ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.35K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.2K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር አዛዥ አርበኛ አብነው ታደሰ የተላለፈ የትግል ጥሪ!!

በመጀመሪያ ደረጃ ለሁሉም አማራ እና የህልውና ትግላችን ደጋፊዎች ለሆናችሁ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ ማለት የምሻው የአማራ ፋኖ የጄኔራል አሳምነው ፅጌን የኑዛዜ ቃል አክብሮ በቅንጅት እና በአንድነት እየታገለ መሆኑን በማብሰር ነው:: ቀሪው ስራችን አንድ እናት ድርጅት መመስረት ነው ይህም በቅርቡ እንደሚሳካ ጥርጥር የለኝም::

እንደምታውቁት እኛ አማሮች በፋሽስቱ አብይ አህመድ መንግስት የተከዳን እና ጥርስ የተነከሰብን ነን:: "አማራን ላጠፋ ነው" በማለት አብይ አህመድ ቃል በቃል ለኦሮሞ ተወላጅ የፌደራል እና ኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት መናገሩን የተከበሩ አቶ ታዬ ደንደአ ማጋለጣቸው ይታወሳል:: የማጥፋት ፕሮጀክቱ ትግበራ ከተጀመረ እነሆ ዓመታት ተቆጠሩ:: አብይ አህመድ እነ ጄኔራል አሳምነው ጽጌን ገድሎ ክልላችንንም አስወርሮ በክተት መክት ስትራቴጅ ህዝባችንን አስጭውፍጭፎ ሲያበቃ በድህረ ሰሜኑ ጦርነት ወቅት ፋኖን ትጥቅ አስፈትቶ አማራ ክልልን አባውራ የሌለው ቤት በማስመሰል ህዝባችንን ለማጥፋት እና የአማራን ጥንተ እርስት ለመቀማት አስቦ ብዙ እርቀት ሄዷል:: በዚህም መሰረት በህግ ማስከበር ስም አማራን ለመጨፍጨፍና ፋኖን ትጥቅ ለማስፈታት ዘመቻ መጀመሩና በርካታ ንፁሀንን መግደሉ ይታወቃል:: ይህን መንግስታዊ ክህደት በመቃወም አማራ አይጠፋም ትጥቁንም አይፈታም ብለን ወደ ጫካ በመግባት አፈሙዝ ወደ ህዝባችን ጠላት አዙረናል::

አማራ ሲፈናቀል፣ ሲገደል፣ ሲታሰር እና ሀብት ንብረቱ ሲዘረፍ ቆመን አናይም ይልቁንስ ባለጋራችንን እየገደልን እንሞታለን ብለን ፈንነናል::

ኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚኖሩ አማሮችን ፀረ ህዝቦች በጅምላ ሲያቃጥሏቸው እና የአንድት ነፍሰ ጡር እናትን ሆድ በስለት ሰንጥቀው ሽሉን ሲያፈነዱት አማራ የሆነ ፅንስ ጭምር መኖር የለበትም ብለው ማወጃቸው መሆኑን ልብ ይሏል::

አዲስ አበባ አማራ እንዳይገባ ሸኖ እና ሰንዳፋ ላይ በኦሮሞ መንገድ ሲዘጋበት እና በየጊዜው ሀገር አቋራጭ አውቶቢስ እየታገተ መንገደኞች ታፍነው ተወስደው በሸኔ ሲገደሉ፣ መስጅድ እና ቤተክርስቲያን ሲቃጠል አማኞችም ሲረሸኑ እንድሁም አማራ በመሆናቸው ብቻ ወገኖቻችን በኦሮሚያ ክልል በየጊዜው በኦነግ ሸኔ ሲገደሉ እና ሲፈናቀሉ ይህም አልበቃ ብሎ እዚሁ ክልላችን ውስጥ የአብይ መንግስት ተላላኪው ካድሬ ለአርሶ አደራችን በቂ ማዳበሪያ ላለማረቅብ ወስኖ አማራን በርሀብ እንቀጣለን ብሎ ቆርጦ ሲነሳ አስተውለናል:: ገበሬው "የገመድ መሬቴ ጦም አደረ" ብሎ ሰልፍ ሲወጣ "የጅራፍ ፓለቲካ" የሚል ስላቅ ነበር የብልጽግና መልስ::

ክልላችን ውስጥ የማዳበሪያ እጥረት የገጠመን ተረኞች ሆን ብለው ማዳበሪያውን ኦሮሚያ ክልል ከዝነውት ነበር:: ለአማራ ያላቸው ጥላቻ ከልክ ያለፈ ነው:: ስለሚፈሩን እንደምንም ብለው ለርሀብ እና ስደት እንድሁም ሞት እንድንጋለጥ ይሰራሉ:: ይህ ሴራቸው የገባውና ቀድሞ የነቃው ፋኖ በአራቱም የአማራ ግዛት አገር ያወቀው ፀሀይ የሞቀውን አኩሪ ገድል ፈጽሟል::

ወገኖቻችንን አትግደሉብን ብለን ሰልፍ ስንወጣ "ልቅሶ አይሰለቻቸውም ወይ?" በማለት ሰላማዊ ትግልን ብልጽግናዎች አጣጥለዋል:: ችግር አለ ችግሩ ይፈታ ስንልም ችግር ፍቱልን ያለውን አካል በማሰር ነው መልስ የሰጡን::

