ዓለም አቀፍ ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.39K subscribers
4.12K photos
329 videos
17 files
2.15K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
እዋዋ ጎቤን የዘነገዉ ዝክረ ወልቃይት የሚል ዝባዝንኬ በወልቃይት ሲከናወን ትልቅ ትዝብትን ይፈጥራል!!!
በ803ኛ ኮር 61ኛ ክ/ጦር ስር የ1ኛ ሻምበል አዛዡ ከነሙሉ ትጥቁ ፋኖን ተቀላቀለ!

በሰሜን ምስራቅ ዕዝ 803ኛ ኮር 61ኛ ክፍለ ጦር 3ኛ ሬጅመንት የ1ኛ ሻምበል አዛዡ አስር አለቃ ሸጋው ንጉስ ከነ ሙሉ ትጥቁ የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ስር የሚገኘው ላስታ ጄነራል አሣምነው ፅጌ ኮርን መቀላቀሉን የመረብ ሚዲያ ዘጋቢዎች በስፍራው ተገኝተው ተመልክተዋል።

የሻምበል አዛዡ አስር አለቃ ሸጋው፡ ፋኖ ወዳለበት ቀጠና ሲደርስ የላስታ ጀኔራል አሣምነው ፅጌ ኮር ምክትል አዛዥ አርበኛ ኮማንዶ ፍቅሩ ሙልየ እና የኮሩ ፋይናንስ ኃላፊ አርበኛ ሲሳይ ተስፋው እንዲሁም የኮሩ የፖለቲካ ዘርፍ መኮነን አርበኛ ግርማ ቅባቴና ሌሎች የኮሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

በተደረገለት ደማቅ አቀባበል የተሰማውን ልባዊ ደስታ የገለፀው የሻምበል አዛዡ አስር አለቃ ሸጋው ንጉስ፡ ሌሎች የመከላከያ ሰራዊት አዛዦችና አባላት አገዛዙ በአማራ ሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍና መከራን በመቃዎም ከፋኖ ጎን እንዲሰለፉ ጥሪ አቅርቧል።
👍5
ከአረመኔው አገዛዝ እየከዱ ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው የአማራ ፋኖ በጎጃም ሶስት ክፍለጦሮችን የተቀላቀሉ ዝርዝር :-

1/ ከአረመኔው አገዛዝ በመክዳት ሐዲስ ዓለማየሁ ሰባተኛ  ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ የአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት አባላት የነበሩ አባላት
       አድማ ብተና
1.ዮሐንስ ይንገስ---ተድላ ንሉ
2.ቢኒያም ተስፋዬ---ተድላ ጓሉ
             መከላከያ
3.ደሴ ገደፋው --አብራጂት
4.ፈንታው ገደፋው--አብራጂት
5.ሞገስ መና ----አብራጂት
6.አብርሃም ቻሌ---መብረቁ
7.ደርብ በላይ-----መብረቁ
8.ተሾመ ደረጀ---መብረቁ
9.ደሴ ቢቀላ----መብረቁ
             ምሊሻ
10.ሀብታሙ ጌታቸው-አብራጂት
11.መቅጫ አጥናፍ--አብራጂት
12.ይላቸው ንጉሴ--አብራጂት
13.ሁነኛው ስዐሉ--አብራጂት
14.ተሾመ ዘገየ--አብራጂት
15.አሸናፊ አበባው--አብራጂት
16.እንደገና ደረሰ---አብራጂት
17.ሀይማኖት ዘውዱ--አብራጂት

2/ ከግንቦት 16/2017 ዓ.ም - ሐምሌ 05/2017 ዓ.ም ከአረመኔው አገዛዝ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር የተቀላቀሉ የአረመኔው ሠራዊት አባላት።
~ ቀስተ ደመና ብርጌድ
1/ ዳዊት ንጉሤ   መከላከያ
2/ አለሌኝ ለገሰ   "    "
3/ ዘሪሁን ጌትነት     አድማ ብተና
4/ ቁምላቸው ብርሃን    "    "
5/ ጥላሁን አያሌው     "     "
6/ አበጀ ሙሉጌታ        "     "
7/ ተስፋየ ውቤ           "     "
8/ ማርየ ወዳጀ           መከ
9/ አለሙ ተዘራ            "
10/ ውበት ሰገነት ...ሰ/አስከባሪ
11/ ላቃቸው ምትኩ.   "

