ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.21K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
ሰበር ዜና ‼️

በአዲስ አበባ ከለገጣፎ አቅራቢያ በሚገኘው የመከላከያ ካምፕ ላይ ከባድ የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ 12 የመከላከያ አባላት መገደላቸው ተሰማ! በመከላከያ ካምፕ ውስጥ በተነሳ የእርስ በእርስ ውጊያ የአገዛዙ ወታደሮች እርስ በእርስ ተጫርሰዋል ነው የተባለው!

በካምፕ ውስጥ በነበረው የእርስ በእርስ ውጊያ 12 ወታደሮች ሲገደሉ አንድ የቡናና ሻይ ቁርስቤት ሰራተኛም በተኩስ ልውውጥ መሀል መገደሏ ተነግሯል ! የእርስ በእርስ ውጊያው የተደረገው ዛሬ ከሰአት ሲሆን ወደ ወሎ ዛሬ ትሄዳላችሁ ተብለው የነበሩ የ94ኛ ክፍለጦር ወታደሮች በዝግጅት ላይ ባሉበት ወቅት የኦሮሚያ ልዩሀይል እና ሚሊሻ ወደ ካምፑ በመግባት የመከላከያ ዩኒፎርም እየለበሱ ከነሱ ጋር መቀላቀል ሲጀምሩ ይሄ ለምን ይሆናል የመከላከያን ስም እያጎደፍን ነው ይህን አንቀበልም ያሉ ወታደሮች መረሸናቸውን ተከትሎ ሲሆን የሚሰራው ህገወጥ ስራ ሳያንስ ጓዶቻችንን እንዴት ትረሽናላችሁ በሚል የእርስ በእርስ ውጊያ የተደረገ ሲሆን ለ1 ሰአት እርስ በእርስ ተታኩሰዋል ነው የተባለው። በዚህም 12 ወታደር ሲሞት የቆሰሉም ብዙ ናቸው። ተኩሱን ለማስቆም ከፍተኛ ጀነራሎች ወደቦታው በፍጥነት የሄዱ ሲሆን ተኩሱን አረጋግተው አሁን ተቃውሞ ያስነሱትን ወደ ወታደራዊ እስርቤት እያጋዟቸው ነው ተብሏል !
🙏3👍1
💪ሰበር መረጃ💪

ከወልድያ በቅርብ ርቀት አማየ ሚጫ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ በተፈፀመ ደፈጣ ጥቃት አንድ ኦራል ሙሉ የአገዛዙ ወታደር ሙትና ቁስለኛ ተደርጓል!

ምስራቅ አማራ ኮር 2 ዞብል አምባ ክፍለጦር 6ኛ ሻለቃ ከመርጦ ወደ ወልድያ ከተማ ይጓዝ የነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ላይ አማየ ሚጫ በሚባል ቀጠና ደፈጣ በመያዝ በፈፀሙበት ጥቅት ኦራል ላይ የነበረውን ሙሉ ለሙሉ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ እንዲሁም በእግር ይጓዝ የነበረውን ከሙትና ቁስለኛ የተረፈውን ብትንትኑን በማውጣት ከባድ ሰብዓዊ ኪሳራ በማድረስ ታላቅ ጀብድ ፈፅመዋል ሲል የዕዙ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ አስታውቋል።

በቀጣይም የፋሽስቱ ብልፅግና አገዛዝ ሰራዊት ላይ የሚወሰደው እርምጃ በደፈጣ ጥቃት ረፍት በመንስስትና በማዋከብ እንዲማረር በማድረግ ሲያመች በመደበኛ ውጊያ በመደምሰስና በመማረክ ብሎም በማስኮብለል አገዛዙን የማፈራረሱ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያለው ዕዙ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያው በኩል ለጣቢያችን በላከው መረጃ።
4🙏1
ምኒልክ ዕዝ የአደረጃጀት ዜና!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ ዕዝ ልጁ እያሱ ኮር ራሱን እንደ ንስር ማንቆሪያውን እና ጥፍሩን አድሶ ላባውን ቀይሮ በአዲስ አደረጃጀት በአዲስ ስያሜ እና በአዲስ የድል መንፈስ ከከፍተኛ እስከ ዝቅተኛ የአመራር ሪፎርም በማድረግ ብቅ ብሏል፡፡