ሰላማዊ አማራጭ እንደማያዋጣ አውቀን እጅጉን ተገፍተን እና ግፍ ተፈጽሞብን ዘራችንም እየሳሳ ስለሆነ ነው የትጥቅ ትግል የጀመርነው:: ይህን የህልውና ትግል ለማደናቀፍ የሚጥር ባንዳ ወዮለት::


ባንዳ የሆንክ ሁሉ ዋ! ለራሴ በል:: እንግዲህ ባንዳን አንምርም:: አንድት ብርጭቆ ውሀ ውስጥ ጠብታ አንድ መርዝ ከተጨመረ ውሀው ይመረዛል::

ንፁህ ህዝብ ውስጥ አንድ ባንዳ ካለ ህዝቡ በየጊዜው ዋጋ ይከፍላል:: በአንዳንድ ባንዳ ምክንያት ህዝባችን ዋጋ መክፈል ስለሌለበት ተባብረን ባንዳን እናፀዳለን:: ለዚህ ተልእኮ ደግሞ ህዝባችን ሊተባበረን ይገባል::

የአማራን ህዝብ ክብር እና ጥቅም የሚያስከብር እንዲሁም አማራ የሚለውን ስም በበጎ የሚያስጠራ የአባቶቻችንን አትንኩኝ ባይነት የሚዘክር ድንቅ ስራ እየሰራ ያለው የአማራ ፋኖን ከድሉ አደባባይ ሳይደርስ ለመመለስ የሚታትር ባንዳ መጨረሻው ሞት ነው::

ከእንግዲህ በራሳችን ባንዳዎች ላይ የምንወስደው እርምጃ ከባድ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም::

ፋኖ የበረሃው ሙቀት እና የደጋው ብርድ፤ የስንቅ እጥረት ብሎም የጥቁር አማሮች እንቅፋትነት ሳይበግረው የክረምቱ ዶፍ ዝናብ ሳይገታው ለአማራ ህዝብ ዘብ ሆኖ ሌት ከቀን ትንቅንቅ ላይ ነው።

መከላከያ ሰራዊት የኦሮሞ ወንበር አስጠባቂ ዝና የአብይ አህመድ ገረድ ነው:: ይህን ሰራዊት አጥፍቶ አብይን ለፍርድ ማቅረብና የአማራን ህዝብ እንባ ማበስ የፋኖ ግደታ ነው::

አማራውያን ሆይ ሚሊሻ፣ አድማ ብተና እና ፓሊስ እንድሁም መከላከያ ውስጥ ዘመድ ወዳጅ ያላችሁ መክራችሁ ወደ ቤቱ አስገቡ። በተለይ ሚሊሻ በአስቸኳይ ቢቻል አዳሩን ወደ ቤቱ እንድገባ ይነገረው:: ይህ ሳይሆን ቢቀር እኛ እንግዲህ ባንዳን ስለማንምር በገቡበት ገብተን እንደመስሳለን::

ይህ አዋጅ ታውጆ የሚተርፍ ባንዳ ላይኖር ይችላል:: አንዳንዶች ተደብቀው ውለው ቢያድሩም መጨረሻቸው አያምርም!

መንግስትን አሽመድምደነዋል:: ክልላችንን ከ80 ፕርሰንት በላይ ተቆጣጥረናል:: ይህን ሀቅ ቢቢሲም ለዓለም አውጆታል:: በቅርቡ የማዕከላዊ መንግስት መቀመጫ የሆነችውን አዲስ አበባ ከተማን እንደምንቆጣጠር ተገማች ነው:: አዎ፤ ፋኖ በጎጃም እና ሸዋ እንድሁም በሸዋ እና ጎንደር ብሎም ወሎ ሰፊ ግዛት ተቆጣጥሮ እያስተዳደረ ሲሆን ወደፊት የሚያደርገው ግስጋሴም እንደቀጠለ ነው::

በምዕራብ ወሎ ግንባርም ከፋሽስቱ አብይ አህመድ መንግስት በርካታ ቀጠናዎችን ነፃ አውጥተን የጊዜያዊ መንግስት መዋቅር ዘርግተን ህዝባችንን እያስተዳደርን ነው::

የድል ባለቤት መሆናችን አይቀርም፤ እውነትን ስለያዝንና ግፍ አንገሽግሾን ስለተነሳን እናሸንፋለን ስለዚህ ባንዳ ሆይ ቶሎ ወደ ቤትህ ተመለስ::

በየእለቱ የወገኖቻችን ደም እየፈሰሰ ነው:: ተሰምቶ የማይታወቅ ግፍም በአማራ ምድር እየተፈፀመ ነው::

በያዝነው ወርም የካህን ሚስትን ጨምሮ በድምሩ 3 እመጫት እናቶች መካነሰላም ከተማ የሚገኘው አድማ ብተና ካምፕ ውስጥ በአንድ የፋሽስቱ መንግስት የፀጥታ ኃይል አባል መደፈራቸው ይታወቃል:: ከለላ ወረዳ ዉስጥም ቲርቲራ ታዳጊ ከተማ አጠገብ የቀነሶ መንደር ነዋሪ የሆነው አቶ ሁሴን ከማል የተባለው አርሶ አደር አጨዳ ላይ ሳለ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም በአድማ ብተናዎች እንደተረሸነ ለማረጋገጥ ችለናል::

