ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.21K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
#በምዕራብ_ሐረርጌ_የታፈነው_ጩኸት_እና_በአርሲ_የቀጠለው_ዘር_ፍጅት!

በምዕራብ ሐረርጌ ዞን፣ ጭሮ ወረዳ፣ ላሎ ጉዶ ቀበሌ፣  ኢፈ ባስ(ifabaas) በምትባል የገጠር መንደር ውስጥ በኅዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 እልፌ ተስፋ ወሌ የሚባሉ እናት በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል። በዚኹ ቀበሌና በአጎራባች ቀበሌዎች ያብዶ ሸንበቆ፣ ረብሱ፣ ሼክ አደም፣ ሉጎ በርካታ ሃይማኖትና ማንነትን ማዕከል ያደረጉ ጭፍጨፋዎች የሚካሄዱባቸው ናቸው። ብንናገርም ሰሚ የለም። ሕዝቡና ሚዲያውም እኛን ረስቶናል ይላሉ የአካባቢው ነዋሪዎች በምሬትና በፍርኃት ተውጠው።

በወረዳው በቅርቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት የኾኑ ተፈሪ መንገሻ ከነ ባለቤቱ ቀለሟ በለጠ ጋር፣ ባለው መንገሻ፣ አሳምነው አባይነህ የተባሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በአሰቃቂ ኹኔታ በስለትና በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል፤ በርካቶችም ቆስለዋል። ግድያውን የሚፈጽመው በአካባቢው ሰዎች አጠራር ኦነግ ሸኔ(ራሱን ኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል) ነው።

ይኽን መረጃ እያጣራን ባለንበት አፍታ በአርሲ ዞን በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ፣ በቀቅሳ ቀበሌ በአጨዳ ላይ የነበሩ ከ19 በላይ ገበሬዎች ኅዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ታፍነው መወሰዳቸውን ከቦታው ለማረጋገጥ ችለናል። በዚኹ አካባቢ በቅርቡ ወንድማማቾችን ጨምሮ ሦስት ንጹሓን እንደተገደሉ ይታወሳል።

እናት ፓርቲ በምዕራብ ሐረርጌ ባሉ በርካታ ቀብሌዎች በጥንቃቄ ተደብቆ የሚካሄድውን ጭፍጨፋና እገታ፤ እንዲኹም በአርሲ እየተካሄደ ያለውን ዘር ፍጅት በጽኑ እናወግዛለን፤ የታገቱትም ያለምንም ቅድመ ኹኔታ እንዲፈቱ እንጠይቃለን።

ፈጣሪ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!

እናት ፓርቲ
ኅዳር ፲፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
1💔1
ፋኖ ጠላትን ስቦ በመምታት የውጊያ ስልት ባደረገው ማጥቃት ድል መቀዳጀቱን አስታወቀ!

በምስራቅ አማራ ቀጠና በደላንታና በአምባሰል ወረዳ አዋሳኝ ልዩ ስሙ ተሬ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ጠላትን ስቦ በምታት የውጊያ ስልት ፋኖ ባደረገው ማጥቃት፡ በርካታ የብልፅግና ቡድን ተላላኪ ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ መደረጋቸውን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።

በአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒሊክ ዕዝ በቅርቡ በኮር ደረጃ ከተዋቀረበት እለት ጀምሮ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ በጠላት ላይ ከባባድ ጥቃቶችን በመሠንዘር ታላላቅ ድሎችን እየተቀዳጀ የሚገኘው የደጋው መብረቅ ኮር፡ ትናንት ህዳር 18/2018 ዓ/ም ከረፋድ ጀምሮ እስከ አመሻሹ በተሬ ቀጠና ባደረገው ተጋድሎ በጠላት ላይ ከባድ የሆነ የሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረስ ችሏል።

በትናቱ ውጊያ ፋኖ የጠላትን ኃይል ወደ ተሬ ቀጠና ስቦ ካስገባው በኋላ ነው መውጫ መግቢያውን በመዝጋት ማጥቃት የጀመረው የተባለ ሲሆን፡ በዚህም በርካታ የፀረ አማራው ብልፅግና ቡድን ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ ሲደረጉ ቀሪዎቹ ደግሞ የወደቁ ጓዶቻቸውን ሳያነሱ ወደ ተንታ ወረዳ መፈርጠጣቸውን መረብ ሚዲያ ከደጋው መብረቅ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለማረጋገጥ ችሏል።

በተሬ ቀጠና በርካታ የጠላት አ*ስ*ከ*ሬ*ን በየአርሶ አደሩ ማሣ ወድቆ እንደሚገኝም ነው የተገለፀው።
1🙏1
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒሊክ ዕዝ የደጋው መብረቅ ኮር በፋሽስቱ ሰራዊት ላይ ከባድ ጥቃት ተፈፅሟል!

