ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.33K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.21K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
የደጋው መብረቅ ክፍለጦር ከስድስት ወራቶች በላይ የኮማንዶ ስልጠናን ሲወስዱ የነበሩ የልዩ ኮማንዶ አባላቶች በዛሬው እለት በርካታ ህዝብ በተገኘበት መድረክ አስመረቀ::

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒልክ ዕዝ የደጋው መብረቅ ክፍለ ጦር ከስድስ ወራቶች በላይ ልዩ የኮማንዶ ስልጠና ሲሰጣቸው የቆዩ ልዩ ኮማንደዎችን ጥቅምት 20/2018 ዓም አስመርቋል። የተለያዩ ትርዒቶችን ያሳዩ በአማራ ህዝብ ላይ የሚደርሰውን የዘር ጭፍጨፋ ተመራቂዎቹ በግጥም አዋዝተው ለተመልካች ህዝቦች ገልፀዋል። ከዚህ ጋር ተያይዞ ልዩ ኮማንዶዎቹ በአማራ ህዝብ ፊት ቃለማህላ መሀላ ፈፅመዋል።ለአማራ ህዝብ የህልውና ዘቦች መሆናቸውን ጭምር ተመራቂዎች ገልፀዋል።

በምርቃት ፕሮግራም ላይ የፋኖ ከፍተኛ አመራሮች፤ የክብር እንግዶች፤ የአማራ ህዝቦች እና የትግሉ ደጋፊዎች የተገኙ ሲሆን ልዩ ኮማዶዎቹ ያሳዩት ትርዒት ህዝቦችን በደስታ እና ለካም እንችላለን በሚል ቁጭት አዘል ያስነባ ትርዒት ሆናል።

እውቀትንና ጥበብን በተካኑት አሰልጣኞች
#በመቶ አለቃ ሲሳይ መልካሙ
#በኮማንዶ ጋሻው ቢያርጎ
#በኮማንዶ ይልቃል አስማረ እና በርካታ የማሰልጠን ብቃት ያላቸው አሰልጣኞች ሙያቸውንና ጥበባቸውን ሙሉ ተጠቅመው ያሰለጠኗቸው የልዩ ኮማንዶ አባላቶች በስነ-ምግባርና በራዕይ ተገብተው የአማራን ህዝብ ሰለቸኝ ደከመኝ ሳይሉ ሌት ተቀን የተጋረጠበትን የህልውና አዳጋ ለመመከት ብቁ የነፃነት ፍሬ እዳፈሩ ተደርገው ታንፀዋል።

ተመራቂ ልዩ ኮማንዶዎቹ በእሳት ላንቃ መሀል እንደ አቦሸማኔ እየተምወገዘጉ፤የእጅ ለእጅ የሳንጃ ግጥሚያን ፤የካታ አርትን ትርዒቶችን በማሳየት ከስድስት ወራቶች በላይ ዋጋ የከፈሉበትን ውጤታቸውን ለህዝባቸው ሲያሳዩ የአማራ ህዝብ ወደር አልባ ደስታ ከፊታቸው ሞልቶ ይታፈስ ነበር።

በዚህ የምርቃት ፕሮግራም ላይ አርበኛ ተመስገን አለባቸው፤ ሻለቃ ሀብቴ እባቡ፤ አርበኛ ጨለፍ ተስፋው እና በርካታ የፋኖ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው የምርቃት ስነ ስርዓቱን የከፈቱት ሲሆን ከፍተኛ አመራሮቹም "ከዚህም በላይ እናሰለጥናለን፤ እንደራጃለን፤ ጥላታችንን ደምስሰን የአማራን ህዝብ ነፃ እናዎጣለን። ለዚህ ደግሞ ሁሉም አቅሙ የሚፈቅድ አመራ ሁሉ መሰልጠን አለበት። እደህዝብ ሊያጠፋን የመጣን ወራሪ ሀይል እደ ህዝብ ልንመክተው ይገባናል።" ሲሉ ገልፀዋል።

