከሁለት ቦታ ላይ በክላሽ በማቁሰል፣አውድማ በማለቅለቅ ላይ የምትገኝን የ17 አመት ልጃገረድ በክላሽ በማቁሰል፣በአዉድማ ላይ የተከማች እህል በማቃጠል፣መስቀለ ክርስቶስ ቀበሌ ላይ ቤት ለቤት በመዞር ህዝቡን ገንዘብ በመዝረፍ አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ የጭካኔ በትሩን አሳይቶ ሄዷል።

በዚህ ያላበቃው የአገዛዙ ሰራዊት አይና ከተማ ላይ ህዝቡን በየቤቱ በመግባት አስገድዶ በማስወጣት፣መነሀሪያ የሚገኝን ደንብ አስከባሪና ተሳፋሪን እንዲሁም በትምህርት ገበታቸው የሚገኙ ተማሪዎችን አስገድዶ በማስወጣት ስብሰባ ሰብስቦ ከልጆቻችሁ ጋር አስታርቁን እና አስታራቂ ሽማግሌ መልምሉ እንዲሁም የሦስት አመት ግብር ትከፍላላችሁ ሲሏቸው ህዝቡም ሽማግሌ አንመለምልም ልጆቻችን የወጡት እውነትን ይዘው ነው ከዚያ ውጭ ቡግና በጦርነት፣በድርቅና በወረርሽኝ ሲሰቃይ የነበረ ህዝብ የት አምጥቶ ግብር ይከፍላል እናንተ እኛን የፈለጋችሁን ገንዘብ ለመሰብሰብ ነው የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው የውስጥ መረጃዎች ያመላክታሉ።

በመጨረሻም ጠላት ክንዳችን ያውቀዋል፣ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የብልፅግናንና ጄሌዎቹን እስትንፋስ ለመቁረጥና የህዝባችንን ዕምባ የምናብስበት ቀን ቅርብ መሆኑንን ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን ሲሉ በአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ምክትል አዛዥ አርበኛ ኮማንዶ ሃምሳ አለቃ ፍቅሩ ሙሉዬ አሳስበዋል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ ፋኖ ሽፈራው አለልኝ መረጃውን አድርሷል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ
3
"ዓብይ አህመድ በማናሸንፈው ጦርነት ዘፍቆናል"
ዛሬ ህዳር 29/2018 ዓ.ም ከድተው ፋኖን የተቀላቀሉ ወታደሮች መልዕክት ነው።

የጠላት 96ኛ ክ/ጦር 5ኛ ሬጅመንት የሰራዊት ዓባላት ናቸው።
፩...አብዱልሰመድ ሀሰን እና
፪...ፍቃዱ በላይ ይባላሉ

ሁለት ክላሽኮቭ የጦር መሳሪያ : 8 ካዝና፣ 5ቦምቦ፣ ከ300 በላይ ተተኳሽ በመያዝ ፋሽስቱን አገዛዝ በመክዳት አፋብኃ በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ፪ኛ ኮርን ተቀላቅለዋል።

ዓብይ አህመድ በማናሸንፈው ጦርነት ውስጥ ዘፍቆናል። የግፍ አገዛዙን በመክዳት ከአማራ ፋኖ ጎን እንሰለፋለን በማለት እስከ ሙሉ ትጥቃቸው እንደከዱ ያስረዱት ወታደሮቹ ጓዶቻቸው ተመሳሳይ ውሳኔ እየወሰኑ ፋኖን እንዲቀላቀሉ ጥሪ ከስተላልፈዋል።

አፋብኃ በላይ ዘለቀ ዕዝ
ህዳር 29/2018 ዓ.ም
ሰበር ዜና

በመጨረሻም እጅ ሰተው ተማርከዋል!!

