ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.21K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
ሰበር የድል ዜና!

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ የልጅ እያሱ ኮር በድጋሜ እንኳን ለ2018 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል አማራ ጠል ከሆነው የብልፅግና ስርዓት የከባድ መሣሪያ ግድያ ጠብቆ በፅናት አደረሳችሁ እያልን በዛሬው እለት ማለትም ጳጉሜ 05/13/2017ዓ.ም በልጅ እያሱ ኮር ስር ያለችው የቤተ አማራ ክፍለ ጦር ግሽን ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ ሞርተር እና ድሽቃ በማጥመድ መህበረሰቡን መውጫ መግቢያ በማሳጣት ለንግስ እየመጡ ያሉ እንግዶችን በመደብደብ ማንገላታቱን አጠናክሮ የቀጠለውን የወራሪ ጦር ውጊያ ገጥማለች።

የቤተ ክርስቲያኑን ዙሪያ ደግሞ ብሬን ስናይፐር እና የነፍስ ወከፍ መሣሪያ በማጥመድ ሰው በፍርሃት ቆፈን እንድዋጥ አድርጎታል በዚህም ምክንያት የቤተ አማራ ክፍለ ጦር አውሬ የሆነውን የስርዓቱ ወንበር አስጠባቂ ጥምር ጦር ላይ ውጊያ ለማድረግ ተገዱለች።

እንደ ፋኖ እና እንደ አንድ ጤነኛ ሰው ይህ ቦታ እንኳንስ ኢትዮጵያዊ መላ ዓለም የሚሳሳለት ቅርስ ያለበት እና መነኮሳት ቀሳውስጥ ድያቆናት የሚያገለግሉበት ቦታ በመሆኑ ፋኖ ይህንን ከግምት ውስጥ በማስገባት ቦታውን ለቆ ቢወጣም ፋኖ እግሩ እንደለቀቀ ከ ሶስት በላይ ክፍለ ጦር የተውጣጣ ኃይል በማስገባት ፋኖ ከወጣ ጀምሮ ቦታውን ይዞት ይገኛል።

ስለሆነም ማህበረሰቡ በሰላም እንዳይኖር በማሳቀቅ እና የቤተ ክርስቲያን አባቶች በነፃነት ቅዳሴም ውዳሴም ማድረስ እንዳይችሉ ተደርጓል።
ይህ ፀረ ህዝብ ፀረ ኦርቶዶክስ ፀረ ሙስሊም የሆነው ስርዓት ከዚህ በላይ እምነቱንም ሲያረክሰው የአካባቢውን ማህበረሰብ እና የሚመጡ እንግዶችን ሲያንገላታ የምናይበት ትግዕስታችን ስላለቀ ተዋግተን ለማስለቀቅ ወስነናል።

በመሆኑም አባቶች ይህ ሰው በላ ስርዓት ከቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ እንድወጣ የማድረግ ሀላፊነታችሁን እንድትወጡ እያልን ይህ የማይሆን ከሆነ ግን እኛ በጉልበታችን በመጠቀም ያለንን መሣሪያ ሁሉ ተጠቅመን ለመምታት የምንገደድ ሲሆን ለሚደርሰው ጥፋት ሁሉ ፋኖ ተጠያቂ እንደማይሆን ጭምር እያሳወቅን የጀመርነውን ውጊያ አጠናክረን እየቀጠልን መሆኑን ሁሉም ህዝብ እያየ ነው አሁንም እስከ ቀራኒዎ ውጊያችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ የልጅ እያሱ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ጳጉሜ 5/2017 ዓ.ም
🙏1
የአፋህድ የአዲስ ዓመት እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት---2018 ዓ.ም የተስፋ ዓመት ነው!!!

---ጳጉሜ 5፣ 2017 ዓ.ም

ሰሞኑን የታዘብነውን የጨረቃ ግርዶሽ በጥንታዊ አባቶቻችን ቀደም ብሎ ተተንብዮ የተቀመጠ መሆኑ፣ የዘመን አቆጣጠራችን ልንኮራባቸው ከሚገቡ ታሪካዊ ውርሶቻችን አንዱ መሆኑን በተጨባጭ አሳይቶናል ።

