ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.32K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.23K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
የጎንደሬ በጋሻው ከፍለ ጦር ምክትል ሻለቃውን ጨምሮ ጠላትን ደመሰሰ ።

የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል (አፋብኃ ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ዳግማዊ ቴውድሮስ /አምስተኛ/ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር አካል የሆችው ቃኘው ብርጌድ ዛሬ መስከረም 18 /2018 ዓ/ም ከጠዳ ከተማ በመውጣት በዙሪያው ያሉ አርሶአደሮችን ቤት ለቤት በመቀስቀስ ሁላችሁም ፋኖ ናችሁ ፋኖ ልጅም አላችሁ ምረሽ መግባትና ማስገባት አለባችሁ እያለ ሲደሰኩር ቆንጆዎቹ ምክትል ሻለቃውን ጨምሮ አምስቱን ወደ ላይኛው ላይመለሱ በመቀንደሽ ሸኝቷቸዋል።

ህብረተሰቡን ለማወናበድ የመጣው የብርሃኑ ጁላ ወንበዴ ሙትና ቁስለኛውን ይዞ በወጣበት እግሩ እየፈረጠጠ ወደ መገጭ ግድብ ተመልሶ ገብቷል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
መስከረም 18/2018 ዓ.ም
ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው)

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ ዕዝ ልጅ እያሱ ኮር ነፃ ባጣቸው የሰሜን እና የደቡብ ወሎ ዞን እና ወረዳ ከተሞች ላይ ሰፊ ህዝባዊ ውይይቶች በማድረግ የከረፋውን የብአዴን መዋቀር እየናደ የራሱን መዋቀር እየዘረጋ ይገኛል፡፡

ዛሬ በቀን 18/01/2016 ዓም በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ ውጫሌ ከተማ ከነዋሪው ጋር ህዝባዊ ውይይት በማድረግ ማህበረሰባዊ የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

በውይይቱ የተነሱ ኮር ሃሳቦች

1 የትግሉ መነሻ ምክኒያቶች ምን ነበሩ?
* ትግሉ አሁን ያለበት ጠቅላላ ሁኔታ
* ትግሉ ያመጣው መልካም አጋጣሚ
* የትግሉ ተግዳሮቶች
* የትግሉ የቀጣይ አቅጣጫ

2 መንግሥት አሁን ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ
* በወታደራዊ ቁመና
* በፖለቲካ ተቀባይነት
* የዲፕሎማሲ አቅም እና ሌሎችም

3 በራስ አስተዳደር እና በፀጥታ ጉዳይ
* የሃገር ሽማግሌዎች የሰላም ኮሚቴዎች የቅሬ እና የእድር እንዲሁም የእምነት አባቶች ማና
* የህዝብ እና የኛ ግኑኝነት ምን መሆን አለበት
* ከጠላት ጋር በጥቅምም ሆነ በፆታዊ ግኑኝነት እያደረጉ ባሉ ሰዎች ጉዳይ

4 ይህን ትግል እንዴት የራሳችሁ እንደሆነ አምናችሁ ኮትኩታችሁ ታሳድጉታለችሁ?

በሚሉ አንኳር ጉዳዮች ተነስተው ሰፊ ውይይት በማድረግ ህዝብ ላይ የነበረን የተዛባ አረዳድ እና ስሁት እሳቤ ለማጥራት ተመኩሯል፡፡

በውይይቱም ህዝቡ ደስተኛ እንደነበር እና እስከዛሬም ዘግይታችሃል በማለት ቁጭቱን በአደባባይ ገልፆል፡፡

በቀጣይም ሰፊ ውይይቶች እንዲደረግ እየጠየቁ ቀጠናውን እናንተ በመያዛችሁ ሰላም አግኝተናል ከመሳቀቅ ድነናል ሲሉ መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡


የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ ዕዝ ልጅ እያሱ ኮር ምክትል ሰብሳቢ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ
መስከረም 18/2018 ዓ.ም
3👍2
በጉራጊ ህዝባዊ አመፅ ተቀስቅሷል!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምሥራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ዛሬ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ ወጣቶች ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር ባደረጉት ግጭት ሰዎች ሳይቆስሉና ሳይሞቱ እንዳልቀረ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ ፡፡
ወጣቶቹ ዛሬ ከፖሊስ ጋር የተጋጩት “ የሲናኖ ሴራ “ የተባለው ባህላዊ የሽምግልና ሥረዓት የባለቤትነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በተከሠተ አለመግባባት ነው ተብሏል ፡፡
ወጣቶቹ የከተማዋን ጎዳናዎች በድንጋይ እና በጎማ ዘግተው መዋላቸውን የአይን እማኖች ተናግረዋል ፡፡ በከተማው እስከ ቀኑ ሰባት ሰዓት ድረስ የተኩስ እሩምታ ይሰማ እንደነበር የጠቀሱት ነዋሪዎቹ የአምቡላንሶች ምልልስም በርቀት ተሰምቷል ብለዋል ፡፡
በከተማው መረጋጋት ባለመስፈኑ ምን ያህል ሰዎች እንደተጎዱ ለማወቅ አስቸጋሪ መሆኑንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል ፡፡
“ ሲናኖ ሴራ “ የተባለው ባህላዊ የሽምግልና ሥረዓት በመስቃን እና በዶቢ የቤተ ጉራጌ ማህበረሰቦች መካከል የባለቤትነት ይገባኛል ጥያቄ ሲነሳ መቆየቱ ይታወቃል ፡፡
4
ለሶስተኛ ጊዜ በስርዓቱ የወደሙ ማህበራዊ ተቋማት!!

የእስቴ ወረዳ እና የመካነየሱስ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ሁሉንም ማህበራዊ ተቋማት አወለደመዋል።

ከዚህ በፊት የእስቴ ወረዳ አስተዳደር ሁሉም ቢሮዎች፣የመካነየሱስ ከተማ አስተዳደር ሁሉም ቢሮዎች እና የእስቴ ወረዳ ግብርና ቢሮ ሁሉም ሁሉም ቢሮዎች፣ዛሬ አዳሩን ደግሞ የህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሹ በአገዛዙ ካድሬዎች እንዲወድም ተደርጓል።

ጉድ በል ጎንደር!!
1
ሰሞኑን ሕዝቡ "ሰሜን ምስራቅ ዕዝ ከነሙሉ ሰራዊቱና የጦር መሣሪያው ምኒልክ ዕዝን ተቀላቅሎ ነው?..ወይስ?" ብሎ ግራ እስኪጋባ ድረስ፡ የወገንን ኃይል በድል ቁንጣን ያጨናነቀ በምትኩ ደግሞ የጠላት ኃይልን ወሽመጥ ብጥስ ያደረገው ዘመቻ...በክቡር ሰማዕቱ አርበኛ ሳጅን አደም አሊ/አባ ናደው/ ስም የተሰየመ ነው።

እጅግ በጣም ሀቀኛና ጀግና፣ ታማኝና አማኝ፣ ፅኑና ከአላማው ዝንፍ የማይል፣ሩህሩህና ቸር፣ ፍትህ አዋቂና አስተዋይ መሪ እንዲሁም አልሞ ተኳሽ ነው ይሉታል አብረውት ከምሽግ ውሎው የሚያድሩ ጓዶቹ።

ሳጅን አደም "አባ ናደው" የሚለውን ስያም ያገኘው የጎላሌውን ምሽግ በሰበሩበት ወቅት ነበር።

መረብ ሚዲያ ከዓመት በፊት ስለ ጎላሌው ምሽግ መሰበር ዘግቦት የነበረውን መለስ ብለን እናስታውሳችሁ....

ወቅቱ ወርሃ መጋቢት 2016 ዓ/ም ነበር። በደቡብ ወሎ ዞን ወግዲ ወረዳ ጎረንጅ ቀጠና ልዩ ስሙ ጎላሌ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ።

ከወግዲ ወረዳ ወደ ጎረንጅ ያቀናው የአገዛዙ ጥምር ጦር፣ በጎረንጅ ቀጠና እልህ አስጨራሽ ውጊያ ሲያካሂድ አርፍዶ ከሰዓት ከባድ ዶፍ ያዘለ ዝናብ መዝነብ በመጀመሩ ውጊያው ጋብ አለ።

ዝናቡ አላቆመም ዶፍና ውሽንፍር የቀላቀለ ዝናብ እየዘነበ ነው።

ጊዜው እየመሸ ነበር። ጀንበር ልግባ ልግባ እያለች በምትጣደፍበት በዚህ ቅጽበት አባ ናደው እስኪ በጎቼን ላሙቅ ብሎ ቦምብ በሽርጡ ቋጥሮ ከተቀመጠበት ብድግ አለ።