የከባቢውን ወጣትና ህዝብ ሞራል የሚነሽጠው የልዩ ኮማንዶ የምርቃት ፕሮግራም ከምንጊዜውም በላይ አማራ የይቻላል የሞራል ተነሳሽነትን ያሳዩበት ንቅናቄም ነበር። ከምርቃት ፕሮግራሙ በኋላም የከባቢው ማህበረሰብ የልዩ ኮማንዶ ተመራቂዎችን በስስት አጅቦ ብሮ ወሸባዬ ያለበት አማራዊያን አውድ ሆኗል።

"ሰልጥነን እንዋጋለን እየተዋጋን እንሰለጥናለን!"

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
የደጋው መብረቅ ክፍለጦር
ጥቅምት 20/2018 ዓ.ም
2🙏2
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ እዝ ወታደራዊ አማካሪ ኮሎኔል ሞገስ ዘገየ
ምልምል የፋኖ ኮማንዶ ሰልጣኞችን በማበረታታት ላይ ሳለ ያስተላለፈው መልእክት!
🙏2
የዮሐንስ አለማየሁ ብርጌድ በጠላት ላይ ድንገተኛ ጥቃት ፈፅሟል።

በአፋብኃ ምዕ.አ.ቀ.ቴ.ዕዝ የዮሐንስ አለማየሁ ብርጌድ በጠላት ላይ ድንገተኛ ጥቃት ፈፅሞ ድል ተቀናጅቷል።

ጥቃቱ የተፈመው በትላንትናው እለት መንግስት ተብዮው የህዝብ ጠላት ከአዴትና ከሌላም ቦታ በመሰባሰብ የተለመደ ፕሮፖጋንዳውን ለመርጨት በሚዶልቱበት ወቅት ለዙሪያ ጥበቃ ባስቀመጧቸው ሆድ አደሮች ላይ ነው።
ጥቃቱ የተፈፀመው ጠላትን ከሁለት አቅጣጫ በመክበብ ሲሆን በዚህ ጥቃትም 5 የመከላከያ አባላት ሲሞቱ 3ቱ ቁስለኛ ሆነዋል።

በዚህ የተበሳጨው የአገዛዙ ሰራዊት  በዙ-23 ደብረ -ፅላሎ ወደተባለ ቀበሌ አርሶ አደሮች ለስራ እንደተሰማሩ ፣ህፃናቱና ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች በተበተኑበት ህዝቡን ለመምታት በታሰበ መልኩ ከርቀት ሲደበድብ ውሏል።

         አዲስ ትውልድ
         አዲስ አስተሳሰብ
         አዲስ ተስፋ
የዮሐንስ አለማየሁ ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት

          ጥቅምት 20/2018 ዓ.ም
🙏3
ምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ ለወራቶች ያሰለጠናቸውን ልዩ ኮማንዶዎች በድምቀት አስመረቀ::

አፋብኃ ምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ ለወራቶች ያሰለጠናቸውን ልዩ ኮማንዶዎች ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል::

የአማራን ህዝብ ህልውና ለማረጋገጥ ሁለንተናዊ ተጋድሎ እያደረገ ያለው ፋኖ አዳዲስ ምልምል ፋኖዎችን በእግረኛ እና በልዩ ኮማንዶ ብሎም በመካናይዝድ ደረጃ እያሰለጠነና እያስመረቀ ነባሩን የፋኖ ሰራዊት በሰው ሃይል እያጠናከረ ይገኛል::

ከዚህ ጋር ተያይዞም የዕዙ ስልጠና መምሪያ በበርካታ ቀጠናዎች ምልምል ፋኖዎችን እያሰለጠነ እያስመረቀ ሲሆን በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል::

ሰልጥነን እንዋጋለን እየተዋጋን እንሰለጥናለን!

