ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.21K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
አፋብኃ ምኒሊክ ዕዝ በበርካታ ቀጠናወች ምልምል ፋኖዎችን እያሰለጠነ ራሱን በሰው ሀይል እያጠናከረ ያለ ሲሆን ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሎ በመደራጀትላይ ያለችው በላጎ ተወርዋሪ ሻለቃ በደሴ ዙሪያ ወረዳ ለወራቶች ያሰለጠኗቸውን በቀን 27/2/2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ማስመረቁን ይታወቃል::

ይህን ሁኔታ ያየው የደሴ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና እና የብርሀኑ ጁላ ሰራዊት በቀን 28/2/2018 ዓ.ም በደሴ ዙሪያ ወረዳ የሚቀሳቀሰውን ፋኖ አጠፋለኩ ብሎ የመጣው የመከላከያ ሰራዊት ተብየውና የአድማ ብተና ሚኒሻና ፖሊስ ጥምር ጦር በሁለት አቅጣጫ መነሻውን ከደሴ አዲርጎ በጉጉፍቱና ከደሴ የተነሳው በአስግዶ በኩል በሁለት አቅጣጫ መቶ ፋኖ በሚቀሳቀስባቸው ቦታወች የገባው ጥምር ጦር

አፋብኃ ምኒሊክ ዕዝ በላጎ ተወርዋሪ ሻለቃና አዲስ ተመራቂ ሰልጣኖች በምርቃት ማግስት የመጣውን ጥምርጦር ቀድሞ መረጃው ስለደረሰን አጥትመስበሪያና እሁዲት ተብለው የሚጠሩ ቦታወችላይ ደፈጣ በመያዝ የመጣውን ጥምርጦር በላጎ ተወርዎሪ ሻለቃ ሙትና ቁስለኛ አርጎ መልሶታል በዚክም መብረቃዊይ ጥቃት ሁለት መኪና እሬሳውንና ሶስት አቡላስ ቁስለኛውን ከደሴና ኮምቦልቻ ከኩታበር ወረዳ ተጨማሪ ሀይል አምጥቶ ሙትና ቁስለኛውን ጭኖ እግሬአውጭኝ ብሎ ወደ ደሴ ከተማ ተመልሶ ገብቷል::

መዳረሻችን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልወና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል

ህልውናችን በተባበረ ክዳችን
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒሊክ ዕዝ
ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም
2🙏1
በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ሜክሲኮ በምርመራ ስም ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው ለሚገኙ አማራዎች ድምፅ እንሁናቸው!

ጠበቆች ፣ የሰብአዊ መብት ተቋማት ፣ ቀይ መስቀልና ጋዜጠኞች በስፍራው ተገኝታችሁ እንድትጎበኟቸውና ድምፅ እንድትሆኗቸው ተጠይቃችኋል።

በድብደባ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውና ሕክምና ተከልክለው በስቃይ ከሚገኙት በርካታ የማንነት ፣ የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞች መካከል ፦

1. ተመስገን አቤ፣
2. ያለም ሰው፣
3. ብሩክ እና
4. አለም የተባሉ እስረኞች ይገኙበታል።

ፍትህ ለሁሉም!

(አውሎግሶን አንድነት ፣ ጥቅምት 28/2018)
በሽብር ወንጀል የተከሰሱት እነ እስራኤል መስፍን ፍ/ቤት ቀርበዋል ፤ ተከሳሽ ልዑል እማዩ በአንድ የፌደራል ፖሊስ አባል ስለተፈፀመበት ድብደባ አቤቱታውን ለፍ/ቤት በጽሁፍ አቅርቧል ፤ ችሎቱ እንዳይናገር ከልክሎታል።  

በሽብር ወንጀል የተከሰሱት እነ እስራኤል መስፍን ጥቅምት 26/2018 ፍ/ቤት ቀርበዋል ፤ በእለቱም ተከሳሽ ልዑል እማዩ በሚኖርበት በቂሊንጦ ማ/ቤት በአንድ የፌደራል ፖሊስ አባል ጥቅምት 20/2018  ስለተፈፀመበት ድብደባ አቤቱታውን ለፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በጽሁፍ አቅርቧል።

ይሁን እንጅ ተበዳይ ልዑል እማዩ ስለ አቤቱታው በቃል ለመናገር እድሉ እንዲሰጠው ቢጠይቅም ችሎቱ እንዳይናገር ከልክሎታል። 
 
መዝገቡ የተቀጠረው የዐቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማት ቢሆንም ምስክሮችን አሟልቶ ባለመቅረቡ ተከሳሾች ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