የደጋው መብረቅ ኮር ፅናት ክፍለ ጦር ቅስፈታዊ ጥቃትን በጥላት ላይ በመክፈት ከፍተኛ ድልን ተጎናፅፈዋል!!!
ተንታ መገንጠያ(ተሪ) ላይ ከሁለት ወረዳ ያመጣውን የፋሽስቱን ሰራዊትን ወደ ደሴ ለማሻገር ሲሞክር ቅስፈታዊ የደፈጣ ጥቃት ተፈፀመበት።
ህዳር 19/2018 ዓ/ም ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ላይ የፅናት ክፍለጦር ባደረገችው የደፈጣ ኦፕሬሽን በርካታ ሙትና ቁስለኛ ተደርገዋል። የጥላት ሰራዊት በመኪና እየተንቀሳቀሰ ሳለ ከፋኖዎች በደረሰበት የደፈጣ በትር በርካቶች በመኪናው ውስጥ እያሉ በተሰነዘረ ጥቃት ሙትና ቁስለኛ የተደረጉ ሲሆን ቀሪዎች ከመኪና እየወረዱ እያለ ተቀድሸው ተሸኝተዋል። ከደላንታ እና ከተንታ ወረዳ በጥምረት አዋጥቶ ወደ ደሴ ሊያሳልፍ በነበረው የጥላት ሰራዊት ላይ የፅናት ክፍለጦር ፋኖዎች አፍ በእጅ የሚያስጭን ድልን ማስመዝገብ ችለዋል።

ከፋኖዎች በተሰነዘረበት ዶፍ ያነባ ጥቃትን መቋቋም የተሳነው ጨፍጫፊው የፋሽስቱ ሰራዊት እስሳዊ ድበራው ከሞት ሳይታደገው የአሞራ እራት ተደርጓል። ህዳር 18/2018 ዓ/ም ማለትም በትናንትናው እለት በዚሁ ቦታ ላይ የጥላት ሰራዊት በደረሰበት ከፍተኛ ጥቃት
ሽንፈትን የተከናነበው የፋሽስቱ ሰራዊ ሙትና ቁስለኛውን ሳያነሳ የፈረጠጠ ሲሆን፤ዳግም በዛሬው እለት የክፍለ ጦሯ ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ የሲሳይ ተሾመ(ጨልጤ)ን የእስናይበር ብራቅና ቅደሻ ጀባ ተብለዋል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
የደጋው መብረቅ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ህዳር 18/2018 ዓ.ም
🙏1
ፋኖ በተቆጣጠራቸዉ ቀበሌዎች ህዝባዊ ዉይይቶች ተጠናክረው መቀጠላቸዉ ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ  ኃይል ደቡብ አማራ ቀጣና አሳምነው ዕዝ ከሰም ኮር ኃይለማሪያም ማሞ ክፍለጦር በተቆጣጠራቸዉ አካባቢዎች ከማህበረሰቡ ጋር የተሳካ ዉይይት አካሂዷል።

ዉይይቱ ከሀገረማሪያም ከሰም ወረዳ ሾላ ከተማ 5 ኪ.ሜ ባልሞላ ቅርብ ርቀት ተካሂዷል።

 በሸዋ ከሰም ሀገረማሪያም ወረዳ ካሉ 21 ቀበሌዎች ዉስጥ የሀይለማሪያም ማሞ ከፍለጦር 19 ቀበሌዎች ተቆጣጥሮ እያስተዳደረ ይገኛል። ከተቆጣጠራቸዉ 19 ቀበሌዎች አንዱ በሆነዉ ጎርፎ ቀበሌ፣ ማህበረሰቡን በመሰብሰብ በወቅታዊ  ጉዳይ ላይ ውይይት አድርጓል።