ሰኞ ማለትም ህዳር 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጃማ ወረዳ ደጎሎ ከተማ ውስጥ አንድት ከአረብ ሀገር ተመላሽ እህታችንን መከላከያ ሰራዊት ተኩሶ ገድሏታል:: ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር በሚንቀሳቀስበት በምዕራብ ወሎ ግንባር ብቻ ሳይሆን በመላው አማራ ዘግናኝ ግፍ በህዝባችን ላይ እየተፈፀመ ነው:: ይህ የግፍ ግፍ አንገፍግፍ ሊቆም የሚችለው አንድ ሆነን መታገል ስንጀምር መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል::
2
ስለዚህ ከጠላት ጎን ተሰልፋችሁ ወገናችሁን እየወጋችሁ ያላችሁ የሚሊሻ፣ አድማ ብተና እና ፓሊስ እንድሁም መከላከያ ሰራዊት አባላት ከዛሬ ህዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ የምህረት አዋጅ ይፋ ስላደረግን ይህን ወርቃማ እና ታሪካዊ እድል እንድትጠቀሙበት ስንል ከወዲሁ እያሳሰብን ጠላትን ከድታችሁ ስትመጡ እኛ በበኩላችን ለምታስረክቡን ትጥቅ ተገቢውን ካሳ በመስጠት ወደምትፈልጉበት ቦታ ለመላክ ዝግጁዎች መሆናችንን እንገልፃለን:: አብሮን ለመታገል ፈቃደኛ ለሚሆነውም ሁኔታዎችን የምናመቻችለት ይሆናል::



መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም
🙏2
የአማራ ሰቆቃ በወልድያ ዩንቨርስቲ !

በአማራ ምድር በሰሜን ወሎ ዞን በወልዲያ ዩኒቨርስቲ የግቢ ተማሪዎች በፌደራል ፖሊሶች እየተደፈሩ ነው ሁለት ሴት ተማሪዎች ከጠፉ ከ3 ቀን በኃላ አንዷ ትላንት በፌደራል ፖሊስ ተደፍራ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድላ አንገቷ ታጥፋ ተጥላ ተገኝታለች አንዷ እስከ አሁን አልተገኘችም መረጃው እንዳይወጣ ሁሉም የዩኒቨርስቲው ሰራተኞች ተነግሯቸዋል።

ነገሩን አጠፋፍተው ሊያልፉ አስበው ግን ይሄ ነገርን ተደጋጋሚ እየተፈፀመ በመሆኑ መረጃው ለመውጣት ችሏል።

በተጨማሪ ደግሞ ቀን በቀን የቆሎ ተማሪዎችን ያተኮረ አፈና እየተደረገ ነው ሊያመልጡ የሚሞክሩትንም ተኩሰው እየገደሉ ነው ሚሊሻ እና ፖሊስ የየጁ ገነት 04 ቀበሌ እና ቲንፋዝ 02 ቀበሌ በታፈኑ ሰዎች ሞልቶ አገልግሎት አንሰጥም ከአሉ ሰነባብተዋል ።

27/ዐ3/2018 ዓ.ም
💔3
"የአፋር ሕዝብ በፌድራል መንግስት ተብዬው ስፖንሰርነት የተከፈተበተ ወረራ እንዲቀለበስ እየሰራን እንገኛለን" የአፋር ብሔራዊ አንድነት አብዮታዊ ግንባር (ኡጉጉሞ)

ከአፋር ብሔራዊ አንድነት አብዮታዊ ግንባር (ኡጉጉሞ) የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ!

የአፋር ብሔራዊ አንድነት አብዮታዊ ግንባር (ኡጉጉሞ) ባለፉት አንድ አመት አስደናቂና አመርቂ የመደራጀትና የማደራጀትን ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝና አሁን ላይ ወደ ሙሉ ማጥቃት ለመሸጋገር ሙሉ ዝግጅትችን ማጠናቀቃችን ስናበስር በታላቅ ደስታ ነው።

ብልጽግና መሩ ጦረኛው የአብይ አህመድ አገዛዝ ያለጦርነት ውሎ ማደር አይችልምና አገሪቱን የጦርነት ሜዳ ከአደረጋት እነሆ ስምንት ዓመታት ተቆጠሩ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብም በኑሮ ውድነት፣ በሰላም እጦት፣ በሙስና፣ ሌብነት :  ከአቅም በላይ በሆነ የግብር ብዝበዛ፣ በእገታ እና ወ.ዘ.ተ. እየተሰቃዬ ይገኛል። የብልጽግና አገዛዝ ጦርነት እስትንፋሱ ነውና ውድ የኢትዮጵያ ልጆችን በካኪ ልብስ እየጠቀለለ ወደ ጦርሜዳ በመሸኘት እናት ያለጦሪ ቀባሪ እየወረች ትገኛለች፤ ወጣቶች አጽማቸው የት እንደወደቀ ሳይታወቅ የአሞራ ቀለብ ከሆነ አመታት ተቆጠሩ፤ በመሆኑም ይህ ጦረኛ አገዛዝ እንዲገረሰስ እኛ የአፋር ብሔራዊ አንድነት አብዮታዊ ግንባር (ኡጉጉሞ) ሕዝባችን ከላላ አድርገን የአብይ አህመድ አገዛዝ ለመጣል ጠንካራ ስራዎችን እየሰራን እንገኛለን።