ትግሉን እና ዘመኑን መዋጀት ለምናደርገው ረጅም እና ፈታኝ የትግል ጉዞ ትልቅ ስንቅ እና ጡንቻ እንደሚሆን ግልፅና የማይካድ ሃቅ ነው።

የልጅ እያሱ ኮር ከፍተኛ የኮር አመራርን ጨምሮ በውስጡ የሚገኙቱን

** ራንቦ ክፍለ ጦር
** ቤተ አማራ ክፍለ ጦር
** ራስ አሊ ክፍለ ጦር
** የጁ ክፍለ ጦር ከሻለቃ መሪ በላይ ያሉ አመራሮችን ትግል በሚፈልገው ደረጃ በጥልቀት በማወያየት እና በማገማገም ችግሮችን ነቅሶ በማውጣት እና ለችግሮቹ የመፍትሔ አቅጣጫ በማስቀመጥ ጉባዔውን አጠናቋል፡፡

ጉባዔው በታቀደው መሠረት ግለቱን ጠብቆ እንዲሄድ ከድርጅት በመጡ የወታደራዊ እና የፖለቲካ ክንፍ አመራሮች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል፡፡

በስፍራው በተገኙት የድርጅቱ የዘመቻ መምሪያ ሃላፊው አርበኛ በለጠ ሸጋውን (ተራራው) ን ጨምሮ የድርጅቱ የአደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ እና ምክትል ሃላፊ የሆኑት አበበ ቀዮ እና አሰፋ መሰለ (አሳምነው) በተገኙበት ጉባዔ እጅግ ድንቅ እና ለቀጠናው አስተማሪ የሆነ ሪፎርም ለመስራት ተችሏል፡፡

በሪፎርሙ ከኮር አመራርን ጨምሮ የክፍለ ጦር አመራር ለውጥ ከማድረግ ጀምሮ አራቱን ነባር ክፍለ ጦሮች መጠሪያቸውን ስም ጭምር በመቀየር ሠራዊታቸውም አዲሱ አመራር በፈለገው ሂደት ተሰባጥሮ ወደ ሁሉት ግዙፍ ክፍለ ጦር እንዲታጠፉና መጠሪያ ስያሜያቸውም ወደ ቁጥር በመለወጥ የልጅ እያሱ ኮር 23ኛ እና 24ኛ ክፍለ ጦር እየተባሉ እንዲጠሩ ተወስኗል፡፡

በቀጠናው የመጀመሪያ የሆነውን እና ፈር ቀዳጅ የሆነውን የሠራዊት ውህደት እና የቁጥር ስያሜ ለሌሎችም አርአያ እንደሚሆን ታምኗል፡፡

በሪፎርሙ መሠረት የኮሩ ወታደራዊ ክንፍ ላይ ሠፊ ሪፎርም የተደረገ ሲሆን የቤተ አማራ ክፍለ ጦር አዛዥ የነበረው እንዳሻው ወታደራዊ አዛዥ ሆኖ ሲሾም የየጁ ክፍለ ጦር አዛዥ የነበረው ፶ አለቃ ሞላ አባተ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ በመሆን ኀላፊነታቸውን ተረክበዋል፡፡

አዲሱ መዋቀር

1 አርበኛ ሰለሞን አሊ ሰብሳቢ
2 አርበኛ እንዳሻ ጌታሁን ምክትል ሰብሳቢ እና ወታደራዊ አዛዥ
3 አርበኛ ሲሳይ አየለ (ሳተናው) ምክትል ሰብሳቢ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ኀላፊ
4 አርበኛ ፶ አለቃ ሞላ አባተ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ
5 አርበኛ ዳንኤል አስረስ አስተዳደር
6 አርበኛ ቦጋለ ሞሌ ምክትል አስተዳደር
7 አርበኛ ሽመልስ አወል ሎጅስቲክ
8 አርበኛ እርገት አያሌው ም/ሎጅስቲክ
9 አርበኛ ሱሃሊ ሸኩር ዘመቻ
10 አርበኛ ዳንኤል ዋጋው ህዝብ ግኑኝነት
11 አርበኛ መሃመድ ፈንታው ኦርድናንስ
12 አርበኛ አሰፋ አባተ የሰው ኀይል
13 አርበኛ ዮሃንስ ከልክሌ ፋይናንስ

