የኢትዮጵያ ሥም ይቀየር የሚል ጥያቄ ቀርቦልናል” -የምክክር ኮሚሽን
ከኢትዮጵያ ውጭ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አጀንዳዎችን ማሰባሰብ የጀመረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን “የኢትዮጵያ ሥም ይቀየር የሚል ጥያቄ ቀርቦልኛል” አለ። ይህንን የተናገሩት ኮሚሽኑ ካሉት 11 ኮሚሽነሮች ውስጥ አንዱ የሆኑት ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ናቸው።
ኮሚሽነር ዮናስ ነገ ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም. በሰሜን አሜሪካ የሚካሔደውን የአጀንዳ ማሰባሳብና የተወካዮች ምርጫ አስመልክቶ “ሉዓላዊ” ለተሰኘ ሚዲያ በሰጡት ማብራሪያ፤ በስካሁኑ ሒደት ለኮሚሽኑ ስለቀረቡ አጀንዳዎች ተናግረዋል። ተጠሪነቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሆነው የኢትዮጵያ የምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመ አራት ዓመታት ሆኖታል።
በእነዚህ ጊዜያት ከትግራይ ውጭ ባሉ ሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የተወካዮች ምርጫ ማድረጉን ኮሚሽኑ ተናግሯል። ከነሐሴ ወር መጀመሪያ አንስቶ ደግሞ ከዲያስፖራው ጋር ምክክር ማድረግ ጀምሯል። የመጀመሪያ ውይይቱን በደቡብ አፍሪካ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ማድረጉን ያስታውቀው የምክክር ኮሚሽን፤ በውይይቱ “ከ 300 የሚበልጡ ሰዎች” መሳተፋቸውን ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
ተመሳሳይ ምክክር በሰሜን አሜሪካ ለማድረግ ሰባት ኮሚሽነሮች ያሉት ልዑክ ዋሽንግተን ዲሲ ገብቷል። ነገ በሚጀምረው ምክክር እስከ 30 የሚደርስ የዲያስፖራው ተወካዮች እንደሚመረጡ ዮናስ (ዶ/ር) ገልጸዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፤ እስካሁን ባተደረጉ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሒደት ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ “አንኳር ጥያቄዎች” እንደቀረቡለት አብራርተዋል።
ከቀረቡት ጥያቄዎች ውስጥ “ከሕገ መንግሥት ጋር የተያያዙ፣ ከቅርፀ መንግሥት [ወይም] መንግሥቱ ምን መምሰል አለበት?፣ከሙስና ጋር፣ ከትምሕርት ሥርዓቱ ጋር፣ ከቋንቋ ጋር የተነሱ ነጥቦች አሉ” በማለት አስረድተዋል። በተለይ “ስለአዲስ አበባ ጉዳይ እጅግ በጠለቀ ሁኔታ” መነሳቱን ጠቁመዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም በይፋ ባልጠቀሱት ቦታ “የኢትዮጵያ ስም ይቀየር” የሚል ጥያቄ እንደቀረበላቸው ተናግረዋል።
“ሌላ ቦታ የተጠየቅሁት የኢትዮጵያ ሥም እንዲቀየር እንፈልጋለን ብሎ የጠየቀ ሰው አለ። የኢትዮጵያ ሥም ይቀየር እስዚህ ድረስ[ነው የሚነሱት ጥያቄዎች]።” ሲሉ በምክክር ሒደቱ ስለሚነሱ አጀንዳዎች አብራርተዋል።
በነዚህ አጀንዳዎች ረገድ ኮሚሽኑ ስለሚኖረው ሚና ሲያስረዱ፤ ሕዝቡ በመጨረሻ በሚያስተላልፈው ውሳኔ መሰረት ጥያቄዎቹ “ለሚመለከታቸው የተወካዮች ምክር ቤት እና ለሚንስትሮች ምክር ቤት አቅርበን መፈጸማቸውን የምንከታተልበት ሁኔታዎች ናቸው የሚኖሩን” ብለዋል። ከኢትዮጵያ ውጭ የሚገኘው 7 ኮሚሽነር ያሉት የልዑክ ቡድን በቀጣይ ካናዳ፣ እንግሊዝ፣ ስዊድን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እንደሚጓዝ ተገልጿል።
ከኢትዮጵያ ውጭ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አጀንዳዎችን ማሰባሰብ የጀመረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን “የኢትዮጵያ ሥም ይቀየር የሚል ጥያቄ ቀርቦልኛል” አለ። ይህንን የተናገሩት ኮሚሽኑ ካሉት 11 ኮሚሽነሮች ውስጥ አንዱ የሆኑት ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ናቸው።
ኮሚሽነር ዮናስ ነገ ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም. በሰሜን አሜሪካ የሚካሔደውን የአጀንዳ ማሰባሳብና የተወካዮች ምርጫ አስመልክቶ “ሉዓላዊ” ለተሰኘ ሚዲያ በሰጡት ማብራሪያ፤ በስካሁኑ ሒደት ለኮሚሽኑ ስለቀረቡ አጀንዳዎች ተናግረዋል። ተጠሪነቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሆነው የኢትዮጵያ የምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመ አራት ዓመታት ሆኖታል።
በእነዚህ ጊዜያት ከትግራይ ውጭ ባሉ ሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የተወካዮች ምርጫ ማድረጉን ኮሚሽኑ ተናግሯል። ከነሐሴ ወር መጀመሪያ አንስቶ ደግሞ ከዲያስፖራው ጋር ምክክር ማድረግ ጀምሯል። የመጀመሪያ ውይይቱን በደቡብ አፍሪካ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ማድረጉን ያስታውቀው የምክክር ኮሚሽን፤ በውይይቱ “ከ 300 የሚበልጡ ሰዎች” መሳተፋቸውን ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
ተመሳሳይ ምክክር በሰሜን አሜሪካ ለማድረግ ሰባት ኮሚሽነሮች ያሉት ልዑክ ዋሽንግተን ዲሲ ገብቷል። ነገ በሚጀምረው ምክክር እስከ 30 የሚደርስ የዲያስፖራው ተወካዮች እንደሚመረጡ ዮናስ (ዶ/ር) ገልጸዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፤ እስካሁን ባተደረጉ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሒደት ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ “አንኳር ጥያቄዎች” እንደቀረቡለት አብራርተዋል።
ከቀረቡት ጥያቄዎች ውስጥ “ከሕገ መንግሥት ጋር የተያያዙ፣ ከቅርፀ መንግሥት [ወይም] መንግሥቱ ምን መምሰል አለበት?፣ከሙስና ጋር፣ ከትምሕርት ሥርዓቱ ጋር፣ ከቋንቋ ጋር የተነሱ ነጥቦች አሉ” በማለት አስረድተዋል። በተለይ “ስለአዲስ አበባ ጉዳይ እጅግ በጠለቀ ሁኔታ” መነሳቱን ጠቁመዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም በይፋ ባልጠቀሱት ቦታ “የኢትዮጵያ ስም ይቀየር” የሚል ጥያቄ እንደቀረበላቸው ተናግረዋል።
“ሌላ ቦታ የተጠየቅሁት የኢትዮጵያ ሥም እንዲቀየር እንፈልጋለን ብሎ የጠየቀ ሰው አለ። የኢትዮጵያ ሥም ይቀየር እስዚህ ድረስ[ነው የሚነሱት ጥያቄዎች]።” ሲሉ በምክክር ሒደቱ ስለሚነሱ አጀንዳዎች አብራርተዋል።
በነዚህ አጀንዳዎች ረገድ ኮሚሽኑ ስለሚኖረው ሚና ሲያስረዱ፤ ሕዝቡ በመጨረሻ በሚያስተላልፈው ውሳኔ መሰረት ጥያቄዎቹ “ለሚመለከታቸው የተወካዮች ምክር ቤት እና ለሚንስትሮች ምክር ቤት አቅርበን መፈጸማቸውን የምንከታተልበት ሁኔታዎች ናቸው የሚኖሩን” ብለዋል። ከኢትዮጵያ ውጭ የሚገኘው 7 ኮሚሽነር ያሉት የልዑክ ቡድን በቀጣይ ካናዳ፣ እንግሊዝ፣ ስዊድን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እንደሚጓዝ ተገልጿል።
የድል ዜና !