በዚህም መሰረት ዐቃቤ ሕግ ምስክሮችን አሟልቶ በመቅረብ ለታህሳስ 13/2018 እንዲያስመሰክር ቀጠሮ ተሰጥቷል።

በመዝገቡ ሁለተኛ ተከሳሽ የሆነው የፖለቲካ እስረኛው ልዑል እማዩ በእለቱ ለፍ/ቤቱ በጽሁፍ ካመለከተው አቤቱታ ላይ እንደገለፀው በሚኖርበት ቂሊንጦ ማ/ቤት በአንድ የፌደራል ፖሊስ አባል ጥቅምት 20/2018 በዱላ እና በቦክስ ድብደባ እና የግድያ ዛቻ ተፈጽሞበታል።

በጥቃቱም አካላዊ እና የስነ ልቦናዊ ጉዳት የደረሰበት ስለመሆኑ ለችሎቱ አሳውቋል።
 
ጥቅምት 25/2018 በተጻፈ በዚሁ ደብዳቤውም ስለደረሰበት ድብደባ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እና የቂሊንጦ ማ/ቤት ኃላፊዎች ተገቢ ማጣራት እንዲያደርጉ ፍ/ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥለት ነው የጠየቀው።

የወንጀል ድርጊት የፈፀመው አባልም ተይዞ በሕግ ፊት ቀርቦ እንዲጠየቅለት ነው ተበዳዩ ያመለከተው። 

ልዑል ጥቅምት 21/2018 በተጻፈ ማመልከቻውም ለቂሊንጦ ማ/ቤት አስተዳደር የደረሰበትን ጥቃት አሳውቆ ፍትህ እንዲሰጠው መጠየቁም ተመላክቷል።

የቂሊንጦ ማ/ቤት በተለይም ከነሃሴ 2017 ጀምሮ ከሕግ ውጭ በፌደራል ፖሊስ እየተጠበቀ ነው ፤ በሕግ እስረኞችና በቤተሰቦቻቸው ላይም ከማ/ቤቱ አባላት ጋር በመሆን ሰብአዊነት የጎደለው ፍተሻ እያካሄደ ነው ፣ እስረኞችን በሌሊት እየፈተሸ ነው ፣ እያጀበ ነው ፣ በየትኛው ሕግ ነው ይህ ሊሆን የቻለው? እየተፈጠረ ላለው ችግርስ ማን ተጠያቂ ሊሆን ነው በሚል በተለይም ጥቅምት 18/2018 በእነ የተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው መዝገብ ተከሳሾች እንዲሁም ከችሎቱም ጭምር ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ኢ/ር ድሪባ ሰንበታ አምነው ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል።
 
ይኸውም ከፌደራል ፖሊስ ጋር በፍተሻ እና በእጀባ አብረው እንዲሰሩ የቃል አቅጣጫ ከበላይ እንደተሰጣቸው ጠቅሰው በፌደራል ፖሊስ ችግር ከተፈጠረ ማ/ቤቱ ኃላፊነቱን ይወስዳል ማለታቸው ይታወቃል።

©
ፋሽስቱ አገዛዝ በአንጎት ወረዳ የግለሰብ ተሽከርካሪ (ባጃጅ) እና እንስሳቶችን አወደመ።

ስርዓቱ የግለሰብ ባጃጅ ያቃጠለ ሲሆን፤እንስሳዎችን ደግሞ ተኩሶ ገሏቸዋል።

ጥቅምት 29/2018 ዓ/ም የፋሽስቱ ስርዓት
ከአስር በላይ ላም፤በሬና በጎች በአገዛዙ ሰራዊት ሲገድሉ፤አንድ ባጃጅ ደግሞ ሙሉ በሙሉ አቃጥለውታል።

ለብልፅግና ስርዓት የአማራ ህዝብ አይደለም እንስሳቱም፤እፅዋቱም፤ንብረቶችም ጥላት ናቸው ብሎ የዘመተባቸው ስርዓት በአንጎት ወረዳ የህዝቡን ንብረት በዛሬው እለት አውድሟል።

ባጃጆች ማንነት አላቸው፤እንስሳዎችም አማራ ናቸው። የአማራ ህዝብ ህይዎቱ ብቻ ሳይሆን ኢኮኖሚውም መውደም አለበት ብሎ የሚያስበው የበሻሻው ስብስብ አፀያፊ ድርጊት በእንስሳቶችና በተሽከርካሪ ንብረቶች ላይ ፀያፍ ድርጊት ፈፅሞባቸዋል።

