ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.33K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.22K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
የምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ ራያ ቆቦ ተኩለሽ ግንባር ልዩ ስሙ አካምባ የተባለ ቦታ ላይ በፈፀሙት የደፈጣ ትቃት ከ50 በላይ የአገዛዙ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሆነ::

አፋብኃ ምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ ለወረራ የመጣውን የፋሽስቱ ብልፅግና ሰራዊት ሰሞኑን በበርካታ ግንባሮች በሚደረጉ ተጋድሎዎች ከባድ ምት በማሳረፍ እያፈረሱት ይገኛሉ::

ከዚህ ጋር ተያይዞም ዛሬ ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ረፋድ ራያ ቆቦ ተኩለሽ ግንባር በተሽከርካሪ ይንቀሳቀስ የነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ላይ ልዩ ስሙ አካምባ የተባለ ቦታ ላይ የደፍጣ ጥቃት በመፈፀም አንድ ኦራል ሰራዊት ሲሸሽ በመገልበጥ እና በጥቃቱ አጠቃላይ ከ50 በላይ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ጀብድ ፈፅመው ድል ተጎናፅፈዋል::

ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም በነበረ ተጋድሎ አካምባ ላይ በተመሳሳይ አንድ በዲሽቃ የሚታጀብ ከፍተኛ አመራር ከሰባት አጃቢዎቹ ጋር ከነ ተሽከርካሪው በአሳምነው ክፍለጦር መካናይዝድ ሙሉ ለሙሉ መደምሰሱ የሚታወቅ ነው::

በሌላኛው ተጋድሎ በተመሳሳይ ዕለት ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም ጮቢ ግንባር ከፍተኛ የመከላከያ አመራርና የሬድዮ ኦፕሬተሮች በሐውጃኖ ክፍለጦር መካናይዝድ በሞርተር ጥቃት ሙሉለሙሉ ተደምስሰዋል::

ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም በተመሳሳይ ተኩለሽ ግንባር የዞብል አምባ ክፍለጦር መካናይዝድ ምሽግ የያዘ በርካታ የጠላት ሰራዊት ላይ ከባድ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ በማድረስ ታላቅ ጀብድ ፈፅመዋል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ጥቅምት 12/2018 አ.ም
🙏5
ቀጥታ ስርጭት | የአብይ አህመድ የጦርነት ጉሰማና የአማራ ፋኖ የህልውና ትግል ግስጋሴ
ሰበር ዜና - ሰራዊቱ እየተናደ አለቀ | ከ 100 ሚንሻና አድማብተና ፋኖን ተቀላቀለ | ኮማንዶ ኃይሉ ኮበለለ - ጎጃም - ጎንደር - ድል ተበሰረ
🙏1
ከዓለም አቀፍ የአማራ ግብረኃይል የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ

የአረመኔው የአብይ አህመድ ፋሽስት ሰራዊት በወጣት አርበኛ ሴቶቻችን ላይ የፈጸመውን የጭካኔ ጥግ መላው ዓለም ሊያውቀውና ሊያወግዘው ይገባል!!! ፋኒት በዓለም ዋሴ ፋኒት ትግስት ወዳጅ ይመር ፋኒት መቅደስ ተስፋዬ
የፋኖ አርበኞች የብልፅግና ሥልጣን አስጠባቂ ሰራዊትን ቁስለኛና ምርኮኛን በቅድሚያ የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ አድርገው በምህረት ወደ የቤተሰቦቻቸው እንዲሄዱ አድርገዋል፡ እያደረጉም ነው። ምርኮኞች ቁጥራቸው በርከት ሲሉም ለዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ያስረክባሉ። የታወቀውን የዓለም አቀፍ ምርኮኛ አያያዝን ህግ ያከብራሉ። ይህ በፋኖ ዘንድ የተለመደ አሰራር ነው።