የአማራ ፋኖ በጎጃም ሶስተኛ ጎጃም አገው ምድር ክፍለጦር በዘመቻ ሰማዕታት ባደረገው የከበባ ማጥቃት በአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት ላይ ከባድ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሷል።
በውጊያው የተማረኩ
1/ 3 _ ብሬን
2/ 1 _ ስናይፐር
3/ 18 _ ክላሽ
4/ 8700 _ የክላሽና የብሬን ተተኳሽ
5/ 108 _ ወታደራዊ ትጥቅ
6/ 4 _ የብሬን ሸንሸን ተማርኳል።
በውጊያው ያደረሰው ሰብዓዊ ኪሳራ
1) 70 ሙት
2) ከ30 በላይ የቆሰለ የአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት አባላት
በአጠቃላይ አውደ ውጊያው ከቀኑ 6:00ሰዓት የጀመረ እስከ ማታ ድረስ የዘለቀ ሲሆኑ የክፍለጦሩ አመራሮች እና አባላት በሳል አመራርነት እና የጀግንነት ፍልሚያ የታየበት ነበር።
መደምሰስ እና መማረክ ልምዱ የሆነው ጎጃም አገው ምድር ክፍለጦር በየ አውደ ውጊያው በሚፈጽመው መብረቃዊ ጥቃት የማህመድ ተሰማን ቅስም ሰብሯል።
ዘመቻ ሰማዕታት ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ክብር ለሰማዕታት !!
የአማራ ፋኖ በጎጃም ሶስተኛ ጎጃም አገው ምድር ክፍለጦር በዘመቻ ሰማዕታት ባደረገው የከበባ ማጥቃት በአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት ላይ ከባድ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሷል።
በውጊያው የተማረኩ
1/ 3 _ ብሬን
2/ 1 _ ስናይፐር
3/ 18 _ ክላሽ
4/ 8700 _ የክላሽና የብሬን ተተኳሽ
5/ 108 _ ወታደራዊ ትጥቅ
6/ 4 _ የብሬን ሸንሸን ተማርኳል።
በውጊያው ያደረሰው ሰብዓዊ ኪሳራ
1) 70 ሙት
2) ከ30 በላይ የቆሰለ የአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት አባላት
በአጠቃላይ አውደ ውጊያው ከቀኑ 6:00ሰዓት የጀመረ እስከ ማታ ድረስ የዘለቀ ሲሆኑ የክፍለጦሩ አመራሮች እና አባላት በሳል አመራርነት እና የጀግንነት ፍልሚያ የታየበት ነበር።
መደምሰስ እና መማረክ ልምዱ የሆነው ጎጃም አገው ምድር ክፍለጦር በየ አውደ ውጊያው በሚፈጽመው መብረቃዊ ጥቃት የማህመድ ተሰማን ቅስም ሰብሯል።
ዘመቻ ሰማዕታት ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ክብር ለሰማዕታት !!
😁1
ምስራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ስሬና ጉቶ ጊዳ ወረዳ የሚኖሩ አማሮች ከፊታቸው ከባድ አደጋ መጋረጡንና ከዳርቻ አካባቢዎች መፈናቀል መጀመራቸውን ኗራዎች ለቢዛሞ ሚዲያ ተናገሩ።
ኗሪነታቸው ሲቡ ስሬና ጉቶ ጊዳ ወረዳዳዎች ልዩ ስሙ መዳሎ የሆኑት ነገደ አማራውያን ከአጎራባች ማለት ከዲጋና ከሳሲጋ ወረዳዎች የሚነሳ የኦነግ ሀይል ተደጋጋሚ ጥቃት ቢከፍትባቸውም ጥቃቱን ተቋቁመው ጥላትን አንገት በማስደፋት እስከ ዛሬ ድረስ እራሳቸውን ከአጥፊው ቡድን በመከላከል ቢቆዩም ሰሞኑን መከላከያ ወደ አካባቢው በመግባትና የአካባቢውን አርሶ አደር ትጥቅ እዬቀማ መሆኑን ተከትሎ የአካባቢው ኗሪዎች ወደፊት ለፍተኛ አደጋ መጋለጣቸውን ለቢዛሞ ሚዲያ ተናግረዋል።
የአካባቢው ኗሪዎች መከላከያ ወደ አካባቢያችን በመግባት ለሳምንት መሳርያ ያለውን እያሳደደ እዬቀማና በከፊል አካባቢውን ለቆ እዬወጣ መሆኑን ተከትሎ ከአጎራባች ወረዳዎች ኦነግ ሀይሉን አሰባስቦ ተጠግቶናል እንዲሁም ዳርቻ አካባቢዎችን ህዝቡ እዬለቀቀ ወደ ምሃል መግባት መጀመሩን ነው የአካባቢው ኗሪዎች ለቢዛሞ ሚዲያ የገለጹት።
በተያያዘ ዜና ምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ ከአንዶዴ ዲቾ ወደ አሊ ምንም አይነት ትራንስፖርት እንዳይደረግ በብልጽግና ሚኒሾች መታገዱን የከተማዋ ኗሪዎች ለቢዛሞ ሚዲያ ገልጸዋልና ከአሊ አንዶዴ እንዲሁም ከአንዶዴ አሊ እንቅስቃሴ የምታደርጉ ወገኖቻችን አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ በቢዛሞ ሚዳያ ስም ጥርያችንን እናቀርባለን።
ነሐሴ 23/2017ዓ.ም
ቢዛሞ ሚዲያ
ኗሪነታቸው ሲቡ ስሬና ጉቶ ጊዳ ወረዳዳዎች ልዩ ስሙ መዳሎ የሆኑት ነገደ አማራውያን ከአጎራባች ማለት ከዲጋና ከሳሲጋ ወረዳዎች የሚነሳ የኦነግ ሀይል ተደጋጋሚ ጥቃት ቢከፍትባቸውም ጥቃቱን ተቋቁመው ጥላትን አንገት በማስደፋት እስከ ዛሬ ድረስ እራሳቸውን ከአጥፊው ቡድን በመከላከል ቢቆዩም ሰሞኑን መከላከያ ወደ አካባቢው በመግባትና የአካባቢውን አርሶ አደር ትጥቅ እዬቀማ መሆኑን ተከትሎ የአካባቢው ኗሪዎች ወደፊት ለፍተኛ አደጋ መጋለጣቸውን ለቢዛሞ ሚዲያ ተናግረዋል።
የአካባቢው ኗሪዎች መከላከያ ወደ አካባቢያችን በመግባት ለሳምንት መሳርያ ያለውን እያሳደደ እዬቀማና በከፊል አካባቢውን ለቆ እዬወጣ መሆኑን ተከትሎ ከአጎራባች ወረዳዎች ኦነግ ሀይሉን አሰባስቦ ተጠግቶናል እንዲሁም ዳርቻ አካባቢዎችን ህዝቡ እዬለቀቀ ወደ ምሃል መግባት መጀመሩን ነው የአካባቢው ኗሪዎች ለቢዛሞ ሚዲያ የገለጹት።
በተያያዘ ዜና ምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ ከአንዶዴ ዲቾ ወደ አሊ ምንም አይነት ትራንስፖርት እንዳይደረግ በብልጽግና ሚኒሾች መታገዱን የከተማዋ ኗሪዎች ለቢዛሞ ሚዲያ ገልጸዋልና ከአሊ አንዶዴ እንዲሁም ከአንዶዴ አሊ እንቅስቃሴ የምታደርጉ ወገኖቻችን አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ በቢዛሞ ሚዳያ ስም ጥርያችንን እናቀርባለን።
ነሐሴ 23/2017ዓ.ም
ቢዛሞ ሚዲያ
😁1
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና ደ/በላይ ዘለቀ እዝ ፩ኛ ኮር የጣና ገላውዴዎስ ክፍለ ጦር የ2018 ዓ.ም ትምህርት ለማስጀመር በዛሬው ዕለት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት አደረገ!