በማድረግ ነባሩን እና አዲሱን አመራር በማጣመር ኮሩን በታላቅ ኀላፍነት ክብሩን እና ሞገሱን አሁን ካለው በላይ በማግዘፍ በጥበብ በማስተዋል እና በፍፁም አማራዊ ስነልቦና እንዲመሩ ቃለ መሃላ ጨምሮ አደራም ጭምር ተሰጥቷቸዋል፡፡

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 2/2018 ዓ.ም
🙏31
የአገዛዙ አረመኔዊ ሰራዊት በሰከላ ወረዳ በንፁሀን እና በት/ት ተቋማትን ላይ የድሮን ጥቃት ፈፀመ!

የአገዛዙ አረመኔው ሰረዓት ህዳር 02/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:00 ሰዓት በሰከላ ወረዳ አጉት የመጀመሪያ ት/ቤትን በድሮን ጥቃት አንድ ንፁሀን ሴት ማቁሰሉን እና የአጉት ት/ቤትን ሙሉ በሙሉ ማውደሙ ተረጋግጦል።

በሁሉም ቦታ የምትገኙ የፋኖ ሀይሎች በሙሉ የአገዛዙ ሀይል ሽንፈቱ እየተቃረበ በመምጣቱ የሽንፈቱን ጥግ ንፁሀን በመጨፍጨፍ እና የት/ት ተቋማትን በድሮን እያወደመ ይገኛል።

በመሆኑም የዚህ አረመኔዊ አገዛዝ አፀያፊ ተግባሩ እንደቀጠለ ስለሆነ በሁሉም ቦታ የምትገኙ የፋኖ ሀይሎች እና የተከበረከው የአማራ ህዝብ ጥብቅ ጥንቃቄ ልታደርጉ ይገባል።
💔3
ሁለት ክላሽንኮቭ መሳሪያ ይዞ ጎንደሬ በጋሻዎችን ተቀላቀለ

የአማራ ክልል አድማ ብተና አባል የነበረው ዳዊት ሀብታሙ የተባለው ወጣት ሁለት ክላሽንኮቭ መሳሪያዎችን ይዞ በጀግንነት የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል (አፋብኃ ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳግማዊ ቴውድሮስ /አምስተኛ/ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር አካል የሆነውን አፄ ፋሲለደስ ብርጌድ ተቀላቅሏል።

ዳዊት ሀብታሙ አዲስ ተመራቂ ሲሆን ከተመደበ ሁለት ሳምንት ሳይሞላው ከጠዳ ከተማ መገጭ ግድብ በለሊት ተነስቶ ዛሬ ህዳር 2/2018 ዓ/ም አማራ ህዝብ ላይ አልተኩስም በማለት የጓዱን መሳሪያ ጨምሮ በመያዝ ጎንደሬዎቹን በጀግንነት ተቀላቅሏል።

ወጣቱን የአድማ ብተና አባል የጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ዘመቻ መሪ አርበኛ ሞላ ከፌ ፣ የገስጥና ይላቅ ሻለቃዎች አመራሮች በመገኘት ደማቅ አቀባበል አድርገውለታል።

ዳዊት ሀብታሙ "ወደ አድማ ብተና የገባውት መሳሪያ ለመታጠቅ ስለነበረ ሰልጥኘ አንድ ጥይት ህዝቤ ላይ ሳልተኩስ ምኖቴን ሁለት ክላሽ በማምጣት አሳክቻለሁ" ብሏል።

የጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ዘመቻ መሪ አርበኛ ሞላ ከፌ የአድማ ብተና፣የመከላከያ፣ የሚኒሻ እና የፖሊስ አባላትን ጨምሮ እስካሁን በተለያየ ጊዜ ከ50 በላይ አባላት ክፍለ ጦራችን መርጠው የተቀላቀሉ ሲሆን እንደየ ምርጫቸው የሚታገሉ እየታገሉ የሚሸኙም የተሸኙ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በሰላም ተቀላቅለዋል።
አርበኛ ሞላ ከፌ አክሎም የአድማ ብተና፣የመከላከያ፣ የሚኒሻ እና የፖሊስ አባላት አገዛዙ ፀሀይ እየጠለቀችበት ስለሆነ አሽከርነታቸውን አቁመው ህዝባቸውን መርጠው ህዝባዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርቧል።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !!!!
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
ህዳር 2/2018 ዓም
🙏3
አማራነትን እንደ ወንጀል በቆጠረው የብልፅግና አገዛዝ ተይዘው ከሁለት ዓመታት በላይ በእስር ላይ የነበሩ የግፍ እስረኞች ከ13 ዓመት እስከ 23 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደባቸው!