ጓዶቹ ዝናቡ በረድ እስከሚል መታገስ እንዳለባቸው ደጋግመው ቢነግሩትም አሻፈፈኝ አለ። "ሰዓቷ የወንድ ልጅ ሰዓት ናት" ነበር አጅሬ ምላሹ።

"አትከተሉኝ።ታሪክ ሰርቼ አስደምማችኋለሁ" ብሎ እግሮቹ በቅርብ ርቀት ወደ ሚገኘው የጠላት ምሽግ መራመድ ጀመሩ።ማምረሩን ያወቁ የተወሰኑ ጓዷቹ በቅርብ ርቀት ተከተሉት።

ሳጅን አደም ያን ከባድ ዶፍና ውሽንፍር ዝናብ መሀል ለመሀል ሰንጥቆ የጠላት ምሽግ ላይ ሲደርስ በሽርጡ ታቅፎ ይዞት የነበረውን ቦምብ በግራ እጁ እያነሳ፡ ቀለበቱን በጥርሱ እየነቀለ አከታትሎ ይወረውር ጀመር።

ቀን ላይ ሲዘንብ የዋለው ዝናብ ለብርድ የሰጣቸው የጥምር ጦር አባላት ሙቀት በሙቀት ሆኑ። ምሽጉ በዋይታ ተዋጠ። የድረሱልኝ ተማፅኖ የሚያቀርቡና የጣር ድምፅ  የሚያሰሙ የመከላከያና የአድማ ብተና እንዲሁም ሚሊሻ አባላት ስፍር ቁጥር አልነበራቸውም። ገሚሱ ጥሩ ባለሙያ እንደሰራችው ፍርፍር አካሉ ተቆራርሷል።ገሚሱ ደግሞ "ወይኔ እግሬ፡ ወይኔ እግሬ" ይላል። ገሚሱ ደግሞ "ማሎ፡ ማሎ፡ ሀደኮ፡ ሀደኮ" ይላል። ገሚሱ በዛ ዝናብ መሀል "ውሃ ስጡኝ? ውሃ ስጡኝ?" ይላል።

አባ ናደው በሽርጡ ታቅፎ የያዘውን ቦምብ መወርወሩን አላቆመም። እየመረጠ ቦምቡ ወዳልነካው የምሽጉ ስፍራ ይወረውራል።

ከሰማዩ ጉርምርምታ ጋር ተዳምሮ በቦምቡ ፍንዳታ ምድር ቃጤ ሆነች። ያሁሉ የወታደሩ ዋይታና የጣር ድምፅ ከግማሽ ሰዓት በኋላ ፀጥ እረጭ አለ።ሰማዩም ከነ ሳጅን አደም አሊ ጋር ምክር እንዳለው ሁሉ መስኮቱን ጥርቅም አድርጎ ዘጋ። ያ አስፈሪው የጎለሌ ምሽግ፣ መከላከያ ሰራዊቱ ለወራት ያህል በግሬደር ታግዞ የሰራው የጎላሌው የኮንክሪት ምሽግ በነሳጅን አደም አሊና በጓዶቹ ክንድ ተደረመሰ።

በእለቱ በስፍራው የነበሩ ሰዎች በምሽጉ ውስጥ የሬሳ ክምር የሬሳ ነዶ ነው ያየነው ሲሉ የአይን ምስክርነታቸውን ሰተዋል።

ከዚህን ዕለት ጀምሮ ሳጅን አደም አሊ አባ ናደው ተባለ።የለጋምቦው አንበሳ እና የገነቴ ጌጥ የሆነው አባ ናደው እጅግ በጣም ደፋር በዛው ልክ ደግሞ እሩህሩህ ነው ይሉታል የትግል አጋሮቹ። የጎላሌን ምሽግ ደርምሶ ታሪክ የሰራው አባ ናደው በጀግንነት እና በወታደራዊ ጥበቡ የተመሰከረለት ነው።

ይህ ጀግና ከወራት በፊት ስለ አማራ ሕዝብ ሲል የክብር መስዋዕትነትን ተቀብሏል።
(የአርበኛውን ሙሉ የትግልታሪክ መረብ ሚዲያ ከወራት በፊት ለአድማጭ ተመልካቾቹ ማድረሱ ይታወሳል።)

ምኒልካውያኑ ዛሬ በዚህ ለምድር ለሰማይ በከበደ አርበኛ ስም ዘመቻ አውጀው የአማራ ሕዝብ ለምዕተዓመታት የሚፎክርበትንና የሚመካበትን ድል አስመዝግበዋል።