የወረዳው 10 ሚሊሻዎች ተማረኩ...
የአፋብኀ በላይ ዕዝ ራስ አሞራው ውብነህ 3ኛ ኮር ሰሜን ብርቅዬ ክ/ጦር ራስ ገብሬ ብርጌድ በሰሜን ቀጠና በዋግ ዝቋላ ወረዳ ጀብድ ፈፀመች።

ብርጌዷ በተጠና ኦፕሬሽን ህዳር 28/2018 ዓም የሎሌውና ባንዳው ብአዴን የጀርባ አጥንት የሆኑትን ቅጥረኛ ሚሊሻዎችን በጥይት ቆልታ ማርካለች።

የቀበሌ ሊቀመንበር : የፀጥታ አስተዳደር : የብልፅግና ፓርቲ ሃላፊ : የወጣቶች ጉዳይን ጨምሮ 10 ሚልሻዎች እስከነ ሙሉ ትጥቃቸው ማርከናቸዋል።

እነዚህ ቅጥረኞች በህዝባችንና በትግላችን ላይ አያሌ ጉዳት ሲያደርሱ የነበሩና በተኩስ ልውውጥ ዕድለኛ ሁነው እጃቸውን ወደ ሰማይ ቀስረው የማረክናቸው ናቸው። በርካቶች በፈቃዳቸው ፈርሰው እየተቀላቀሉ ሲሆን ቀሪው ፈቃደኛ ያልሆነው ላይመለስ እየተሸኘ ይገኛል።
2
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክ/ጦር በሰራዉ አስደማሚ ኦፕሬሽን ከአብይ አህመድ ተላላኪ ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ጋር ለተከታታይ 5 ቀናት በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ ኮሎኔል #የሽጥላ እና ሻለቃ #ታምራትን ጨምሮ በርካታ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች ተደምስሰዋል።

ለጊዜዉ ስማቸዉ ያልታወቀ ከመቶ አለቃ ጀምሮ እስከ ኮሎኔል ማዕረግ ያላቸው የመከላከያ አመራሮች ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል።

በአጠቃላይ በአምስት ቀን ፍልሚያ ዉስጥ:- ከ67 በላይ የጠላት ኃይል መደምሰስ ሲቻል ከ75 በላይ የጠላት ኃይልን ከባድ እና ቀላል ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል።

ከ32 በላይ ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያ፣03 አስቃጥላ የብሬን ጥይት፣ 01 የጦር ሜዳ መነፀር፣ 01 የስናይፐር መነፀር፣ ከ17 በላይ የእጅ ቦንቦች፣ ከ1500 በላይ የክላሽ ተተኳሽ፣ 2 የብሬን ሸንሸል፣ከ100 በላይ የዲሽቃ ተተኳሽ መማረክ (ማግኘት ) ተችሏል።

ለ4 ተከታታይ ቀናት ዘንዘን ከተባለ ቦታ በቀበሮ ጉድጓድ ዉስጥ ተቀብሮ የሰደድ እሳት በሆነዉ ፋኖ ተከቦ ሲወቀጥ ሰንብቶ መዉጫ ሲያጣ በዙ-23 እና በBM ከባድ መሳሪያ የታጀበ ተጨማሪ ሃይል ከፓዊ እና ከተለያዩ ቀጠናዎች በማሰባሰብ የተንቀሳቀሰ ሲሆን አሁንም በበረሃ መብረቆቹ 66ኛ ክ/ጦር የፋኖ አባላት እየተቀጠቀጠ ይገኛል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በ66ኛ ክ/ጦር የፋኖ ነበልባሎች የተቀጠቀጡት የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች በቀን 29/03/2018 ዓ.ም ዘንዘን ከተባለ ቦታ ላይ የተደመሰሱ ከፍተኛ መኮነኖችን #በሂሊኮፍተር  ተነስተዋል

@የአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
1🙏1
በላጎ ተወርዋሪ ልዩ ሻለቃ ደሴ ዙሪያ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒሊክ ዕዝ በላጎ ሻለቃ በደሴ ዙሪያ ወረዳ ሞቴ ከተማ ላይ ምሽግ ሰርቶ ሊቀመጥ የነበረው አድማ ብተናና ሚኒሻ ምሽጉን ሰርቶ አንድም ቀን ሳይውልና ሳያድር የበላጎ ተወርዋሪ ሻለቃ በዛሬው እለት ማለትም ህዳር 29/2018 ዓ.ም ምሽጉ ድረስ ዘልቆ በመሄድ መብረቃዊ የሆነ ጥቃት አድርሶ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::