የስርዓቱ አሻንጉሊት በመባል የሚታወቁት ፍርድ ቤቶች፡ እስረኞቹን ተደጋጋሚ የሆነ ፍትሕ አልባ ቀጠሮ በመስጠት ከሁለት ዓመታት በላይ ካመላለሷቸው በኋላ ነው ጥቅምት 25/2018 ዓ/ም ባዋሉት ችሎት ብይኑን ያስተላለፉባቸው።

በምስራቅ ወለጋ ዞን አንገር ጉቴ ከተማ እና በሌሎች የዞኑ አከባቢዎች በአማራነታቸው ምክኒያት ለእስር ተዳርገው ነቀምት በሚገኘው የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ ተመስርቶባቸው ለዓመታት ሲከራከሩ የቆዩት ተከሳሾች እያንዳንዳቸው 13 ዓመት ከስድስት ወር እስከ 23 ዓመት የሚደርስ ፅኑ እስራት እንደተፈረደባቸው ታውቋል።

ከፍርደኞቹ መካከል የተወሰኑት በምርመራ ወቅት በተፈፀመባቸው ድብደባ የተነሳ ለከባድ የአካል ጉዳት መጋለጣቸውን ጣቢያችን መረብ ሚዲያ ባደረገው ማጣራት ለማረጋገጥ ችሏል።

የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥቅምት 25/2018 ዓ/ም ባዋለው ችሎት በሙሉቀን አንተነህ የክስ መዝገብ ስር ከሚገኙ ሦስት ንዑስ የክስ መዝገቦች መካከል አንዱ በሆነው በሰለሞን አሰፋ ክስ መዝገብ ተከሰው በእስር ላይ ሆነው ሲከራከሩ በቆዩ የአማራ ተወላጆ ላይ ፍርደ ገምድል የሆነ ብይን አስተላልፎባቸዋል።

በክስ መዝገቡ ከተከሰሱ 31 የአማራ ተወላጅ ተከሳሾች መካከል፡ 14ቱ ከሁለት ዓመታት በፊት ለእስር ከተዳረጉ በኋላ የዋስትና መብት ተነፍገው በማረሚያ ቤት የድብደባ መዓትና አይነት ሲፈፀምባቸው የቆዩ መሆናቸውን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።

በችሎቱ፡ ከተከሳሾቹ መካከል 17ቱ በሌሉበት የእስር ፍርድ የተላለፈባቸው ሲሆን፡ ለእስር ከተዳረጉት 14 የአማራ ተወላጆች መካከል ሁለቱ በማረሚያ ቤት እንዳሉ በደረሰባቸው ድብደባ ምክኒያት ሕይወታቸው አልፏል፡ አንዱ ከመያዙ በፊት ከፀጥታ አካላት ጋር በነበረ የተኩስ ልውውጥ ቆስሎ በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሕይወቱ አልፏል ተብሎ ብይን ሳይተላለፍባቸው ቀርቷል።

በተጨማሪም በምርመራ ወቅት በተፈፀመባቸው ቶርች ከባድ ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል የሚጠቀሱት ሦስቱ ተከሳሾች በነፃ የተሰናበቱ ሲሆን፡ ችሎቱ በስምንት ተከሳሾች ላይ 13 ዓመት ከስድስት ወር እስከ 23 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶባቸዋል።

በዚህም፦
1ኛ፦ እሸቱ ከበደ 23 ዓመት
2ኛ፦ አበባው አድማሱ 23 ዓመት
3ኛ፦ ጌታቸው ሽፈራው 23 ዓመት
4ኛ፦ ሰለሞን አሰፋ 22 ዓመት
5ኛ፦ ጀማል ሲራጅ 14 ዓመት
6ኛ፦ አህመድ አያሌው 13 ዓመት ከ6 ወር
7ኛ፦ እንድሪስ ሀሰን 13 ዓመት ከ6 ወር
8ኛ፦ ስንታየሁ አዲስ 13 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል ነው ያሉት መረብ ሚዲያ ያነጋገራቸው የግፍ ፍርደኞቹ ቤተሰቦች።