መዳረሻችን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልወና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል

ህልውናችን በተባበረ ክዳችን
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒሊክ ዕዝ
ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም
በአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና የምንሊክ እዝ - ወታደራዊ አዛዥ ድርሳን ብርሃኔ :
- ዋና አዛዥ ዋርካው ምሬ ወዳጆ እና
- ፋኖ አበበ ፈንታው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
ፋኖ በሰሜን ጎንደር አዳርቃይ እና ዛሬማ አካባቢ ታላቅ ድል ፈፅሟል።

የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ  የራስ አሞራዉ ዉብነህ ሶስተኛ ኮር ድብ ጠለምት ተከዜ እና ጭና ክፍለጥር በጡት ቆራጩ የአብይ አህመድ ሰራዊት ላይ ከፍተኛ የሆነ ድል መቀዳጃታቸዉን አስታዉቀዋል።

ከጥቅምት 26/2018 ዓ.ም እስ ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም ድረስ በነበረዉ እልህ አስጨራሽ አዉደዉጊያ በመደርዘን የሚቆጠር የስርአቱ አገልጋይ ሰራዊት ድል ተደርጓል።

የአገዛዙ ብልፅግና የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ሶስት ክፍለጦር ሰራዊት በአዳርቃይ እና ዛሬማ ቢሰማራም አብዛኛው ሰራዊት መደምሰሱ ተገልጿል።ለአራት ተከታታይ ቀናት በተደረገዉ እልህ አስጨራሽ አዉደዉጊያ ከ90 በላይ የጠላት ሰራዊት ሲደመሰስ 80 የነፍስወከፍ ክላሽንኮቭ መሳሪያ ደግሞ ምርኮ ተደርጓል።

ጥቅምት 27 ለጥቅምት 29 አጥቢያ ሌሊቱን የድብ ጠለምት ተከዜ ክፍለጦርን የከበበዉ የአገዛዙ ሰራዊት ከፍተኛ የሆነ ሽንፈትን አስተናግዷል።በለሊቱ በተደረገዉ አዉደዉጊያ ቁጥሩ በዉል ያልታወቀ ሰራዊት መደምሰሱን የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ራስ አሞራዉ ዉብነህ ሶስተኛ ኮር ድብ ጠለምት ተከዜ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አርበኛ እሸቱ መለሰ ለግሎባል ፋኖ ሚዲያ ተናግሯል።

አዉደዉጊያዉ ዛሬም ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ፋኖ በርካታ ወታደራዊ ቦታዎችን ተቆጣጥሯል ።በፋኖ ከፍተኛ ምት ያስተናገደዉ እና አብዛኛው ሰራዊት የተደመሰሰበት የብልፅግ ጡት ቆራጭ ሰራዊት በሰላማዊ ዜጎች ሀብት እና ንብረት ቁሳዊ ጉዳት አድርሷል።
የአርበኛ ታድሎ ደሴ ፩ኛ ዓመት መታሰቢያ

አርበኛው፣ የትሕነግ ሕወሓት ወታደር አከርካሪ ሰባሪው፣ የፋሽሥቱ አቢይ ሸኔ ወታደር እግር እሣት፣ የጎጠኞች መድኃኒቱ፣ የአጣዬው ዘማቹ፣ (የነአሥቻለው ደሤ፣ ዘማች ሞላ፣ ዳንኤል፣ መልኬ፣ ቢሰጥ፣ አሌክሥና መላሽ) የትግል ጓዳቸው፣ የዳውንትና ጋሸና ምሽግ ደርማሽ፣ የደብረ ዘቢጡ ኮንክሪት ምሽግ አፈራራሽ፣ የአሣምነው ፅጌን አላማ ተግባሪ፣ የአጣዬው ዘማች፣ የተጎዳው አማራ የፍትሕ ዘብ፣ የራያው በላጎ ምሽግ ሰባሪ፣ የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ቀኝ እጅ፣ የነበዕውቀትና ቻይና ዕውነተኛ የትግል ጓድ፣ የብአዴኖች መድኃኒት፣ የአማራ ሕዝብ ሕልውናዊ ትግልን በውል የተረዳ የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ቀኝ እጅና ራዕይ ተጋሪ፣ የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር አባልና አብሪ ኮከብ ታጋይ ለነገደ አምሐራዊ ነጻነቱ በክብር መሥዋዕትነትን የተቀበለ ዕንቁ