ቀሪው የፋሽስቱ ብልፅግና አገዛዝ ሰራዊት እግሬ አውጭኝ ብሎ ወደ ደሴ ከተማ ፍርጥጦ ገብቷል::
በዚክም የተገኙ መሳሪያወች ክላሽኮፍና ተተዃሽም የተገኘ ሲሆን በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ የደረሰበትና የደነገጠ ሲሆን የበላጎ ሻለቃ ተወርዎሪ አናብስቶቹ በሰሩት መብረቃዊ ጥቃት በድል የታጀበውና ድላቸውን እያጣጣሙ ውሏቸውን ሞቴ ከተማ ላይ አድርገዋል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 29/2018 ዓ.ም
2
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክ/ጦር በሰራዉ አስደማሚ ኦፕሬሽን ከአብይ አህመድ ተላላኪ ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ጋር ለተከታታይ 5 ቀናት በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ ኮሎኔል #የሽጥላ እና ሻለቃ #ታምራትን ጨምሮ በርካታ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች ተደምስሰዋል።

ለጊዜዉ ስማቸዉ ያልታወቀ ከመቶ አለቃ ጀምሮ እስከ ኮሎኔል ማዕረግ ያላቸው የመከላከያ አመራሮች ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል።

በአጠቃላይ በአምስት ቀን ፍልሚያ ዉስጥ:- ከ67 በላይ የጠላት ኃይል መደምሰስ ሲቻል ከ75 በላይ የጠላት ኃይልን ከባድ እና ቀላል ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል።

ከ32 በላይ ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያ፣03 አስቃጥላ የብሬን ጥይት፣ 01 የጦር ሜዳ መነፀር፣ 01 የስናይፐር መነፀር፣ ከ17 በላይ የእጅ ቦንቦች፣ ከ1500 በላይ የክላሽ ተተኳሽ፣ 2 የብሬን ሸንሸል፣ከ100 በላይ የዲሽቃ ተተኳሽ መማረክ (ማግኘት ) ተችሏል።

😂ለ4 ተከታታይ ቀናት ዘንዘን ከተባለ ቦታ በቀበሮ ጉድጓድ ዉስጥ ተቀብሮ የሰደድ እሳት በሆነዉ ፋኖ ተከቦ ሲወቀጥ ሰንብቶ መዉጫ ሲያጣ በዙ-23 እና በBM ከባድ መሳሪያ የታጀበ ተጨማሪ ሃይል ከፓዊ እና ከተለያዩ ቀጠናዎች በማሰባሰብ የተንቀሳቀሰ ሲሆን አሁንም በበረሃ መብረቆቹ 66ኛ ክ/ጦር የፋኖ አባላት እየተቀጠቀጠ ይገኛል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በ66ኛ ክ/ጦር የፋኖ ነበልባሎች የተቀጠቀጡት የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች በቀን 29/03/2018 ዓ.ም ዘንዘን ከተባለ ቦታ ላይ የተደመሰሱ ከፍተኛ መኮነኖችን #በሂሊኮፍተር ተነስተዋል።

ከፋኖ ያዕቆብ ጌታሁን
የአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክ/ጦር ህ/ግንኙነት
🙏1
ሜ/ጀ/ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር
ጉና ክ/ጦር
ገ/መሥቀል ብርጌድ
ጣይቱ ሻለቃ

ገና መጫወቻ ከተማ 02 ቦታዎች ላይ በወሰደው የታቀደ የደፈጣ ጥቃት ጠላት ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደረሰበት።
🙏3
‎የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የከሰም 2ኛ ኮር አመራሮችን ይፋ አደረገ
‎=============
‎የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የከሰም ኮር 2ኛ ኮር ተሀድሶ በማካሄድ የኮሩ አመራሮችን ይፋ አድርጓል::

‎የከሰም 2ኛ ኮር ከተመሰረተ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ተሀድሶ ያካሄደው ይህ ኮር የኮር አመራሮችን የአፋብኃ ሴንትራል ኮማንድ አባል ረዳት እና የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የአስተዳደር ጉዳዮች ኃላፊ ረ/ፕሮፌሰር ማርከው መንግስቴ በተገኙበት ይፋ አድርጓል::