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም
🙏4
መንግስት ለአርሲው ግድያ “ ይቅርታ እንዲጠይቅና ካሣ እንዲከፍል ” ኢሕአፓ ጠየቀ፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ይህንን ያለው ዛሬ ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣውና ለአዲስ ማለዳ በላከላት መግለጫ ላይ ነው፡፡

ፓርቲው በመግለጫው “ በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ አርሲ ዞን አስተዳደር እና ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ለሊት በጉና እና በመርቲ ወረዳዎች 17፣ ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሊት በሽርካ ወረዳ 3፣ ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ለሊት በሆሎንቆ ዋቢ ወረዳ 5 በድምሩ 25 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ ምዕመናን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ” ብሏል፡፡

ኢሕአፓ በምዕመኑ ላይ የተፈጸመው ግድያና አካላዊ ጉዳትን አውግዞ መንግስት ተጠያቂነቱን እንዲያምን እና ወንጀሉን የፈጸሙት አካላት በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ አሳስቧል፡፡

ለደረሰው ግድያና አካላዊ ጉዳት የተሰማውን ሐዘን የገለጸው ፓርቲው መንግስት ይቅርታ እንዲጠይቅና አስፈላጊ ያለውን ካሳ ለሚመለከታቸው ሁሉ እንዲከፍል ጠይቋል፡፡ የፓርቲው መግለጫ ሲቀጥል ጉዳት ከደረሰባቸው ባለፈም የዕምነቱን ተከታዮች፣ የእስልምና ተከታዮች ላይ ለደረሱት ጉዳቶች በተመሳሳይ ይቅርታ እንዲጠይቅ አሳስቧል፡፡

ከጥቂት አመታት ወዲህ የተባባሱት መጠነ-ሰፊ በዕምነትና በዘር ልዩነት ላይ የተመሠረቱ ግድያዎች፤ አፈናዎች፣ እገታዎች፣ ማፈናቀሎች፣ የንብረት ንጥቂያዎችና ውድመቶች በአስቸኳይ ሊቆሙ ይገባል ብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤት ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ባወጣው መግለጫ መንግስት የዜጎችን የመኖር መብት እንዲያረጋግጥ ጠይቋል፡፡
2👍1
ብልጽግና በሊቦ ከምከም ወረዳ ንጹሃን አርሶ አደሮችን ጨፈጨፈ።
በትላንትናው እለት ጥቅምት 20 /2018 ዓ.ም በሊቦ ከምከም ወረዳ ቡራ እግዚአራብ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጭሮየ ከተባለው አካባቢ በመከላከያና የአማራ ህዝብ ጡት ነካሽ በሆነው ሚሊሻ አባት እስከነ ልጁን እና ከብቶችን ግጦሽ ላይ በማገት ላይ የነበረን የ8 ዓመት ህፃንን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ 7 በላይ ንጹሃን አርሶ አደር አማሮችን በአሰቃቂ ሁኔታ ረሽነዋል።
ከዚህም በተጨማሪ እዚሁ ቀበሌ ላይ ዘመድ ለመጠየቅ ከሌላ ቦታ የመጡ የቡራ እግዚአራብ ቀበሌ ነዋሪ ያልሆኑ ተጨማሪ አባትና ልጅም በግፍ ተረሽነዋል። ከተረሸኑት ንጹሃን አማሮች መካከል:-
1- ሞላ ታከለ
2-አስቻለው ሞላ
3- ሃብቴ አዲሴ
እንዲሁም ሌሎች ለጊዜው ስማቸው ያልደረሰን ወገኖቻችንም ተወልደው ባደጉበት ፣ ድረው ኩለውና አርሰው አንደፋርሰው በኖሩበት ቀያቸው በብልጽግና አረመኔ አሽከሮች የጭካኔ ጥግ በተሞላበት አኳኋን ተረሽነዋል።
ሌሎች
2 ንጹሃን አማሮችም ክፋኛ ቆስለው አምልጠው በህክምና ላይ ይገኛሉ።
ይህ ዘር የማጥፋት ዘመቻ አሁን ላይ የተጀመረ ባይሆንም ይበልጥ ተባብሶ አድማሱን እያሰፋ በመቀጠል ላይ ነው።
#Stop Amhara Gennocide !!
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ
ጥቅምት 21/2018 ዓም
2🙏1💔1
ጀግኖቹ እስቴ ዴንሳ ብርጌድ የእስቴ ወረዳ ፖሊስ ፅ.ቤት አዛዥን ከባድ ቁስለኛ አድርገዉታል!!!