ስለሆነም በዛሬው ዕለት ሕዳር 28 ቀን 2018 ዓ.ም በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ ለመስጠት ተገደናል። የሚከተሉት ነጥቦችንም መላው የአፋር ሕዝብ ብሎም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና የአብይ አህመድ ጦረኛ አገዛዝ ከሕዝብ ጫንቃ ላይ እንዲወርድ የሚፈልግ ኃይል ሁሉ ትኩረት እንዲሰጥበት ማሳሰብ እንፈልጋለን።

1ኛ. አሁን ላይ የአፋር ሕዝብንና የአፋር መሬትን ቁማር በማስያዝ የጦር ሜዳ ለማድረግ እየሰራ ያለው የአወል አርባ አገዛዝም ሆነ አለቃው አብይ አህመድ እያደረጋችሁት ያለው ነገር ትክክል አይደለም፤ የአፋር ሕዝብም ሆነ መሬት ነጻ ሊወጣ ይገባል እያልን በተለይ በአፋር መሬት ውስጥ ያላችሁ "ሀራ መሬት/ነጻ መሬት" በሚል የተደራችሁ የትግራይ የሰላም ኃይል ነን የምትሉ የአፋር ክልልን በአስቸኳይ ለቃችሁ እንድትወጡ እናሳስባለን። በዚህ ቀጥተኛ ተጎጅ የምትሆነው የአፋር ሕዝብም እነዚህ ኃይሎች ክልሉን ለቀው እንዲወጡ ጫና እንድታደርግ እንጠይቃለን።

2ኛ. በሙስጠፌ መሐመድ የሚመራው የኢሳ ኃይል አሁንም የወሰንና የደንበር ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች በአፋር ሕዝብ ላይ ተከታታይ የሆኑ ኢ- ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ውድመት አሁንም ተጠናክሮ ቀጥሏል። በቀጣይ በምርመራ የምናጋልጠው ሁኖ ዛሬም በኢሳ ኃይሎች ልጃገረጆችን ጨምሮ እናቶች እየተፈሩና እየተገደሉ መሆኑን እየገለጽን የሚዲያ ኃይሎችና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማትና ተሟጋቾች የጉዳዩን አሳሳቢነት በመረዳት ትኩረት እንድትሰጡ ማሳሳብ እንፈልጋለን።

3ኛ. የአወል አርባ አገዛዝ የአፋር ሕዝብን ጥቅምና መብት የሚከራከሩ ምሁራንን፣ ወጣቶችን፣ የፀጥታ ተቋማት አመራሮችን ዛሬም እያሳደደ፣ እያሰረ እና እየገደለ ይገኛል። ከዚህ ድርጊቱ እንዲታቀብ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲታቀብ እያሳሰብን፤ ምሁራን፣ ወጣቶች፣ የፀጥታ ኃይሎች አጠቃላይ በአወል አርባ አገዛዝ እየተሳደዳችሁ ያላችሁ የአፋር ልጆች ወደ አፋር ብሔራዊ አንድነት አብዮታዊ ግንባር (ኡጉጉሞ) እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናቀርባለን።

4ኛ. ጦረኛውን የአብይ አህመድ አገዛዝ እየታገላችሁ ያላችሁ ኃይሎች፦ አብይ መሩ የብልጽግና አገዛዝ አንድ ቀን በሰጠነው ቁጥር ኢትዮጵያን በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ፣ በዲፕሎማሲ እያንኮታኮታትና እየደፈቃት የሚገኝ ኃይል መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው። ይሄን ጉዳይ በአግባቡ በመረዳት የአብይ አህመድ አገዛዝን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስወገድ እንተባበር ስንል የአፋር ብሔራዊ አንድነት አብዮታዊ ግንባር (ኡጉጉሞ) ጥሪውን በይፋ ያቀርባል።

በመጨረሻም አንባገነን አገዛዞች እንደወደቁት፣ ጭፈራዎቻቸውም እንደተሳደዱት ሁሉ አንባገነኑ የብልጽግና አገዛዝ በቁርጠኛ ታጋዮች ይወገዳል፤ የአንባገነኑ መሪም ሆነ አገልጋዮቹ ለፍርድ አደባባይ እንደሚቀርቡ የአለም ታሪክ ምስክር ነውና ይህም በቅርቡ ይሆናል። አንባገነኑ ሕዝብ መጨፍጨፍ የስልጣኑ መሠረት ነውና ሎሌዎቹ ከሕዝብ ጎን እንድትቆሙ የመጨረሻ ጥሪ እናቀርባለን።

ድልና ድምቀት ለአፋር ኡጉጉሞ!
የአፋር ብሔራዊ አንድነት አብዮታዊ ግንባር (ኡጉጉሞ)
ህዳር 28 ቀን 2018 ዓ.ም

Afar National Union Revolutionary Front/ANURF/
2
በማህበረሰቡ ላይ አሰቃቂ ዝርፊያ እየተፈፀመ ነው።
ሕዝብ አላማ ያደረገ ጥቃት እና ዝርፊያ በጎጃም ሕዝብ ላይ እየተፈፀመ ነው።