ይህውም በደራ ወረዳ ሙሉ የቀጠናውን መ/ር/ሱ ፣ ወ/መ/ህ ፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች ፣ ወጣቶችና ከየቀጠናው ያሉ የማህረሰብ ተወካይ ነዋሪዎች በተገኙበት: በመንግስት ተብየው ፀረ_አምሓራ ወራሪ ኃይል ለሁለት አመት ተቋርጦ የነበረውን ትምህርት በ2018ዓ.ም ለማስጀመር ትልቅ መድረክ በመፍጠር ዝርዝር ጉዳዮችን በሚገባ ነቅሶ መወያየት ተችሏል።
መድረኩን ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር ከ2000 በላይ ታዳሚዎች የተሳተፉበትና ከተቀመጡት ውጭ ለ4 ሰአት አዳራሽ ውስጥና ውጭ ታግሰው የተወያዩ የጠየቁና ያዳመጡ ሀገር ወዳድ ምሁራን መኖራቸው ነው።
በተቋማችን በኩልም የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና አመራሮች ፣ የጣና ገላውዴዎስ ክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የአምበሶና አፈረዋናት ብርጌድ አመራሮች የተገኙበት ሲሆን አፄ ገላውዴዎስ ሻለቃ አመራሮችም ተሳትፈውበታል።
በተከበረው ትልቅ መድረካችን የተገኙት ባለድርሻ አካላትም ትምህርት ከየትኛውም የፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ ሁኖ እንዲሰጥ የተናገሩ ሲሆን በጣና ገላውዴዎስ ክፍለ ጦር ተቋም በኩል ሊደረግላቸው የሚገቡ ድጋፎችን ጠይቀው ምላሽ አግኝተዋል።
በተጨማሪም ከምዝገባ እስከ መማር ማስተማር ሂደቱ እንዴት እናስቀጥል በሚለው አጀንዳ ላይ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተው የመፍትሔ አቅጣጫዎች የተሰጡ ሲሆን በጠያቂዎች በኩል የሚጠበቅባቸው ጉዳይ መኖሩንም ማሳዎቅ ተችሏል።
እስካሁን በፋኖ ቁጥጥር ስር ያሉ ትምህርት ቤቶች ደህንነታቸው ተጠብቆ መቆየቱን ሲገነዘቡ በአብይ ጥምር ጦር ወራሪ ሀይል ስር ወድቀው የቆዩት ተቋማት በሙሉ መውደማቸውን እንዳረጋገጡ አያይዘው ገልፀዋል።
በመጨረሻም በመሪ ድርጅታችን አፋብኃ ሰ/አ/ቀ/ደ/በ/ዘ/እ/፩ኛ/ኮ/ በወረደልን መርህ መሰረት በጣናገላውዴዎስ ክፍለጦር ተቋም ኃላፊነት የማንወስድባቸው ጉዳዮችና በተቋማችን የሚከለከሉ ነገሮች በአጭሩ የተገለፁ ሲሆን ድጋፋችንን በተመለከተም በተረዱበት ልክ ተነጋግረን በጥብቅ በመግባባት መድረኩ ተጠናቋል።
ፋኖ ሙሉቀን አለኸኝ
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ ፩ኛ ኮር የጣናገላውዴዎስ ክፍለጦር ዋና ሰብሳቢ
ይህውም በደራ ወረዳ ሙሉ የቀጠናውን መ/ር/ሱ ፣ ወ/መ/ህ ፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች ፣ ወጣቶችና ከየቀጠናው ያሉ የማህረሰብ ተወካይ ነዋሪዎች በተገኙበት: በመንግስት ተብየው ፀረ_አምሓራ ወራሪ ኃይል ለሁለት አመት ተቋርጦ የነበረውን ትምህርት በ2018ዓ.ም ለማስጀመር ትልቅ መድረክ በመፍጠር ዝርዝር ጉዳዮችን በሚገባ ነቅሶ መወያየት ተችሏል።
መድረኩን ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር ከ2000 በላይ ታዳሚዎች የተሳተፉበትና ከተቀመጡት ውጭ ለ4 ሰአት አዳራሽ ውስጥና ውጭ ታግሰው የተወያዩ የጠየቁና ያዳመጡ ሀገር ወዳድ ምሁራን መኖራቸው ነው።
በተቋማችን በኩልም የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና አመራሮች ፣ የጣና ገላውዴዎስ ክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የአምበሶና አፈረዋናት ብርጌድ አመራሮች የተገኙበት ሲሆን አፄ ገላውዴዎስ ሻለቃ አመራሮችም ተሳትፈውበታል።
በተከበረው ትልቅ መድረካችን የተገኙት ባለድርሻ አካላትም ትምህርት ከየትኛውም የፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ ሁኖ እንዲሰጥ የተናገሩ ሲሆን በጣና ገላውዴዎስ ክፍለ ጦር ተቋም በኩል ሊደረግላቸው የሚገቡ ድጋፎችን ጠይቀው ምላሽ አግኝተዋል።
በተጨማሪም ከምዝገባ እስከ መማር ማስተማር ሂደቱ እንዴት እናስቀጥል በሚለው አጀንዳ ላይ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተው የመፍትሔ አቅጣጫዎች የተሰጡ ሲሆን በጠያቂዎች በኩል የሚጠበቅባቸው ጉዳይ መኖሩንም ማሳዎቅ ተችሏል።
እስካሁን በፋኖ ቁጥጥር ስር ያሉ ትምህርት ቤቶች ደህንነታቸው ተጠብቆ መቆየቱን ሲገነዘቡ በአብይ ጥምር ጦር ወራሪ ሀይል ስር ወድቀው የቆዩት ተቋማት በሙሉ መውደማቸውን እንዳረጋገጡ አያይዘው ገልፀዋል።
በመጨረሻም በመሪ ድርጅታችን አፋብኃ ሰ/አ/ቀ/ደ/በ/ዘ/እ/፩ኛ/ኮ/ በወረደልን መርህ መሰረት በጣናገላውዴዎስ ክፍለጦር ተቋም ኃላፊነት የማንወስድባቸው ጉዳዮችና በተቋማችን የሚከለከሉ ነገሮች በአጭሩ የተገለፁ ሲሆን ድጋፋችንን በተመለከተም በተረዱበት ልክ ተነጋግረን በጥብቅ በመግባባት መድረኩ ተጠናቋል።
ፋኖ ሙሉቀን አለኸኝ
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ ፩ኛ ኮር የጣናገላውዴዎስ ክፍለጦር ዋና ሰብሳቢ
🙏6❤2
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይልና አፋብኃ እና የአማራ ፋኖ በጎጃም አሃዶች በጥምረት የጠላትን ምሽግ ሰበሩ!!