እስቴ መካነየሱስ ከተማ ቀበሌ 1 ታረቀኝ መታሰቢያ ሆቴል በተፈፀመ የቦንብ ጥቃት ባህሩ አዳነ የተባለ የወረደዉ ፖሊስ ፅ.ቤት አዛዥ ከባድ ጉዳት ሲያስተናግድ አንድ ሚሊሻ ደግሞ እስከ ወዲያኛዉ ተሸኝቷል።ቁጥሩ በዉል ያልታወቀ ደግሞ ቁስለኛ ተደርጓል።

ዝርዝር መረጃዉን እንመለስበታለን!!!
@ግሎባል ፋኖ ሚዲያ!!
🙏3
በሚዳና ሬማ ቀጠና 264 የሚኒሻ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እጃቸውን ለፋኖ መስጠታቸው ታወቀ!

በቀጠናው ከነበረው የሚኒሻ ኃይል መካከል ከ80% በላይ የሚሆነውን ማፈራረሱን ፋኖ አስውቋል።

ለፀረ አማራው ብልፅግና ኃይል ተላላኪ እና የአማራን ሕዝብ የከዳ የባንዳ ስብስብ የሆነው የበአዴን ቡድን በሸዋ ቀጠና በሚዳና ሬማ ወረዳ ያሰፈረው "የጭንቅ ቀን አሻጋሪየ" በሚል የሚጠራው የሚሊሻ ኃይል እየፈራረሰ እጁን ለፋኖ እየሰጠ መሆኑን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።

የተላላኪ ተላላኪ በመሆን በራሱ ሕዝብ ላይ ህልቆ መሳፍርት ግፍና መከራ እየፈፀመና እያስፈፅመ ካለው እራሱን "የሚኒሻ ኃይል" እያለ የሚጠራው የሆድ አደር ስብስብ፡ በመስተመጨረሻም የነሽመልስ አብዲሳ ቡድን <<አማራን ከአማራ ጋር የማጫረስ ሴራ>> ገብቶት ከነ ሙሉ ትጥቁ ከስምሪት ቀጠናው በመጥፋት ፋኖን እየተቀላቀለ ይገኛል።

ፀረ አማራውና የሆድ አደሮች እንዲሁም የባንዳዎች ስብስብ የሆነው የበአዴን ቡድን በሸዋ ቀጠና በሚዳና ሬማ ወረዳ አስፍሮት ከነበረው የሚኒሻ ኃይል መካከል በቁጥር 264 አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው በአፋሕድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ስር የሚገኘው አፄ ዳዊት ክ/ጦርን ስለመቀላቀላቸው የኮሩ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ክፍል ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ አስታውቋል።

በሚዳና ሬማ ወረዳዎች ስር ከሚገኙ ቀበሌዎች ማለትም፡ ከቄጠማ እና ሙህሬ ቀበሌ 32 የሚኒሻ አባላት፣ ከይጎቢያ ቀበሌ 79፣ ከአዝማ ቀበሌ 28፣ ከጠባቢት ቀበሌ ዘጠኝ(09)፣ ከመጅት ቀበሌ 35፣ ከአላቦ ቢራባ ቀበሌ 81፡ በድምሩ 264 የሚኒሻ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው አፄ ዳዊት ክ/ጦርን ተቀላቅለዋል ነው ያለው የኮሩ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ክፍል ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ።

እነዚህ የሚኒሻ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እጃቸውን ለፋኖ መስጠት የጀመሩት ካለፈው ሳምንት ጀምሮ መሆኑን ለጣቢያችን የገለፀው የኮሩ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ክፍል፡ በሁለቱም ወረዳዎች ከ80% በላይ የሚሆነውን የሚኒሻ ኃይል ሙሉ ለሙሉ ማፍረስ ችለናል ብሏል።
🙏2