ጥቅምት 28/2017ዓ.ም ከሰዓት የጠላት ጦር ከደብረ ታቦርና ከወረታ በአለም በር በኩል ከጀርባ ፋኖን ሊወጋ ተንቀሳቀሰ። የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ቃኝ ሻለቃም ለ4 ተከታታይ ሠዓታት እልህ አሥጨራሽ ውጊያ አድርገው በውሥን የአማራ ፋኖ የአቢይ መከላከያ ወደ ደብረታቦር እንዲፈረጥጥ አደረጉ።

ከደብረ ታቦር የመጣው መከላከያ ከአማራ ፋኖ ጋር ሲገጥም በሌላ አቅጣጫ አማራ በታኙ አድማ ብተና የፋኖ ቤተሰብ የሆኑ የቁም ከብቶችን(በቁጥር 23) በምን ታመጣላችሁ ወደ ደብረታቦር እየነዳቸው ነበር። በእብሪት የተወጠረውን አማራ በታኝ በትኖና 23ቱንም ከብቶች ከእገታና ከመታረድ ታድጎ በመሐል አለም በር ከተማ ወደ መዳረሻቸው እየመለሷቸው እያለ ከወረታ የመጣው የአቢይ መከላከያ ገጠማቸው።

አርበኛው ጠላቶቹን ከረፈረፈ በኋላ በጀግንነት መሥዋዕትነትን ተቀበለ። የጀግና ሞቱ ክብሩ ነውና አርበኛው ጠላትን ረፍርፎ በአማራዊ ጀግንነት በክብር ሰማዕትነትን ተቀብሏል። አሁን አንድ አርበኛ ታድሎ ደሤ በእልፍ አእላፋት ታድሎዎች ተተክቷል።

በዕውነት ሥለ ዕውነት ለመናገር ይህ ዋጋ እየተከፈለለት ያለ የአማራ ትግል በጎጠኞች እንዲቆሽሽ ለናኖ ሰከንድ ልንፈቅድላቸው አይገባም። ፀሐይ የመግባት የመውጣቷን ያክል የአማራ ትግልም እንደሚያሸንፍ ቅንጣት ታክል አንጠራጠርም፤ ፩ አምሐራ ያሸንፋል

አርበኛ ታድሎ ደሤ አማራ ሆኖ ተፈጥሮ፣ ለአማራ ታግሎ፣ አማራ ሆኖ በክብር አልፏል።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ነፍሥ ሔር ወንድማለም

@ሀቅያለው አለባቸው
በአፋብኃ በላይ እዝ ሜጄር ጄኔራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ከህዝብ የተሰጠ የኒሻን ሽልማት የለም ሲሉ የጎንደር ከተማ ኗሪዎች ተናገሩ።

በአገዛዙ ልሳናት በኩል የኒሻን ሽልማት ተሰጠዉ የሚለዉ ዘገባ የጎንደር ህዝብ የማያዉቀዉ እና ሽልማቱም በህዝቡ የተሰጠ አደለም ብለዋል።

ትናንት ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም በጎንደር ከተማ የተገኛዉ ምስለኔዉ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ የጎንደር ህዝብን እድሉን ተጠቀሙበት ሲል ንግግር አድርጓል።ይህንን የኮሪደር ልማት የገነባነዉ መንግስታችን ብልፅግና በፈተና ዉስጥ ሆኖ ነዉ ያለዉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጎንደር ህዝብ ብልፅግናን መታደግ አለበት የሚል ንግግር አድርጓል።የጎንደር ህዝብ በአብይ አህመድ የስልጣን ዘመን ልጆቹ በጀምላ ተገድለዉበታል፣ቤተክርስቲያን እና መስጅድ ተቃጥለዋል፣የሀይማኖት አባቶች ተገድለዋል፣ህፃናት እና አዛዉንት በግፍ በድሮን ተገድለዋል፣መሰረተ ልማቶችም በድሮን እና በከባድ መሳሪያ እንዲወድሙ ተደርገዋል።

ይሄን በደርዘን የሚቆጠር ወንጀል የፈፀመዉ አገዛዝ ትናንት ለጎንደር ህዝብ ፃድቅ መስሎ መቅረቡ ሁሉንም አሳዝኗል።ጦርነት ተኮር መርህ የሚከተለዉ የበሻሻዉ አለቃ ቤተመንግሥት አድሻለሁ እና እኔን የጎንደር ህዝብ ሊያመሰግነኝ ይገባል ሲል መናገሩ ይታወሳል።የአገዛዙ ልሳናት እና አክቲቪስቶችም ግንደርን አብይ ሞሸራት ሲሉ የተለመደ ቅጥፈታቸዉን አስተጋብተዋል።ልጇን የገደለባት እናት አባቷን የገደለባት ልጅ ለአብይ አህመድ አሊ ኒሻን የምትሸልምበት ሞራል የለም ሲሉ ኗሪዎች ሽልማቱን አጣጥለዉታል።