በቁሙ ትግል የሚሰምርለት፣ ሞቶሞ በስሙ ድል የሚታፈስበት እንቁ አርበኛ..ሳጅን አደም አሊ( አባ ናደው )

ክብርና ዘላለማዊ ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!
@መረብ ሚዲያ
1🙏1
🔸የአማራ ፊኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)

ሰሜን ብርቅዬ ክ/ጦር ጠላትን ደመሰሰች!!
መስከረም 17 የሚከበረውን የመስቀል በዓል እንደ ማዘናጊያ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የተንቀሳቀሰው የጠላት ሰራዊት 55 ሙት፣25 ቁስለኛ ሲሆን 35 የነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያ ምርኮ በማንሳት አኩሪ ተጋድሎ ውጤት አስመዝግበዋል።

በሰ/ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በስቂያ በተል ልዩ ስሙ "ዋሊያ አንገት " የተባለ ቦታ በተደረገ ብርቱ ወታደራዊ ፍልሚያ የአረመኔው ዓብይ ወራሪ ሰራዊት በቆፈረው የቀበሮ ጉድጓድ ተቀብሮበታል።

ድሉን ያስመዘገበው አፋብኃ የራስ አሞራው ፫ኛ ኮር ሰሜን ብርቅዬ ክፍለ ጦር ነው።ክፍለ ጦሩ በቀጠናው በመንቀሳቀስ ተደጋጋሚ ድል እያስመዘገበም ይገኛል።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!

አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ
መስከረም 19/2018 ዓ.ም
ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ
2👍1
ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው)

ንጉስ ሚካኤል ኮር አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር ሸህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ከማሻ እስከ ደብረዘይት ድረሳ ባለው ቀጠና ከባድ ትንቅንቅና ተጋድሎ በማድረግ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::

6ኛ ቀኑን በያዘው ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) ተጋድሎዎችን እያደረገ ያለው አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር ታቦር ተራራ ብርጌድ በንዑስ ወረዳው ካደራጀው ከ500 በላይ አባት አርበኛ ጋር በመጣመር መስከረም 18/2018 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ ከማሻ እስከ ደብረዘይት ባለ ቀጠና ያገኘውን ፀረ አማራ ሰራዊት ሲጠርጉት ውለዋል::

በተጋድሎው የወረዳው ምክትል የፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ ሰይድ አሊን ጨምሮ ከ15 በላይ ጠላት ሲደመሰስ ከ25 በላይ ቁስለኛ ሆኗል:: በዚህ ውጊያ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ከጊንባ ከአጅባርና ከማሻ ተሰባስቦ የመጣ አድማ ብተናና ሚሊሻ ነው ጉዳቱን ያስተናገደው:: በግል ትጥቁና ተተኳሹ ተጋድሎ እያደረገ ያለው አባት አርበኛ ጦር ታላቅ ጀብዱ እየፈፀመ ይገኛል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
መስከረም 19/2018 ዓ.ም
🙏1
ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው)

ንጉስ ሚካኤል ኮር አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር ታቦር ተራራ ብርጌድ እዋ ቀጠና ተጋድሎ በማድረግ ድል አስመዘገቡ::

አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር ታቦር ተራራ ብርጌድ መስከረም 18/2018 ዓ.ም እዋ ቀጠና ላይ እዋ ትምህርት ቤት መሽጎ የነበረን ጠላት በከበባ አስገብቶ በማፈን በርካታውን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል አስመዝግበዋል::

በተጋድሎው ታቦሮች በርካታ ጠላት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ጠላት ላይ ሰብዓዊ ኪሳራ ከማድረስ ባሻገር ስድስት ክላሽ ማርከዋል:: በተጨማሪም ከጠላት ጋር በማበርና በመወገን ህዝባቸው ላይ የሚፈፀመውን ዘር ማጥፋት መረጃ በመስጠትና በዘረፋ እንዲሁም በሌሎች እኩይ ተግባሮች እየተሳተፉ ያሉ ግለሰቦች መታቀብ ባለመቻላቸው የማያዳግም አስተማሪ እርምጃ የሚወስዱ መሆኑን ብርጌዱ አሳውቋል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
መስከረም 19/2018 ዓ.ም
🙏21
ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው)