_____፩ ሰሜን ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ
የአገዛዙ ሥርዓት ጠባቂ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ዘረፈ።

በጦር ሜዳ ሽንፈት የተከናነበው የአገዛዙ ወንበር ጠባቂ በትናንትናው ዕለት ኅዳር 26/2018 ዓ/ም ሜጫ ወረዳ አማሪት ፣አውጣ(አንድነት) ፣ ጠለታ ፣ እድገት ፣ ተክለድብ ፣ ቆለላና እንጉቲ ቀበሌዎች በጋራ በመሆን ለመስኖ ልማት የሚውል የማዳበሪያና ለተለያዩ ወጭዎች አርሶ አደሮቹ በማህበር ያሰባሰቡትን ብር 2 ሚሊዮን በላይ ደብድበውና አሰቃይተው በኃይል ገንዘቡን በመቀማት በልማት ስራ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደርና የአርሶ አደር ልጆችን በማገት ገንዘብ አምጡ በማለት ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል።

በተጨማሪም ባችማ : አንድነት(ኢፊሳ ሀሙሲት)ና አብሮ መኖር ቀበሌ የሚገኙ አርሶ አደሩን ቤቱ ውስጥ ድንገት ከበባ በማድረግ ፋኖ የት ነው የሚገኘው መሳሪያም አላችሁ አምጡ በማለት በጥይት ደብድበውና አቁስለው ከቀላል እስከ ከባድ ጉዳት አድርሰው 5 ክላሽንኮቭ ጠመንጃና 13 የቃታ መሳሪያዎችን በመውሰድ 2 የግለሰብ ሱቆችንና መኖሪያ ቤቶችን አቃጥለዋል።
ሱቅ የተቃጠለባቸው ግለሰቦች:-
1ኛ, አታላይ አለሙ
2ኛ, ዘመነ ታምሩ ሱቅ የተቃጠለበትና 25ሺህ ብር የተዘረፋ ናቸው።
መሳሳሪያ አምጡ ተብለው በጥይት የተደበደቡ ቁስለኞች በማህበረሰቡና በቀጠናው የሚገኝ የአፋብኃ ምዕ/አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 102ኛ ኮር 22ኛ ክ/ጦር 2ኛ ሻለቃ ጦር ቀጠናውን ከጠላት በመታደግ ወደ ህክምና በማድረስ ክትትል እያደረጉ ይገኛል።

በመሆኑም ማህበረሰቡ ራሱንና የጦር መሳሪያውን ከወራሪው ኃይል በመጠበቅ በየቀጠናው ወደ ሚገኙ የፋኖ ካምፖች በመቅረብ የስርዓቱን ስልጣን ጠባቂ ኃይል በጋራ እንድንታገለው ክፍለ ጦራችን ጥሪ ያቀርባል።

_____፪ ሰሜን ጎጃም ጎንጅ ቆለላ ወረዳ

ራሱን "የሀገር መከላከያ" ብሎ የሚጠራው ተቅበዝባዡ የዐቢይ አሕመድ አረ መኔ አ ራ ጅ ሠራዊት ዛሬም የንፁሃንን የመኖሪያ ቤት አቃጥሏል።
አፋብኃ ምዕራብ ዐማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 102ኛ ኮር 33ኛ ክ/ጦር አንደኛ ሻለቃ ለተለያየ ግዳጅ አካባቢውን መልቀቋን የሰማው የዐቢይ አሕመድ አረ መኔ አ ራ ጅ ሠራዊት ዛሬም በጎንጂ ቆለላ ወረዳ ዜጋንሳ ቀበሌ አትርሴ በልስቲ የሚባል የአንድ ንፁሃን የመኖሪያ ቤት ሙሉ በሙሉ አቋጥሏል።
በዛሬው ዕለት በአገ ዛ ዙ ሙሉ የቤት ዕቃ፣ ወደ ቤት የተሰበሰበ እኽል፣ የቤተሰቡ አልባሳት፣ ወ.ዘ.ተ. እንደያዘ የወደመው የአቶ አትርሴ በልስቲ ቤት በብር ሲገመት ወደ ሰባት መቶ ሺህ ብር ሊያወጣ እንደሚችል ይገመታል።
#የተወሰነውን_የወደመ_ንብረት_እና_የሀብት_ግምት_ለማሳየት ያክል፦
#72_ዚንጎ ቆርቆሮ ቤት ግድግዳውን ሳይጨምር 250,000 ብር
አንድ ትልቅ በሬ 85,000 ብር
አንድ አህያ 10,000 ብር
15 ኩንታል ጤፍ 150,000 ብር
5 ኩንታል በቆሎ 20 ሺ ብር
2.5 ኩንታል ስንዴ 15 ሺህ ብር
1.5 ኩንታል ባቄላ 14 ሺህ ብር
1.5 ኩንታል አተር 16 ሺህ ብር
የቤት እቃ እና የቤተሰብ አልባሳት 120,000 ብር
#ጠቅላላ_ድምር 680 ሺህ ብር ተገምቷል።

