ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.21K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
"እጄን በካቴና አስሮ "ቅመሰው ፍ/ቤት መጥቶ ያስፈታህ ፤ እደፋሃለሁ ማንም አያዘኝም ፤ ማንም አይጠይቀኝም! እያለ ዝቶብኛል ፤ ...ሕይወታችን አደጋ ላይ መሆኑን እወቁ!"

የተከበሩ ዶ/ር ካሳ ተሻገር ~ ሕዳር 16/2018 በፌ/ከ/ፍ/ቤት ቀርበው ሳላ ከተናገሩት

የተከበሩ ዶ/ር ካሳ ተሻገር ሕዳር 16/2018 በፌ/ከ/ፍ/ቤት ልደታ ም/ችሎት ቀርበው ሳለ በቂሊንጦ ማ/ቤትንና በግቢ ጥበቃ እና ደህንነት ኃላፊ በኢ/ር ድሪባ ሰንበታ ላይ
ካቀረቧቸው አቤቱታዎች መካከል:-

✍️ የተከበረው ችሎት እኔ ከዚህ የተገኘሁት በእግዚአብሔር ኃይል ተርፌ ነው!

✍️ ከፍ/ቤት ትዕዛዝ ውጭ ቀደም ሲል ሕክምና ስትሄድ ካቴና ካላደረክ አልወስድህም በሚል የከለከለኝ ተስፋዬ የተባለ ፖሊስ ከሰሞኑ ይዘህው ሂድ በመባሉ ሕይወቴን ሊያጠፋ ነበር።

✍️ እጄን በካቴና አስሮ "ቅመሰው ፍ/ቤት መጥቶ ያስፈታህ ፤ እደፋሃለሁ ማንም አያዘኝም ፤ ማንም አይጠይቀኝም! እያለ ዝናብኛል።

✍️ ከዛው በፍ/ቤት ጀምረሃል በዛው ጨርስ በማለት እንደሚገድለኝ ዝቶብኛል! ሕይወታችን አደጋ ላይ መሆኑን እወቁ!

✍️ አንድም ትዕዛዝ አልፈፀሙም ፤ ሰብአዊነት የሚባል አልፈጠረባቸውም!

✍️ ፍ/ቤቱ ያዘዘ ቢሆንም አሁንም ከታማሚ ልጄ ጋር አላገናኙኝም!

✍️ ክቡር ፍ/ቤት መሄጃ ካለን ወይ ንገሩን? ሲሉ ጠይቀዋል።

ፍ/ቤቱም ጥብቅ ትዕዛዝ እንሰጣለን ከማለት ያለፈ ምላሽ አልነበረውም! የቀደመው ትዕዛዝ መቼ ተፈጸመና?

(አውሎግሶን አንድነት ፣ ሕዳር 17/2018)
2
ከዓለምአቀፍ ፋኖ ሚዲያ - Global Fano Media የተሰጠ ማብራሪያ

አለማቀፍ ፋኖ ሚዲያ - Global Fano Media ነሐሴ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የአማራ የህልውና ትግልን በይፋ በሚዲያው ዘርፍ በመቀላቀል እለታዊ መረጃዎችንና ፕሮግራሞችን በመስራት ትግሉ አለማቀፋዊ ተደራሽነት እንድኖረውና ያጋጠሙ ችግሮችም የመፍትሄ አቅጣጫ እንዲበጅላቸው በብርቱ ሰርቷል : በመስራት ላይም ይገኛል:: ሚድያችን በሚገርም ፍጥነት ያለምንም ማስታወቂያ ትልቅ ስም(brand) ሊያፈራም ችሏል:: ይሁንና ስራዎቻችን ይተላለፉበት ከነበረው የመረጃ ሳተላይት ቴሌቪዥን በመውረዱ ከፋኖ አባላት: ከአድማጭ ተመልካቾችና ደጋፊዎቻችን ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እየደረሱን በመሆኑ ተከታዩን ማብራሪያ ለመስጠት ወደናል::