~ በረኸኛው ጅበላ ሙተራ ብርጌድ
12/ መኮነን በልስቲ ስራዬ   ሰላም አስከባሪ
13/ ሃይማኖት ስማቸው ደሴ  "         "
14/  ጌታቸው አደመ ደለለ      "         "
15/  እንየው በቀለ ደረጃው      "         "
16/ ቻሌ ዘለቀ መላኩ            "          "
17/ ተሻገር ባወቀ አስረስ         "         "
18/ ስማቸው አዳነ  እና
19/   እንዳወቀ ያደርጋል  ሚሊሻ
20/  ሬድ አማን ጃፋ ......መከላከያ
21/  ሃምዛ ኡስማን .......መከላከያ
22/ ሲሳይ ሞላ ..............አድማ ብተና
23/ ሀብታሙ አዝመራው.... አድማ ብተና
24/  አደራጀው እንግዳው..... አድማ ብተና
25/ ዘመነ እያዩ .................. አድማ ብተና
26/ ስራየ ባሴ ታዴ. .............አድማ ብተና

~ በላይ ዘለቀ ብርጌድ
27/ ልመን ደሴ .................መከላከያ
28/ እምሻው ሙሉነህ ........."         "
29/  አሸናፊ ደባስ .............."        "
30/  ደስታ ቡርቃ................."        "
31/ ጋዲሳ ባያን ጀማል........."        "
32/ አራርሶ ከማል ኢብሮ ...... "      "
33/ ኡስማን አህመድ..........."      "
34/ ቀነኒሳ ኡሴን ................."      "

~ ኢንጅነር ክበር ተመስገን ብርጌድ
35/ ሀያት አብዱ         "  "
36/ አማን ሀሚድ        "  "
37/ ታጅ አህመድ       "   "
38/ ሱልጣን ሙሳ     "   "
39/ አህመድ ሀጅ       "   "
40/ እንድሪስ ታደለ    "   "
41/ የአብስራ አለማየሁ  " "
42/ ቢራ ሻሞ               "   "
43/ የኑስ ኢብራሂም       "   "
44/ አማረ      .................."   "
45/ ቶፊቅ      ................"    "
46/ ወርቅነህ  ..............."      "
47/ ኑሬሳ ከበደ ............"      "
48/ እሸቱ       .............."       "
49/ ለማ         ............."       "
50/ ደጀኔ         ..........."      "
~ ስናን አባጅሜ ብርጌድ
51/ አዲሱ       ..........መከላከያ
52/ ገብረ መስቀል  ...."      "
53/ ለሜ አስፋው   ....."      "
54/  ሙሉሰው አቤ  ...."    "
55/ አለሙ ብርሃኑ  ...."     "

