ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.21K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ሲምፖዚየም - ጷጉሜ 1 እና 2 ቀን 2017 ዓ.ም. ከምሽቱ 1 ሰዓት
👍2
በአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ ዕዝ 2ኛ /ተፈራ ዳምጤ/ ክፍለ ጦር ከመዝገበ ጮቄ ብርጌድ ለሰዴ ከተማና አካባቢው ማህበረሰብ  የተላለፈ መልዕክት

ድሮ ተናግረናል፣ ዘንድሮም እየተናገርን ነው ግን ደግሞ ነገም በተመሳሳይ እንደ ድሮውና እንደ ዘንድሮው ብልሹ የሆነ አሰራር መቀጠሉ አይቀሬ ነው ።ስለዚህ ነገችንን ዛሬ ላይ ሁነን አሰራሮችን ለማስተካከል ትልቅ ትግል ላይ ነን።  ይህንን ደግሞ ከሰልፍ አልፈን ሰይፍ አንስተን እየታገልነው መሆኑን ሁሉም ያውቃል ። ሁኖም ግን ከሞት አፋፍ ላይ ያለው ተስፋ ቆራጩ የብልፅግና መንግስት ነኝ ባዩ አሸባሪ ቡድን እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል በሚል ህዝባችንንና የህዝባችንን ንብረት በእራሱ እንዲሁም በዘመዶቹና በሚቀርባቸው  ስዎች ሀብት እያካበተ ይገኛል።

ገንዘብ ከሚሰበስብባቸው መንገዶች አንዱ የከተማ መሬትን በሊዝ መልኩ ማለትም ውስብስብ በሆነ የማጭበርበር ዘዴ አንድም ለሆዳም የብልፅግና አሽከር አልፎም ለዘመዳ አዝማድ እያስረከበ እንደሚገኝ ደርሰንበታል።

እናም ከሀምሌ 27/11/2015 ዓ.ም ወዲህ በሰዴ ከተማ በየትኛውም መንገድ የሊዝም ሆነ የምራታ መሬት የሚቀበል ግለሰብ ካለ በብርጌዳችንም ሆነ በድርጅቱ  ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እያሳወቅን ከላይ በጠቀስነው መንገድ ቦታ ለመቀበል ሂደት የጀመረ ካላችሁ እንድታቆሙ እናሳስባለን። ይህንን መመሪያ ጥሶ የተገኘ ግለሰብ የገዛውን መሬት ከመነጠቅ አልፎ ተጨማሪ ቅጣት እንደሚጠብቀው ማሳወቅ እንደወዳለን።

መዝገበ ጮቄ ብርጌድ

ድል ለአማራ ፋኖ
ክብር በጀግንነት ለተሰው ሰማዕታት
👍1
ዘመቻ ሰማዕታት እንደቀጠለ ነው።
አፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ  ሀዲስ አለማየሁ ክፍለጦር አብራጅት ብርጌድ ከየጁቤ ከተማ በቅርብ ርቀት የምትገኘው የላምጌጅ ከተማ ላይ ከፍተኛ ጥቃት በመፈፀም የአረመኔው ሰራዋት ጠርናፊ የነበረውን አበበን ጨምሮ በርካታ ሰራዊት መደምሰስ ችሏል።
ከጥዋቱ የጀመረው ውጊያ እስካሁን የቆየ ሲሆን በጠላት ላይ ሰባዊና ቁሳዊ ኪሳራን ማድረስ ችለዋል። 

በተመሳሳይ ቀኝጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለጦር በረኸኛው ጅበላ ሙተራ ብርጌድ ዛሬም ቸርተከል መገንጠያ ሞሰቢት ተራራ ላይ  በሌሊት ጥቃት ፈፅሟል።
አረመኔው ሰራዊት በተኛበት የደረሱት አይበገሬዎቹ የጎዛምን አንበሶች ጠላትን ሲረፈርፉት አድረዋል።

አረመኔው ሰራዊትን እረፍት በመንሳት ፣በመጠዝጠዝ ፣በማዋከብ መድረሻ እንዳያጣ በማድረግ እየተደመሰሰ  ይገኛል።በዚህ የተማረረው እና የፋኖን ክንድ መቋቋም ያቃተው ለፋኖ እጅ እየሰጠ ይገኛል።

በትናትናው እለት  ሁለት የአረመኔው ሰራዊት አባላት ከእነማይ ወረዳ ጠልማ ቀበሌ ከሚገኘው የአረመኔው አገዛዝ ካንፕ  በሐክዳት  የፋብኃ ምዕራብ  አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አባ ኮስትር ብርጌድ ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ተቀላቅለዋል፡፡
ይደርሳል ካሳሁን  እና አማኒኤል አሰፋ አድማ ብተና  የነበሩ ፋኖን ከነሙሉ ትጥቃቸው ሲቀላቀሉ ደማቅ አቀባብል ተደርጎላቸዋል።

አዲስ ትውልድ ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ!
ነሀሴ 28/2017ዓ.ም
👍2
መራሩ የአማራ ህዝብ ሀዘን በኦሮሚያ !!!