ለአማራ ወጣቶችና የአማራን የህልውና ትግል የምትደግፉ ኢትዮጵያውያን በሙሉ:-

ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደተሞከረው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ በተቆጣጠራቸው ቀጠናዎች አዲስ ምልምል የፋኖ ሰራዊት ማሰልጠን ይፈልጋል:-

በዚህ መሠረት ነፃ በወጡ ከተሞችና የገጠር ቀበሌዎች እንዲሁም ነፃ ባልወጡና በተለያየ አካባቢ የምትገኙ ወጣቶች የአማራ ህዝብ የህልውና ትግልን ለአንዴና ለመጨረሻ በድል ለማጠናቀቅ በሚደረገው ርብርብ አማራዊ ግዴታችሁን እንድትወጡ እያሳሰብን በሚከተሉት መመልመያ መስፈርቶች መሰረት ከመስከረም 19/2018 ዓ.ም ጀምሮ ነፃ በወጡ ቀጠናዎች በሚገኙ ቢሮዎቻችን በአካል እየመጣችሁ እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን:-

👉 የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ በተቆጣጠራቸው ቀጠናዎች አዲስ ምልምል የፋኖ ሰራዊት መመልመያ መስፈርቶች:-

1. እድሜው ከ18 እስከ 40ዓመት ለወንድ፣ ከ18 እስከ 35 ዓመት ለሴት
2. መፃፍና ማንበብ የሚችል/ትችል
3. አማራዊ ስሜት ያለው/ያላት
4. በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ህጎች፣መመሪያዎችና ደንቦች ተገዥ የሚሆን/የምትሆን
5. ለማንኛውም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ፋኖ ግዳጅ ዝግጁ የሆነ/ች
6. ከደባል ሱሶች ነፃ የሆነ/ች( ጫት፣ሲጋራ፣ሀሺሽ እና መሰል አደንዛዥ እፆችና አልኮል)
7. ከማንኛውም ወንጀል ነፃ የሆነ /የሆነች
8. በማንኛውም ቦታ ቢመደብ/ ብትመደብ መስራት የሚችል/ የምትችል
9. የአማራ ብሔርተኝነት የገባው/የገባት
10. ሙሉ ጤነኛ የሆነ/የሆነች
11. የሚኖርበትን አካባቢ የሚገልፅ መታወቂያ ያለው /ያላት
12. በአካባቢው ማህበረሰብ የተመሠገነስነ-ምግባር ያለው/ያላት

ማሳሰቢያ:-ከዚህ በፊት በሰሜኑ ጦርነት በፋኖነት የሰለጠነ/የሰለጠነች በክተት ወደ ማሰልጠኛ ተቋሞች እንድትገቡና አማራዊ ግዴታችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን፤ ይህንን ሳትወጡ ብትቀሩ ለአማራ ህዝብ ጥቁር ታሪክ ጥላችሁ እንዳታልፉ ታሪካዊ ጥሪ ተደርጎላችኋል።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ስልጠና መምሪያ
መስከረም 19/2018 ዓ.ም
🙏3
መንግሥታዊ ሽብር በአዲሱ ዓመት ሊገታ ይገባል!
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የተሰጠ የአቋም መግለጫ

በተለያዩ ሥርዓቶች እንደተለመደው ሕዝብ በአዲስ ዓመት ተስፋ እንዲሰንቅ መጠናቸው ቢለያይም ግጭቶችን በማቆም፣ የፖለቲካ እሥረኞችን በይቅርታ በመፍታት፣ የሰውን ኑሮ ያከበዱ ጫናዎችን በማቅለል ጥረቶችን ሲያደርጉ ታዝበናል፤ በታሪክ ድርሳናትም ተጽፎ ይገኛል።

በዚኽ አዲስ ዓመትም ከሂደታዊ አስገዳጅነቱ በመለስ ሥርዓቱ ወደቀልቡ ተመልሶ እንዲኽ ያሉ በጎ መነሳሳቶችን ይወስድ ይኾን ወይ? የሚል ጥቂት የማይባሉ ዜጎች ሀሳብ ነበር። ያ ሳይኾን በተቃራኒው እገታ፣ ግድያ፣ ዛቻ፣ ድሮን ጥቃት፣ ፖለቲካዊ ውጥረቶች፣ የኑሮ ጫና እና መሰል ሥርዓት ወለድ ምስቅልቅሎች ልካቸውን፣ አኃዛቸውንና ቦታቸውን ቀይረው የሕዝቡን ስቃይ እያናሩት ይገኛሉ፡፡