አለማቀፍ ፋኖ ሚድያ በሚሰራቸው ስራዎች ተወዳጅነት እያተረፈ በመሄዱ የበለጠ የትግሉን አድማስ ለማሳደግ: ለህዝባችን ሁለንተናዊ እገዛ እንዲያደርግ ፣ የአገዛዙን ሁሉን አቀፍ ጭፍጨፋ ላለማቀፉ ማህበረስብ ግንዛቤ ለማስጨበጥና የአገዛዙን ወንጀለኝነት ለማጋለጥ በማሰብ ከመረጃ ሳተላይት ቴለቪዥን ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ በመድረስ ካለፉት 8 ወራት በፊት ማርች/2025 ጀምሮ ስርጭቱ እስከተቋረጠበት ጊዜ ድረስ ስንሰራ ቆይተናል። በጋራ በሥራ ላይ በነበርንባቸው ወራትም ሥራዎቻችን ከፍተኛ ተመልካች እንዳለው : የህልውና ትግሉን መሠረት ያደረገ ወቅታዊና ጥራት ያለው ዝግጅት እንደነበር ከጣቢያው ስራአስኪያጅ አቶ ኤልያስ ክፍሌ ተደጋጋሚ አዎንታዊ አስተያየት ይደርሰን ነበር : በዚህም የጣቢያው ወርቃማ ሰዓት/Prime time / በቀዳሚነት ተሰጥቶን ቆይተናል።

ከላይ እንደተገለፀው ባለፍንባቸው ወራቶች በጋራ ለህልውና ትግሉ አመርቂ ስራ የሠራን ቢሆንም ጳጉሜን 1 እና 2 ወይም በፈረንጆቹ Septemper 6-7/2025 ዓ/ም አፋብኃ በጋራ በስኬት ያካሄደውን ሲምፖሲየም ተከትሎ አጠቃላይ የሲምፖዚየም አፈፃፀምን በተመለከተ በነበረ ግምገማ ወቅት የሚድያችን ቦርድ አመራር ቀለብ ስዩም አንዷ አዘጋጅ በመሆኗና በወቅቱ "የሲምፖዝየሙ ውጤትንና የተገኘውን ድጋፍ ለሕዝብ ማሳወቅ እንደሚገባና የኦዲት ክትትል ለአፋብኃ የቦርድ አመራሮች መደረግ ይገባዋል፣ ይህ ከሆነ በቀጣይ ለምናደርጋችው ስራዎች ተዓማኒነትን ያስገኛል " የሚል ቁርጠኛ ተቋማዊ እና የመርህ ጥያቄ መጠየቋን ተከትሎ ሲምፖዚየሙን በበላይነት እኔነትን ባህል ያደረገ በሚመስል መልኩ ከሚያስተባብሩት አንዱ የነበረው የመረጃ ቴሌቪዥን ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ክፍለ ይሄን የመርህ ጥያቄ ለምን እንደዚህ ይደረጋል? በሚል ብስጭት ሴፕቴምበር 22/2025 በአፋብኃ ብር ማሰባሰብ ሲምፖዚየሙ ዝግጅት ጊዜ ቀለብ ስዩም በአፋብኃ ሲምፖዜምና በቴሌቶኑ ስራዎች ባነሳችው የአሰራርና የመርህ ጉዳይ ምክንያት ግሎባል ፋኖ ሚዲያ የራሱ አሰራር ያለው እራሱን የቻለ ተቋም ሆኖ እያለ ኤሊያስ ክፍሌ ግን በማናለብኝ ስሜት ስርጭቱን ሰርዞታል /ዘግቶታል። ይህም ብዙዎችን በተለይ ደግሞ የአፋብኃ ኮማንድ አባላትን ግራ ያጋባ ውሳኔውም መረጃ ቲቪን ከተቋቋመለት አውድ ውጭ በሆነ መንገድ እንደ እጅ መጠምዘዣት በመጠቀም የወሰነው ውሳኔ እና የሲምፖዝየም ስራው የተለያየ መሆኑ ጥርጣሬ ውስጥ ሊከት ችሏል። የመርህ፣ : የተጠያቂነት እና የግልፀኝነት ተጠየቅን ለምን ይነሳል በሚል የግል ጉዳይን የፋኖ ድምፅ የሆነን ሚዲያ በመዝጋት ምላሽ ሰቷል::

ጉዳዩን የሚዲያችን ቦርድ አባላት እና የአፋብኃ የኮማንድ አመራሮች ከአቶ ኤሊያስ ክፍሌ ጋር ውይይት ካደረግንበት እና ራሱም ከስርጭት ማውረዱን ስህተት መሆኑን አምኖበት ይቅርታ በማለት በፈረንጆች ሴፕቴምበር 24/2025 ዓ/ም ድጋሜ ወደስርጭት እንዲመለስ የተደረገ ሲሆን ለ6 ቀናት ስርጭታችን አየር ላይ ከዋለ በኃላ ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ድጋሜ ሚዲያችንን ከስርጭት አግዶታል። ለምን ከስርጭቱ እንደሚያግደው በተደረገለት ተጠየቅ ትግላችንን በማይመጥን ቋንቋ አስተናግዷል።