በርካታ ንፁሀን አማራዎች በኦሮሚያ እና መተከልበ ብልፅግና ሀይሎች ተገደሉ።

ዛሬ በጥዋቱ መተከል ዞን ወደ ድባጤና ቡለን ወረዳዎች የገባው የአገዛዙ ዘራፊ ታጣቂ 12 ንፁሃን አማራዎችን ገድሎ ከ60 በላይ ሰዎችን አግቶ ሲወስድ በርካታ የቁም እንስሳትን ዘርፏል ሀብት ንብረት አውድሟል ሲሉ የአካባቢው ኗሪዎች ገልጸውልናል።

ነሐሴ 28/2017ዓ.ም
1
ከሰሞኑ በተለያዩ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች ያሰለጠናቸዉ ወታደሮችን በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ማስማራቱ ተገለፀ።

ዛሬ ነሀሴ 27/2017 ዓ.ም 79 ታታ ባስ ወደ ጎንደር ቀጠና ተሰማርቷል።ወደ ጎንደር ከተሰማረዉ ሰራዊት አብዛኛዎቹ ህፃናት መሆናቸዉም ታዉቋል።አገዛዙ ብልፅግና ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል በአስገዳጅ ሁኔታ ያፈሳቸዉን ህፃናት በለብለብ ስልጠና አስመርቆ ወደ አማራ ክልል እያሰማራ ይገኛል።ትናንት ከብርሸለቆ ወተ ወደ ጎጃም ቀጠና ሲሰማሩ በነበሩ መሰረታዊ ወታደሮች ላይ በተወሰደ የደፈጣ ጥቃት ከፍተኛ የሆነ ሰባዊ ዉድመት ተፈፅሟል።የድሀ ልጅን በመገብር ስልጣኑን እየራዘመ የሚገኘው አገዛዙ ትናንትም ከብርሸለቆ ያስወጣቸዉ ወታደሮች በአቸፈር በደርዘን የሚቆጠሩ የሰራዊት አባላት ስለመገደላቸዉ ነዉ የታወቀው ።

ዛሬም ወደ ጎንደር ቀጠና ከገቡ 70 የሰራዊት አባላት በቦታዉ ከመድረሳቸዉ መፈጥፋታቸዉ የብልፅግናዉን መንግስት አስደንግጧል።በትናንትናው እና በዛሬው ዕለት ብቻ ከብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ወተዉ ወደ ጎጃምና ጎንደር የገቡት አብዛኞቹ መኮብለላቸዉን ተከትሎ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ወታደራዊ አዛዥ ብርሀኑ በቀለ ሀገር ጠል ባንዳዎች ሲል ሰራዊቱን ወርፏል።በሁለት ቀን ብቻ በመቶዎች የማቆጠሩ አባላት ከመዉጣታቸዉ መኮብለላቸዉን ተከትሎ የዕዙ አዛዥ የፋኖ ግልገሎች ሲል ወቅሷል።

ከወርሶ እና ጦላይ የሰለጠኑ የድሀ ልጆችም በበርካታ ባስ ተጭነዉ ወደ አማራ ክልል እየገቡ ነዉ መሆናቸው ተገልጿል።ጦርነትን አጀንዳዉ ያደረገዉ አገዛዙ የድሀ ልጆችን እያፈሰ በለብ ለብ ስልጠና ወደ አማራ ክልል በማስገባት ጦርነት ከከፈተ ሁለት አመታትን እያሳለፈ ወደ ሶሴተኛዉ አመት ተዘዋዉሯል።ዛሬም እንደ አዲስ ሰልጣኞችን ወደ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ለማስገባት ወጣቶችን በየከተሞች እያፈሱ ወደ ማጎሪያ ቤት ማስገባት ጀምረዋል።በአዲስአበባ፣በጅማ፣በሀረሬጌ፣በወለጋ፣በአርሲ፣በመቱ እና በአማራ ክልል ሁሉም የዞን እና የወረዳ ከተሞች አፈሳዉ ተጠናክሮ ቀጥሏል።ወጣቶች በአስገዳጅ ታፍሰዉ የአገዛዙ ስልጣን ማራዘሚያ ዋና መሳሪያ ከመሆናቸዉ በፊት ወደ ፋኖ ቀጠና በመሄድ ሀገራቸዉን ከመፈራረስ መታደግ እንደሚገባቸዉም ተጠቁሟል።
2🙏1
በአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ ዕዝ 2ኛ /ተፈራ ዳምጤ/ ክፍለ ጦር ከመዝገበ ጮቄ ብርጌድ ለሰዴ ከተማና አካባቢው ማህበረሰብ  የተላለፈ መልዕክት