የ19 ዓመትዋ ወጣት በዓለም ዋሴ እንደማንኛውም ወጣት የራሷን ኑሮ አመቻችታ ተመሳስላ አስመስላ መኖር ትችል ነበር፤ ሆኖም ግን በአማራው ሕዝብ ላይ የሚደርሰው ሰቃይና መከራ፣ ሰደትና መፈናቀል፣ መገደልና መጨፍጨፍ አንገብግቧት ይህን አረመኔ የአብይ አህመድ ፋሽስት አገዛዝን ለመፋለምና ነጻነቷን ለማስከበር ቆርጣ ወስና የህልውና
ትግል ከሚያደርገው ፋኖ ጋር በአርበኝነት ተቀላቀለች። በፋኖም ውስጥ የመደበኛና የኮማንዶ ስልጠናዎችን ጨርሳ የአፋብኃ ቴዎድሮስ እዝ 5ኛ ክፍለ ጦር አባል ሆና ከሌሎች ጓዶቿ ጋር ለቅኝት ሰራ ተሰማርታ እያለ ድንገት በአረመኔው የአብይ አገዛዝ ወታደሮች ቀለበት ውስጥ ወደቀች። ጥቂት አርበኞች ሆነው የሚችሉትን ያህል ቢዋጉም የአብይ አህመድ ወታደሮች በርካታ ነበሩና ጥቅምት 2 ቀን 2018 ዓ/ም በጥይት ቆስላ ተማረከች።
የአረመኔው አብይ አህመድ አገዛዝ ወታደሮች ግን በጥላቻና በሰለጠኑበት የሃሰት ትርክት ስለሚመሩ ይህችን የ19 ዓመት ወጣት ፋኒት በዓለም ዋሴ ቆስላ ስትማረክ የፈጸሙባት ተግባር ግን ተሰምቶና ታይቶ የማያውቅ አስቃቂ የጭካኔ ጥግ ነው። ቁስለኛዋን ምርኮኛ ልብሷን አወላልቀው “አማራ” የሚለውን እጇ ላይ የተነቀሰችውን ንቅሳት በጩቤ ገፈው፤ ሁለቱንም ጡቶቿን በሳንጃ ቆራርጠው፣ መላ ሰውነቷን በሳንጃ ስለት ወጋግተው በኢሰብዓዊነትና እጅግ በሚዘገንን ሁኔታ አስከሬኗን ማንኩሳ ከተማ መሀል አስፋልት ላይ ጥለው የአረመኔነታቸውን ጥግ ለሕዝብ አሳይተዋል። ይህ ነው የአብይ አህመድ ሰራዊት መለያ!

ከዚያ በፊት መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ/ም በወገራ የበላይ ዘለቀ እዝ 3ኛ ኮር አምባራስ ክፍለ ጦር አባል የሆነችው አርበኛ ፋኒት መቅደስ ተስፋዬን በመግደል ሬሳዋን በመኪና በመጎተት አስፋልት ላይ ጥለው እንዳትቀበርም አስከሬኗን በጸሀይና በዝናብ እንዲበላሽ በማድረግ ዘግናኝ ድርጊት በመፈጸም የአብይ ሰራዊት የተካነበትን የኢሰብዓዊ ባሕሪውን ለሕዝብ አሳይቷል።

ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ደግሞ በራያ በጮቢ በር ግንባር ተጋድሎ እያደረገች የተሰዋችው የምሥራቅ አማራ ኮር አንድ
ሀውጃኖ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃ አባል የሆነችው አርበኛ ፋኒት ትግሥት ወዳጅ ይመር ከአስከሬኗ ላይ አንደኛውን ጡቷን ቆርጦ እርቃኗን ሜዳ ላይ ጥሎ ሰቅጣጭና አረመኔያው ድርጊት የፈጸመው በጥላቻ የተሞላው የአብይ አህመድ ሰራዊት ነው።

አማራ ሆኖ በአማራው ላይ ይህንን የመሰለ የጭካኔ ተግባር ተፈጽሞ እያየንና እየሰማን ልባችንን አደንድነን መቀመጥ አለብን ወይ? ብለን መጠየቅና የህልውና ትግሉን በውስጥም በውጭም ያለን ሁሉ መርዳት ካልቻልን በእያንዳንዳችን ቤተሰብ ላይ ተመሳሳይ ድርጊት ሊፈጸም እንደሚችል መገንዘብና ሁላችንም በጭንቀትና በተሰፋ መቁረጥ ከምንቀመጥ በምንችለው አቅምና መንገድ በተግባር የህልውና ትግሉን መደገፍና መርዳት ይኖርብናል። ይህን አስከፊ የጭካኔ ወንጀልንም መላው ዓለም እንዲያወቀውና እንዲያወግዘው ለተለያዩ የዜና አውታሮች ማድረስ፣ ለዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብት ድርጅቶች፣ ለመንግስታት፣ ለኮንግረስና ለፓርላማ አባላት በዘመቻ መልክ ማሳወቅ ይኖርብናል።

በወጣት የሴት አርበኞቻችን ፋኒት በዓለም ዋሴ፣ ፋኒት መቅደስ ተስፋዬና ፋኒት ትእግሥት ወዳጅ ይመር ላይ የደረሰው አስቃቂ አረመኔያዊ ተግባር የፈጸሙት ወንጀለኞችም በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ሰራ መሰራት ይኖርበታል።