ቀደም ሲል እንደገለፅነው ሚድያችን የአማራ ሚዲያ ፎረም አባል ሆኖ ከአፋብሃ የሚዎጡ መረጃዎችን የሚሰራና ትልልቅ ዘመቻዎችም ተደራሽ እንድሆኑ ትልቅ ኃላፊነቱን ተወጥቷል:: ይህ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ጉዳዩን የአፋብኃ የህዝብ ግንኙነትና የፖለቲካ ዘርፍ አመራሮች እንድያውቁት በማድረግ አቶ ኤሊያስም ለፈፀመው ድርጊት ለአመራሮቹ ይቅርታ ጠይቆ ችግሩ ተፈቶ የነበረ ቢሆንም October 14 ቀን 2025 ያለምንም በቂ ምክንያት የአማራ ፋኖ ድምፅ የሆነውን አለማቀፍ ፋኖ ሚዲያ ድጋሜ ከስርጭት አግዶታል::

በጥቅሉ በሁለት ሳምንት ውስጥ ያለ በቂ ምክንያት ሶስቴ አውርዶ መልሶ ይቅርታ እየጠየቀ ሰቅሎታል በመጨረሻም አውርዶታል። የአፋብኃ የሴንተራል ኮማንድ አባሎች እና የእያንዳንዱ የፖለቲካ ዘርፍ ተጠሪዎች፣ የህዝብ ግንኙነት ተጠሪዎች ከኤሊያስ ክፍሌ ጋር ባደረጉት ውይይት የተደረገበት እና ይቅርታ የጠየቀበት የድምፅ ቅጅ እጃችን ላይ ይገኛል።

ከዚህ በኃላ እኛም የአቶ ኤሊያስ ክፍሌ አካሄድ ሚዲያውን በመጠቀም የአማራን ትግል በእጅ አዙር በተለይ ደግሞ የአፋብኃ ሀይልን የመጠምዘዝ እና ክህደት የመፈፀም ድርጊት ተፈፅሟል ብለን ያመንንና ድብቅ ፍላጎት እንዳለው በመረዳት " መረጃ ቲቪ እስከምናውቀው በሚዲያ ህግ የሚመራና የራሱ የሆነ ቦርድ ያለው በመርህ የሚመራ መስሎን ነበር፣ ይሁን እንጅ ሚዲያው ለአማራ ህዝብ ሲሰጠው ከነበረው ዓላማና አውድ ውጭ የግለሰብ እና የቡድን ድብቅ የፖለቲካ መሳሪያ መሆኑን ተረድተን፣ የአማራ ህዝብ ትግል የተነሳው የህዝብን ጥያቄ አዝሎ እንጅ መረጃ ቲቪን ተማምኖ ወደ ትግል እንዳልገባ ፣ በአሁኑ ሰዓት በርካታ የሚዲያ አማራጮች ባሉበት ወቅት ሚዲያን የግልና የቡድን ፍላጎት ማስፈፀሚያ ማድረግ እንደማይቻል አምነንበት" ከአቶ ኤሊያስ ክፍሌ ጋር ያለንን ጉዳይ ፋይሉን ዘግተናል።

*ይሁንና ጉዳዩን ዘግተናል ብለን የምንተወው ሳይሆን የአፋብኃ ማዓከላዊ ኮማንድ ይህንን ትህነግ/ህወሃትና ብአዴን ያደርጉት ከነበረው አፈናና ተቁአም የማፍረስ ሂደት የማይተናነስ ድርጊት እንዴት ትመለከቱታላችሁ የሚል ተጠየቅ ማንሥት እንወዳለን::*

**የአፋብኃ የሴንተራል ኮማንድ አባሎች እና የእያንዳንዱ የፖለቲካ ዘርፍ ተጠሪዎች፣ የህዝብ ግንኙነት ተጠሪዎች ከዚህ ቀደም ላደረጋችሁት ጥረት እያመሰገንን ማአከላዊ ኮማንዱ ይህንን አውቆ ከስርዓቱ ያልተናነሰ በደል እየፈፀመ ያለውን ችግር በኛ ይበቃ ዘንድ :
አፋብኃ አጣርቶ እርምጃ እንድወስድ እንጠይቃለን::*

በዚሁ አጋጣሚ ሁሉንም የውይይት መንገዶችን በአማራዊ ጨዋነት እና ትግሉ በሚጠይቀው ስነ ስርዓት ተጠቅመን የተፈጠረውን ችግር በመቅረፍ ስርጭታችንን በመረጃ ሳተላይት ቴሌቪዥን ለመመለስ ያደረግነው ጥረት ከላይ ባነሳናቸው ምክንያቶች ባለመሳካቱ በጀመርነው የዩቱዩብ ማሰራጫ ተጠቅመን እያስተላለፍን መሆኑን ለመላው የፋኖ አባላትና አመራሮች: ለትግሉ ደጋፊ ለአድማጭ ተመልካቾችና ደጋፊዎቻችን ማሳወቅ እንወዳለን::