ህዝቡ ቢልተገኘበት ከተማዋ ላይ ሰዉ እንዳይንቀሳቀስ ዙሪያዉን በሪፑብሊካኑ ጋርድ፣በአየር ወለድ፣በአጋዚ ኮማንዶ እና በአረጋ ከበደ ቅልብ ሰራዊት ተከባ በዋለችበት በትናንትናው ዕለት የጎንደር ህዝብ ለአብይ አህመድ ኒሻን ሸለመ መባሉ አስደንግጦናል ብለዋል።

የጎንደር ህዝብ ኒሻን ሸለመ የሚለዉን እንደማንኛውም ሰዉ በዜና ነዉ የሰማነዉ ብለዋል።የከተማው የብልፅግና ተላላኪ ባንዳዎች የተከበረዉን የጎንደር ህዝብን ለሆዳቸዉ ማደሪያ አድርገዉታል ያሉ ሲሆን ከዚህ በፊትም የጎንደር ህዝብ ቤተመንግሥቱ በአብይ አህመድ አሊ በመታደሱ የጎንደር ህዝብ አመስግኗል የሚል ሀሰተኛ መረጃ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በኩል መዘገቡን እናስታዉሳለን ሁሉም መረጃ ከእዉነት የራቀ መሆኑን ሁሉም ኢትዮጵያ ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል።በአርሴ ከሶስት መቶ በላይ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን ገድሎ የጎንደር ህዝብ ኒሻን የሚሸልበት ሞራል የለዉም ሲሉ ኗሪዎች የብልፅግናን ዉሸት አጣጥለዋል።

በዉሸት የሚገነባ መንግስት መጨረሻዉ ዉድቀት ነዉ እኛ እንደ አማራ ህዝብ መከራ እና ስቃይን በብልፅግናዉ መንግስት እየተቀበልን ያለን ህዝቦች ነን ይህንን መከራ ለመቀልበስ እንደ አማራ አምርረን የምንታገለዉ መንግስት ነዉ ብለዋል።

የቤተመንግሥቱን እድሳት እንደ አጋጣሚ በመጠቀም ህዝቡ በአብይ አህመድ የጦርነት ፕሮጀክት ተሳታፊ ለማድረግ የታቀደ ቢሆንም የጎንደር ከተማ ህዝብ አብይ አህመድ አሊን እንደ ጀመርክ ጨርሰዉ ብለዉታል።የጎንደር ህዝብ የቀይ ባህር ጉዳይ ጉዳያችን አደለም ጉዳያችን ግዛታችን አሳልፎ ለመስጠት የሚደረገዉ የብልፅግና ሴራ ነዉ ሲሉ ምላሽ ሰተዋል።

የህወሓት እና የሻቢያን ጉዳይ በማንሳት ለተወካዩቹ ንግግር ያደረገዉ አብይ ይህን ሀሳብ ህዝቡን ለህዝቡ በመንገር ወደባችን እንድንስመልስ መስራት አለባቹህ በማለት ለካድሬዎቹ ማስጠንቀቂያ ሰቷል።ቤተመንግስቱን ለጦርነት ቅስቀሳ ለመጠቀም ቢታሰብም በህዝቡ ዘንድ ግን ተቀባይት አቷል።

ዛሬ የጎንደር ከተማ ካድሬዎች የተመረጡ የከተማዋን ኗሪዎች ቤተመንግሥቱን ካስጎበኙ በኋላ አሁን ፍላጎታችን ወደብ ብቻ ነዉ እናንተ ደግሞ ወደቡ እንዲመለስ አስተዋፅኦ ማድረግ አለባቹህ በማለት ለህዝቡ ቢያስረዱም የተመረጡ የከተማ ኗሪዎች ደግሞ የታደሰዉን ቤተመንግሥት እዩልን ስላላቹህ መጣን እንጂ አሰብን እናስመልስ ብላቹህ አልጠራቹንም በአሰብ ጉዳይ የአማራ ህዝብአይመለከተዉም የታደሰዉ ቤተመንግሥትም በገንዘባችን እስከሆነ ድረስ ለህዝባችን ላቅ ያለ ምስግና እናቀርባለን ነገር ግን በቤተመንግሥቱ መታደስ ስም የድሀ ልጆችን ለጦርነት መቀስቀስ የለብንም ከለፈዉ ጦርነት ሙማር አለብን የሚል ቆፍጠን ያለ ምላሽ ሰተዋል።