በተጨማሪም በአካባቢው በሻይ ቡና አገልግሎት በሚተዳደሩ የንፁሃን ቤት በመግባት የሥራ ቁሳቁሳቸውን ሙሉ በሙሉ ማውደሙን ተጎጂዎቹ አሳውቀዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው ዐፋብኀ ምዕራብ ዐማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 102ኛ ኮር 33ኛ ክ/ጦር ጊዜያዊ መንግሥት አስተዳደር የጎንጂ ቆለላ ዋና አስተዳዳሪ ፋኖ አረጋ አበረ በተፈጠረው ችግር አዝነው፤ የአካባቢው ማኅበረሰብ የመረዳዳትና የአብሮነት እሴቱን በማጎልበት ተጎጂዎችን እንዲያቋቁሙ አስተያየት ሰጥተዋል።
በመኾኑም በአቅራቢያው የነበሩ ውስን የ33ኛ ክ/ጦር አባላት በጎንጂ ቆለላ ከተማ በከፈቱት ድንገተኛ ጥቃት ለዝርፊያ ወደ ዜጋንሳ የወጣው አውዳሚ ሠራዊት ተመልሶ ወደ ጉድጓዱ ገብቷል።

____፫ ምስራቅ ጎጃም እነብሴ ሳርምድር ወረዳ


በምስራቅ ጎጃም እነብሴ ሳርምድር ወረዳ በተለያዩ አካባቢዎች የፋኖን ብትር መቋቋም ሲያቅተው የብልፅግናው ሰራዊት ዝርፊያወችን እየፈፀመ ይገኛል።

በሰኞ ገበያ እና ድቦ ቀጠና በንፁሃን ላይ ዝርፊያውን እና የድብደባ ወንጀሉን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ከኛ ጋር ሆናችሁ ፋኖን አልወጋችሁም በማለት፦
➦ከ51 በላይ የግል ባለመሳራያ በሬውን ሸጦ የገዛውን መሳሪያ ቀምቷል
➦ ተዘግተው የነበሩ 13 ባለሆቴሎችና መኖሪያ ቤቶች ቁልፍ በመስበር ውስጥ ያሉ ሃብቶችን ሙሉ በሙሉ ተዘርፏል።
➦5 ባለትዳር ሴቶች ባሎቻችሁን አምጡ ተብለው ታስረዋል፤ 4ሰወች አሰቃቂ ድብደባ ተፈፅሞባቸው ሜዳ ተጥለዋል
➦ 28 የአካባቢወ ንፁሃን ከባድ ድብደባ ተፈፅሞባቸው በእስር ላይ ሲሆኑ ሁሉንም እስረኞ ፋኖ ተኩስ ከከፈቱ ቀድመው እንዲመቱ ለማድረግ እና ከፍተኛ የስነልቦና ጉዳት በማድረስ አረመኔያዊ ድርጊት በመፈፀም ላይ ይገኛል

ወንጀል የተፈፀመባቸው ግለሰቦችም
ከሰኞ ገበያ ቀጠና
በሬ ሸጠው የገዙት መሳሪያ የተወረሰባቸው
1. ደርብ ጌታቸዉ ክላሽ፣
2. አብይ ዮሀንስ ክላሽ፣
3. ይርሴ ክላሽ እና
በስም ያልተጣሩ 31 እንዲሁም 5 ሴቶች ፤
ድቦ ቀጠና=
1. መርሻ አክሊሉ ክላሽ፣
2. ሀብቴ ክላሽ፣
3. ወጣ ገበየ ክላሽ፣
4. መልካ ዘለቀ ክላሽ፣
5. መሰሉ ይመኑ ክላሽ፣
6. ልየው በላቸው ክላሽ፣
7 ሽፈራው ሙንየ እና ሌሎች 10
በድምሩ 51 መሳሪያ በመዝረፍ

3, የወደመ እና የተዘረፈ ሆቴል እና መኖሪያ ቤት
1. ትርንጎስጦታው =ሆቴል
2. ነበረ መለሰ =ሆቴል
3. አዳሙ አለባቸው =ሆቴል
4. ደርብ አድማሴ =ሆቴል
5. አኔ ይበልጣል =መኖሪያ ቤት
6. ተሜ ይልማ =መኖሪያ ቤት
7. የሹ ፈንታ=መኖሪያ ቤት
8. ጌትነት ይሜ=መኖሪያ ቤት
9. ሻምበል ይሜ=መኖሪያ ቤት
10. ምኒሊክ ይሜ =መኖሪያ ቤት
11. ተስፋው ታደሰ =መኖሪያ ቤት
12. ሙንየ ምሬ =መኖሪያ ቤት
13. መልካሙ አብየ =መኖሪያ ቤት
የተሰበረ ስለጠፋባቸው = ውለታው ወሌ፣

ከፍተኛ ድብደባ የተፈፀመባቸው ሜዳ የተጣሉ
1. ጌታቸው ደርብ፣
2. ደርብ አድማሴ፣
3. በላይነህ ተረፈ
4. መርሻ መሰሉ

ድብደባ ተፈፀሞባቸው የታሰሩ ወጣቶች
1. ማማር መንጋው፣
2. ሙሉቀን ዳምጤ፣
3. ውቡ ተምትም፣ በስም ያልተጠቀሱ ከ25 በላይ ንፁሃን ወጣቶች ናቸው።