በችሎቱ የአማራ ተወላጅ እስረኞች ምንም አይነት መከላከያ እንዳያቀርቡ ታግደው ነበር የሚሉት ጣቢያችን ያነጋገራቸው የግፍ ፍርደኞቹ ቤተሰቦች፡ ከዚህ ቀደም በነበረው የክርክር ሂደት ላይም ፍርድ ቤቱ፡ የአገዛዙ ጠበቆች ከኦሮሚያ ልዩ ኃይል ጋር እየተመሳጠሩ የሚያቀርቡትን ሀሰተኛ ማስረጃ ብቻ ነው ሲቀበል የቆየው ብለዋል።

በኦሮሚያ ክልል በርካታ የአማራ ተወላጆች አማራነታቸው እንደወንጀል ተቆጥሮ በገፍ ታስረው በሚፈፀምባቸው ድብድባ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ሕይወታቸው ያልፋል።

በርካቶችም በተለይ የምስራቅ ወለጋ ዞን መቀመጫ በሆነችው ነቀምቴ ከተማ እና የሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን መቀመጫ በሆነችው ሻምቡ ከተማ ውስጥ ከሁለት ዓመታት በላይ ታስረው የሚገኙ ሲሆን፡ ከእስረኞቹ መካከል በምርመራ ወቅት በሚፈፀምባቸው ቶርች ጆሯቸው መስማት፣ አይናቸው ማየት እንዳቆመና ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስም እንደማይችሉ የመረብ ሚዲያ ምንጮች ገልፀዋል።
💔2
⚫️#አሳዛኝ_ዜና‼️
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ወገራ ወረዳ የደረሰ ሰብል በመሰብሰብ ላይ የነበሩ ከ10 በላይ ንፁሀን አርሶ አደሮች በጡት ቆራጩ  የአገዛዙ ወንበር አስጠባቂ ሀይል ስራ ላይ እንዳሉ በወጡበት ተገድለዋል ።

አርሶ አደሮቹ  የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል (አፋብኃ ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳግማዊ ቴውድሮስ /አምስተኛ/ ኮር አካል የሆነው ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር የሚንቀሳቀስበት ቀጠና ነዋሪ ሲሆኑ በዚህ አካባቢ የጀግኖች ፋኖዎቻችን  ምትና ሀይል በተደጋጋሚ መቋቋም ያቃተው ሆድ አደሩ የብልፅግና ሰራዊት ዛሬም የበቀል በትሩን  እንደተለመደው ንፁሀን ላይ በማሳረፍ  የደረሰ ሰብልላቸውን በመሰብሰብ ላይ የነበሩ አርሶአደሮችን በጥይት ገድሏቸዋል ።

ይህ አማራ ጠል የሆነው የብልፅግና መንግስት ተብየው በቀጠናው ምንም ጦርነት ባልነበረበት ሰዓት ሆን ብሎ አልሞና አቅዶ አርሶአደሮችን በመግደል ዛሬም አማራን ከምድረ ገፅ የማጥፋት ስራውን ቀጥሎበታል።