በዘመናት ዑደቶች ውስጥ ከምናከብራቸው በዓላት አንዱ የሆነው ዘመን መለወጫ፣ ከዘመን መለወጫው ዋዜማ ጀምሮ ዕንቁጣጣሽ ተብሎ እንደሚጠራ ኢትዮጰያዊያን አባቶቻችን አስተምረውናል። ዕንቁጣጣሽ "እንኳን መጣሽ" በምትባለው ወርሃ ጳጉሜ በዓለማዊው በባህላዊ ጭፈራዎቻችን እና በቤተ እምነቶቻችን በዜማዎች በተለየ ሁኔታ ይከበራል። ይህ ሁሉ ለሀገራችን የከበረ የባህል ውርስ እና ልዩ መለያ ጌጥ ሆኖ ኖሯል።

“መስከረም ከእነ ሥሩ ለምለም” የሚለው የማህበረሰባችን አነጋገር፣ የተዘሩ አዝርዕት ፍሬ የሚጀምሩበት ፣ውሃ የሚጠራበት ፣ብርሃን የሚገለጥበት ክረምቱ ተግ የሚልበት ጊዜ በመሆኑ፣ በአዲስ ዓመት አዲስ መንፈስ፣ አዲስ እሳቤ፣ አዲስ ውጥን፣ አዲስ ግብ፣ አዲስ ቃል ኪዳን የሚበስርበት የዓመት ዑደት መጀመሪያ ነው።

የባህረ ሀሳብ ሊቃውንቶቻችን እንደሚያስተምሩን፣ መስከረም ቀን እና ሌሊቱ እኩል የሚሆኑበት ነው። ሳይንሱም ፀሐይ በመሬት እኩሌታ የምትስተካከልበት መሆኑን አረጋግጧል። በሀገራችን  “መስከረም ሲጠባ፣ አደይ ሲፈነዳ፣    ሰው  እንኳን ዘመዱን ይጠይቃል ባዕዳ” ይባላል። በመስከረም ውሃዎች ስለሚጎድሉ፣ ሰው  ወንዞችን ተሻግሮ  "ባዕድ ዘመድ" ሳይል የሚጠያየቅበት ጊዜ በመሆኑ፣ አፋህድም አዲሱን ዓመት በዚሁ የተስፋ መንፈስ ሆኖ ይቀበለዋል።

አማራ የ2018ን የዘመን መለወጫ የሚቀበለው ያለፈውን የትግል ዓመት ችግሮች ለመሻገር የሚያስችለው አፋፍ ላይ ቆሞ እና አዲስ የአንድነት ተስፋ ሰንቆ ነው። አፋህድ ህዝባችን በአዲስ መንፈስ በጉጉት የሚጠብቀውን የአንድነት ጥያቄ የመመለስ ግዴታ እንዳለበት ጠንቅቆ የሚረዳ በመሆኑ፣ ለተግባራዊነቱ አመቻች ኮሚቴ አቋቁሞ ከወንድሞቹ ጋር ግንኙነት መጀመሩን የሚገልፀው በታላቅ ደስታ እና ኩራት ነው።

አፋህድ የአዲሱን ዓመት ኃላፊነቱን እና ግዴታውን በቃል ኪዳን ማሰሩ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በትግሉ ውስጥ በቀጥታ እየተሳተፉ ለሚገኙት የአማራ ህዝብ እና የፋኖ አባላት የሚከተሉትን ጥሪዎች እናስተላልፋለን:-

1ኛ---ጄኖሳይድ ታውጆብህ ህልውናህን በትጥቅ ትግል እያስከበርክ የምትገኘው የአማራ ህዝብ :-

የፋኖ አንድነት እውን እንዲሆን ግፊት እንድታደርግ እና ጦርነቱን በአጭር ጊዜ ለመጨረስ እንዲቻል ትግሉን እንደተለመደው በሙሉ ኃይልህ መደገፉን እንድትቀጥል ጥሪ እናቀርባለን፣

2ኛ--- ጄኖሳይድ ለታወጀበት ለየአማራ ህዝብ ህልውና መረጋገጥ በዱር በገደሉ እየተዋደቃችሁ የምትገኙ  ፋኖዎች ሁሉ፣

በዚህ ዓመት ትግላችን ትላልቅ የውስጥ እና የውጭ ድሎች የምናስመዘግብበት እንዲሆን ሁላችንም ለፋኖ አንድነት ልባችንን እንድንከፍትና እንድንታገል ጥሪ እናቀርባለን።

በተጨማሪም፣ በአምባገነኖች ጭቆና እና በመንግሥታዊ ዘረፋ ፣ በዘረኝነት እየተሰቃየ የሚገኘው ወገናችን የኢትዮጰያ ህዝብ፣ በአዲሱ ዓመት የፋኖን ትግል ከመቼውም ጊዜ በላይ ይደግፋል ብለን በጉጉት እየጠበቅን እንገኛለን። እየተጨፈጨፍንም ቢሆን፣ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችንን እና ሀገራችንን ለአፍታም ቢሆን ዘንግተን አናውቅም።