በጀግንነት የተሰዉትን የነፋኒት በዓለም ዋሴንና ጓዶቿ ምስልና ታሪክ በሁላችንም ልብ ተቀርጾ እንዲቀመጥ በየአገሩ ያለን ሁሉ የተለያዩ የፈጠራ ሰራዎች በመስራት ለምሳሌ ምስሎቻቸው ያለበትን ቲሸርት በመልበስ፣ የሻማ ምሽቶች በማዘጋጀት በስማቸው ዝግጅት በማዘጋጀትና የመሳሰሉትን ቢያንስ ማከናወን ይኖርብናል።

የዚህ ፋሽስት ሰራዊት መሪ የሆነው የአብይ አህመድ አገዛዝን ዘመን እንዲያበቃ የማያቆም ዘመቻ መካሄድ ይኖርበታል።

በአገርም ሆነ በውጭው ዓለም የሕዝብን ትኩረት ወደ ሌላ አቅጣጫ በማስቀየር የዘረኛውና አረመኔው አብይ አህመድ
አገዛዝን እድሜ ለማስቀጠል ፕሮፓጋንዳ በመስራት የሚዳክሩ የሚዲያ ክፍሎች፣ የኢንቨስትመንት ደላላዎች፣ አገር ለአረብ እየተሸጠች “አዲስ አበባ አሽበረቀች አማረች” እያሉ ከንቱ ስብከታቸውን የሚያሰሙና በውስጥም በውጭም ሕዝብን ማዘናጊያ በርካታ የመዝናኛ እና የተለያዩ ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት ሀገር ሰላም የሆነች ይመስል ሕዝብን ዳንኪራ የሚያስረግጡና ገንዘቡን በአልባሌና ጭፈራ እንዲያባክን ሰራ የሚሰሩ ግለሰቦችም ሆኑ ተላላኪዎች እንዲሁም ማንኛውም ሰው ከዚህ የሆዳምና የባንዳ ሰራቸው እንዲታቀቡ እንመክራለን። ሀብት ለመሰብሰብ በመሯሯጥና የጨለማና የሀዘን
ዘመንን በጭፈራና በደስታ ለማሳለፍ የሚዳክሩትን ሁሉ እግዚአበሔር ልቦና ይስጣችሁ፣ ነገ ይህች አገር ሰትጠፋ
ተመልሳችሁ አገር አልባና ጨለማ ውስጥ የምትወድቁ መሆናችሁን እንድታወቁት፤ በታሪክም በሕዝብም ተወቃሽና ተጠያቂ መሆናችሁንም አትዘንጉ እንላለን!

የነፋኒት በዓለም ዋሴ ጀግንነት አርዓያ ሊሆነን፣ የተፈጸመባቸው አስቃቂ ድርጊትና እንዲዘገንነን እንዲቆጠቁጠን ነግ ተነግወዲያ በሌሎችም ጀግና እህቶችና ወንድሞቻችን ላይም እንዳይደገም ማድረግ የሁላችንም የህሊና ግዴታ ነውና በየከተማው በተለያዩ ምክንያቶች ተዳክመን፣ ፈዘንና ደንዝዘን በተለያዩ ምክንያቶች ተስፋ ቆርጠን የቆየን ሁሉ፤ የባሰ
እየመጣ ነውና ወጣት አርበኞቻችንን ወገኖቻችንን ተጋድሎ ስቃይና ግፍን በማስታወስ እንደገና እንነሳ! እንበረታታ!

እግዚአብሄር ለተሰዉት አርበኞቻችን ቤተሰቦችና ጓዶች መጽናናቱን ይስጥልን። ፈጣሪ ነፍሳቸውን በገነት ያኑርልን።
እግዚአብሔር የአማራውን የህልውና ትግል ይባርክ!

ድል ለአማራ የህልውና ትግል!
የአማራው ህልውና የኢትዮጵያም ህልውና ነው!!!

የአረመኔው አብይ አህመድ አገዛዝ ያብቃ! ወንጀለኞችም ለፍርድ ይቅረቡ!!!