3/ አፋጎ 8ኛ በሌይ ዘለቀ ክፍለ ጦር  የአረመኔውን ስርዓት በመክዳት ወደ ክፍለ ጦራችን የተቀላቀሉ።

1.ተተካ አበበ  .... ሚኒሻ ... ሽፈራው ገርባው ብርጌድ
2.ተመስጌን ሙንየ ...ሚኒሻ ... ሽፈራው ገርባው ብርጌድ
3.ባየ አወቀ   ...   ሚኒሻ ...  ሽፈራው ገርባው ብርጌድ
4.መልካው ከፋለ ...ሚኒሻ ...ሽፈራው ገርባው ብርጌድ
5.በውቀት አያሌው ... ሚኒሻ    ...   አባ ኮስትር ብርጌድ
‎6.በላይነህ ዳምጤ ...  ሚኒሻ  ...   አባ ኮስትር ብርጌድ.
7.ምትኩ መድፉ ...    ሚኒሻ  ...     አባ ኮስትር ብርጌድ
‎8.ልንገረው ሰውነት  ...  ሚኒሻ  ...    አባ ኮስትር ብርጌድ
9.ጌጥየ ሞትባይኖር..አድማ ብተና..አባ ኮስትር ብርጌድ
‎10.አብነት ጀግናው...አድማ ብተና...አባ ኮስትር ብርጌድ
‎11.አበበ አባተ...  አድማ ብተና...   አባ ኮስትር ብርጌድ
12.በለጠ መንገሻ ...  አድማ ብተና ...  አባ ኮስትር ብርጌድ
‎13.ዳንኤል ሙሉጌታ... አድማ ብተና...  አባ ኮስትር ብርጌድ
14.ደቻሳ ዱሬ ነጌሶ... መከላከያ   ...   አባ ኮስትር ብርጌድ
15.ቤቢሻ አልዬ ውንዲ... መከላከያ  ... አባ ኮስትር ብርጌድ
16.ጋሸው ፈቃዱ ...  አድማ ብተና ... ዛምበርሃ ብርጌድ
5👍3
👉አባት አርበኛ አየልኝ ፈረደ ማለት እሄ ነው!!!
👉እንደ አውራ በሬ የተጀነነው::
🙏መኪናው ይመጣል እያለደለደ:
🙏የብልፅግና ባል አየልኝ ፈረደ::
👉ቅራቅር ምን አለ ጠገዴ ምን አለ ስምንቱ ማይ ቤት:
👉አየልኝ ፈረደ ብልፅግና ገዳይ ጠላት ለህወኃት!!!
ቀን ሐምሌ 5/2017 ዓም
የአፋብኃ ሰሜን አማራ ጎንደር ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ሜጀል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ጉና ክ/ጦር የተላለፈ እለታዊ ዘገባ።
መንግስት ነኝ ባዩ ብልፅግና መከላከያ ተብየው፣ አላማ የለሹ አድማ ብተና፣ ሆድ አደሩ ሚኒሻ እና ፖሊስን ቢያሰልፍም ሁልጊዜ አሳፋሪ ታሪክ እየተከናነበ የሚገኘው እና የሜጀል ውባንተ አባተን የመንፈስ ልጆች መቋቋም ማሸነፍ እንደማይችል የተረዳው ከሰሞኑ ድል የራቀው ብልፅግና ከትናንት ሐምሌ04/2017 ዓም 2:00 ጀምሮ እስከ ዛሬ ሐምሌ 5/2017 ዓም ሺሞፈና፣ አቱይ ባታ እና ግራሪያ ቁስቋም ላይ ዝርክርኩ ወጥቶ ውሏል ሙት እና ቁስለኛውን ማንሳት እስኪያቅተው በዙ 23፣ ሞርተር፣ BM ፣ ዲሺቃ እና ሌሎች አሉኝ ያላቸውን መሳሪያዎችን ቢጠቀምም የጀግናው የሜጀል የውባንተ አባተ ልጆች ወይ ፍንክች። በዚህ አውደውጊያ የተሳተፉት ሜጀል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ተወርዋሪ፣ የሜጀል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለጦር፣ የታላቁ ጉና ክ/ር ቃኝ እና መሀንዲስ፣ መቅደላ አምባ ብርጌድ ታጠቅ ሻለቃ እና ገብርየ ሻለቃ እንዲሁም ገብረ መስቀል ደርብ ብርጌድ ጣይቱ ሻለቃ በጥምረት በከባድ መሳሪያ የታገዘ ውጊያ ያካሄዱ ሲሆን የአማራዎችን ክንድ መቋቋም ያቃተው የብልፅግና ወንበር ጠባቂው ጥምር ሀይል ንፁህ ዜጋን አንዲት እናት አቁስሏል ልጇን እረሺኗል።
ውድ አማራዎች ይህን እያያችው የገጠመውን መምታት ያቃተው እርካሹ እና ጥምር ሀይል ነኝ ባይ ወንበር ጠባቂ መበቀል የሚፈልገው ከገጠመው የውባንተ ልጆች ሳይሆን ንፁሀን በማሰቃየት እና በመረሸን ነው።
ይህን ገዳይ ሀይል ደግፋችው የምትንበጫበጩ በአማራ ደም መቀለድ እና መዘባበት ነው ለሆዳችሁ ከማደር:- ለህሊናችሁ ለማንነታችሁ ኑሩ እንተባበር ወገናችን እና እራሳችን ከጭቆና አገዛዝ በጋራ እንውጣ።
። ።ድል ለአማራው ፋኖ።።።።
መምህር አሃዱ በዬነ የጉና ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት።
👍2
ዝክረ ሀምሌ 5 እና እዋዋ ጎቤ!!!!