በማህበረሰቡ በኩል በርካታ ሀሳቦች እና ጥያቄዎች ተነስተዉ የተሳካ ዉይይት የተካሄደ ሲሆን ከማህበረሰቡ የተሰነዘሩ ሀሳቦች እና ጥያቄዎች ተገቢ በመሆናቸዉ የማስተካከያ እርምጃ እንደሚወሰድ ክፍለጦሩ አስታዉቋል።

ከዚህ በፊት የነበሩ ክፍተቶች እና የአሰራር ችግሮች እንዳይደገሙ ማህበረሰቡ ከፋኖ ጋር በመሆን አካባቢው እንደሚያስከብር ስምምነት ላይ የተደረሰ ሲሆን በማህበረሰቡ በኩል የተነሱ ወቅታዊ ችግሮች እንዲፈቱ እና አፋጣኝ ምላሽ እንዲያገኙ ማህበረሰቡ  ጠይቋል።

የዉሀ እጥረት ችግር እንዲቀረፍ፣የሲቪል አስተዳደር እንዲቋቋም፣በአገዛዙ  አገልጋይ ሰራዊት ጉዳት የደረሰባቸዉ የህዝብ መገልገያ ተቋማት እንዲጠገኑ፣ከፖለቲካ ነፃ የሆኑ እንደ ግብርና፣ትምህርት እና ሌሎችም ተቋማት ለማህበረሰቡ ተገቢዉን አገልግሎት እንዲሰጡ በማህበረሰቡ በኩል የተነሱ ጥያቄዎች ሲሆኑ ችግሮችን እና የተነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነዉ ዕዝ ኃይለማርያም ማሞ ክፍለጦር አመራሮች ተናግረዎል።


በዉይይቱ የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነዉ ዕዝ የሃይለማርያም ማሞ  ክፍለጦ ዋና ሰብሳቢ  አርበኛ ደመላሽ መንግስቴ፣ የሃይለማርያም  ማሞክፍለ ጦር ሲቪል አደረጃጀት  ሀላፊ አርበኛ ኢንጂነር እደገው ሽፈራው እንዲሁም የሃይለማርያም  ማሞ ክፍለ ጦር ፓለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አርበኛ  መምህር ሔኖክ ጌትዬ እና የሃይለማርያም  ማሞ ክፍለ ጦር ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ  መለሰ ካሳዬ  ተገኝተዉ ከማህበረሰቡ ጋር የተሳካ ዉይይት አካሂደዋል።

ዉይይቱ ጊዚያዊ የሲቪል አስተዳደር በመምረጥ እና በማደራጀት የተጠናቀቀ ሲሆን ዉይይቱ በሌሎች ቀበሌዎችም ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የሃይለማርያም ማሞ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ኃቀኛዉ ይታፈር መረጃዉን አድርሶናል።

https://t.me/+APfg2ZKNKrhhMTlk
1🙏1
ሰበር ዜና

በጎጃም ግንባር ከመሸ የጠላት ሀይል በጋራ ሆነው ፋኖን ተቀላቀሉ::

በዛሬዉ እለት ህዳር 19/2018 ዓ.ም ዲጎ ፅዮን ከመሸገዉ 25ተኛ ክፍለ ጦር አንደኛ ሬጅመንት ከመከላከያ በመውጣት ፋኖን ተቀላቅለዋል።

1) ዮናስ ዘገየ ጥቁር ክላሽ እና 220 ጥይት
2) ሰለሞን ሳሙኤል
3) ስጦታ በሪሁን
4) አብዴ ጀማል አንድ ኮርያ ክላሽ እና 220 ጥይት በመያዝ ቴወድሮስ እዝ 54 ክፍለ ጦርን  ተቀላቅለዋል።

መረጃው የቴወድሮስ እዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ነው

በተመሳሳይ ዜና
የአፋብሃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር ስቦ ማስከዳትን በአግባቡ አየተጠቀመበት ይገኛል።

በዚህም በዛሬው እለት
1) አረጋ አበባው .... ኮሪያ ክላሽ ከ
150 የክላሽ ጥይት ጋር
2) መልሰው ክንዱ .... ኮሪያ ክላሽ ከ90 ጥይት ጋር ከፈለገ ብርሃን ከተማ 14ኛ ክ/ጦር 
3) ሸግየ ዳኝ ከግንደወይን ከተማ ምኒሻ መዋቅር አብራራው መሳሪያ ከ30 የብሬን ተጠኩአሽ ጋር : በአጠቃላይ 240 የክላሽ እና 30 የብሬን በድምሩ 270 ጥይት በመያዝ
ፋኖን ተቀላቅለዋል::