ከተገደሉት ንፁሀን አርሶ አደሮች መካከል ጥቂቶቹ
1; አቶ ሞላ ደርብ ዕድሜ 56 ቀበሌ ሚጦ
2;  አቶ ይርዳው ዘመነ ዕድሜ 28 ቀበሌ ሚጦ
3; ወጣት እያያለም ውዱ ዕድሜ 16 ቀበሌ ሚጦ
4; አስማረ በላይ ዕድሜ 38 ቀበሌ ጭልፋ ወንዝ
5; አለምነህ ቀኔ ዕድሜ 60 ቀበሌ ጭልፋ ወንዝ
6; ድረስ ፀሐይ ዕድሜ 62 ቀበሌ ጭልፋ ወንዝ
7; መልካሙ አለሙ  ቁስለኛ ጭልፋ ወንዝ
8; ታደሰ ይግዛው ቁስለኛ ቀበሌ ሚጦ
9; አዋጅ በላይ ቁስለኛ ቀበሌ ሚጦ ሲሆኑ  እንዲሁም  ወ/ሮ ካሳየ ያለው የተባለች እናታችን ሳንቃ ጥቅም ቀበሌ የፋኖ አገርነው እናት ሰባት ልጆችን ያለ አባት ስታሳድግበት የነበረው ቤቷ  ሙሉ በሙሉ በእሳት እንዲወድም በማድረግ ከእነ ልጆቿ ሜዳ ላይ እንድትወድቅ አድርገዋል።
በአጠቃላይ በዚህ ጭፍጨፋ በርካታ የቁም እንስሳትን በመግደል እና ንብረታቸውን ሽጠው የገዙትን የጦር መሳሪያ ጭምር በመቀማት  አርሶአሮችን ለከፍተኛ የሆነ ሰባዊ፣ ቁሳዊና ስነ- ልቦናዊ ጉዳት አድርሶባቸዋል ።

ስለሆነም የሰባዊ መብት ተሟጋች ቦታው ድረስ በአካል በመገኘት ጉዳዩን አጣርተው ለአለማቀፋ ማህበረሰብና መንግስታት ይህ አምባገነን የሆነው የአገዛዙ ስርዓት በእየ ጊዜው ምን ያህል የገዛ ዜጎቹን እየፈጀ እንደሆነ እንዲያውቁልንና እንዲያሳውቁልን ጥሪ እናቀርባለን።

ለሟቾች ነብሳቸውን በአፀደ ገነት እንዲያሳርፍልን  ቤተሰቦች ደግሞ መጽናናትን እንመኛለን ።

  ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !!!!
©አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
💔4
የአርበኛ ጌትነት መሳፍንትን መስዋዕትነት አስመልክቶ ከዋርካው ምሬ ወዳጆ የተላለፈ መልዕክት!

ዘመናትን ተሻግሮ የመጣውን የአማራ ህዝብ ግፍና በደል ለማስቆም ህዝቡንና መላ ቤተሰቡን አስተባብሮ ሲታገል የኖረው የትግል አባታችን አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ዛሬም የዘመናት ግፉ ወደ ዘር ማጥፋት አድጎ የህልውና አደጋ ውስጥ የገባውን የአማራ ህዝብ ለመታደግ እየተደረገ ባለው ተጋድሎ ከባድ ዋጋ እየከፈለ ይገኛል::

በዚህ መራር ዋጋ እየተከፈለበት ባለ ትግል ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ አጅሬ የተሰኘች ታዳጊ ከተማ የሰሜን አምባራስ ክፍለጦር አዛዥና የራስ አሞራው 3ኛ ኮር አስተዳደር ሃላፊ የሆነው አርበኛ ጌትነት መሳፍንት ተስፉ መስዋዕትነት የከፈለ ሲሆን በዚህም ከባድ ሃዘን እንደተሰማኝ ለመግለፅ እወዳለሁ::

ትግላችን እስከቀራኒዮና አባታችን አርበኛ መሳፍንት ተስፉ እስከ ቤተሰብዎ ለአማራ ሕዝብ በደማቅ የደም ቀለም እየተጻፈ ነውና ትውልድ በጀግንነትና ለአማራ ሕዝብ የተከፈለ እውነተኛ አማራነት ነውና ለእሱ በግሌ አመሰግናለሁ ማለት እወዳለሁ። ይህ መስዋዕትነት የአንድ ጀግና መስዋዕትነት ብቻ ሳይሆን ለአማራነት ዋጋ መክፈል ምን ማለት እንደሆነ በሕይወት እያሉ ህያው ምስክር ነዎት!