የ27 አመታት የጭቆና ቀንበር በቃ የተባለበት፣ወጣቶች በአደባባይ የተዋደቁበት፣ለነፃነት ህይወታቸዉን አሳልፈዉ የሰጡበት፣ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የትግል ድወል የተደወለበት፣የዘመናት ግፍ እና መከራ በቃ የተባለበት በወቀቱ አራት ኪሎ ተደላድሎ የተቀመጠዉን ባለጊዜ አምባ ገነኑን ህወሃት ብርክ ብርክ የተሰኘበት ለትዉልዱ ነፃነት ሲባል ትዉልዱ እራሱን አሳልፎ የሰጠበት ሀምሌ 5/2008 ዓ.ም።

ያ ራሱን ለትዉልዱ ነፃነት ሲል እራሱን አሳልፎ የሰጠዉ ጀግና በዛሬዋ ዕለት ህይወቱን ያለ ስሰት ገብሯል።የዚያ ዘመን የነፃነት ቀንዲል ፊትአዉራሪ፣ልበ ሙሉ፣ባለፀጋ፣ተኳሻ፣አራሽ እንደሆነ ሁሉም ይመሰክርለታል።ባርነትን የሚፀየፍ፣ሁሉንም የሚያከብር፣ሀይማኖተኛ፣ደፋር፣ሀገር ወዳድ አልሞ ተኳሽ፣ለወዳጁ ቅዱስ ለጠላቱ ዕርኩስ ቀጠን ያለ ለግላጋ አመለ ሸጋ እዋዋ በሁሉም ሰዉ ልብ የተቀመጠ የቁልምጫ ስሙ  የበረሀዉ ብርቱ ሰዉ የዛሬዋ ቀን የማትረሰዉ ጀግና ከጓዶቹ ጋር ደማቅ ታሪክ ፅፎባት አልፏል።ሀምሌ 5 እና እዋዋ ጎቤን በትንሹ እናስታዉሳቹሀለን።

ከአርማጭሆ ቤቱ ወንድ አንድ ለእናቱ
ጠላትን ድል አርጎ ፎከረ እንዳባቱ ሲል ጀግንነቱን የተመለከተዉ ባለማስንቆ ተቀኝቶለታል።የገብርየ የካሳ ሲገርመኝ ጎቤ ደገመኝ ሲል አርቲስት ወርቁ ሞላ ሳንኪ አድርገዉ ዘፍኖለታል።

በብዙዎች ልብም ተደልድሎ ተቀምጧል ጎቤ የሚለዉ ስም መማያ እስከመሆን ደርሷል።አሁንም ጀግኖች በስሙ ከማሏ እህል አይቀምሱም።ያ የሀምሌዉ በረዶ ከበረሀ ወርዶ ጎንደር ታራክ የሰረዉ የጦሩ አለቃ ጎቤ መልኬ ሀምሌን በጀግንነት አልፏታል።

የዛሬዋ ቀን ለወጥ የተጠነሰሰባት በስተመጨረሻም ለዉጡ እዉን ሁኖ ሌላ መከራ እንዲመጣ ምክናየት የሆነች እስካሁን ድረስ ብዙ ዉጣ ዉረዶችን እያስመለከተችን ቀጥላለች።በዚች ዕለት ያ የአርማጭሆዉ የጦር አለቃ ታሪክ የተጎናፀፈባት ዕለት ነበረች።ያ ደጀኔ ማሩ ቃቆና ሙሀቤ
ጠርቷቸዉ መች ቀሩ ያ ታላቁ ጎቤ
ጠላትም ሮጠ ትንፍስ አለ ልቤ ሁሉም ጎንደሮች የተቀባበሉት ሰንኝ ነበር።የበጌምድሯ የፖለቲካ የስበት ማዕከል የሆነችዉን ጎንደር በጉለበት የነጠቋት ህዎቶች የማይነካዉን ሰዉ ነክተዉ ጎንደርን የጦር መንደር አደረጓት።