@የቴወድሮስ እዝ 2ዐ1ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 19/2018ዓ.ም
1🙏1
ሰበር ዜና

በአልዩ አምባ ከተማ በተደረገው ፍልሚያ የአድማ ብተና አዛዥን ጨምሮ አንድ አይሱዝ ሙሉ የአገዛዙ ኮማንዶ ተደመሰሰ።

‎በአንኮበር ወረዳ አልዩ አምባ ከተማ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር  ሰር የሚገኙት ጣይቱ ክፍለጦር እና ወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለጦር በተውጣጡ ሻለቆች በተደረገ ፍልሚያ በጠላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል:: በአንኮበር እና አልዩ አምባ ከተማ መካከል የምትገኝ ልዩ ቦታው ጥድ አምባ የሚባል ቦታ ላይ ለዕገዛ የመጣ የአገዛዙ ኮማንዶ አንድ አይሱዝ ሙሉ ተደምስሷል።

‎በተጨማሪ በአልዩ አምባ ከተማ በተደረገው ፍልሚያ የአድማ ብተና አዛዥ የሆነው አማረ የተባለ ፀረ አማራ የአገዛዙ ቀኝ እጅ በጀግኖቹ እርሳስ ከባድ ጉዳት ደርሶበት በከፍተኛ  ህክምና ላይ ይገኛል።

‎እንዲሁም አንድ የአድማ ብተና የሻምበል አመራር  በአናብስቶቹ አፈሙዝ በደረሰበት ምት አንገቱ ላይ ተመቶ በሒወት እና በሞት መካከል እንዳለ ለማረጋገጥ ተችሏል።
በተጨማሪም  የአድማ ብተና ተመራጭ የሆኑ የቡድን መሳሪያ ተኳሾች አንድ የስናይፕር እና የብሬን ተኳሾች ከነመሳሪያቸው በወገን ጦር በቦንብ ጋይተዋል።

‎ጥድ አምባ የምትባል ቦታ ላይ  አንድ አይሱዝ ሙሉ ከተደመሰሰው ውጭ በተጨማሪ በአልዩ አምባ ከተማ በነበረው ፍልሚያ  ከጠላት በኩል በውስጥ በደረሰን መረጃ መሰረት 13 የአገዛዙ ጥምር ጦር እስከወዲያኛው የተሸኙ ሲሆን 18 የሚሆኑ ከባድ ቁስለኛ ተደርገዋል።

በአውደውጊያው ‎7 ነፍስ ወከፍ መሳሪያ : 554 የብሬንና የክላሽ ተተኳሽ : 2 የብሬን ሸንሸል እና 4 የክላሽ ካዝና ተማርኩአል::

‎በአጠቃላይ በነበረው በአውደ ውጊያው የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር የኮሩ ቃኝዎችም ታላቅ ጀብድ ፈፅመዋል።

‎@ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ
1🙏1
ምስራቅ አማራ ኮር 2 ታጠቅ ክፍለጦር ዙፋን ጠባቂ ሰራዊቱ ላይ ድል ተጎናፀፉ::

ምስራቅ አማራ ኮር 2 ታጠቅ ክፍለጦር ወዳለችበት ቀጠና ህዳር 19/2018 ዓ.ም ከመርሳ ከተማ እና ኒኒ በር በመነሳት ማጥቃት ያደረገ ጠላት ጋር ከባድ ትንቅንቅና ተጋድሎ በማድረግ ከባድ ሰብዓዊ ኪሳራ በማድረስ ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::

የጠላት ሃይል ከመርሳ ከተማ እና ኒኒ በር በሁለት አቅጣጫ ለማጥቃት እንቅስቃሴ ያደረገ ሲሆን ታጠቅ ክፍለጦር 2ኛ ሻለቃ ጠዶት ሚካኤል ላይ ደፈጣ ይዘው በመጠበቅ በርካታ ሃይል ላይ ያላሰበው ጥቃት በማድረስ ሙትና ቁስለኛውን ይዙ እንዲመለስና ወደ መጣበት ምሽጉ እንዲገባ አድርገው ድል ተጎናፅፈዋል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 19/2018 ዓ.ም
🙏1