ድሮ ተናግረናል፣ ዘንድሮም እየተናገርን ነው ግን ደግሞ ነገም በተመሳሳይ እንደ ድሮውና እንደ ዘንድሮው ብልሹ የሆነ አሰራር መቀጠሉ አይቀሬ ነው ።ስለዚህ ነገችንን ዛሬ ላይ ሁነን አሰራሮችን ለማስተካከል ትልቅ ትግል ላይ ነን።  ይህንን ደግሞ ከሰልፍ አልፈን ሰይፍ አንስተን እየታገልነው መሆኑን ሁሉም ያውቃል ። ሁኖም ግን ከሞት አፋፍ ላይ ያለው ተስፋ ቆራጩ የብልፅግና መንግስት ነኝ ባዩ አሸባሪ ቡድን እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል በሚል ህዝባችንንና የህዝባችንን ንብረት በእራሱ እንዲሁም በዘመዶቹና በሚቀርባቸው  ስዎች ሀብት እያካበተ ይገኛል።

ገንዘብ ከሚሰበስብባቸው መንገዶች አንዱ የከተማ መሬትን በሊዝ መልኩ ማለትም ውስብስብ በሆነ የማጭበርበር ዘዴ አንድም ለሆዳም የብልፅግና አሽከር አልፎም ለዘመዳ አዝማድ እያስረከበ እንደሚገኝ ደርሰንበታል።

እናም ከሀምሌ 27/11/2015 ዓ.ም ወዲህ በሰዴ ከተማ በየትኛውም መንገድ የሊዝም ሆነ የምራታ መሬት የሚቀበል ግለሰብ ካለ በብርጌዳችንም ሆነ በድርጅቱ  ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እያሳወቅን ከላይ በጠቀስነው መንገድ ቦታ ለመቀበል ሂደት የጀመረ ካላችሁ እንድታቆሙ እናሳስባለን። ይህንን መመሪያ ጥሶ የተገኘ ግለሰብ የገዛውን መሬት ከመነጠቅ አልፎ ተጨማሪ ቅጣት እንደሚጠብቀው ማሳወቅ እንደወዳለን።

መዝገበ ጮቄ ብርጌድ

ድል ለአማራ ፋኖ
ክብር በጀግንነት ለተሰው ሰማዕታት
2
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ 2ኛ ኮር
ፊታውራሪ ገበየሁ ክ/ጦ

በምዕራብ ጎንደር መተማ ወረዳ እንደ አዲስ ሁለት ክ/ጦሮችን በማዋሃድ የተደራጀው ፊት አውራሪ ገበየሁ ክ/ጦር ረጅም ሰዓት በወሰደ የደፈጣና መደበኛ ውጊያ ቅይጥ ወታደራዊ አማራጭ ጠላትን ደምስሷል።

በፊውታራሪ ገበየሁ የክ/ሩ ሰብሳቢ አርበኛ አስናቀው ጌታው እና በዘመቻ መሪው አርበኛ ባበይ እያዩ የተመራው ኦፕሬሽን የአገዛዙን ሀይል ክፉኛ እያርበተበተውና እንደ ልቡ እንዳይንቀሳቀስ ከጎንደር ገንዳውሀ ጥቁር አስፓልት የእግር እሳት ሁኖበታል እንዲሁም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአገዛዙ ጥምር ታጣቂ ከባድ ምት ደርሶበታል።

በትናንትናው ዕለት ነሐሴ 27/2017 የአገዛዙ ሀይል ከጎንደር ወደ ገንዳውሀ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአገዛዙ ጥምር ሀይል የቡድን መሳሪያ ሞርተርና ዙ-23 ይዞ ሬሽንና የብልፅግና አሽከሮችን አጅቦ ሲንቀሳቀስ እንዲሁም ቀጠናውን ከመፍራት አኳያ ከጎንደር የተነሳውን ሀይል ለማገዝ ቀድሞ ከገንዳውሀ ተነስቶ ኩመርን ይዞ የቆየውን የጠላት ኦፕሬሽን መልኩን ቀይሮ ከሁለቱም አቅጣጫ ማለትም ከጎንደር የተነሳው አውላላ ሲደርስ እና ከገንዳውሀ የተነሳው ኩመር ከምትባል ቦታ ሲደርስ በተሰነዘረበት የደፈጣ ጥቃት ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት ደርሶበታል።