አለማቀፍ ፋኖ ሚዲያ - Global Fano Media
የፋኖ ድምፅ !
3
📝የፋኖ ደጋፊ ተብለው ከቤተክርስቲያን ተባረሩ

👉የኔታ ተስፋ ማርያም ይባላሉ አራት አይና ሊቅ የጎንደር ፊት ሚካኤል ከሰላሳ ሁለት አመት በላይ ያገለገሉ ፣ በርካታ ሊቃውንትን ያፈሩ ታላቅ አባት ናቸው።

👉 የድጓም መህምር፣ የሐድስ ኪዳን ፣ ትርጓሜ መህምር ናቸው ባህታዊ ሥጋ ባፋቸው ገብቶ አያውቅም መጠጥ ምን እንደሆነ አያውቁም የሚኖሩት መቃብር ቤት ነው

👉የቤተ ክርስቲያኑ መምህር እና አስተዳዳሪ ናቸው ፣ መነኩሴ ሆነው አንድ ቀን እንኳን እንደ መነኩሴ ቀሚስ ለብሰው ቆብ አጥልቀው ለሰው አይታዩም፦

👉 በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ለሰው ልጅ በህይዎታቸው የሚያስተምሩ የሕይወት መምህር ጭምር ናቸው ፦

👉ታዲያ የማይከላዊ ጎንደር ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዮሐንስ በውጭው ሲኖዶስ በአቡነ መርቆሬዎስ የተሾሙ ፣ሥራ አስኪያጃቸው አባ ዮሴፍ የብልጽግና የቁም ተጠሪ እና ካድሬ እንደሆኑ የመረጃ ምንጮቻችን ይናገራሉ ፣ ሊቀ ጳጳሱም ጉዳዩን በጥልቀት ሳይመረምሩ ፣ ከሥራ አስኪያጁ ጋር በመሆን ከቤተክርስቲያን እንዲወጡ የተደረገ ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ፦

👉 የፋኖ ደገፊ ፣ ቤተክርስቲያኑን የፋኖ አደረጉ ተብለው ከቤተ ክርስቲያን በሰባት (7) ፖሊስ ተባረው በአሁኑ ጊዜ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጊቢ እንዳይገቡ ተደርገው አቤቱታ እንዳያቀርቡ በስቃይ በችግር ውስጥ እንደሚገኙ የመረጃ ምንጮቻችን መረጃውን አድርሰውናል ፦

🙏 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ፣ ካህናት አገልጋዮች እና ምዕመናኑ በሙሉ ድምፅ ሊሆናቸው ይገባል ።
🔥2💔1
206ኛ ኮር ደጀን ላይ የተጠና ኦፕሬሽን ካደረገ በኋላ በከተማው የመሸገው የአረመኔው ሰራዊት ፍርስርሱ እየወጣ ነው።

ም/ኢንስፔክተሩን ጨምሮ በተደመሰሱበት ኦፕሬሽን የተደናገጠው ጠላት ፍርስርሱ እየወጣ ከ30 በላይ ሚኒሻዎች የከዱ ሲሆን ይህንን መቋቋም አልቻልክም በሚል ምክንያት አሰተዳደር ፀጥታ የነበረው ዳኘ ደነቀው ዘብጥያ ካወረዱት በኋላ ከኃላፊነቱ ተነስቷል።

  ይህን ተከትሎ ትርምሱን መቋቋም ያልቻለው የደጀን ካድሪ  ውጥረት ውስጥ ሲገኝ ፈርሰው ከከዱ የጠላት ኃይሎች መካከል
1) በላይ አየለ
2) ንፁህ ግዛቸው
3) አባትህ ሙንየ
4) ሀብቴ ታደለ
5) ከፌ ሙንየ
6) ፀሀይነህ ማናየ
7) ሀውልቱ አያሌው
8) ብርሌው ብሬ
9) ተሜ አበባው
10) እንደግ ጤናው
11) ደመቀ ሙሉ 
12) አሳቤ ተዋዶ
13) ብርሌው አሻግሬ 
14) ጌታቸው አብነህ
15) ቀስቅስ አስማረ
16) ጐዴ አድማሱ
17) ደጓላ ማናየ
18) አማረ መንገሻ
19) ተሾመ አዳነ
20) ደባስ አባተ
21) ጥላሁን ዘውዱ
22) ጌትሽ ደመቀ
23) ደመላሽ ደርሰህ
24) አላምኔ አወቀ
25) ብዙነህ ግዜ
26) ስላምሰው አሻግሬ 
27) አላምረው ማማሩ
28) ማሟሽ ደሳለኝ
29) ይደግ አደመ
30) ምስና አፍራሽ
31) ተመስገን ውዱ
32) በልስቲ ሀብታሙ ፣መሆናቸው  ተረጋግጧል።

አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ የአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
1🙏1
ሰበር ዜና!