እንዲሁም፣ ሁሌም ለወገኑ እና ሀገሩ ተቆርቋሪ የሆነው ዲያስፖራ እና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር ያለን ግንኙነት በ2018 ዓ.ም እንደ አዲስ የሚታደስበት ዓመት እንዲሆን ቆርጠን ተነስተናል።

በመጨረሻም፣  ባለፉት 2 ዓመታት በነበረው እልህ አስጨራሽ ትግል የተሰው የታጋዮች እና የንፁሃንን ነፍስ ቸሩ ፈጣሪ በአፀደ ገነት ያኑርልን !!!

ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!!!

ድል ለአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት!!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
/
ጳጉሜ 5፣ 2017 ዓ.ም
1
ሰበር የድል ዜና

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ የልጅ እያሱ ኮር የቤተ አማራ ክፍለ ጦር እና የምኒልክ እዝ ልዩ ሻለቃ በመጣመር ባደረጉት ተጋድሎ የብልፅግናን ጥምር ጦር ድባቅ መትተው ድል ተጎናፀፉ::

ትናትና 05/2017 ዓ.ም የቤተ አማራ ክፍለ ጦር አንድ ሻለቃ እና የምኒልክ እዝ ልዩ ሻለቃ ጥምረት በመፍጠር በተደረገ ተጋድሎ በደሴ ዙሪያ ያሉ ከተሞችን ተቆጣጥረዋል።

በዚህ የተሳካለት ዘመቻ ከደሴ በቅርብ ርቀት የሚገኙ ሀያታ ሞቴ እና ዳባ የሚባሉ የደሴ ዙሪያ ከተሞችን ከእልህ አስጨራሽ ውጊያ በሗላ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብተዋል።

የእነዚህ ከተሞች በፋኖ መያዝ ወደ ደሴ ለሚደረገው ግስጋሴ ጉልህ አሰተዋፅኦ እንደሚኖራቸው የፋኖ ከፍተኛ የጦር አማካሪዎች እየገለፁ ይገኛሉ::

በዚህ ውጊያ በርካታ የጥምር ጦሩ ወታደሮች ሙት እና ቁስለኛ ሲሆኑ ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ተተኳሽ እና መሣሪያ በምርኮ ተገኝተዋል። ውጊያው የፋኖ አቅም መጎልበት የታየበት እንደሆንየአካባቢው ነዋሪዎች ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የልጅ እያሱ ኮር ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 1/2018 ዓ.ም
2🙏1
የድል ዜና!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
መስከረም 1/2018 ዓ.ም
የልጅ እያሱ ኮር ለአንድ ወር ያህል እራሱን ሲያደረጅ እና ሲመክር ከቆዬ በሗላ ከደቡብ ወሎ የአንባሰል ተራሮች እስከ ተሁለደሪ ከወረባቦ እስከ ደሴ ዙሪያ ወራሪውን ኃይል መግቢያ መውጫ እያሳጣው ይገኛል::

ትላንት ጳጉሜ 5/2017 ዓ.ም ግሽን ላይ የመሸገውን የጠላት ጦር የቤተ አማራ ክፍለ ጦር ሻለቃዎች ሲለበልቡት ወለው ሲያድሩ በተመሳሳይ ቀን የቤተ አማራ ሌላኛዋ ሻለቃ እና የምኒልክ እዝ ልዩ ሻለቃ ደሴ ዙሪያ ያሉ ሶስት ትነነሽ ከተሞችን ተቆጣጥረዋል::

በሌላ ዜና መስከረም 1/2018ዓ.ም በልጅ እያሱ ኮር ስር ያለችው የራስ አሊ ክፍለ ጦር አራተኛ ሻለቃ በተሁለደሪ ወረዳ ከሀይቅ ከተማ አፍንጫ ስር ቆሎባቄላ የተባለውን ምሽግ ከእልህ አስጨራሽ ውጊያ በሗላ በመቆጣጠር ለአድሱ አመት የደስታ ብስራት እንካችሁ ብላለች።

የራስ አሊ ልጆች የአባታቸው ልጆች መሆናቸውን በተግባር በተደጋጋሚ ያስመሰከሩ ቢሆንም እንደዚህ ግን እረዥም የእግር ጉዞ በመጓዝ የሀይቅ ከተማን ስጋት ውስጥ ማስገባት ከተጋድሎም በላይ ተጋድሎ ነው።

