ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.33K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.22K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
አሁን በደረሰን መረጃ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሆንቆሌ ዋቤ ወረዳ በቀቅሳ ቀበሌ ጥቅምት 18 ለ19 አጥቢያ 5 ምእመናን በታጣቂዎች መገደላቸውን ምእመናን ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን በስልክ አድርሰዋል።

መረጃ ሰጭዎቻችን አሁንም በከፍተኛ ስጋት ውስጥ መሆናቸውን ገልጸዋል።
@ሞአ ሚዲያ
💔1
ተቃውሞ ሰልፍ እና ሻማ ማብራት በስቶኮልም
💚💛❤️🇸🇪

በአማራ ህብዝ ላይ እየተፈጸሙ ያሉትን ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶች የጦር ወንጀሎች እና ንጹሀን ላይ እየተፈጸመ ያለውን የድሮን ጥቃት እናውግዝ ‼️

ቀን : November 1,2025

ሰአት : Klockan 15 till 17

Plats : Medborgarplatsen Torg

አዘጋጅ: ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ
💔2
የአደረጃጀት ዜና !!

በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ( አፋብኃ ) የቴዎድሮስ ዕዝ የ201ኛ ኮር የ74ኛ ክፍለጦር ምስረታ ተጠናቋል።

በአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ የመልሶ ማደራጀት እና የመዋቅር ማሻሻል ተግባራት መካከል አንዱ የሆነው የኮር አደረጃጀት እና የክፍለጦር መልሶ ማደራጀት ይገኝበታል ።

ክፍለጦሩ በአምስት ሻለቃ የተዋቀረ ሲሆን ለቀጣይ የህልውና ትግል ዝግጁ መሆናቸውን የክፍለጦሩ ፣ የሻለቃ አመራሮች እና አባላት አረጋግጠዋል ።

የክፍሐጦር መልሶ ማደራጀት ስራው በአርበኛ ማርሸት ፅሐው ፣ በአርበኛ ይትባረክ አንዳርጌ እና በመቶ አለቃ አበበ አስተባባሪነት እንዲሁም በ201ኛ ኮር ሰብሳቢ አርበኛ ላይችሉህ ገበየሁ እና በኮሩ አደረጃጀት ሀላፊ አርበኛ አንለይ እንየው ተባባሪ አስተባባሪነት ተጠናቋል ።

አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ !!
2
ሰበር ዜና!

የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝና አፋህድ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት እዝ ኃይሎች በጥምረት በጠላት ወንበር አስጠባቂ ሰራዊት ላይ ድል ተቀዳጁ!
      
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ ፭ ኮር ክ/ጦሮችና አፋህድ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት እዝ ክ/ጦሮች የጋራ ጠላትን በጋራ መደምሰስ የሚል እቅድን አንግበው የጠላት ኃይል ሰፍሮ በሚገኝባቸው በተለያዩ ከተማዎች ሰርጎ በመግባት አስደናቂ ጀብዶችን ሰርተዋል።
       
በትላንትናው እለት የዳግማዊ ቴዎድሮስ ፭ ኮር አካል የሆኑት ጎ/በጋሻው ክ/ጦርና ጥቁር አንበሳ ክጦር አሃዶች እንዲሁም አፋህድ ጎንደር ጠቅላይ እዝ በአርበኛ ታርቆ ከበደ የሚመራው አሃድ በጋራ በመሆን በምዕራብ በለሳ አበየና ድርቃ ልደታ በተባሉት አካባቢዎች የብልጽግናን ወንበር አስጠባቂ ኃይል ሲያበራዩት ውለዋል።
   
በውጊያው የሞቱበትን 3 መከላከያዎችና
3 ሚሊሻዎችን ድርቃ ልደታ ቤተ ክርስቲያን ላይ ቀብሮ የሄደ ሲሆን  ሌሎች ቁጥራቸው በርከት ያሉ የመከላከያና የሚሊሻ ቁስለኞችን ወደ አርባያ ከተማ ይዞ ፈርጥቶ አምልጧል። የአርባያ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞችም ቁስለኞችን ለማትረፍ ሽር ጉድ ሲሉ ተስተውለዋል።
   
ከዚሁ የአንድነት ዜና ሳንወጣ ዛሬ ጥቅምት 19ለ 20 2018 ዓ.ም አጥቢያ ከንጋቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ ጥቁር አንበሳ ክ/ጦር አሃዶችና አፋህድ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት እዝ አፄዎቹ ክ/ጦር ማክሰኝት ከተማ በ3 አቅጣጫ ዘልቆ በመግባት የጠላትን ኃይል መውጫ መግቢያ አሳጥተውት አርፍደዋል።
   