የመይሳው ካሳ 2ኛ ኮር ፊታውራሪ ገበየሁ አናብስቶች የአገዛዙን የእንቅስቃሴ ኦፕሬሽን በቀላሉ መቆጣጠርና ማክሸፍ ችለዋል። ከጧቱ 3:00 ስአት ጀምሮ ከጎንደር የመጣውን አውላላ ላይ ከገንዳውሀ የመጣውን ኩመር ላይ በሁለት አቅጣጫ ቀኑን ሙሉ እና ምሽቱን እስከ 2:00 ስዓት ሲያበራዩት ውለው አምሽተዋል።

በ11:00 ስዓት የአውደ ውጊያ ቆይታ እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ የበዛበት ከቡድን መሳሪያ እስከ ቦንብ እና የክላሽ የጨበጣ ውጊያ የተደረገ ሲሆን በአሁኑ ስአት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ቁስለኛ ገንዳውሀ ሆስፒታልን አጨናንቆት ይገኛል።ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአገዛዙ ጥምር ሰራዊትም እስከወዲያኛው ተሸኝቷል።በሁለቱም አቅጣጫ የመጣው የጠላት ሀይል ሳይገናኝ ወደ መጣበት ወደ ጎንደርና ወደ ገንዳውሀ ጨለማውን ተገን አድርጎ ቁስለኛውንና አስክሬኑን እያዝረከረከ ወደ መጣበት እግሬ አውጭኝ ፈርጥጦ ከቀጠናው ወጧል።በየ ሸንተረሩ እና በየ በየ ማሳው ያልተነሳ የጠላት ሬሳ ተለቅሞ እየተቀበረ ይገኛል።

የፋኖን በትር መቋቋም ሲያቅተው በንፁሀን ላይ ጥፋት ፈፅሟል።ኩመር ከተማን በከባድ መሳሪያ በመደብደብ ብዙሀኖችን ለከፍተኛ ስቃይ ከመዳረጉ ባሻገር ቤትና ንብረታቸውን አውድሟል።አንዲት ነብሰ ጡር እናትን ጨምሮ ከ7 በላይ ንፁሃን የኩመር ከተማ ነዋሪዎች በአገዛዙ በዘግናኝ ሁኔታ ተገድለዋል።

በንፁሃን መኖሪያ ቤቶችና በንግድ ቤቶች ላይ ያረፈው የጠላት የሞርታር ቅንቡላ በንብረት ላይ ውድመት አድርሷል።አገዛዙ በከተማ ላይ ያነጣጠረ ጉዳት ሲያደርስ ይህ ለሁተኛ ጊዜ ነው።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
በላይ ዘለቀ ዕዝ
ነሐሴ 28/2017
2🙏1
አሁናዊ መረጃ_ወለጋ

በትናንትናው ዕለት ምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ አሊ ቀበሌ የአካባቢውን ማህበረሰብ ቀንድ ከብቶች ሰብስቦ ይዞ ሊወጣ የነበረው የአገዛዙ ጥምር ሀይል በአማራ ፋኖ በወለጋ መከበቡን ተከትሎ ያለምንም ቅድመሁኔታ ሙሉ ከብቶቹን ለማህበረሰቡ የመለሰ ሲሆን በአሁኑ ስዓትም ምሽግ ውስጥ መግባት ተጨማሪ ሀይል እዬጠበቀ እንደሚገኝ የአካባቢው ማህበረሰብ ለቢዛሞ ሚዲያ ገልጸዋል።

በተያያዘ ዜና በትናንትናው ዕለት ከ40በላይ ሙትና ብዛት ያለው ቁስለኛ ያስተናገደው የኦሮሚያ ጥምር ጦር ከደንጎሮ ሀይል በማስጨመር ጫንጮ ልዩ ስሙ ብጅት ላይ በከባባድ መሳርያ የታገዘ ከባድ ጦርነት ከፍቷል ጦርነቱ በጧቱ የጀመረ በአሁኑ ስዓትም ተባብሶ መቀጠሉንና ክፉኛ የተጎዳው ጥምር ጦር ቤት እያቃጠለ እንደሚገኝ ነው የአካባቢው ኗሪዎች ለቢዛሞ ሚዲያ የገለጹት።
4👍1
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ 2ኛ ኮር
ፊታውራሪ ገበየሁ ክ/ጦ