የህወሓት ጦር የወልቃይቱን ቁልፍ ሰዉ የሚባለዉን ኮሎኔል ደመቀ ዘወዱን አፍኖ ለመዉሰድ ቤቱን ከቧል። እኔ በጌምድሬ ነኝ መሬቱም በጌምድር ያለዉ ወታደር በጣላት መዳፍ ሊገባ ደቂቃዎች ቀርተዋል።ብቻዉን የሚፋለመዉ ወታደሩ በጌምድሬ በጭንቅ ጊዜ ዋሴ ጠበቆቸ  ብሎ ላሰባቸዉ ጓዷቹ ድረሱልኝ ሲል ድወል ደወለ።በዚህ ጊዜ አንድ የማይታመን ነገር ተደረገ።አይኑን የታመመዉ ጓዱ በሆስፒታል አልጋ ላይ ሆኖ የድረሱልኝን ጥሪ ሰማ ጀግናዉ ግን ኣላመነታም ለጓዱ ሲልም ህመሙ አልገደበዉም ምክናየቱም እሱ ለቃሉ ታማኝ ጎንደሬ ነዉ እና።

አይኑን ቢያመዉም አልሞ ከመምታት ያገደዉ አንዳች ነገር አልነበረም።እስከነ ህመሙ ሌሎች ጓዶቹን ከሰሜን፣ከደቡብ፣ከምስራቅ እና ከምዕራብ ከጎኔ ተሰለፉ እኔ ከፊት አለሁ ሲል ጠራቸዉ እነሱም ኣላመነቱም ፈጥነዉ ከቦታዉ ደረሱ።

ደጀኔ ማሩ፣ሙሀቤ በለጠ፣ደሳለኝ አዱኛ፣ቃጨዉ ሙላ፣ቃቁየ አወቀ፣ሰጠኝ ባብል እና ሌሎችም ጀግኖች በተጠሩት አቅጣጫ ከተፍ አሉ።

ጀግናዉ ጎቤ መልኬ ምላጩን ስቦ ከጠላት ፊት ደረሰ፣ደጀኔ ማሩ በግራ ቃቁየ አወቀ በቀኝ ቃታቸዉን ከፍተዉ እንደ ቲወድሮስ፣ገብረየ እና ገልሞ ተማምለዉ እና ተማምነዉ ጠላትን ያስጨንቁት ጀመር።

ያ እምቢኝ በጌምድሬ ነኝ ያለዉ ኮሎኔል ጥይቱ ሊያልቅበት መሆኑን ሲረዳ ለዕራሱ ብቻ ለማስቀረት እርሳስ በመቁጠር ላይ ነበር።በአንደበቱ የቲዎድሮስ ታሪክ ይደገማል እንጂ ጎንደር ላይ እጅ አልሰጥም ብሏል።

ጎንደሮች በየቤታቸዉ የተኩሱን አቅጣጫ በማዳመጥ ከጓዳ የደበቁትን መሳሪያ መላጥ ጀምረዋል።ሁሉም ለመዉጣት የዋዋ ጎቤን ምላጭ መሳብ ይጠባበቃሉ።በጌምድሬዉ ደመቀ ዘወዱ አሁንም እርሳስ እየቆጠረ መፋለሙን ቀጥሏል።ግልኮስ ነቅሎ ምላጭ ስቦ የደረሰለት የክፉ ቀን ደራሹ የመጀመሪያውን ጥይት ተኩሶ ከጠላት ግንባር ላይ አሳረፋት።