በሰሜን ወሎ ዞን ከወልዲያ 20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኘው ሣንቃ ከተማ በመስቀል በዓል ዕለት ከቀኑ 6፡00 ጤና ጣቢያ ላይ ከቀኑ 6:00 ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ቤተሰብ ሲያስታምሙ የነበሩ 3 ሰዎች ተገድለዋል፤ አንዲት የጤና ጣቢያው የጽዳት ሠራተኛ ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባታል፤ 3 የጤና ጣቢያው የሕክምና ባለሙያዎች ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ የ 6 ዓመት ሕጻን ልጅ ከፍተኛ ጉዳት አስተናግዳለች። ከዚኹ ጋር ተያይዞ ላሊበላ ከተማ ከሚገኙ ቅርሶች መሐል የኾነውና ከአንድ ቋጥኝ ፍልፍል የተሠራው ገነተማርያም ቤተክርስቲያን አቅራቢያ የድሮን ጥቃት ተፈጽሞ እስከአኹን ባለን መረጃ የተጎዳ ሰው ባይኖርም "የቅርሱን መሠረት ነክቶት ይኾን ወይ?! ብለን ሥጋት ገብቶናል" ብለውናል የአካባቢው ነዋሪዎች። ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት እንዲኽ ያለውን ዘፈቀዳዊና ሥርዓት ወለድ መንግሥታዊ ሽብር በጽኑ ያወግዛል፤ ለሞቱትም ልባዊ ኃዘኑን ይገልጻል። በቅንጅታችን ደጋግመን እንዳልነው ጦርነቶች በተኩስ አቁምና በድርድር እንዲቋጩ፣ ሕዝቡም የሰላም አየር እንዲተነፍስ፣ ወንድም ወንድሙን የሚገድልበት የደም ቁማር በአስቸኳይ እንዲቆም ኹሉም ተፋላሚ ወገኖች ሕዝብን በማስቀደም ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እናሳስባለን፡፡  

በሌላ በኩል እሑድ መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም በጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ በመስቃን ወረዳ በሚኖሩ ኹለት ወንድማማች ሕዝቦች ስናኖ ሴራ በተሰኜ የአካባቢው ባሕላዊ እሴት አከባበርና ባለቤትነት ዙሪያ በተነሳ ብጥብጥ ጉዳቶች እንደተከሰቱ ከአካባቢው ምንጮች ለማወቅ ችለናል፡፡ የፀጥታ ኃይሉ ችግሩ ሲፈጠር በቅርበት በመገኘት ለማረጋጋት ያደረገው ጥረት በበጎ የሚታይ ኾኖ በዘፈቀዳዊ ተኩስ ሳቢያ እስከሞት የደረሰ ጉዳት መድረሱን መስማት ልብ ሰባሪ ክስተት ኾኖ አግኝተነዋል፡፡ ከኹሉም ነገር በፊት የማኅበረሰብ ደኅንነት ቅድሚያ ተሰጥቶት በአካባቢውም ያለው አስተዳደራዊ ችግር በስክነትና በወንድምአማችነት መንፈስ እንዲፈታ በአደራ ጭምር ማሳሰብ እንወዳለን፡፡  

ፈጣሪ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!

ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት
መስከረም ፲፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
👍2
ፍ/ሰላም ገራይ ላይ የጠላት ሃይል እርምጃ ተወሰደበት።

የአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቴዎድሮስ ዕዝ ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም ፭ኛ ክፍለጦር
አረንዛው ዳሞት ብርጌድ ብርጌድ ዛሬ ማለትም መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ/ም ጠላት ፍኖተ ሰላም ከነበረ ጎሬው በመውጣት ወደ ጀግኖቹ ሀገር ገራይ ለመግባት ያለ የሌለ ኃይሉን ሰብስቦ ቢሄድም በእነ አይቀመሴ ሻለቃ አበረ ምናሉ ልጆች ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት እስከ ረፋዱ 5:30 በተደረገ ውጊያ የጠላት ኃይል ረግፏል።

በዚህም
ከ  20 በላይ ሙት
ከ18 በላይ ቁስለኛ ሲሆን 2 ክላሽ መማረክ ተችሏል።

@አረንዛው ዳሞት ብርጌድ ብርጌድ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፍሥሓ አደራው
🙏2