በምዕራብ ጎንደር መተማ ወረዳ እንደ አዲስ ሁለት ክ/ጦሮችን በማዋሃድ የተደራጀው ፊት አውራሪ ገበየሁ ክ/ጦር ረጅም ሰዓት በወሰደ የደፈጣና መደበኛ ውጊያ ቅይጥ ወታደራዊ አማራጭ ጠላትን ደምስሷል።

በፊውታራሪ ገበየሁ የክ/ሩ ሰብሳቢ አርበኛ አስናቀው ጌታው እና በዘመቻ መሪው አርበኛ ባበይ እያዩ የተመራው ኦፕሬሽን የአገዛዙን ሀይል ክፉኛ እያርበተበተውና እንደ ልቡ እንዳይንቀሳቀስ ከጎንደር ገንዳውሀ ጥቁር አስፓልት የእግር እሳት ሁኖበታል እንዲሁም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአገዛዙ ጥምር ታጣቂ ከባድ ምት ደርሶበታል።

በትናንትናው ዕለት ነሐሴ 27/2017 የአገዛዙ ሀይል ከጎንደር ወደ ገንዳውሀ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአገዛዙ ጥምር ሀይል የቡድን መሳሪያ ሞርተርና ዙ-23 ይዞ ሬሽንና የብልፅግና አሽከሮችን አጅቦ ሲንቀሳቀስ እንዲሁም ቀጠናውን ከመፍራት አኳያ ከጎንደር የተነሳውን ሀይል ለማገዝ ቀድሞ ከገንዳውሀ ተነስቶ ኩመርን ይዞ የቆየውን የጠላት ኦፕሬሽን መልኩን ቀይሮ ከሁለቱም አቅጣጫ ማለትም ከጎንደር የተነሳው አውላላ ሲደርስ እና ከገንዳውሀ የተነሳው ኩመር ከምትባል ቦታ ሲደርስ በተሰነዘረበት የደፈጣ ጥቃት ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት ደርሶበታል።

የመይሳው ካሳ 2ኛ ኮር ፊታውራሪ ገበየሁ አናብስቶች የአገዛዙን የእንቅስቃሴ ኦፕሬሽን በቀላሉ መቆጣጠርና ማክሸፍ ችለዋል።

ከጧቱ 3:00 ስአት ጀምሮ ከጎንደር የመጣውን አውላላ ላይ ከገንዳውሀ የመጣውን ኩመር ላይ በሁለት አቅጣጫ ቀኑን ሙሉ እና ምሽቱን እስከ 2:00 ስዓት ሲያበራዩት ውለው አምሽተዋል።

በ11:00 ስዓት የአውደ ውጊያ ቆይታ እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ የበዛበት ከቡድን መሳሪያ እስከ ቦንብ እና የክላሽ የጨበጣ ውጊያ የተደረገ ሲሆን በአሁኑ ስአት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ቁስለኛ ገንዳውሀ ሆስፒታልን አጨናንቆት ይገኛል።ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአገዛዙ ጥምር ሰራዊትም እስከወዲያኛው ተሸኝቷል።

በሁለቱም አቅጣጫ የመጣው የጠላት ሀይል ሳይገናኝ ወደ መጣበት ወደ ጎንደርና ወደ ገንዳውሀ ጨለማውን ተገን አድርጎ ቁስለኛውንና አስክሬኑን እያዝረከረከ ወደ መጣበት እግሬ አውጭኝ ፈርጥጦ ከቀጠናው ወጧል።በየ ሸንተረሩ እና በየ በየ ማሳው ያልተነሳ የጠላት ሬሳ ተለቅሞ እየተቀበረ ይገኛል።

የፋኖን በትር መቋቋም ሲያቅተው በንፁሀን ላይ ጥፋት ፈፅሟል።ኩመር ከተማን በከባድ መሳሪያ በመደብደብ ብዙሀኖችን ለከፍተኛ ስቃይ ከመዳረጉ ባሻገር ቤትና ንብረታቸውን አውድሟል።

አንዲት ነብሰ ጡር እናትን ጨምሮ ከ7 በላይ ንፁሃን የኩመር ከተማ ነዋሪዎች በአገዛዙ በዘግናኝ ሁኔታ ተገድለዋል።

በንፁሃን መኖሪያ ቤቶችና በንግድ ቤቶች ላይ ያረፈው የጠላት የሞርታር ቅንቡላ በንብረት ላይ ውድመት አድርሷል።አገዛዙ በከተማ ላይ ያነጣጠረ ጉዳት ሲያደርስ ይህ ለሁተኛ ጊዜ ነው።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
በላይ ዘለቀ ዕዝ
ነሐሴ 28/2017
🙏1
ሰበር ወለጋ!!

ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤዶንጎሮ ወረዳ ጫንጮ ቀበሌ ልዩ ስሙ ብጅት ላይ የአገዛዙ ጥምር ሀይል በከባባድ መሳርያ የታገዘ ጦርነት መክፈቱን መዘገባችን ይታወሳል በአሁኑ ስዓት የገባው ሀይል ሙሉ በሙሉ በሚል ደረጃ ተደምስሶ አካባቢው ላይ ኔትወርክ ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ከምስራቅ ወለጋና ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞኖች በከባባድ መሳርያ የታጀበ ብዛት ያለው የአገዛዙ ሰራዊት ለ3ኛ ግዜ ወደ ቦታው እያመራ እንደሚገኝ ቢዛሞ ሚዲያ ከአይን እማኞች ባገኘው መረጃ አረጋግጧል።

የአማራ ፋኖ በወለጋ ያለ እረፍት ለ4ኛ ቀን እያደረገ ባለው ከባድ ትንቅንቅ ከፍተኛ ድል ማስመስገቡንና የወለጋ ዞን አመራሮች ላይ ከፍተኛ ሽብር መፍጠሩን ተከትሎ ያለየሌለ ሀይላቸውን ወደ አቤደንጎሮና ጊዳ አያና ወረዳዎች እያስገቡ እንደሚገኝ ቢዛሞ ሚዲያ ከአባቢው ኗሪዎች ባገኘው መረጃ አረጋግጧል።

ነሐሴ 28/2017ዓ.ም
👍2🙏2
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ
የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ዋና ሠብሣቢ አመኑ ዓለምአንተ እና የኮሩ ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ በላይነው ዳኘው
የጉና ክፍለ ጦር ዋና ሠብሣቢ አርበኛ ወንዱአንተ አሠፋ እና የጉና ክፍለ ጦር ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ አዛዥ ደሣለኝ
ነሐሴ 28/2017ዓ.ም

ትናንት በአማራ ምድር የመጀመሪያ የሆነው ጉና ክፍለ ጦር አደረጃጀት ፈጣሪና ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ፣ አርበኛ አምሣሉ ማዘንጊያ(ሻምበል) እና አርበኛ ቢራራ ደምሤ ከሌሎች የትግል አጋሮቻቸው ጋር ጉናን እንደ ሥሙ በግብር አግዝፈው ተፈትነው አልፈው፤ አሁን ላይ ደግሞ ግዙፉ ጉና፣ ተዋጊው ጉና፣ ተቋም ጠባቂው ጉና፣ አፋብኃው ጉና፣ የመርህ አሠራር ባለቤቱ ጉና፣ ሠራዊትን አክባሪው ጉና፣ ለሕዝብ ደካሚው ጉና፣ የለምንነት ተጠየቅ ባለቤቱ ጉና፣ በአመክንዮ አማኙ ጉና፣ አሠላለፍን አበጥሮ ተመልካቹ ጉናና በጥቅሉ ፋኖነትን በግብር ሆኖ ተከሣቹ ጉና አሁን ላይ በዋና ሠብሣቢው አርበኛ ወንዱአንተ አሠፋ እና በዋና ወታደራዊ አዛዡ አርበኛ አዛዥ ደሣለኝ እየተመራ ከ20+ ሥራ አሥፈጻሚዎችን አካትቶ የነጻነት ሐዲድ ጠረጋውን በመርህ እየተገበረ፣ ሠራዊቱን በአካልም በአእምሮም እያነቃ፣ የማሕበረሰቡን ችግር እየፈታ፣ ፋኖነትን ምሽግ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ጭምብል ለባሾችን እየተጋፈጠ፣ ጠላትን በክንዱ እያንበረከከ፣ ኃይሉን ከጊዜ ወደጊዜ እያደራጀና እያዘመነ ወቅቱ የሚጠይቀውን አምሐራዊ ትግል በትክክል እየተገበረ ያለ ግዙፍ ክፍለ ጦር ነው።