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ ፪ኛ ኮር
በሊበን ወረዳ ሰሜን አሸፈር በተለምዶ ዳርፉር የተሰኘች ከተማና በአቅራቢያ በሚገኘው ግመል ተራራ ሰፍሮ የነበረውን የጠላት ዓብይ አህመድ ሰራዊት የአፋብኃ በላይ ዘለቀ ዕዝ አድዋ ክ/ጦርና የአፋጎ ቢትወደድ አያሌው ብርጌድ በጥምረት ከሌሊቱ 10:00 እስከ ረፋዱ 4:00 ሰዓት በተደረገ 6 ሰዓታት የፈጀ አውደ ውጊያ የጠላት ቋሚ የመከላከል ምሽጎቹ ተደርምሰዋል።
የአገዛዙ ሰራዊት ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ የደረሰበት ሲሆን የወታደራዊ ግብዓቶችም ተማርከዋል።
አድዋ ክ/ጦርና ቢትወደድ አያሌው ብርጌድ በትስስር እና በጥምረት በወሰዱት ወታደራዊ ማጥቃት ከሊበን አቅጣጫ የሚነቃነቅ ጠላትን የቢትወደድ አዳነ ብርጌድ በተጨማሪ በመዝጋት የአድዋ ክ/ጦር ንጋት ጮራ ብርጌድና የቢትወደድ አያሌው ቀሪ ሻለቆች ሙሉ ትኩረታቸው ምሽጉን መስበር ላይ አድርገው ብርቱ ውጊያ በጠላት ቁጥጥር ስር የነበሩትን በተለምዶ ዳርፉር ተብላ የምትጠራ አነስተኛ ከተማ እና ጠንካራው የግመል ተራራ ምሽግ በጥምር ሰራዊቱ ቁጥጥር ስር ገብተዋል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
በላይ ዘለቀ ዕዝ
ነሃሴ 24/2017 ዓ.ም
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ ፪ኛ ኮር
በሊበን ወረዳ ሰሜን አሸፈር በተለምዶ ዳርፉር የተሰኘች ከተማና በአቅራቢያ በሚገኘው ግመል ተራራ ሰፍሮ የነበረውን የጠላት ዓብይ አህመድ ሰራዊት የአፋብኃ በላይ ዘለቀ ዕዝ አድዋ ክ/ጦርና የአፋጎ ቢትወደድ አያሌው ብርጌድ በጥምረት ከሌሊቱ 10:00 እስከ ረፋዱ 4:00 ሰዓት በተደረገ 6 ሰዓታት የፈጀ አውደ ውጊያ የጠላት ቋሚ የመከላከል ምሽጎቹ ተደርምሰዋል።
የአገዛዙ ሰራዊት ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ የደረሰበት ሲሆን የወታደራዊ ግብዓቶችም ተማርከዋል።
አድዋ ክ/ጦርና ቢትወደድ አያሌው ብርጌድ በትስስር እና በጥምረት በወሰዱት ወታደራዊ ማጥቃት ከሊበን አቅጣጫ የሚነቃነቅ ጠላትን የቢትወደድ አዳነ ብርጌድ በተጨማሪ በመዝጋት የአድዋ ክ/ጦር ንጋት ጮራ ብርጌድና የቢትወደድ አያሌው ቀሪ ሻለቆች ሙሉ ትኩረታቸው ምሽጉን መስበር ላይ አድርገው ብርቱ ውጊያ በጠላት ቁጥጥር ስር የነበሩትን በተለምዶ ዳርፉር ተብላ የምትጠራ አነስተኛ ከተማ እና ጠንካራው የግመል ተራራ ምሽግ በጥምር ሰራዊቱ ቁጥጥር ስር ገብተዋል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
በላይ ዘለቀ ዕዝ
ነሃሴ 24/2017 ዓ.ም
❤5🙏1
ኢትዮጵያ፣ ከዓለም ሀገሮች በቀዳሚነት ህዝቦቿ በሰላም እጦት የሚሰቃዩባት ዋና ሀገር ተባለች‼️
ኢትዮጵያ በዓለም 2025 መዘርዝር ዝቅተኛ ሰላም ያለባት ሀገር ተባለች
ዓለም አቀፉ የምጣኔ ሀብት እና የሰላም ጥናት ተቋም (IEP) ባወጣው ዓመታዊ "ዓለም አቀፍ የሰላም መረጃ ጠቋሚ" ዘገባ ኢትዮጵያ ደካማ የሰላም ሁኔታ ያላት ሀገር መሆንዋን ገለፀ። በዚህ መሰረት በዚህ ዓመት ከተመለከታቸው 163 ሀገራት ውስጥ ኢትዮጵያ 138ኛ ደረጃ ላይ ስትቀመጥ ኤርትራ በ132ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
ኢትዮጵያ በዓለም 2025 መዘርዝር ዝቅተኛ ሰላም ያለባት ሀገር ተባለች
ዓለም አቀፉ የምጣኔ ሀብት እና የሰላም ጥናት ተቋም (IEP) ባወጣው ዓመታዊ "ዓለም አቀፍ የሰላም መረጃ ጠቋሚ" ዘገባ ኢትዮጵያ ደካማ የሰላም ሁኔታ ያላት ሀገር መሆንዋን ገለፀ። በዚህ መሰረት በዚህ ዓመት ከተመለከታቸው 163 ሀገራት ውስጥ ኢትዮጵያ 138ኛ ደረጃ ላይ ስትቀመጥ ኤርትራ በ132ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
ዝክረ ሻለቃ ኃይለእየሱስ አድማሱ(ሻለቃ ኃይሌ)
🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸
ሻለቃ ኃይለእየሱስ አድማሱ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ ሻፍራ ዳውሪት ቀበሌ ሐምሌ 3/1984 ዓም ተወለደ። ሻለቃ ኃይሌ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነው ክርስቲያን ታደለ ከተማረበት ሀሙስ ወንዝትምህርት ቤት የተማረ ጀግና ኮከብ ተሸላሚ ተማሪ ነበረ፣
የአባ ኮስትር መዲና በሆነችው ጎጃም የተወለደው ሻለቃ ኃይሌ የጀኔራል አሳምነውን ጽጌ ጥሪ በመቀበል ከአድማ ብተና ወደ አማራ ልዩ ኃይል በመቀላቀል በሰሜኑ ጦርነት :-