ከጎኑ ያሉት ጓዶቹ ኢላማ ዉስጥ ያስገቡትን የወያኔ ጎረምሳ ቡችሌ ግንባር ግንባሩን ይነርቱት ጀመር።ያቺ በአርባ አራት ታቦት ተከባ እንቢልታ እና ቃጭል፣ቅዳሴ እና ዜማ የሚሰማባት እናትዋ ጎንደር ሌላ ድምፅ የናፈቃት ትመስላለች።ወዳ ሳይሆን ተገዳ እንድትሰመዉም ተደረገች።ዋዋ ጎቤ የሚሙራዉ ፈጥኖ ደራሽ ጦር በኮሎኔል ደመቀ ዘወዱ ቤት ዙሪያ የሰፈረዉን ቡችሌ ነፍሱን ለሰማይ ስጋህን ላፈር ብሎታል።የዋዋ ጎቤን፣የደጀኔ ማሩን፣የቃቁየን፣የሙሀቤ በለጠን የምላጭ አሳሳብ የተረዱ የሚመስሉ እነዚያ በጊዜ ቃታ ከፍተዉ የሚጠባበቁት ጎንደሬዎች በእየ አቅጣጫው ያስጓሩት ጀመር።ሀምሌ 5 በከበሮ የምደምቀዉ ጎንደር በዲሽቃ፣በሜዉይዘር፣በምንሽር እና በስኬስ ደመቀች።

የኮሎኔል ደመቀ ዘዉዱን ቤት የከበበዉ የጠላት ነፍስ በእነ አጅሬ አፈሙዝ ወደ በድንነት ተቀየረ።ሌላም ይመጣል ይሸኛል፣ሌላም ይተኩሳል እራሱን ይሰዋል ቢመጣም ቢሄድም ከእነ ዋዋ ጥይት ማምለጥ አልተቻለም።

ሸብ ረብ ሲል የነበረዉ የወያኔ ወጠጤ በያለበት ሁሉ ፀጥ ረጭ ተደረገ።ጀግኖቹ በብርቱ ክንዳቸዉ ኮሎኔል ደመቀ ዘወዱን ከከበባ አዉጥተዉ ድላቸዉን በክንዳቸዉ አበሰሩ።

ይህን የተመለከተዉ ስንኝ ቋጣሪዉ የጎንደር ሰዉ እንዲህ ሲል ገጠመ።
ሙሀቤ በለጠ የወንዶች ቁና
ጦር ገባ ቢሉት ወርዶ ገጠመዉ ከጀግኖች ጎራ
ብቻዉን አደል ከጎቤ ጋራ።
ማዕበሉ ቃቆ መጣ ዘለቀ እንደ በካር ምጥ እያስጨነቀ።

ጎቤ መልኬ እንደ ቲወድሮስ መህቤ በለጠ እንደ ገብርየ።ደሳለኝ አዱኛ ቆላ ወገሬዉ፣ቃጨዉ ሙላ፣ቃቁየ አወቀ የተዋደቁበት ሀምሌ 5 የ27 አመታት ግፍን በመቃወም የማይደፈረዉን ደፍረዉ በአደባባይ አዋረዱት።።

ያ የላሞቹ ጌታ፣ቀጠን ያለዉ ለግላጋ መልከ መልካሙ የተዋደቀለት አላማዉ በመጨረሻ ቢሳካም እሱ ግን ያን አላየም።ወልቃይት ብረሳሽ ቀኘ ትርሳሽ ያለዉ የጦሩ ኮከብ ወልቃይት ነፃ ሲወጣ አልተመለከተም።

ጎንደሮች አብዝተዉ ከሚወዷቸዉ ጀግኖች ተርታ የተሰለፈዉ ጀግና በስሙ ዋዋ ጎቤ የሚል ክፍለጦር ተሰይሞለታል።በአባቱ ዕግር የተተካዉ ልጁ አንተነህ ጎቤም የዚህ ክፍለጦር አመራር ነዉ።

@ግሎባል ፋኖ ሚዲያ!!!
የፋኖ ድምፅ!!!!
3🙏1
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው እንሆ ዛሬ 05/11/2017ዓም በታሪክቷ ቦታ እውን ሆነ።

እኩል ከኛ ቀናት እየቆጠራቹ ብስራቱን ስትጠባበቁ የነበራቹ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኋይል ደቡብ አማራ ቀጠና_አሳምነው ዕዝ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድ አባላትና አመራር እንዲሁም መላው የትግሉ ደጋፊዎች እንሆ ዛሬ 05/11/2017ዓም ነበልባል ብርጌድ ሁሉም መስፈርቶችን በማማላት ወደ ነበልባል ክ/ጦር አድጓልና እንኳን ደስ አላቹ!!!