ጉና ክፍለ ጦር በውሥጡ 05 ግዙፍ ብርጌዶች ሢኖሩ ከ05 እና 06 በላይ ወረዳዎችን አካልሎ የያዘ ነው። በጉና ክፍለ ጦር መዳረሻ የአገዛዙን የጭካኔ ጥግ እና ፋኖነትን ምሽግ አድርገው የሕዝብን ሥነልቦናና አሁናዊ የትግል ሁኔታ ያልተረዱ ብቻ ሳይሆን የብአዴን ብልጽግና ጭምብል ለባሽ ፋኖ ነን ባዮች በሕዝባችን ላይ የሚፈጽሙትን የውንብድና ግብር ያሥቆማቸው ታላቁ ጉና ክፍለ ጦር ነው። ጉና መሠረቱን በቅልጤ አለት ላይ በመጣሉ ከትናንት እሥከ ዛሬ ግብረ ብአዴናዊያኖቹ ፋፍዴኖች ጆፌያቸውን ቢጥሉም በታላቁና ሁለገቡ ጉና አላማቸው ሳይሳካ እንዲቀር ተደርጓል። ፋፍዴን ከሚዲያ ባሻገር መሬት ላይ በጉና ቀጠና ነፍሥ ዘርቶ እንዳይራመድ፣ በሕልም እንዲኖርና በላም አለኝ በሠማይ እንዲናኝ የተደረገው በዕውነት አንጋቢዎቹ የነጻነት ተፋላሚዎች ነው።

ፋኖነትን አራካሽ፤ ጎጠኝነትን አንጋሽ፣ አማራነትን ረጋሚ፤ አውራጃዊነትን ባራኪ፣ ትግልን በገንዘብ ገዢና ሻጭ፣ አምሐራነትን አጥፊ፤ ብአዴናዊነትን አሥፋፊዎቹ የዚህ ትውልድ የእንግዴ ልጆች የሆኑት መልዕክተ ብአዴኖቹ ፋፍዴኖች የፋኖነትን ጭምብል አጥልቀው ጉና ክፍለ ጦር ላይ የትግል ጓድን ከትግል ጓድ ለመለየት የሚሄዱበት የፈጠራ ድርሰት አየር ላይና ሚዲያ ላይ እንዲጮህ ሢደረግ ተመልክተናል። ወዳጄ ጉና ክፍለ ጦር በጩኸት አልተመሠረተም፤ በጩኸት አይፈርሥም። ጉና ክፍለ ጦር ከመሪዎቹ እሥከ ሠራዊቱ ጥንካሬው የአረብ ብረትነትን የተላበሰ ነው። ጉና ክፍለ ጦር ላይ የሚጮኹ ሚዲያዎችና ጭምብል አጥላቂዎች ሊያውቁት የሚገባ መራራ ዕውነታ ቢኖር የአምሐራ ሕዝብ ትግል አረምና ካንሰር የሆኑ ምሥለ ፋኖ አታላዮችን በነፍጡ ያናፈጣቸው፣ በዕውነት ሰይፍ የመተራቸው፣ ዕብሪታቸውን በክንዱ ያሥተነፈሣቸው፣ ከሚዲያ እሥከ መሬታዊ እንቅሥቃሤ አፋቸውን ያዘጋቸው፣ ትክክለኛ የትግል መሥመሩን ለይቶ የአማራን ሕዝብ ዘርፈ ብዙ የሕልውና ጥቃት ለመመከት የተነሳባቸው፣ መዋቅራዊ የፋሽሥት አቢይ ሸኔ ጥቃቶችን እየመለ
ሰ ያለው፣ ርሥትና ማንነቱን ከታሪካዊ ማሥረጃዎች ጋር አጣቅሶ የለምንነት ተጠየቅን በነፍጡ ያነሳባቸው፣ የኢፌዲሪ ሕገ አራዊትነትን በአመክንዮ የተመለከተውና በጥቅሉ ልክ ያልሆነ ሥራ የሚከውኑ የአገዛዙ መልዕክተኞችንና ጭራቅ ፋፍዴኖችን ከማንም በፊት በነፍጡ አደብ ያሥያዛቸው ታላቁ ጉና ክፍለ ጦር እንደሆነ አሥረግጠን ማሣወቅ እንወድዳለን።