‎በዚሁ መሰረት የከሰም 2ኛው ኮር አመራሮች

‎1ኛ. አርበኛ መቶ አለቃ ይላቅ ብርሃኔ ዋና መሪ
‎2ኛ .አርበኛ ደጉ ተሥፋዬ ድርጂት ጉዳዮች ኃላፊ
‎3ኛ. አርበኛ እንዳልካቸው ግርማ የአሥተዳደር ጉዳዮች ኃላፊ
‎4ኛ.አርበኛ ሃምሳ አለቃ ጎሽመው ኃይሌ ወታደራዊ አዛዥ
‎5ኛ.አርበኛ እሸቱ ተ/ሚካኤል ም/አዛዥ ለኦፖሬሽናል።
‎6ኛ. አርበኛ ገረመው ታደሰ ም/አዛዥ ለአሥተዳደር
‎7ኛ.አርበኛ ፍቃደ ወርቁ ም/አዛዥ ለሎጀሥቲክ
‎8ኛ.አርበኛ ወርቁ ደርቤ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ
‎9ኛ . አርበኛ ምክሩ ብዙነህ የፋይናንሥ ኃላፊ
‎10.አርበኛ አሥር አለቃ ሙልጌታ ፍቅሬ ዘመቻ መምሪያ
‎11ኛ.አርበኛ ወርቁ ሽመልሥ ምክትል ዘመቻ መምሪያ
‎12ኛ.አርበኛ   ይታገሥ ጌታሁን ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
‎13ኛ.ትምህርትና ሥልጠና ኃላፊ----------
‎14ኛ. አርበኛ ሳሙኤል ፀጋዬ አደረጃጄት ዘርፍ ኃላፊ
‎15ኛ.አርበኛ ኃይሌ መሥፍን ኦዲት እና ቁጥጥር ኃላፊ
‎16ኛ.አርበኛ ይታገሥ ተሾመ ህግ ክፍል
‎17ኛ.አርበኛ ኮማንደር ነጋሽ አሠፋ ህግ ክፍል
‎18ኛ.አርበኛ ብርሃነ ቀፀላ ህግ ክፍል ኃላፊ
‎19ኛ.አርበኛ ሃምሳ አለቃ ሰለሞን አድነው ሥልጠናና ክህሎት ኃላፊ
‎20ኛ. አርበኛ እንግዳ በላይነህ ሃብት አሰባሳቢ ኃላፊ
‎21ኛ.አርበኛ አሸናፊ ብርሃኑ ፐረሶኔል
‎22ኛ አርበኛ ደመቀ ሥለሺ የኮር ፀኃፊ
‎23ኛ.አርበኛ ዘላለም ወርቅነህ ኦርዲናንሥ
‎24ኛ አርበኛ ክትነህ ሽፈራ ኦዲትና ቁጥጥር
‎25ኛ .አርበኛ አባይ ተሾመ ግዥ ክፍል
‎26ኛ.መረጃና ደህንነት ---------------
‎27ኛ አርበኛተፈሪ ሀይሉ የህዝብ ደህንነትና ፀጥታ ኃላፊ
‎28ኛ.አርበኛ አይናለም ዘረጋው ሴቶችና ማህበራዊ ዘርፍ ኃላፊ
‎29ኛ.አርበኛ ተመሥገን ባረጋ ህክምና ክፍል
‎30ኛ.አርበኛ አለማዬሁ ጌታነህ ኦዲትና ቁጥጥር
‎31ኛ.አርበኛ የሺጌታ ተገኝ ም/ ፋይናንሥ ኃላፊ
‎32ኛ. አርበኛ ሃምሳ አለቃ ሰይፈ ም/ሥለጠናና ክህሎት
‎33ኛ.አርበኛ ጋዜጠኛ አበባዬሁ ሰይፊ ሪፖርተር
‎34ኛ .አርበኛ ሰለሞን ገብሩ ባዶ አምሥት መሆናቸው ይፋ ተደርጓል።
‎እነዚህ አመራሮች የተሰጣቸውን ሀላፊነት ተቀብለው ወደ ስራ የገቡ መሆናቸውንም የአማራ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና 2ኛ  ከሰም ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል መረጃውን አድርሶናል::
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"
‎አፋብኃ ደቡብ  አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ዜና ክፍል።
2🙏2