በወልድያ፣በላሊበላ፣በአላማጣ፣በራያ፣በጋሸና፣በደሴ፣በኮምቦልቻ፣በመካነሰላም፣በደብረታቦር፣በጋይንት እና በሌሎች ግንባሮች በመዋጋት ታላቅ ጀብድ ሲሆን ህወሀት ዳግመኛ አማራ ክልልን በወረረ ጊዜ ሻለቃ ኃይሌ የወሎ ፋኖን በመያዝ አላውሀ፤ ጎብዬ ላይ የጠላትን ምሽግ በመሰባበር 5 ክላሽ፣አንድ የጦር መነጸር እና አንድ የሬዲዮ መገናኛ የማራከ ዳግማዊ በላይ ዘለቀ ነው።
ሻለቃ ኃይሌ በአማራ ህዝብ ላይ እየተሰራ ያለውን ግፍና መከራ በመረዳት ከሰሜን ወሎ ወደ ተወለደበት ምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ በመመለስ፤ የአባቱን የጀኔራል አሳምነው ጽጌን አደራ ለማስፈጸም በበወረዳው ባሉ 33 ቀበሌዎች በመዘዋወር ማህበረሰቡን የማንቃት ስራ ሰርቷል፣በራሪ ወረቀቶችን በመበተን ወጣቱን በመመዝገብ ያደራጀ ሲሆን በዚህ እንቅስቃሴው የወረዳው የብልጽግና ቡድን አይን ውስጥ ገባ፤ ጥርስም ተነከሰበት።
👉አርበኛ ጌራ ወርቁ * ሞትን ድል ያደረገ ትዉልድ * በሚለው ጦማሩ ፡-
የሻለቃ ኃይሌ አድማሱ፦ ፀጉሩን በአጭሩ የሚስተካከል፣ ብዙዉን ጊዜ ኮፍያ የሚያዘወትር፣ የኮፍያዉን ጫፍ ወደ አይኑ አዉርዶ የሚለብስ፣ አፍንጫዉ ሰልካካ የሚባል፣ ቁመቱ መካከለኛ፣ ቀጭን ደርባባ ሰዉነት ያለዉ፣ ፈጣን፣ እድሜዉ እስከ ሰላሳ ባለዉ የሚገመት ወጣት ነዉ።
በሁሉም ዘርፍ፦ ፍጥነት ኃይሌ አድማሱ ልክ የለም፤ መንገድ እንኳን ሲጓዝ ከእሱ ጋር መጓዝ ልብን ማዉለቅ ነዉ። ኃይሌ ጊዜ የለህም የተባለ ይመስል በሁሉም ነገር መፍጠንን ይወዳል። በሚፈልገዉ ልክ ነገሮች ካልሆኑለት፥ አንድ ልዩ ምልክት ይሰጣል፤ ሽርጡን ተከናንቦ እስከ አፍንጫዉ ማጣፋት። ኃይሌ በሽርጡ አፍንጫዉን ከሸፈነ ከፍቶታል ማለት ነዉ። ኃይሌ የወንድ ልክ፤ ከግንባሩ ወደ አፍንጫዉ የሚወርደዉ የወንድነት ሸንተረሩ ሁሌም የተቋጠረ ወንድ ነዉ።
በዉጊያ ወቅት "መሬት እናት ናት" የሚለዉ አስተምህሮ ለሀይሌ አይሰራም፤ ዉጊያ ሲጀመር ጀምሮ የቆመ፣ ቲንሽ እንኳን ሸብረክ ሳይል "በለዉ፣ ያዘዉ፣ ትሰደዉና...." እንዳለ ዉጊያዉን ይጨርሳል። ኃይሌ ተሸንፎ የሚሮጥን ጠላት ከኋላ መምታት አይፈልግም። ከቻለ አሩጦ ይይዘዋል፣ ካልያ መምታት እየቻለ ይተወዋል።
ቡሬ 'ዉንድጊ' ላይ በነበረዉ 07/12/2015 የዕለተ እሁድ ዉጊያ፦ ከመስመር በእስተ ምስራቅ የሻለቃ እንደሻዉ ጌታነህ የሚመራዉ ጦር ጠላትን ደምስሶ ወደ ፊት ሲነቃነቅ፤ ከእንደሻዉ ወደ ምዕራብ ካለዉ ሸንተረር ላይ ጀግናው አንዷለም አሳብነህ እየፎከረ ሲተኩስ፤ መሀል አስፓልቱን ሻለቃ ኃይሌ እያፀዳ ሲወርድ፤ ከመስመር በቀኝ ያለዉን እኛ እየሸበለልን ስናጠቃ፤ ከእኛ ወደ ቀኝ የሁዲቱ ካሳ ወደፊት ሲገሰግስ፤ መስመር ዳር ባሉ ቤቶች ተደብቆ የነበረ አንድ ጠላት፥ ከተደበቀበት ወጥቶ ወደ ቡሬ አቅጣጫ አዉጭኝን እሮጠ " እንዳትመታዉ፣ አሩጠህ ከእነ ነፍሱ ያዘዉ " በማለት መምሪያ ይሰጥ እንደነበር ምስክርነቱን ገልጾልናል።
ሻለቃ ኃይሌ በሰከላ ወረዳ ህዝብ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የልጅ አዋቂ የሆነ ልበ ብርሃን፣ደፋር፣ቅን እና ቆራጥ የህዝብ ልጅ ነው።
ሻለቃ ኃይሌ ከ500 በላይ ወጣቶችን በመመልመል በግሽ አባይ ከተማ እና በሁሉም ቀበሌዎች ሲያሰለጥን የነበረ ሲሆን ሰልጣኝ ልጆቹን አይዟችሁ እኔ ሳልሞት እናንተ አትሞቱም በማለት በልበ ሙሉነት እንዲሰለጥኑ ያበረታታ ነበር። ሻለቃ ኃይሌ ከግዮን ብሮጌድ አልፎ ዘንገና ብርጌድ እና ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ እንዲመሰረትና እንዲጠናከር ያለሰለሰ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል።
ጀግናው በተቀነባበር በብልጽግና ሴራ ነሐሴ 24/2015 ለአማራ ህዝብ ሲል ተሰዋ።
🔹🔹🔹🔹🔹
ጀግናስ ተውት ይሙት መሞት ይገባዋል፣
ደሙ ያረፈበት ሽህ ጀግናን ያበቅላል።
🔹🔹🔹🔹🔹🔹
ሻለቃ ኃይሌ ቢሰዋም በእሱ መስዋዕትነት ሽህ ኃይሌዎች ተፈጥረዋል። ግዮን ብርጌድ የሰከላው ነብር የሻለቃ ኃይሌን አደራ በመረከብ በ5 ሻለቃዎች (ኃይለዬሱስ አድማሱ ሻለቃ፣መብረቁ ሻለቃ፣ናደው ሻለቃ፣አባግስ ሻለቃ እና ግትም ሻለቃ) በመደራጀት ጠላትን በመደምሰስ፣ክላሽ-ብሬል፣ ከእስናይፐር-እስከ ዲሽቃ፣ ከእግረኛ እስከ ሻለቃ እና ኮለኔል ድረስ የማረኩ አለምን ጉድ ያስባለ ታላቅ ጀብድ እየሰሩ ይገኛል።
ነፍስህን በአጸደ ገነት ያሳርፍልን
አደራህ አለብን የጀመርኸውን ትግል ከዳር ለማድረስ ቃል እንገባለን‼️
ድል ለተገፋው ለአማራ ህዝብ! ድል ለፋኖ‼️
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ‼️
ግዮን ብርጌድ
[ነሐሴ ፳፬/፳፻፲፯ ]
ጎጃም-ዓምሓራ
🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸
ሻለቃ ኃይለእየሱስ አድማሱ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ ሻፍራ ዳውሪት ቀበሌ ሐምሌ 3/1984 ዓም ተወለደ። ሻለቃ ኃይሌ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነው ክርስቲያን ታደለ ከተማረበት ሀሙስ ወንዝትምህርት ቤት የተማረ ጀግና ኮከብ ተሸላሚ ተማሪ ነበረ፣
የአባ ኮስትር መዲና በሆነችው ጎጃም የተወለደው ሻለቃ ኃይሌ የጀኔራል አሳምነውን ጽጌ ጥሪ በመቀበል ከአድማ ብተና ወደ አማራ ልዩ ኃይል በመቀላቀል በሰሜኑ ጦርነት :-
በወልድያ፣በላሊበላ፣በአላማጣ፣በራያ፣በጋሸና፣በደሴ፣በኮምቦልቻ፣በመካነሰላም፣በደብረታቦር፣በጋይንት እና በሌሎች ግንባሮች በመዋጋት ታላቅ ጀብድ ሲሆን ህወሀት ዳግመኛ አማራ ክልልን በወረረ ጊዜ ሻለቃ ኃይሌ የወሎ ፋኖን በመያዝ አላውሀ፤ ጎብዬ ላይ የጠላትን ምሽግ በመሰባበር 5 ክላሽ፣አንድ የጦር መነጸር እና አንድ የሬዲዮ መገናኛ የማራከ ዳግማዊ በላይ ዘለቀ ነው።
ሻለቃ ኃይሌ በአማራ ህዝብ ላይ እየተሰራ ያለውን ግፍና መከራ በመረዳት ከሰሜን ወሎ ወደ ተወለደበት ምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ በመመለስ፤ የአባቱን የጀኔራል አሳምነው ጽጌን አደራ ለማስፈጸም በበወረዳው ባሉ 33 ቀበሌዎች በመዘዋወር ማህበረሰቡን የማንቃት ስራ ሰርቷል፣በራሪ ወረቀቶችን በመበተን ወጣቱን በመመዝገብ ያደራጀ ሲሆን በዚህ እንቅስቃሴው የወረዳው የብልጽግና ቡድን አይን ውስጥ ገባ፤ ጥርስም ተነከሰበት።
👉አርበኛ ጌራ ወርቁ * ሞትን ድል ያደረገ ትዉልድ * በሚለው ጦማሩ ፡-
የሻለቃ ኃይሌ አድማሱ፦ ፀጉሩን በአጭሩ የሚስተካከል፣ ብዙዉን ጊዜ ኮፍያ የሚያዘወትር፣ የኮፍያዉን ጫፍ ወደ አይኑ አዉርዶ የሚለብስ፣ አፍንጫዉ ሰልካካ የሚባል፣ ቁመቱ መካከለኛ፣ ቀጭን ደርባባ ሰዉነት ያለዉ፣ ፈጣን፣ እድሜዉ እስከ ሰላሳ ባለዉ የሚገመት ወጣት ነዉ።
በሁሉም ዘርፍ፦ ፍጥነት ኃይሌ አድማሱ ልክ የለም፤ መንገድ እንኳን ሲጓዝ ከእሱ ጋር መጓዝ ልብን ማዉለቅ ነዉ። ኃይሌ ጊዜ የለህም የተባለ ይመስል በሁሉም ነገር መፍጠንን ይወዳል። በሚፈልገዉ ልክ ነገሮች ካልሆኑለት፥ አንድ ልዩ ምልክት ይሰጣል፤ ሽርጡን ተከናንቦ እስከ አፍንጫዉ ማጣፋት። ኃይሌ በሽርጡ አፍንጫዉን ከሸፈነ ከፍቶታል ማለት ነዉ። ኃይሌ የወንድ ልክ፤ ከግንባሩ ወደ አፍንጫዉ የሚወርደዉ የወንድነት ሸንተረሩ ሁሌም የተቋጠረ ወንድ ነዉ።
በዉጊያ ወቅት "መሬት እናት ናት" የሚለዉ አስተምህሮ ለሀይሌ አይሰራም፤ ዉጊያ ሲጀመር ጀምሮ የቆመ፣ ቲንሽ እንኳን ሸብረክ ሳይል "በለዉ፣ ያዘዉ፣ ትሰደዉና...." እንዳለ ዉጊያዉን ይጨርሳል። ኃይሌ ተሸንፎ የሚሮጥን ጠላት ከኋላ መምታት አይፈልግም። ከቻለ አሩጦ ይይዘዋል፣ ካልያ መምታት እየቻለ ይተወዋል።
ቡሬ 'ዉንድጊ' ላይ በነበረዉ 07/12/2015 የዕለተ እሁድ ዉጊያ፦ ከመስመር በእስተ ምስራቅ የሻለቃ እንደሻዉ ጌታነህ የሚመራዉ ጦር ጠላትን ደምስሶ ወደ ፊት ሲነቃነቅ፤ ከእንደሻዉ ወደ ምዕራብ ካለዉ ሸንተረር ላይ ጀግናው አንዷለም አሳብነህ እየፎከረ ሲተኩስ፤ መሀል አስፓልቱን ሻለቃ ኃይሌ እያፀዳ ሲወርድ፤ ከመስመር በቀኝ ያለዉን እኛ እየሸበለልን ስናጠቃ፤ ከእኛ ወደ ቀኝ የሁዲቱ ካሳ ወደፊት ሲገሰግስ፤ መስመር ዳር ባሉ ቤቶች ተደብቆ የነበረ አንድ ጠላት፥ ከተደበቀበት ወጥቶ ወደ ቡሬ አቅጣጫ አዉጭኝን እሮጠ " እንዳትመታዉ፣ አሩጠህ ከእነ ነፍሱ ያዘዉ " በማለት መምሪያ ይሰጥ እንደነበር ምስክርነቱን ገልጾልናል።
ሻለቃ ኃይሌ በሰከላ ወረዳ ህዝብ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የልጅ አዋቂ የሆነ ልበ ብርሃን፣ደፋር፣ቅን እና ቆራጥ የህዝብ ልጅ ነው።
ሻለቃ ኃይሌ ከ500 በላይ ወጣቶችን በመመልመል በግሽ አባይ ከተማ እና በሁሉም ቀበሌዎች ሲያሰለጥን የነበረ ሲሆን ሰልጣኝ ልጆቹን አይዟችሁ እኔ ሳልሞት እናንተ አትሞቱም በማለት በልበ ሙሉነት እንዲሰለጥኑ ያበረታታ ነበር። ሻለቃ ኃይሌ ከግዮን ብሮጌድ አልፎ ዘንገና ብርጌድ እና ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ እንዲመሰረትና እንዲጠናከር ያለሰለሰ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል።
ጀግናው በተቀነባበር በብልጽግና ሴራ ነሐሴ 24/2015 ለአማራ ህዝብ ሲል ተሰዋ።
🔹🔹🔹🔹🔹
ጀግናስ ተውት ይሙት መሞት ይገባዋል፣
ደሙ ያረፈበት ሽህ ጀግናን ያበቅላል።
🔹🔹🔹🔹🔹🔹
ሻለቃ ኃይሌ ቢሰዋም በእሱ መስዋዕትነት ሽህ ኃይሌዎች ተፈጥረዋል። ግዮን ብርጌድ የሰከላው ነብር የሻለቃ ኃይሌን አደራ በመረከብ በ5 ሻለቃዎች (ኃይለዬሱስ አድማሱ ሻለቃ፣መብረቁ ሻለቃ፣ናደው ሻለቃ፣አባግስ ሻለቃ እና ግትም ሻለቃ) በመደራጀት ጠላትን በመደምሰስ፣ክላሽ-ብሬል፣ ከእስናይፐር-እስከ ዲሽቃ፣ ከእግረኛ እስከ ሻለቃ እና ኮለኔል ድረስ የማረኩ አለምን ጉድ ያስባለ ታላቅ ጀብድ እየሰሩ ይገኛል።