እነኝህ ሰውነታቸው ሀሰት ከተባለ ንጥረ ነገር የተሰራባቸው ፋፍዴን የተባሉ ርኩሳን አረሞችና ልሳኖቻቸው ከትናንት እሥከ ዛሬ እንደ ዓይን ብሌናችን ከምንጠብቀው ጉና ክፍለ ጦር ላይ ሸውራራ ዓይናቸውን ጥለዋል። የፈጠራ ድርሰትን በማቅረብ በአርበኞች ላይ ልዩነት ለመፍጠር በፋፍዴን፣ ሥኳድ፣ አፋሕድና ልሳኖቻቸው በኩል ዕንቁ የነጻነት ታጋይ ወንድሞቻችን ላይ ጥቁር ወጥመድ አዘጋጅተው ወንድሞቻችንን ለማሥጠላትና ለማሥበላት ደናቁርት አፈ ፋፍዴኖች ሢለፍፉ ተመልክተናል።ነገር ግን ጥቋቁር አናብሥቶቹ ጉና ክፍለ ጦሮች ቤታቸውን ጠርቅመው ይነጋገራሉ፣ ይወያያሉ፣ መሆን ያለበትን ሁሉ ይፈጽማሉ፣ ተቋማቸውን ይጠብቃሉ፣ ሀሳዊያንን ያሣፍራሉ፣ ባንዳን እንደ አመጣጡ ይቀጣሉ፣ አምሐራ ዋጋ እየከፈለ ያለው በነገደ አምሐራነቱ እንደሆነ እንጅ በግዛቱ እንዳልሆነ አበክረው ይሰራሉ፣ ብአዴን የአምሐራ ሕዝብ ቁጥር ፩ ጠላት እንደሆነ አምነው ፥
ይታገላሉ፣ የአምሐራ አንገት ፩ እንደሆነ በጽኑ ያምናሉ፣ ትግሉ በአእላፋት አምሐሮች ደም የቆመ እንደሆነ ያምናሉ፣ ለአምሐራነት የተሰው አምሐሮችን ትግል በደማቸው ያሥቀጥላሉ፣ ሥራዎችን ሁሉ በሰፌዳቸው ያበጥራሉ፣ ተላላኪነትን በእጅጉ አምርረው ይጸየፋሉ ብቻ ሳይሆን ለአምሐራነት የመጨረሻው መጨረሻን የሕይወት መሥዋዕትነት ይከፍላሉ።

የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ሥራ አሥፈጻሚዎችና የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ሥራ አሥፈጻሚ እና የጉና ክፍለ ጦር ባለበት በተደረገ ዕንቁ ውይይት የያዝነው አምሐራዊ ትግል ከፈጣሪ ቀጥሎ ብቸኛው መዳኛችን እንደሆነ በገቢር የተገለጠበት፣ ኃይላችን ያለው ፩ አምሐራ ከሚለው ነገደ መጠሪያችን እንደሆነ የተመሰጠረበት፣ ትግሉ የመገፋታችን እምቢ ባይነትና የፈጣሪያችን ሥጦታ መሠባሠቢያችን፥ የጥቃት መመከቻችን፥ የሕልውናችን መሰረት ዘላለማዊ ጌጠ አምሐራ እንደሆነና ይህ ዕንቁ ትግሌ ሲከፋን የምንይዘው ሲደላን የምንተወው ሳይሆን ከማንነታችን መኖር አለመኖር ጋር ተነጽሮ የተቸረን የፈጣሪ ጸጋ ነው። ሥለሆነም በትክክል መብቀልን ከትግል አባታቸው ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ በግብር የተማሩት ዘረ ውባንተዎቹ ጉናዎች እንደ ንሥር ታድሰው እንደ አምበሣ አግሥተው ትግላቸውንና ትግላቸውን ብቻ መሠረት አድርገው የትኛውንም የትግሉ ደንቃራ ሁሉ በእሣተ ገሞራ ክንዳቸው ይፋጃሉ።

ጉና ክፍለ ጦር የአምሐራ ትግል የዕለተ አርብ ሁነት እንደሆነ ተረድቶ በሁለ ገቡ አባቱ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ የተደሰ የትግል መንገድ እሥከ ቀራኒዮ አደባባይ ይጓዛል።

ድላችን በተባበረ ክንዳችን
ዝንተዓለም ዐምሐራ Forever Amhara

ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር
ዘረ ውባንተ አባተ ፋኖ ሀቅአለው ፀጋ ዘ ብሔረ አምሐራ ከቦታው

ቋሚ ምሥል፦ሁለገቡ አርበኛ አመኑ ዓለምአንተ፣ ዕድሜ ያልበገረው ጀግና አርበኛ ወንዱአንተ አሠፋ፣ አርበኛ በላይነው ዳኘው፣ አርበኛ አዛዥ ደሳለኝ፣ የጉና ክፍለ ጦር ሥራ አሥፈጻሚና የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ሥራ አሥፈጻሚ በከፊል
4🙏1