@ዓለም አቀፍ የአምራ ግብረኃይል (ዓ/አ/አ/ግ/ኃ)
2🙏1
የምኒልክ ዕዝ ተወርዋሪ በላጎ ሻለቃ ከአራት ወረዳ የተውጣጣ አድማ ብተናና ሚሊሻ እንዲሁም ከብልፅግና መከላከያ ጋር ተጋድሎ በማድረግ ድል አስመዘገቡ::

ከደሴ ከተማ ከደሴ ዙሪያ ወረዳ ከኩታበርና ተንታ አጅባር ወረዳዎች የተውጣጣ አድማ ብተናና ሚሊሻ ከብልፅግና ከመከላከያ ጋር በመጣመር በመደራጀት ላይ ያለው በላጎ ሻለቃ ነፃ ያወጣቸውን የደሴ ዙሪያ ወረዳ ቀጠናዎች ማለትም ፅዲ ገበያ፣ አያታ፣ በፋላ እና በሙሚ አካባቢዎች የፋኖን ይዞታ ለማስለቀቅ ማጥቃት ቢያደርግም ባግባቡ በመመከትና መልሶ ማጥቃት በማድረግ ሙትና ቁስለኛውን አሸክመው ወደመጣበት በመመለስ ታላቅ ድል አስመዝግበዋል::

ተጋድሎው ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ እስከ ምሽት 1:00 የተደረገ ሲሆን የበላጎ ባለታሪኮቹ የመጣውን ጠላት ባግባቡ በማስተናገድ በርካታ የጠላት ሃይል ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ቀጠናቸውን አስከብረው ድል ተጎናፅፈዋል ሲል የምኒልክ ዕዝ ምክትል ህዝብ ግንኙነት አርበኛ ኑረዲን አበበ ገልፀጿል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ጥቅምት 13/2018 አ.ም
የአፍብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒሊክ ዕዝ

የደጋው መብረቅ ክ/ጦር ከፋሽስቱ አብይ አህመድ ወታደር ጋር በተደረገ ወጊያ የፍሽስቱን ወታደር ወደ መግደያ ወረዳ ስቦ በማስገባት በርካታ ሃይሉን በመምታት ታላቅ ጀብድ ፈፅሞ ድል ተጎናፀፈ::

ትናትና ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ ያላሰበው ድብደባ የደረሰብት የብርሀኑ ጁላ ሰራዊትም ሙትና ቁስለኛውን ጭኖ ሲፈረጥጥ የነበረበትን ፓትሮልም በክንደ ብርቱዎቹ አነጣጥሮ ተኳሾች ተመቶ ወድሟል። ምንም እንኳን የሚሰራውና የሚያደርገው ቢያጣ ይህ ዘረ ጨፍጫፊ ሰራዊት እግሬ አውጭኝ ብሎ ሲፈረጥጥ ከፊቱ ያገኘውን የጋማ ከብቶችን ሳይቀር እየገደለ ነበር።

ከዚህ ጋር ተያይዞም እንስሶችን በጥይት በመደብደብ አፀያፊ ተግባር የፈፀመ ሲሆን በርካታ እንስሶችን ገድሏል።ይህ አፀያፊ ተግባሩ አልበቃው ያለው ሽመልስ አብደሳ ከፍቶ የለቀቀው አማራ ጠል ሰራዊት በጋዞ ወረዳ ሸራገነት ጤና ጣቢያ በመግባት የህሙማን መገልገያ የሆኑ ቁሳቁሶችን፣
መድሃኒት፣ ስትሬቸር፣ ዊልቸር እና ሞተር ዘርፎ የአካባቢውን ማህበረሰብ የህክምና ተቋም አውድሟል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ጥቅምት 13/2018 አ.ም
1😁1
ሰሞኑን የውቤ ልጆች ከፍተኛ ድል በተቀዳጁበት በእስቴ ቀጠና ከተማረከው የጦር መሣሪያ መካከል ጥቂቱ።

በአፋብኃ አርበኛ በላይ ዘለቀ ዕዝ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር ስር የሚገኙት የጉና ክፍለጦር አናብስቱ ጥቅምት 09/2018 ዓ/ም ከንጋት ጀምሮ በእስቴ መካነየሱስ ቀጠና በነበሩ የጡት ቆራጩ ብልፅግና ቡድን ተላላኪ ወታደሮች ላይ ከባድ እርምጃ በመውሰድ ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሳቸውን መረብ ሚዲያ መዘገቡ አይዘነጋም።

ይህ የምታዩት ምስል በጉና ክ/ጦር እስቴ ዴንሣ ብርጌድ ስር በምትገኝ በአንዲት ሻለቃ የተማረከ ሁለት ብሬንና አስራ አምስት ክላሽ ነው። ቀሪዎቹ በክ/ጦሩ ስር የሚገኙ ሻለቃዎች የማረኩትን የመሣሪያ አይነትና ብዛት ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
🙏32👎2
Operation Aba Nadew: A Triumph For Humanity!
Fano Abebe Fentaw,
Head Of Public Relations, AFNF Menelik Command