ለሰዓታት ያህል ከተማዋን  በቁጥጥር ስር አድርገዋት የቆዩ ሲሆን የከተማዋ ሚሊሻና የስርዓቱ አገልጋይ ካብኒዎች እግራቸው ወደአመራቸው መፈርጠጣቸውን የመረጃ ምንጫችን ገልጿል።
     
ቁጥራቸው በእውን ማወቅ የማይቻል የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛ መሆናቸውንም ለማወቅ ተችሏል።
  
ከዚሁ ዜና ጋር በተያያዘ የዳግማዊ ቴዎድሮስ ፭ ኮር አካሎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የጠላት ኃይል ሰፍሮ በሚገኝባቸው ከተሞች  አምባ ጊዮርጊስና አዲስ ዘመን ላይ ከትላንት ማታ ጀምሮ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ እልህ አስጨራሽ ውጊያ እያደረጉ ነው።
      
ማታ አመሻሽ ላይ ጎንደሬ በጋሻው ክ/ጦር  አምባ ጊዮርጊስ ከተማ ላይ በ3 አቅጣጫ በመግባት በአብይ ጡት ቆራጭ ሰራዊት ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወስዷል። 

በጥቃቱ
5 የመከላከያ አባላት ወዲያውኑ ሲሞቱ
8ቱ ደግሞ ክፋኛ በመቁሰላቸው የተነሳ በሪፈር ለከፍተኛ ህክምና ደባርቅ ከተማ ተልከዋል።
     
የጠላት ኃይል ቁሳዊ ፣ ሰባዊና ፖለቲካዊ ኪሳራን ያስተናገደበት ጥቃት እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
       
የጠላት ኃይል ማዘዣ ጣቢያ በሆነችው አዲስ ዘመን ከተማ ላይ ዳግማዊ ቴዎድሮስ ፭ ኮር  በ3 የውጊያ ግንባሮች እየተፋለሙ ይገኛል።
  
በስተ ምስራቅ  አቅጣጫ አፄ እያሱ ክ/ጦር በስተ ስሜን አቅጣጫ መብረቅ ክ/ጦር በ2 ግንባሮች በስተ ሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ ፋናየ ውቤ ክ/ጦር፣ ጥቁር አንበሳ ክ/ጦር ብርጌዶችና የጎንደሬ በጋሻው ክ/ጦር አካል የሆነው ነብዩ አሳምነው ብርጌድ  የአዲስ ዘመን ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን መሬቶች በመጠቀም  በጠላት ኃይል ላይ የበላይነትን ወስደዋል።
       
ከእብናት ድጋፍ ለመስጠት የሚመጣን የጠላት ኃይል አፄ እያሱ ክ/ጦር አግዶ ይዞ እንዳያልፍ ያደረገ ሲሆን አዲስ ዘመን ከተማ ላይ ሰፍሮ የሚገኘውን ግብስብስ ኃይል ያለምንም ስጋት ምሽጉ ድረስ ዘልቆ በመግባት እልህ አስጨራሽ የፊት ለፊት ውጊያ ማካሄድ  ተችሏል።
   
በውጊያው
ከ15 በላይ ሲሞት
   12 የሚሆኑት ደግሞ ቁስለኛ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን በከተማው ሆስፒታል በህክምና ላይ መሆናቸው ታውቋል
  
በአጠቃላይ ከሰሞኑ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ እየተደረጉ ያሉ ወታደራዊ ዘመቻዎች የጠላት ኃይል ከፍተኛ ቁሳዊ ፣ ሰባዊና ፖለቲካዊ ኪሳራዎችን ያስተናገደበት ግዳጅ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።

        ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን።
   አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
             ጥቅምት 20/2018 ዓ.ም
1
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ የክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች ላይ በተፈፀመ ጥቃት የተገደሉ 20 የሚደርሱ ንፁኋኖች አስከሬናቸው ከየወደቀበት እየተለቀመ ስርዓተ ቀብራቸው መፈፀሙ ተነገረ!
💔1
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ( አፋብኃ ) የቴዎድሮስ ዕዝ የ201ኛ ኮር የ74ኛ ክፍለጦር ምስረታ ተጠናቋል።

በአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ የመልሶ ማደራጀት እና የመዋቅር ማሻሻል ተግባራት መካከል አንዱ የሆነው የኮር አደረጃጀት እና የክፍለጦር መልሶ ማደራጀት ይገኝበታል ።