ዞብል አምባ ክፍለጦር 6ኛ ሻለቃ መርጦ ከተማ በጨለማ ሰርጎ በመግባት የፋሽስቱ አራዊት ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮችን በመደምሰስና በመማረክ ታላቅ ጀብድ ፈፅመው ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::

ምስራቅ አማራ ኮር 2 ዞብል አምባ ክፍለጦር 6ኛ ሻለቃ ጉባላፍቶ ወረዳ መርጦ ከተማ መሽጎ ካለው የብልፅግና ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ህዳር 17/2018 ዓ.ም ሌሊት ሰርገው በመግባት አራት አጃቢዎቻቸውን በሳንጃ በመግደል እንዲሁም አንድ ሻምበል መሪ እና አንድ የክፍለጦር ሃኪም በመማረክ ታላቅ ጀብድ ፈፅመው ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::

ሻለቃዋ የሌሊት ጥቃቱን የፈፀመችው ያለምንም የጥይት ተኩስ ሲሆን የከፍተኛ አመራሮቹን አጃቢዎች ቀድመው በማስወገድ አመራሮቹን ከሶስት ጥቁር ክላሽና ሙሉ ትጥቁ ጋር በመማረክ የተሳካ ስራ ሰርተው ወጥተዋል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 18/2018 ዓ.ም
🙏2
ልጅ እያሱ ኮር 23ኛ ክፍለጦር አምባሰል ጊሼን ላይ ተጋድሎ በማድረግ ድል አስመዘገቡ::

ልጅ እያሱ ኮር 23ኛ ክፍለጦር ከአምባሰል ጊሼን አካባቢ ወደ አምባሰል ጅብጎዶ ለማጥቃት የመጣ የፋሽስቱ አገዛዝ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ጋር ብርቱ ትንቅንቅና ተጋድሎ በማድረግና በጠላት ላይ ከባድ ሰብዓዊ ኪሳራ በማድረስ ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::

የፋሽስቱ ብልፅግና አገዛዝ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት አምባሰል ጊሼን ቤተክርስቲያን ውስጥ በብዛት መሽጎ ያለ ሲሆን ከዛ በመነሳት በቅርብ ርቀት ልጅ እያሱ ኮር 23ኛ ክፍለጦር ወዳለችበት ጅብጎዶ ማጥቃት ያደረገ ሲሆን ንስሮቹ ባግባቡ በመመከትና መልሶ ማጥቃት በማድረግ ብሎም ከባድ ሰብዓዊ ኪሳራ በማድረስ ወደ መጣበት ምሽጉ መልሰውታል::

በዚህ የተበሳጨው የጠላት ሰራዊት እንደተለመደው ህዝብ ወደሚበዛበት አካባቢ ወደ ከተማ ሞርተር በማስወንጨፍ ትምህርት ቤት እና ባካባቢው ባሉ መንደሮች በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 18/2018 ዓ.ም

https://t.me/+APfg2ZKNKrhhMTlk
🙏2
ጧሪ የሌላት እናቴን ትቼ ጫካ የገባሁት የአማራ ህዝብ ጭቆና አንገብግቦኝ ነው!
በብዙ ግንባር ከፍተኛ ጀብድ የፈፀመችው እንስቷ ከልጇ ጋር ዛሬም አፋብኃ በላይ ዕዝ በጦር ግንባር ሰራዊት እየመራች ትገኛለች።

ጀግኒት አርበኛ ታድላ ስማቸው

ትግላችን በተባበረ ክንዳችን
👌❤️🔥💪


https://t.me/+APfg2ZKNKrhhMTlk
🙏2
በታሪክም ይሁን በአሁናዊ ኹነት የድርጅትን ዓላማ የሚደግፉ እየመሰሉ፣ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ለጠላት የፕሮፓጋንዳ ማሽን የሚውል መረጃ የሚያሰራጩ ግለሰቦች ይኖራሉ። በርግጥ አንዳንዶቹ የጠላትን ተልዕኮ በመሸከም double agent የሆኑም ይኖራሉ።

ያም ሆነ ይኽ፤ ለድርጅታችን ደጋፊዎች እና አባላት ስለሚዲያ አጠቃቅም ይችን መልዕክት እነሆኝ ማለት ወደድን!