አራተኛ ሻለቃ ባደረገችው ተጋድሎ ጠላትን ሙት እና ቁስለኛ ስታደርግ ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የክላሽ ተተኳሽ እና አስር ክላሽ በመማረክ የጠላትን ቅስም ሰብራለች። ይህች ለጠላት የማትያዝ የማትጨበጥ የሆነች ሻለቃ አሁንም ከቆሎባቄላ ወደ ኃይቅ ከተማ በመገስገስ ላይ ትገኛለች።

ኮሩም በዓሉን ወደጎን በመተው የአማራን ህዝብ ነፃ ለማውጣት በየ ዱር ገደሉ ለምትዋደቁ ፋኖዎች በሙሉ ክብር ይገባችሗል 2018 ዓ.ም የአማራ ህዝብ ነፃ የሚወጣበት አመት እንድሆን እየተመኘን ዘገባችንን እዚህ ላይ እንቋጫለን።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
የልጅ እያሱ ኮር የህዝብ ግንኙነት
መስከረም 1/2018 ዓ.ም
2🙏1
የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ልጅ እያሱ ኮር ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ሰለሞን አሊ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!

ዘመን ይመጣል ዘመን ይሄዳል የሰው ልጅ በዚህ የዘመን ዑደት ውስጥ የመነሳት እና የመውደቅ ኩነቶች ሊገጥሙት ይችላል ለዚህም እንደማሳያ የሚሆነው አሁን አማራ የገጠመው መከራ አንዱ ነው ታዳ በዘመኑ የገጠመህን ውጣ ውረድ በብቃት እና በንቃት ተወጥተህ ማለፍ ከቻልክ ለሚቀጥሉት ዘመናት ተሻጋሪ የሆነ ታሪክ እና ዘመንን መሻገር የሚችል ትዉልድ መፍጠር ይቻላል።

በተቃራኒው ይህ ትውልድ ስህተት ከፈጠረ ወደማይወጣበት ቅርቃር ውስጥ ሊገባ ይችላል ስለሆነም እራሱን አሻግሮ አማራን ማሻገር የሚችል ትውልድ መፍጠር አማራጭ የሌለው አማራጭ መሆኑ ግልፅ ነው::

አማራ ሀገሩ ኢትዮጵያን ሲያስከብር የነበረ ትውልድ እንዳለው ሁሉ አሁንም የሰላም መንገዱን እንዳባቶቹ ከተጠቀመ በሗላ ይህን የሚሰማ አካል ከሌለ ደግሞ እምቢ ለሀገሬ እምቢ ለህዝቤ ካለ ማንም አልፎ ሂያጅ አይደለም ታንክ እና የአየር ኃይል ይዞ የመጣው ጣሊያንም በኋለ ቀር መሣሪያ ክንዳችንን ቀምሶ እንደተመለሰ ዓለም ያውቀዋል።

የአማራ ህዝብ አሁን የገጠመውን ችግር ትውልዱ ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ያለው አማራ አንድ ላይ በመቆም ይህን ሰው በላ ስርዓት ግብዓተ መሬቱን ማፋጠን ይጠበቅብናል።ታዳ ይህ አሁን የያዝነው ዘመን አማራ ነፃ የሚወጣበት ዘመን እንዲሆን እየተመኘሁ በዱር በገደል እየተዋደቃችሁ ያላችሁ የአማራ ታጋዮች በሙሉ  እንኳን ለአዲሷ አመት አደረሳችሁ ማለት እወዳለሁ።

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የልጅ እያሱ ኮር ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ሰለሞን አሊ!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
መስከረም 1/2018 ዓ.ም
👍2🙏1
ሰበር ዜና!

የአፋብኀ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ምስራቅ አማራ ኮር1 ባለሽርጡ ክፍለ ጦር የደቡብ ወሎዋን ሰግለን ከተማን ከበባ ውስጥ በማድረግ በርካታ የብልፅግና ቡድን ምንጣፍ ጎታች ሚሊሻና አድማ ብተና በመደምሰስና በማቁሰል ድል ተጎናፀፈ።