ክፍለጦሩ በአምስት ሻለቃ የተዋቀረ ሲሆን ለቀጣይ የህልውና ትግል ዝግጁ መሆናቸውን የክፍለጦሩ ፣ የሻለቃ አመራሮች እና አባላት አረጋግጠዋል ።

የክፍሐጦር መልሶ ማደራጀት ስራው በአርበኛ ማርሸት ፅሐው ፣ በአርበኛ ይትባረክ አንዳርጌ እና በመቶ አለቃ አበበ አስተባባሪነት እንዲሁም በ201ኛ ኮር ሰብሳቢ አርበኛ ላይችሉህ ገበየሁ እና በኮሩ አደረጃጀት ሀላፊ አርበኛ አንለይ እንየው ተባባሪ አስተባባሪነት ተጠናቋል ።
🙏1
"መሪጌታ በላይ አዳሙ ተደብድበዋል ፤
ቄስ በላይ መኮንን ከተከበሩ መሪጌታ በላይ አዳሙ የማይከበሩበት ምክንያቱ ምንድን ነው?"

(የተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው)

የተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ጥቅምት 18/2018 በነበረው ችሎት በቂሊንጦ ማ/ቤት እና በተለይም በተቋሙ ጥበቃ እና ደህንነት ኃላፊ በኢ/ር ድሪባ ሰንበታ ላይ ካቀረቡት ክስ መካከል በከፊል ፦
 
የወገብ እና የእግር በሽተኛ ነኝ ፤ ፍ/ቤቱ ፈቅዶልኝ በዋና በር እየገቡ ቤተሰቦቼን አገኝ ነበር ፤ ኢ/ር ድሪባ ሰንበታ ከመጡ በኋላ ነው የተከለከልኩት።

እኔ ብቻ ሳይሆን ማህበረሰቤ ጭምር ተሰድቦ እንኳ ችግሩን በሰላም ተነጋግረን እንድንፈታ ነበር ጥረትና ፍላጎቴ ይሁን እንጅ ሊታረሙ ስላልቻሉ ነው ክሱን ወደ ፍ/ቤት ለማምጣት የተገደድኩት።

በእስር ቆይታዬ በበደረሰብኝ እንግልት ቆሜ ማናገር አልችልም ፤ አሁንም ቁጭ ብዬ ቤተሰቦቼን እንዳነጋግር ይፈቀድልኝ።

"ቅዘናም አማራ " ብለው ተሳድበዋል ፤ ዳኝነት ካለ ይማሩ ብለን ነው ያመጣናቸው ፤ ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩን በምርመራ እንዲያጣራው ትዕዛዝ ይሰጥልን።

ከላይ እስከ ታች እኛው ነን ምንም አታመጡም ብለውናል።

መሪጌታ በላይ አዳሙ ተደብድበዋል ፤
ቄስ በላይ መኮንን ከተከበሩ መሪጌታ በላይ አዳሙ የማይከበሩበት ምክንያቱ ምንድን ነው?

በብሔራችን ተሰድበናል ፤ ተዋርደናል ፤ በእኛ ምክንያት ሕዝባችን ሊሰደብና ሊዋረድ አይገባም።

በፍተሻ ወቅት ባልታጠበ እጃቸው ነው እንጀራውን የሚነኩት ፤ ዞን 4 እና ዞን 5 ላይ የተለዬ ጫና እያደረጉብን ነው።

በእኛ ስም የተያዘ ሕገ ወጥ ነገር የለም ፤ አለ ካሉ ተጨማሪ ክስ አድርገው ያምጡ በማለት ተናግረዋል።

በመሀል ችሎቱ እንዳይናገሩ ሲከለክላቸው ፦

ተዉ ይህ ጊዜ ያልፋል ፤ እኔ ብሞት መልሱ ለትውልድ ነው፤ እኛ ያልነውን ብቻ ሰምታችሁ ፍረዱ አላልኩም ፤ ግን ከዚህ በላይ ምን እንሆናለን? ቅዘናም አማራ እየተባልን ነው።

በእርግጥ ይህ ችሎት ስዩም ተሾመን በጓዳ አነጋግሮ የመለሰ ነው ፤ በደል እየተፈፀመብን ነው ፤ አድሎ አለ።

ካጠፋሁ ይቅርታ የሚያናግረኝ ግን ግፉ ነው ፤ በእኔ ብቻ ሳይሆን በአማራ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ እና በደል ፣ ስቃዩ ነው የሚያናግረኝ።

(አውሎግሶን አንድነት ፣ ጥቅምት 19/2018)
💔1