እንደሚታወቀው ዛሬ የምንታገለው በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ አይደለም፤ ትልቁና ወሳኙ ትግል ያለው በማኅበራዊ ሚዲያ  ላይ'ም ነው። ጠላት ሁላችንንም እያየን ነው። ስልቱም ደግሞ ግልጽ ነው። እኛን በራሳችን ማዳከም።

የእኛን ማንነት ለብሰውና ደጋፊ መስለው ጥርጣሬንና መከፋፈልን  የሚፈጥሩ ሐሰተኛ መረጃዎችን ማሰራጨት፤ ጠላት የሚጠቀመ ስልት ነው። በስሜት ተገፋፍተን ወይም በቂ መረጃ ሳይኖረን የምንጽፋቸውን ድክመቶቻችንን፣ ሚስጥራዊ መረጃዎቻችንን እና የውስጥ ቅራኔዎቻችንን፣ ጠላት ለራሱ ፕሮፓጋንዳ በማዋል ይጠቀምባቸዋል።

ስለሆነም፤ እያንዳንዱ ጽሑፍና አስተያየት "የጦር መሣሪያ ነው" ማሰብ ያስፈልጋል። መሣሪያን ወደ ራስ ማዞር ደም ውጤቱ የታወቀ ነው።  ስለዚኽ እነሆ የልጅ ምክር፦

1. መረጃን ማረጋገጥ እና መገደብ

ምንጭዎን ይፈትሹ። አንድ መረጃን ከማጋራትዎ በፊት በይፋዊ የድርጅት ምንጮች የተረጋገጠ መሆኑን ያረጋግጡ። ያልተረጋገጡ ወሬዎችና ግምቶች የጠላት የስንኩል መሣሪያ  ናቸው።

የውስጥ መረጃን አያጋሩ። የድርጅቱ የሥራ አመራር፣ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች፣ የገንዘብ ሁኔታዎች ወይም የውስጥ ስብሰባዎች በተመለከተ ያልተፈቀደ ማንኛውንም መረጃ በግል መልዕክቶችም ቢሆን ማውራት "ከድርጅት ክህደት" አይተናነስም።

2. ስሜትን መቆጣጠርና በጥበብ ምላሽ መስጠት 

በስሜት አይገፉ! ጠላት ሁልጊዜ የሚያበሳጩና የሚያስቆጡ አስተያየቶችን ይጥልብናል። ዋናው ዓላማቸው አንዱ ደጋፊ ከሌላው ጋር እንዲጣላና ለጠላት የፕሮፓጋንዳ መሣሪያ የሚሆን የውስጥ ቅራኔ በአደባባይ እንዲወጣ ማድረግ ነው።

በየትኛውም መንገድ ዘውትር የትግሉን ዓላማ ብቻ ያንጸባርቁ። በትግላችን ውስጥ ዋናው ነገር የግል ውርርድ ወይም ክርክር አይደለም፤ የትግሉ ትልቅ ጉዳይ "የትግሉ ዓላማ" ነው። ጽሑፍዎ ሁሉ "ስለ መጪው ብሩህ ተስፋ እና ስለ ድርጅታችን መርሆችና ግብ" ብቻ ይሁን።

3. ጠላትን ማጋለጥ 

የጠላት ደጋፊዎችን በመለየትሐሰተኛ መረጃዎችን በስፋት የሚያሰራጩና ግልጽ የሆነ የጠላት አቋም ያላቸውን አካውንቶች በማኅበራዊ ሚዲያ ሕግጋት መሠረት ሪፖርት ማድረግ (Report) እንጂ ከእነሱ ጋር ክርክር ውስጥ በመግባት  ጊዜና ጉልበትዎን ማባከን አያስፈልግም።

እንደአጠቃላይ፤ ማኅበራዊ ሚዲያ የጦር ሜዳ ነው። በግዴለሽነት የሚጻፍ አንድ ቃል፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን ዋጋ ሊያስከፍል ይችላል። እያንዳንዱ ደጋፊ የድርጅቱ የመረጃና የደህንነት አካል ነኝ ብሎ ማመን አለበት። በአንድነት ቆመን፣ በንቃትና በጥንቃቄ ጠላትን በመረጃም ጭምር እናስወግደዋለን!

አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ

አፋብኃ|ቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
👍1
የብልፅግና ግፍ እና መከራ!!!