ለወራት ከሀይቅ አቅራቢያ ሰግለን ከሚባል ተራራ መሽጎ ማህበረሰቡን ሲያንገላታ፣ሲዘርፍ፣ሴቶችን ካምፕ አድርጎ ከያዘው ተራራ አስገድዶ ሲደፍር የነበረውን የስርዐቱን ጨፍጫፊ ሰራዊት ከሞርተር ጥቃት ጀምሮ እስከ 4:00 በቆየ አውደ ውጊያ ሽርጥ ለበሽ ኮማንዶዎች በከፈቱበት መብረቃዊ ጥቃት በርካታ የአድማ ብተና ሀይልን በመደምሰስ ገሚሱን ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል።

ዛሬ መስከረም 1/2018 ዓ.ም ከጧቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ቀኑ 4:00 በቆየ አውደ ውጊያ በደቡብ ወሎ ዞን ተውለደሬ ወረዳ 017 ቀበሌ ሰግለን ተራራ መሽጎ የነበረውን ሆድ አደር እና የብአደን ምንጣፍ ጎታች ሚሊሻን የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ በአንቡላንሶች ቁጥሩ ያልታወቀ የአድማ ብተና ሀይልን ቁስለኛ ከሰግለን ወደ ሀይቅ ከተማ ሲያጓጉዝ ውሏል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ምስራቅ አማራ ኮር 1 የባለሽርጡ ክፍለጦር ቃል አቀባይ ፋኖ መሀመድ ሞገስ አስታውቋል::

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
መስከረም 1/2018 ዓ.ም
👍1
ማንነቱ እንደ ወንጀል ተቆጥሮ መንግስትና ሀገር አልባ የተደረገው አማራ እጣፈንታ በወለጋ- የአገዛዙ ጦር እና ፀራ አማራ እርምጃው

በሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን አቢደንጎሮ ወረዳ በአንድ መንደር የሚገኙ አማራዎችን ቤት የጎተራ እህልን ጨምሮ ከእነ ሙሉ ንብረቱ ፋኖን ትቀልባላችሁ በሚል ሰበብ እንዲቃጠል አድርጓል- ፀረ አማራው የዐቢይ አህመድ አገልጋይ ጦር።

ድርጊቱ አስነዋሪ እና ጠያፍ ነው። ለኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ ያደረው እና በተለይም ከሁለት ዓመት በላይ ወደ ክልሉ መካናይዝድ ጦር በማዝመት እና በአየር ኃይል እየታገዘ አማራን በከባድ መሳሪያ ጭምር እየገደለ እና እያፈናቀለ ያለው "የመከላከያ ሰራዊት" እየወደቀ ላለው ስርዓት ውግንናውን አሳይቷል ፤ ፀረ አማራነቱንም እንደዚሁ።

ከዳር ድንበር ጠባቂነት ወደ ብጽግና ፓርቲ አገልጋይነት በመውረድ ማንነት እየቆጠረ አማራን በማሳደድ እና በመግደል ላይ ተጠምዷል።

ከክልሉ ውጭ ያሉ የአማራ ተወላጆችንም በፋኖ ስም እየለቀመ ያስራል ፤ ቤታቸውንም በእሳት ያጋያል።

ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ከወደ ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን አቢደንጎሮ ወረዳ ከሰሞኑ የተሰማው አሳዛኝ መረጃ ነው።

ሎምጫ ቀበሌ ቢጊት በተባለ መንደር ነሃሴ 27/2017 መከላከያ በአማራዎች ላይ የፈፀመው ጥቃት በእርግጥም አሳሳቢ ነው።

ተፈጥሮአዊ ማንነት አማራነት ወንጀል ሆኖ ሕይወትን ጨምሮ ከፍ ላለ ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግር ሲዳርግ መመልከት የተለመደ እና በተለይም የዘረኛው ኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ መገለጫ ከሆነ ከራርሟል።

የተወሰኑ የአካባቢውን ወጣት (ቄሮዎችን) ይዞ ወደ ሎምጫ ቀበሌ ቢጊት መንደር የገባው ይህ የዐቢይ አህመድ አገልጋይ ጦር "ፋኖን ትቀልባላችሁ" የሚል ሰበብ በመፍጠር በነዋሪዎች ላይ ጥቃት ፈፅሟል።

ይኸውም ነሃሴ 27/2017 ብቻ 2 ገበሬዎችን አቁስሏል ፤ 13 የሚሆኑትን አስሯል ፤ 76 የሚሆኑ መኖሪያ ቤቶችን የጎተራ እህልና አልባሳቱን ጨምሮ ከእነ ሙሉ ንብረቱ በእሳት አጋይቷል።