የአማራ ፋኖ የጀመረውን የህልውና ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል፣ የወንድማችን አርበኛ ጌትነት መሳፍንት ተስፉና በአውደ ውጊያ በወደቁ ጀግኖቻችን ዘመቻ አውጀን የአብይ አህመድን አገዛዝ ድባቅ እንደምንመታው ወደ ድልና ነጻነትም እንደምንሸጋገር ከምስራቅ አማራ ቀጠና ሁኜ ይሄን መልዕክት ሳስተላልፍ በታላቅ ቁርጠኝነትና ቁጭት ሁኜ መሆኔን መግለጽ እፈልጋለሁ።

በመጨረሻም ለአርበኛ መሳፍንት ተስፉ፣ ቤተሰቦቹ፣ እና መላው የትግል ጓዶቹ ልባዊ መጽናናትን እመኛለሁ።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብኃ ማዕከላዊ ኮማንድ አባል እና የምኒልክ ዕዝ ሰብሳቢ ዋርካው ምሬ ወዳጆ
3💔1
ህዳር 1/2018 ዓ.ም ላሊበላ የተከሰተው ምንድን ነው?

ሎሌው አረጋ ከበደና ስብስቡ በላሊበላ በተፈፀመባቸው ያልጠበቁት ከባድ ጥቃት ያሰቡትን ሳያሳኩ ወደ ምሽጋቸው ባህርዳር ተመልሰዋል::

ከኦሮሚያ ብልፅግና ጋር በመተባበር የአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየፈፀመ ያለው አረጋ ከበደና ስብስቡ ከፍተኛ ጭንቀት ላይ ያለው አለቃቸው አብይ አህመድ የሰጣቸውን ተልዕኮ ይዘው ወደ ሰሜን ወሎ ዞን ላሊበላ ከተማ የተጓዙ ሲሆን ትናትና ህዳር 1/2018 ዓ.ም ረፋድ ላሊበላ አየር መንገድ ከደረሰ በኋላ ጥቃት ተፈፅሞበታል::

አቶ አረጋ ከበደ እና የክልሉ ልዑካን ጥቃቱ የተፈፀመባቸው በምኒልክ ዕዝ ላስታ ጀኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ተከዜ ክፍለ ጦር 3ኛ ሻለቃና የክፍለ ጦሩ ሜካናይዝድ በጋራ በመሆን ህዳር 1/2018 ዓ.ም ከጧቱ 2:30 እስከ ረፋዱ 3:30 ድረስ በወሰዱት እርምጃ ነው::

ጥቃቱ የክልሉ ፕሬዝዳንት ነኝ የሚሉት አረጋ ከበደ እና ግብረ አበሮቹ ከባህርዳር ኤርፖርት በመነሳት ላሊበላ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሰው ወደ ላሊበላ ከተማ በማቅናት ላይ እያሉ ሹምሽሃ አየር ማረፊያ አጠገብ ልዩ ስሙ በርታ በተባለ ቦታ ድንገተኛና የተጠና ልዩ የሽምቅ ኦፕሬሽን ነው::

በዚህም ሎሌዎቹ አቶ አረጋ ከበደና ግብረአበሮቹ ከአምላካቸው አብይ አህመድ የተሰጣቸውን ተልዕኮ ሳይፈፅሙ በከባድ ፍርሃትና ድንጋጤ ውስጥ ሆነው ወደ ባህርዳር ተመልሰዋል:: በጥቃቱ ከአስር በላይ ቀይ ቦኔት ለባሽ አጃቢዎቻቸው የተደመሰሱ ሲሆን የተወሰኑ ቁስለኞችም ነበሩ::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ህዳር 2/2018 ዓ.ም
5💔1
የአገዛዙ ብልፅግና ገመና ተጋለጠ!!!!

በጎንደር ቋራ ወስድኩት ባለዉ የድሮን ጥቃት የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ አመራሮችን ገደልኩኝ በሚል በልሳናቱ በኩል ማስራጨቱ ይታወሳል።

ተገደሉ፣ተደመሰሱ የተባሉት የሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ አመራሮች ሰራዊቱን እየመሩ፣እያደራጁ በስራ ላይ መገኘታቸዉ እና መታየታቸዉ የአገዛዙን ገመና አጋልጠዋል።

ተገደሉ በሚል በወቅቱ ዜና ያሰራጩት የአገዛዙ ልሳናት ጀግኖቹን የቲዎድሮስ ልጆች በጀግንነት ስራቸዉን እየከወኑ ሲመለከቱ የሚደበቁበት መጋረጃ፣የሚገቡበት ጉድጓድ አተዋል።

በዝርዝር እንመለስበታለን!!!
@ግሎባል ፋኖ ሚዲያ!!!
👍71