አሳዛኝ መረጃ
በጠገዴ ወረዳ ገጠራማ ስፍራ በ4 የመከላከያ ሰራዊት አባላት የተደፈረችዉ የ55 ዓመት እድሜ ያላት እናት መረጃ እንዳታወጣ ህክምና መከልከሏን ተከትሎ በዛሬዉ ዕለት ራሷን ማጥፋቷ ተሰምቷል።


https://t.me/+APfg2ZKNKrhhMTlk
በታሪክም ይሁን በአሁናዊ ኹነት የድርጅትን ዓላማ የሚደግፉ እየመሰሉ፣ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ለጠላት የፕሮፓጋንዳ ማሽን የሚውል መረጃ የሚያሰራጩ ግለሰቦች ይኖራሉ። በርግጥ አንዳንዶቹ የጠላትን ተልዕኮ በመሸከም double agent የሆኑም ይኖራሉ።

ያም ሆነ ይኽ፤ ለድርጅታችን ደጋፊዎች እና አባላት ስለሚዲያ አጠቃቅም ይችን መልዕክት እነሆኝ ማለት ወደድን!


እንደሚታወቀው ዛሬ የምንታገለው በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ አይደለም፤ ትልቁና ወሳኙ ትግል ያለው በማኅበራዊ ሚዲያ  ላይ'ም ነው። ጠላት ሁላችንንም እያየን ነው። ስልቱም ደግሞ ግልጽ ነው። እኛን በራሳችን ማዳከም።

የእኛን ማንነት ለብሰውና ደጋፊ መስለው ጥርጣሬንና መከፋፈልን  የሚፈጥሩ ሐሰተኛ መረጃዎችን ማሰራጨት፤ ጠላት የሚጠቀመ ስልት ነው። በስሜት ተገፋፍተን ወይም በቂ መረጃ ሳይኖረን የምንጽፋቸውን ድክመቶቻችንን፣ ሚስጥራዊ መረጃዎቻችንን እና የውስጥ ቅራኔዎቻችንን፣ ጠላት ለራሱ ፕሮፓጋንዳ በማዋል ይጠቀምባቸዋል።

ስለሆነም፤ እያንዳንዱ ጽሑፍና አስተያየት "የጦር መሣሪያ ነው" ማሰብ ያስፈልጋል። መሣሪያን ወደ ራስ ማዞር ደም ውጤቱ የታወቀ ነው።  ስለዚኽ እነሆ የልጅ ምክር፦

1. መረጃን ማረጋገጥ እና መገደብ

ምንጭዎን ይፈትሹ። አንድ መረጃን ከማጋራትዎ በፊት በይፋዊ የድርጅት ምንጮች የተረጋገጠ መሆኑን ያረጋግጡ። ያልተረጋገጡ ወሬዎችና ግምቶች የጠላት የስንኩል መሣሪያ  ናቸው።

የውስጥ መረጃን አያጋሩ። የድርጅቱ የሥራ አመራር፣ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች፣ የገንዘብ ሁኔታዎች ወይም የውስጥ ስብሰባዎች በተመለከተ ያልተፈቀደ ማንኛውንም መረጃ በግል መልዕክቶችም ቢሆን ማውራት "ከድርጅት ክህደት" አይተናነስም።

2. ስሜትን መቆጣጠርና በጥበብ ምላሽ መስጠት 

በስሜት አይገፉ! ጠላት ሁልጊዜ የሚያበሳጩና የሚያስቆጡ አስተያየቶችን ይጥልብናል። ዋናው ዓላማቸው አንዱ ደጋፊ ከሌላው ጋር እንዲጣላና ለጠላት የፕሮፓጋንዳ መሣሪያ የሚሆን የውስጥ ቅራኔ በአደባባይ እንዲወጣ ማድረግ ነው።

በየትኛውም መንገድ ዘውትር የትግሉን ዓላማ ብቻ ያንጸባርቁ። በትግላችን ውስጥ ዋናው ነገር የግል ውርርድ ወይም ክርክር አይደለም፤ የትግሉ ትልቅ ጉዳይ "የትግሉ ዓላማ" ነው። ጽሑፍዎ ሁሉ "ስለ መጪው ብሩህ ተስፋ እና ስለ ድርጅታችን መርሆችና ግብ" ብቻ ይሁን።

3. ጠላትን ማጋለጥ 

የጠላት ደጋፊዎችን በመለየትሐሰተኛ መረጃዎችን በስፋት የሚያሰራጩና ግልጽ የሆነ የጠላት አቋም ያላቸውን አካውንቶች በማኅበራዊ ሚዲያ ሕግጋት መሠረት ሪፖርት ማድረግ (Report) እንጂ ከእነሱ ጋር ክርክር ውስጥ በመግባት  ጊዜና ጉልበትዎን ማባከን አያስፈልግም።

እንደአጠቃላይ፤ ማኅበራዊ ሚዲያ የጦር ሜዳ ነው። በግዴለሽነት የሚጻፍ አንድ ቃል፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን ዋጋ ሊያስከፍል ይችላል። እያንዳንዱ ደጋፊ የድርጅቱ የመረጃና የደህንነት አካል ነኝ ብሎ ማመን አለበት። በአንድነት ቆመን፣ በንቃትና በጥንቃቄ ጠላትን በመረጃም ጭምር እናስወግደዋለን!

አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ

አፋብኃ|ቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
👍2
ቴዎድሮስ ዕዝ በመተከል የማምቡክ ከተማ ሚሊሻ ፅ/ቤት ኃላፊ ላይ እርምጃ ሲወስድ፡ በተመሣሣይ ምኒልክ ዕዝ ደግሞ የአልብኮ ወረዳ ብልፅግና አመራሮች ላይ ከባድ እርምጃ መውሰዱን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።

በምዕራብ አማራ ቀጠና የቴዎድሮስ ዕዝ ፋኖዎች
በመተከል የማምቡክ ከተማ ሚሊሻ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ደረጀ ለሚሳን ጨምሮ በርካታ የአድማ ብተና አባላትን ሲገድሉ ሦስት ወታደሮችን ደግሞ መማረካቸው ታውቋል።

በምስራቅ አማራ ቀጠና ደግሞ የምኒልክ ዕዝ ፋኖዎች የአልብኮ ወረዳ መቀመጫ የሆነችው ሳልመኔ ከተማ ዘልቀው በመግባት የወረዳውና የከተማ አስተዳደሩ ብልፅግና አመራሮች ላይ በፈፀሙት ጥቃት በርካቶችን ሙትና ቁስለኛ ማድረግ ችለዋል።

https://t.me/gfmn21
🙏2
ከግብረ ሰናይ ድርጅቶች ለህዝብ እርዳታ የመጣ ገንዘብ በወረዳ የብልጽግና አመራሮች መዘረፉ ታወቀ!
    
በደቡብ ጎንደር ዞን በመና መቀጣዋ ወረዳ ህዝብን ለመርዳት በሚል ከተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የመጣ የእርዳ ገንዘብ በበልጽግና አመራሮች እየመዘበረ የግል ኪሳቸውን እያደለቡበት መሆኑ ታውቋል።
     
ከመዘበሩ የአገዛዙ አመራሮች መካከል
1 - ምስጋናው ሆነ ➢ የመቀጣዋ አስተዳዳሪ የነበረ በሚስቱና በራሱ  ከ2 መቶ ሺ ብር በላይ ዘርፏል።

2 - አሰፋ ➢ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ 230 ሺ ብር ዘርፏል።

3 - በርየ ደምሴ ➢የብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ 200 ሺ  ብር በሚስቱና በራሱ መዝብረዋል።

4 - አደራጀው ጌትነት ➢ የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ
              
ለልማት የመጣን የህዝብ አፈር መዳበሪያ በይፋ በመሸጥ  ድብረታቦር ላይ በ12 ሚሊዮን ብር የመኖሪያ አፓርትማ / ቅንጡ መኖሪያ ቤት / ገዝቷል።
   
ከዚህም ጋር ተያይዞ በምስራቅ በለሳ ወረዳም በሴፍትኔት ስም የሚመጣን የእርዳታ ገንዘብ ለብልጽግና ወታደራዊ መሪዎች እጅ መንሻ እየተጠቀሙበት እንደሆነም ታውቋል።
   
በዋነኛነት ይህን የእርዳታ ገንዘብ ከታለመለት ዓላማ ውጭ ተግባር ላይ እንዲውል እያደረጉት ያለው የወረዳ አስተዳዳሪዎች መሆናቸው ታውቋል።
     
ይህ የእርዳታ ገንዘብ የሚሰጥበት ዓላማም ወረዳችንን አንድም የፋኖ አባል በከተማችን ተኩስ እንዳይከፍት ነቅታችሁ ጠብቁልን የሚል የእጅ መንሻ እንደሆነም ተገልጿል።
     
እጅ መንሻው ከተሰጣቸው ወታደራዊ መኮንንኖች መካከል ማዘዣ ጣቢያዋን ደጎማ ላይ ያደረገችው 57ኛ ክ/ጦር አዛዥ ኮሎኔል ኃይሉ ግንባር ቀደም ሆኖ ይጠቀሳል።
           
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ ፭ ኮር ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ  ኃላፊ
                                    አብነት ሞላ    
                             ህዳር 18 /2018 ዓ.ም
💔1