ለብልፅግና ወንበር መፅናት ሲባል የአማራ ህዝብ የጦርነት ሰለባ እንደማይሆን ከአዲስአበባ እስከ ባህርዳር ጎንደር ድረስ በቂ መልስ ተሰቶበታል።

ሁለቱ የአማራ ህዝብ ቋሚ ጠላቶች ብልፅግና እና ህወሓት በአፋር በኩል ጠንከር ያለ ጦርነት መጀመራቸዉ ደግሞ አብይ አህመድ ጊዜዉ አሁን ነዉ በሚል በቤተመንግስት እድሳት ስም አማራን ማታለል አለብኝ ብሎ በጎንደር መገኘቱ ህዝቡን የበለጠ እንዲነቃ እና እንደጀመርከዉ ጨርሰዉ እንዲል አስብሎታል።

የበሻሻዉ የንግር ልጅ በህወሓት የተከፈተበትን ጦርነት እና አሰብን ከአማራ ህዝብ ዉጭ ማሸነፍ እና ማስመለስ እንደማይችል የተረዳ ይመስላል።ትናንት ቀይ ባህርን ለማስመለስ በሚዲያ ሲፎክር የነበረዉ ብልፅግና አሁን ላይ የአፋሯን ሰመራ ከተማን ላለመስጠት እየተፍጨረጨረ ይገኛል።ሁለቱ የአማራ ህዝብ ታሪካዊ ጠላቶች ግን በአፋር በኩል በከባድ መሳሪያ የታገዘ ዉጊያ ከከፈቱ ሶስተኛ ቀናትን አስቆጥረዋል።

በእነዚህ ቀናቶች ዉስጥ የአብይ  አህመድ አሊ የእግረኛ ሰራዊት የህወሓቱን ታጣቂ ቡድን መቋቋም ባለመቻሉ መካናይዝድ እና አየር ኃይሉን ብቻ ቀመጠቀም ጦርነቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።አሰብን ለማስመለስ ቡሬ ሰፍሮ የነበረዉ የአብይ አህመድ አሊ ምስለኔ መከላከያ ሰራዊት ሰመራን ከተማ እየተከላከለ ይገኛል።

በሚዲያ በኩል አክቲቪስቱን እና የአገዛዙን ባለስልጣን ያስፎከረዉ የብልፅግና ሰራዊት በህወሓት መጠናኛ ትንኮሳ ብቻ ከቡሬ ሰመራ እንዲደርስ ሆኗል።ወደብ ያስመልሳል የተባለዉ ጦር የራሱን ህይወት ከህዎት ታጣቂ ቡድን ለማትረፍ እየተራወጠ ቀጥሏል።

@ግሎባል ፋኖ ሚዲያ!!
የፋኖ ድምፅ!!!
2
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር!

የአገዛዙ ብልፅግና ሰራዊት ዙ-23 ከጥቅም ውጭ ተደረገ!

ጥቅምት 29/2018ዓ.ም

በአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ተከዜ ክፍለ ጦር ልዩ ዘመቻ ባደረገው ትንቅንቅ ልዩ ቦታው ቻይና ካምፕ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ ላይ በተደረገ ትግል አንድ የአገዛዙ ዙ-23 ከጥቅም ውጭ የተደረገ ሲሆን እዛው የነበሩ አራቱ ሲደመሰሱ ሦስቱ ቆስለዋል።

በተያያዘ መረጃ ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም በተከዜ ክፍለ ጦር ስር የሚገኘው አምስተኛ ሻለቃ ባደረገው ተጋድሎ ከወደ ደላንታ በግለሰብ አይሱዙ ይመጣ የነበረውን ጠላት ዥጣ ወንዝ ላይ በመጠበቅ አምስቱን ሲደመስስ ዘጠኙን አቁስሏል። በዚህ የተናደደው የጠላት ኃይል የግለሰብ ባጃጅ አቃጥሎ ሄዷል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ተከዜ ክፍለጦር ቃል አቀባይ ፋኖ ኢንጅነር አማረ ካሳ መረጃውን አድርሷል።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥቅምት 29/ 2018 ዓ.ም
1