ነፍስህን በአጸደ ገነት ያሳርፍልን
አደራህ አለብን የጀመርኸውን ትግል ከዳር ለማድረስ ቃል እንገባለን‼️
ድል ለተገፋው ለአማራ ህዝብ! ድል ለፋኖ‼️
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ‼️
ግዮን ብርጌድ
[ነሐሴ ፳፬/፳፻፲፯ ]
ጎጃም-ዓምሓራ
❤4
አገዛዙ ብልፅግና ባለፉት ሁለት አመታት በአስር ዙር ስልጠና አንድ ሚሊዮን የተጠጋ ሰራዊት አሰልጥኖ ወደ አማራ ክልል መግባቱ ይታወቃል።
በአራት መሰረታዊ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በ 24 ወራት ውስጥ 10 ዙር ወታደራዊ ስልጠና ተሰቷል።በብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት፣በዉርሶ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት፣በጦላይ እና በአዋሽ አርባ ስልጠናዉ የተሰጠ ሲሆን ስልጠነዉም በየሶስት ወሩ አሰልጥኖ በማስመረቅ ወደ አማራ ክልል አስገብቷል።
ዛሬ ነሀሴ 24/2017 ዓ.ም አገዛዙ በአራቱም ወታደራዊ ትምህርት ቤቶች ያሰለጠናቸውን ወታደሮች አስመርቂያለሁ ሲል አስታዉቋል።ይህ ስልጠና ለአስረኛ ጊዜ የተደረገ ስልጠና ነዉም ተብሏል።
በብርሸለቆ እና ዉርሶ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ብቻ ላለፉት 24 ወራት ከ20 ሺህ በላይ ሰራዊት በእያንዳንዱ ዙር ሰልጥነዉ የተመረቁ ሲሆን በጦላይ እና በዉርሶ ደግሞ ከ18 _20 ሺህ ሰራዊት በአስር ተከታታይ ዙር ስልጠነዉ ወደ አማራ ክልል ለግዳጅ ተልከዋል።ከዚህ በተጨማሪ በደብረዘይት በየአንዳንዱ ዞር ከ7 ሺህ በላይ ሰራዊት የአየር ሀይል ስልጠና የወሰደ ሲሆን በብላቴ ደግሞ ለ9 ተከታታይ ዙር የኮማንዶ፣የአየር ወለድ ፣እና የሪፐብሊካን ጋርድ አባላት በእያንዳንዱ ዙር 12ሺህ ሰራዊት ተመርቆ ወደ አማራ ክልል ገብቷል ።
በዚህ መሰረት በዉርሶ፣በብርሸለቆ፣በጦላይ እና በአዋሽ አርባ 786 ሺህ 653 ሰራዊት፣በደብረዘይት 72 ሺህ 441 እንዲሁም በብላቴ መሰረታዊ ዉትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት 111 ሺህ 923 እና 16ሺህ 301 የባህር ኃይል በአጠቃላይ 987 ሺህ 318 ሰራዊት አሰልጥኖ ወደ አማራ አስገብቷል።ከዚህ ውስጥ 65 በመቶ የሚሆነዉ በፋኖ የተደመሰሰ እና ከአገዛዙ አገልጋይነት በመዉጣት የፋኖ ሀይሎችን እና የሸኔ ታጣቂዎችን እንዲሁም ቤተሰቦቻቸዉን ተቀላቅለዋል።
መረጃዉ የመከላከያ ሰዉ ሀብት አስተዳደር ነዉ!!!
@ግሎባል ፋኖ ሚዲያ!
የፋኖ ተቀዳሚ ድምፅ!!!
በአራት መሰረታዊ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በ 24 ወራት ውስጥ 10 ዙር ወታደራዊ ስልጠና ተሰቷል።በብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት፣በዉርሶ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት፣በጦላይ እና በአዋሽ አርባ ስልጠናዉ የተሰጠ ሲሆን ስልጠነዉም በየሶስት ወሩ አሰልጥኖ በማስመረቅ ወደ አማራ ክልል አስገብቷል።
ዛሬ ነሀሴ 24/2017 ዓ.ም አገዛዙ በአራቱም ወታደራዊ ትምህርት ቤቶች ያሰለጠናቸውን ወታደሮች አስመርቂያለሁ ሲል አስታዉቋል።ይህ ስልጠና ለአስረኛ ጊዜ የተደረገ ስልጠና ነዉም ተብሏል።
በብርሸለቆ እና ዉርሶ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ብቻ ላለፉት 24 ወራት ከ20 ሺህ በላይ ሰራዊት በእያንዳንዱ ዙር ሰልጥነዉ የተመረቁ ሲሆን በጦላይ እና በዉርሶ ደግሞ ከ18 _20 ሺህ ሰራዊት በአስር ተከታታይ ዙር ስልጠነዉ ወደ አማራ ክልል ለግዳጅ ተልከዋል።ከዚህ በተጨማሪ በደብረዘይት በየአንዳንዱ ዞር ከ7 ሺህ በላይ ሰራዊት የአየር ሀይል ስልጠና የወሰደ ሲሆን በብላቴ ደግሞ ለ9 ተከታታይ ዙር የኮማንዶ፣የአየር ወለድ ፣እና የሪፐብሊካን ጋርድ አባላት በእያንዳንዱ ዙር 12ሺህ ሰራዊት ተመርቆ ወደ አማራ ክልል ገብቷል ።
በዚህ መሰረት በዉርሶ፣በብርሸለቆ፣በጦላይ እና በአዋሽ አርባ 786 ሺህ 653 ሰራዊት፣በደብረዘይት 72 ሺህ 441 እንዲሁም በብላቴ መሰረታዊ ዉትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት 111 ሺህ 923 እና 16ሺህ 301 የባህር ኃይል በአጠቃላይ 987 ሺህ 318 ሰራዊት አሰልጥኖ ወደ አማራ አስገብቷል።ከዚህ ውስጥ 65 በመቶ የሚሆነዉ በፋኖ የተደመሰሰ እና ከአገዛዙ አገልጋይነት በመዉጣት የፋኖ ሀይሎችን እና የሸኔ ታጣቂዎችን እንዲሁም ቤተሰቦቻቸዉን ተቀላቅለዋል።
መረጃዉ የመከላከያ ሰዉ ሀብት አስተዳደር ነዉ!!!
@ግሎባል ፋኖ ሚዲያ!
የፋኖ ተቀዳሚ ድምፅ!!!
❤2🙏2
ጥብቅ የማስጠንቀቂያ መልዕክት ለጎንደር ዮኒቨርሲቲ!
በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ የቆየውንና ተባብሶ የቀጠለውን ስርዓትና መዋቅር መራሽ የህልውና አደጋ ለመቀልበስ ከሁለት ዓመታት በላይ በትጥቅ ትግል የአማራ ፋኖ ፋሽስታዊ አረመኔ አገዛዙን እያፈራረሰው ይገኛል።
ሆኖም በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዳ/ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር ቀጠና ስር የሚገኘው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በማስተማሪያ ካምፓሶቹ ከመደበኛ ተግባሩ ውጭ የዓብይ አገዛዝ ለንፁሃን ማጎሪያነት፣ለወታደራዊ ምሽግነት፣ለወታደራዊ ማሰልጠኛነት፣ለፖለቲካዊ ርካሽ ተግባራት አገልግሎት እየዋሉ ይገኛል።ድርጊቱ መላ ህዝባችን እያስከፋ ይገኛል።
ስለሆነም ከዚህ እኩይ ድርጊቱ እንዲቆጠብ የተሰጠውን ምክርና ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት በሁሉም ካምፓሶቹ የህልውና ትግሉን በግልፅ ከመፃረሩ በላይ ቅርብ ቀናት ከተለያዩ ቦታዎች በግድም በውድ ታፍሰው የመጡ "የቀድሞ ፀረ ሰላም ኃይሎች" የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ወገኖች በጎንደር ዮኒቨርሲቲ ጠዳ ካምፓስ ለማጎር በዝግጅት ላይ እንዳላችሁ ተደርሶበታል።
ከመደበኛ ተልዕኳችሁ በማፈንገጥ የአማራ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ ዘር ተኮር የጦር ወንጀል ቀጥተኛ ተሳታፊ ከመሆን ትቆጠቡ ዘንድ እያስጠነቀቅን ማስጠንቀቂያውን ተላልፎ ከተገኘና ጠላትን ከማስተማርያ ክልሉ ካላራቀ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ለሚገጥሙት ችግሮች ኃላፊነቱን የማይወስድ መሆኑን ያሳውቃል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
ዳ/ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር
ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም
በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ የቆየውንና ተባብሶ የቀጠለውን ስርዓትና መዋቅር መራሽ የህልውና አደጋ ለመቀልበስ ከሁለት ዓመታት በላይ በትጥቅ ትግል የአማራ ፋኖ ፋሽስታዊ አረመኔ አገዛዙን እያፈራረሰው ይገኛል።
ሆኖም በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዳ/ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር ቀጠና ስር የሚገኘው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በማስተማሪያ ካምፓሶቹ ከመደበኛ ተግባሩ ውጭ የዓብይ አገዛዝ ለንፁሃን ማጎሪያነት፣ለወታደራዊ ምሽግነት፣ለወታደራዊ ማሰልጠኛነት፣ለፖለቲካዊ ርካሽ ተግባራት አገልግሎት እየዋሉ ይገኛል።ድርጊቱ መላ ህዝባችን እያስከፋ ይገኛል።
ስለሆነም ከዚህ እኩይ ድርጊቱ እንዲቆጠብ የተሰጠውን ምክርና ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት በሁሉም ካምፓሶቹ የህልውና ትግሉን በግልፅ ከመፃረሩ በላይ ቅርብ ቀናት ከተለያዩ ቦታዎች በግድም በውድ ታፍሰው የመጡ "የቀድሞ ፀረ ሰላም ኃይሎች" የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ወገኖች በጎንደር ዮኒቨርሲቲ ጠዳ ካምፓስ ለማጎር በዝግጅት ላይ እንዳላችሁ ተደርሶበታል።
ከመደበኛ ተልዕኳችሁ በማፈንገጥ የአማራ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ ዘር ተኮር የጦር ወንጀል ቀጥተኛ ተሳታፊ ከመሆን ትቆጠቡ ዘንድ እያስጠነቀቅን ማስጠንቀቂያውን ተላልፎ ከተገኘና ጠላትን ከማስተማርያ ክልሉ ካላራቀ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ለሚገጥሙት ችግሮች ኃላፊነቱን የማይወስድ መሆኑን ያሳውቃል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
ዳ/ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር
ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም
🙏4❤2👏2
የአገዛዙ ጥምር ሀይል ከጎንደር ወደ ገንዳውሀ ሲንቀሳቀስ በምዕራብ ጎንደር መተማ ወረዳ ኩመራ አውላላ ላይ በደፈጣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሙት እና ቁስለኛ ሊሆን ችሏል።
በትናንትናው እለት ነሐሴ 23/2017 የአገዛዙ ጥምር ሀይል መነሻውን ጎንደር በማድረግ በጭልጋ ወረዳ በአይከል ከተማ አድርጎ መዳረሻውን ምዕራብ ጎንደር መተማ ወረዳ ገንዳውሀ በማድረግ ማርተር፣ ዙ-23 እና ዲሽቃ ታጥቆ ሲንቀሳቀስ ኩመራ አውላላ ላይ ደፈጣ በማድረግ ከቀኑ 10:00 ስዓት ገደማ አፋብሀ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ 2ኛ ኮር ፊታውራሪ ገበየሁ ክ/ጦ ላመነው ብርጌድ ንስር ሻለቃ በአርበኛ ደርሶ ጌጡ እየተመራ ረመጥ ሻለቃ በአርበኛ ሩፌ ፈንታቢል መሪነት ሁለቱን ሻለቃዎች በማጣመር የክ/ጦሩ ም/ዘመቻ መሪ አርበኛ ደርሴ አጉማስ ባደረጉት ልዩ ኦፕሬሽን በጀግኖች የአማራ የቁርጥ ልጆች ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል።
በዚህ ልዩ ኦፕሬሽን የተገኘ ድል: ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሙትና ቁስለኛ ከመሆኑ ባሻገር አስክሬኑን ጥሎ እግሬ አውጭኝ በማለቱ የአካባቢው ነዋሪ እስከ ነሀሴ 24/2017 ድረስ በርካታ ቁጥር
ያለው ሙት በጡርንባ ወጦ ተቀብሯል።
10 የነፍስ ወከፍ ክላሽ እስከ ሙሉ ትጥቁ ለማንሳት ተችሏ።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
ፋኖ መ/ር አስተውል አምሳሉ
አፋብሀ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ 2ኛ ኮር የህ/ግ
በትናንትናው እለት ነሐሴ 23/2017 የአገዛዙ ጥምር ሀይል መነሻውን ጎንደር በማድረግ በጭልጋ ወረዳ በአይከል ከተማ አድርጎ መዳረሻውን ምዕራብ ጎንደር መተማ ወረዳ ገንዳውሀ በማድረግ ማርተር፣ ዙ-23 እና ዲሽቃ ታጥቆ ሲንቀሳቀስ ኩመራ አውላላ ላይ ደፈጣ በማድረግ ከቀኑ 10:00 ስዓት ገደማ አፋብሀ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ 2ኛ ኮር ፊታውራሪ ገበየሁ ክ/ጦ ላመነው ብርጌድ ንስር ሻለቃ በአርበኛ ደርሶ ጌጡ እየተመራ ረመጥ ሻለቃ በአርበኛ ሩፌ ፈንታቢል መሪነት ሁለቱን ሻለቃዎች በማጣመር የክ/ጦሩ ም/ዘመቻ መሪ አርበኛ ደርሴ አጉማስ ባደረጉት ልዩ ኦፕሬሽን በጀግኖች የአማራ የቁርጥ ልጆች ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል።
በዚህ ልዩ ኦፕሬሽን የተገኘ ድል: ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሙትና ቁስለኛ ከመሆኑ ባሻገር አስክሬኑን ጥሎ እግሬ አውጭኝ በማለቱ የአካባቢው ነዋሪ እስከ ነሀሴ 24/2017 ድረስ በርካታ ቁጥር
ያለው ሙት በጡርንባ ወጦ ተቀብሯል።
10 የነፍስ ወከፍ ክላሽ እስከ ሙሉ ትጥቁ ለማንሳት ተችሏ።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
ፋኖ መ/ር አስተውል አምሳሉ
አፋብሀ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ 2ኛ ኮር የህ/ግ
❤1👍1🙏1