እነዚህን ገበሬዎች በጭካኔ በማፈናቀል ሜዳ ላይ እንዲወድቁ እና ለመጠለያ እጦትና ለርሃብ እንዲጋለጡ አድርጓል።

ቤታቸውን በማቃጠል ሜዳ ላይ ከበተናቸው እና ሀገር እና መንግስት አልባ ካደረጋቸው 71 ንጹሃን አማራዎች መካከልም ፦

1) አለባቸው ካሴ፣
2) አንበሳው አባተ፣
3) ዘመኑ ተበጀ፣
4) አይናለም አንባዬ፣
5) ቄስ ይሄነው በላይ፣
6) የኔአለም አበበ እና
7) አባቢል ወንዴ የተባሉ አርሶ አደሮች ይጠቀሳሉ።

"ለአማራ ጋር ትወግናላችሁ" ፣ "አብራችሁ ማህበር ትጠጣላችሁ" እንዲሁም "ፋኖንም ትቀልባላችሁ" በሚልም የአምስት የኦሮሞ ተወላጆችን ቤት በተመሳሳይ ከእነ ጎተራ እህሉ እንዲቃጠል አድርገዋል።

ለአማራ ትወግናላችሁ በሚል ቤታቸው የተቃጠለባቸውም የኦሮሞ ተወላጆችም ፦

1) ተሾመ አበበ፣
2) ታከለ ጉታ እና ወንድሙ፣
3) አዱኛ እና
4) አቢደንጎሮ ላይ ከአማራዎች ጋር ተባብረህ የኦሮሞ ተወላጆችን ቤት አቃጥለሃል በሚል በሽብር ወንጀል ተከሶ 9 ዓመት ተፈርዶበት በዝዋይ ማ/ቤት የሚገኘው የአቶ ታከለ ኃይሉ ናቸው።

ሁለት የኦሮሞ ተወላጆችን ጨምሮ ሰባት አማራዎች ማለትም አባቡ አንለይ እና እንድሪስ አባቡ የተባሉ አባት እና ልጅን ጨምሮ 9 የሚሆኑ የአቢደንጎሮ ነዋሪዎች በሽብር ተከሰው ከ6 ዓመት በላይ ተፈርዶባቸው ወደ ዝዋይ ማ/ቤት ከተጫኑ አንድ ዓመት አልፏቸዋል።

በአገዛዙ ጦር ቤታቸው የወደመባቸውም ሆነ በግፍ እስር ላይ የሚገኙ የአቢደንጎሮ ነዋሪዎች ፍትህ ይፈልጋሉ ፤ አማራነት ወንጀል አይደለም!

የሚመለከታችሁ ሁሉ ስለ ሰው ልጅ ስትሉ ከንጹሃን ጎን በመቆም ኃላፊነታችሁን ተወጡ።

(አውሎግሶን አንድነት ፣ መስከረም 1/2018)
3
አሰደንጋጭ ዜና፦
ፀረ ህዝብ የሆነዉ ብልፅግና በእስቴ መካነየሱስ ከተማ አሰቃቂ ተግባር መፈፀሙ ተሰማ!!

የእስቴ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ማንተፋርዶ ሞላ የተባለ ሆድ አደር ባንዳ የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ የሜጀር ጀኔራል ዉባንተ አባተ ኮር አንድ ጉና ክፍለጦር አስቴ ዴንሳ ብርጌድ ሻለቃ ሁለት ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ታርቆ ታመነ ቤትን በቦንብ በመምታት በቤቱ ላይ ከባድ ጉዳት እንዲደርስ ተደርጓል።

በእስቴ መካነየሱስ ከተማ ቀበሌ01 የሚገኘውን መኖሪያ ቤት ከሌሊቱ 6 :00 ሰአት ቤቱ ውስጥ የሚገኙትን ሰወች እንደተኙ በስከውጭ እንዳይወጡ በመቆለፍ ቤቱን በጋዝ በማርከፍከፍ በቦንብ ጭምር ቤቱ እንዲቃጠል አድርገውታል።

6 ሰው የአርበኛ ቤተሰቦች እብረው እንዲቃጠሉ ከተፈረደባቸው የሞት ፍርድ በእሪታ አካባቢ ሰው ደርሶ አትርፏቸዋል።

በከተማዋ የሚፈፀሙ አሰቃቂ ድርጊቶች ተጠናክረው የቀጠሉ ሲሆን የሚፈፀሙ አሰቃቂ ግፎችን በበላይነት የሚፈፅመዉ የወረደው አስተዳዳሪ አቶ ማንተፋርዶ ሞላ ነዉ።
💔42