___፬ በሰሜን ጎጃም አዴት ወረዳ

የአማራን ህዝብ ያነጣጠረ ጥቃት በኦህዴድ መራሹ አገዛዝ ሰራዊት በህዝቡ ላይ የንብረት ጉዳት አደረሰ።
ሰሞኑን ከሌላ ተጨማሪ ኃይል በማምጣት በይልማና ዴንሳ ወረዳ ላይ ኀይሉን በብዛት በማሰማራት የተንቀሳቀሰ ሲሆን ከተንቀሳቀሰባቸው ቦታዎች መካከል ዴንሳ ባታ፣ድንጅ፣አግታ፣አንጋርና ተጨማሪ ቀበሌዎች ላይ በህዝቡ ላይ ከባድ ውንብድናና ዝርፊያ ፈፅሟል።
1👎1
1.የይግረመው ሽቴን 1 በሬ
2.የጋሻው ሞገስ 1ላምና 1በሬ
3.የአንተነህ ምስጋናው 1በሬና 1 ጊደር
4.ክንዴነህ አድማሱ 1ላምና 2 ጊደር
5.አወቀ በላይነህ 2በሬ
6.ቀኔ ጌቴ 1ላምና 1በሬ
7.መልካሙ አገኘሁ 1ላም
8.አዱኛ ይታይህ 1ላም
9.የ፲አለቃ ንብረት 5በግ
10.የጎላ ንግሩ 4በግ
11.የመልካሙ አገኘሁን 3በግ በአጠቃላይ 14ላምና በሬ እና 12 በግ እያረደ ሲበላ ሰንብቶ የተረፈውን ወደ ከተማ ጭኖ ሲወስድ
➯ በተጨማሪም
12.4ሞተርና 3ባጃጅ በማቃጠል፤በአቶ ጌታሲል ቢሻው የልብስ ስፌት ቤት ውስጥ ያለን ጣቃ ከልብስ መስፊያ መኪና ጋር ሙሉ ጣቃውን በመዝረፍ የውንብድና ተግባር ሲፈፅም፦
13.የአቶ ድረስ ሞላን የወፍጮና የባጃጅ ቅያር እቃዎችን ሙሉ ለሙሉ ዘርፎ ወስዷል።
14.የደረጀ አያሌውን ቤት ሙሉ በሙሉ ዘርፈው ቀሪውን አውድመዋል።
➯ አሁንም ከዚያው ዴንሳ ባታ ቀበሌ ላይ አርሶ አደር ቤት በመግባት እህልን በመመረዝ ቤተሰቡ በሙሉ እንዲያልቅ ለማድረግ ሚሊሻው መርዝ መጨመሩን የተመለከተ ግለሰብ ለባለቤቶች በሰጠው ጥቆማ የተመረዘውን እህል በማስወገድ ቤተሰቡን መታደግ ተችሏል።

አግታ ቀበሌ ላይ
በመግለጫችን የወረዳው የብል*ፅግና አመራር ሁሉንም አዋሳኝ የገጠር ከተሞች የትራንስፖርት እገዳ አድርጎ ወላድ እናቶችና ፅኑ ህሙማን ተጨማሪ ህክምና ሳያገኙ ለህልፈተ ህይዎት መዳረጋቸውን ገልፀናል። እናም ይህ አገዛዝ ህዝባቸውን ሲያገለግሉ የነበሩ ባለባጃጆችን
1. ወጣት አከለን በመግደል ባጃጁን አቃጥለዋል።
2.የወጣት ያየው ሰው አታላይን ፋራ ሞተር
3.የወጣት ጌታየ ሙሉን ፍራ ሞተር
4.የወጣት አበባው ጌትነት ባጃጅ
5.የወጣት አንሙት ገብሬ ባጃጅ
ሲወስዱ
6.የወጣት ወለላው ደሴን ሞተር በማቃጠል ሳምሰንግ ሞባይሉን እንዲሁም የየንጉሴ ዳኛውን ተች ስልክ ዘርፈው ወስደዋል
7.አየለ መኳንንት የተባለን ነጋዴ 97 ኩንታልና 2ኢታሊይ ሚዛን
8.ከአቶ ዘሩ ያየህ ቤት ሰብሮ በመግባት 15000ብር
9.የወይዘሮ የንጉሴን መቀነት በማስፈታት 1500ብር
10.የአቶ አውግቸው ዘሪሁንን ሙጢ ጓንዴና 3000ብር የተገዛ የሌሊት ብርድልብስ
11.የአቶ አታላይ ከበደን ሙጢ
12.የአቶ ሙላት መኮነን ሚኒሽር
13.የአቶ ሀብቴ ወርቁን ማይካ ክላሽና ቤተሰቡን በሬ ይልማ የተባለን ግለሰብ አፍኖ ወስዷል።
14.የተዋበ ክንዴን የግል ልብሱን በሙሉ
15.የቻሌ ጌቴን ፀረ አረም መድሃኒት ቤት በመስበር ዝርፊያና ውድመት አድርሰዋል።

በአጠቃላይ ንፁሃን ማህበረሰብን ያነጣጠረ ግድያና ዝርፊያ በሚሊሻና በጨፍጫፊው መከላከያ ተፈፅሟል።

በተመሳሳይ ምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን ወረዳ ፣ደብረኤልያስ ወረዳ እና ባሶሊበን ወረዳ ፣እንዲሁም በምዕራብ ጎጃም ደንበጫ ወረዳ ከባድ ዝርፊያ ዝርፊያ የተፈፀመ በመሆኑ በዝረዝር ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የምናደርስ ይሆናል።

ሕዝባችን የገባበትን የህልውና ስጋት ለመቀልበስ በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚገኝ አማራ የሆነ ሁሉ ይህን አስከፊ ድሪጊት በሚችለው ሁሉ ሊቃወመው ይገባል።

አዲስ ትውልድ፣አዲስአስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !

አፋብኃ| ቴወድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ህዳር 29/2018 ዓ.ም
"የሐሰት ድምፅ ቅጂው አገዛዙ ድል እንደራበው የሚያሳይ ነው"

የአገዛዙ ብልፅግና የሐሰት ዘገባዎች ሲገለጡ እርቃኑን እያስቀሩ መሳቂያ መሳለቂያ እያደረጉት ነው:: ከሰሞኑ በማስረሻ ሰጤ ክህደት ተጠቅሞ ድርጅቱን ጭምር ተደራደረኝ ያለው ብልፅግና ንፁሃን ታጋዮችን ጭምር ስም እያጠፋ የፋኖና ህዝብን አንድነት ለማላላት : የመሪዎችን ግንኙነት ለመሸርሸርና የአንድነት ውይይቶችን ለማበላሸት ጥረት ቢያደርግም ሊሳካለት ቀርቶ የህዝቡ ምላሽ የፌዝ ሳቅ ሆኗል : የነአብይ አህመድ ድራማ ጠላቴ ብለው ለፈረጁት ሕዝብ ይቅርና ለራሳቸው ሎሌ አገልጋዮች እንኩአን የሚያሳምን አልሆነም::

የጎንደር ጠቅላይ ግዛት እዝ ዋና አዛዥ የሆነው አርበኛ ተሾመ አበባው እጁን ሊሰጥ ነው የሚለው የሐሰት የድምፅ ቅንብር መሰረታዊ ስህተት በራሱ በአርበኛው አንደበት ተነግሯል:: አርበኛው "በዚህ ትግል ብቻዬን እንኩአን ብቀር የምሰጠው እጅ የለም" ሲል ቁርጡን ነግሯቸዋል::

የልጅ አዋቂው : የጦር ፊታውራሪው : ደግ ቅን ታጋዩ አርበኛ ተሾመ አበባው "ጠላት ከፈለገ ያለንበትን ያውቀዋል ይሞክረን : እንደየአመጣጡ እናስተናግደዋለን ብሏል::

@አለማቀፍ ፋኖ ሚዲያ
የፋኖ ድምፅ
1🙏1
የድል ዜና

‎የከሰም ኮር ኃይለማርያም ማሞ ክ/ጦር አራተኛ ቦጋለ ሬጅመንት ከአባት አርበኞች ጋር በመጣመር ታላቅ ጀብዱ ፈጸመ
‎===========
‎የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የከሰም 2ኛ ኮር ኃይለማርያም ማሞ ክ/ጦር አራተኛ ቦጋለ ሬጅመንት ከአባት አርበኞች ጋር ተቀናጅቶ ሸኖ ከተማ በመግባት በጠላት ላይ ከባድ ኪሳራ አድርሷል::

‎የኃይለ ማርያም ክ/ጦር አራተኛ ቦጋለ ሬጅመንት ከአባት አርበኞች ጋር ከአዲስ አበባ 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ሸኖ ከተማ ድረስ ዘልቆ በመግባት የብልጽግናን አራጅ ሰራዊት ረፍርፎታል::

‎የብልጽግና ዙፋን አስጠባቂ ሰራዊት የሸኖ ከተማን እና የአካባቢውን ማህበረሰብ አስገድዶ ለስብሰባ እያስወጣ ባለበት ወቅት የኃይለ ማርያም ማሞ አራተኛ ቦጋለ ሬጅመንት ከአባት አርበኞች ጋር ሰርጎ በመግባት ሶስት የጠላት ኃይል እስከወዳኛው ሸኝተው አምስቱን ደግሞ አቁስለዋል::

‎የወገን ምት ያበሳጨው የብልጽግና ዙፋን አስጠባቂ ሰራዊት ያለ የሌለ ግትልትል ኃይሉን ከሰንቦና ጫጫ አግተልትሎ በሶስት ግንባር አውደ ውጊያ ቢያካሄድም በሚገባው ቋንቋ በማናገር ልክ አስገብተውታል::

‎ይህ ግትልትል ሰራዊት በፊጦ አላ መሥኖ ቀበሌ ግንባር÷ በጫጫ መንደር በአራጌቻ ግንባር እና በሸኖ ከተማ ዳር ለማጥቃት ቢሞክርም አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ እና ተዋርዶ ወደመጣበት ጥሎ ፈርጥጧል።

‎ በመጨረሻም  የኃይለማርያም ማሞ ክፍለ ጦር አራተኛ የቦጋለ ሬጂመንትና የአባት አርበኞች ጠላት ያቀደውን   የሥብሠባ አጀንዳ እንዲቋረጥ በማድረግ በሰላም ወደ ምድብ ቦታቸው ተመልሰዋል።

‎     መረጃውን ያደረሰን የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ከሰም ኮር የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ አርበኛ ይታገሱ  ጌታሁን  ነው።
‎                 " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"
‎አፋብኃ ደቡብ  አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ዜና ክፍል።    
‎ህዳር 29/2018 ዓ.ም
🙏1