ይህ ብስራት ለመስማት ከ15ቱ ሻለቃዎች 3ቱ ሻለቃዎች እና አንዱ የብርጌዱ ተወርዋሪ ብቻ ከተለያየ አቅጣጫ ወደ አንድ ቦታ በመትመም የነበልባል ክ/ጦር ምስረታ በዓል ተካፋይ በመሆናቹ እንዲሁም በግዳጅ ያላቹና በየምሽጉ ያላቹ መላው የነበልባል ክ/ጦር አባላት ህልማቹ እውን ሆኗልና አሁንም ደግመን ደጋግመን እንኳን ደስ አላቹ ለማለት እንወዳለን።

የነበልባል ኮር አመራሮች
1ኛ ተወርዋሪ ሚሳኤል በሚል ቅፅል ስም የምናውቀው የነበልባል ክ/ጦር ዋናው የጦር አዛዥ 50 አለቃ ፍቃዱ ጥላሁን ከልክሌ

2ኛ አባ መላ በሚል ቅፅል ስሙ የምናውቀው የነበልባል ክ/ጦር ምክትል የጦር አዛዥ ለኦፕሬሽናል 10 አለቃ ሸዋቀና ኡርጌሳ

3ኛ አስተዋዩ ጓዳችን በሚል ቅፅል ስሙ የሚታወቀው የነበልባል ክ/ጦር አስተዳደር ዋና ሃላፊ በላይሁን አድማሱ

4ኛ ቅን ጓዳችን በሚል ቅፅል ስሙ የምናውቀው የነበልባል ክ/ጦር ሎጂስቲክ ዋና ሃላፊ ደሴ ሞገሴ

5ኛ ሞተር ጓዳችን በሚል ቅፅል ስሙ የምናውቀው የነበልባል ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ዋና ሃላፊ እንጅነር ታደሰ ወንድሙ እና መላው የነበልባል ክፍለጦር ስራ አስፈፃሚ እንዲሁም አባላትና በተጨማሪም የብርጌድና የሻለቃ አመራሮች በአመት ልፋት ከተፈሪና ጠንካራ ነበልባል ብርጌድ ወደ የተሳካና የተደራጀ ነበልባል ክ/ጦር እንዲሸጋገር ላበረከታቹሁት ሁሉ በትግሉ ሰማእታት ስም የነበልባል ክ/ጦር ሚድያና ኮሚኒኬሽን ክፍል ምስጋናችን እናቀርባለን።
የተከበራቹ
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኋይል ደቡብ አማራ ቀጠና_አሳምነው ዕዝ ነበልባል ክ/ጦር ኮር አመራርና አባላት እዚህ ለመድረስ በርካታ ጓዶቻችን ሂወታቸው ሰውተውበታል አካላቸው ገብረውበታል ትግሉ ከዳር ለማድረስ ይቺ ቀን ዳግም ለራሳችን ቃል የምንገባባት መሆኗን ተረድተን ከትላንት በተሻለ ዛሬና ነገ በርትተን በመስራት በቅርብ ኮር ለመመስረት ሳንታክት እንስራ በማለት ለማስታወስ እንወዳለን።
የተከበራቹ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኋይል አመራርና አባላት የነበልባል ክፍለ ጦር ጥንኳሬ የናንተም ጥንካሬ ነውና እንኳን ደስ አላቹ ማለት እንወዳለን።
የተከበራቹ የአማራ ህዝብ በተለይ የምንጃር ሸንኳራ ህዝብ የአገዛዙ ባለስልጣን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ 99% አጥፍተኗቿል የሚል የውሸት ፕሮፓጋንዳ ስያስተጋቡ ቡቹሏዎቻቸውም የውሸት ከበሯቸው ሲደልቁ ታዝባቿል ሆኖም እውነቷው እንደምትመለከቱት ነውና ከትላንት ዛሬ በተሻለ የሰው ሃይልና መሳርያ ተደራጅተናል።
👍4
🔱24 ዓመታትን በጫካ ትግል የፀና ጀግና!

አርበኛ አበራ ጎባው...

# ከዱር አራዊት ተላምዶ እንደ አሹሃ የበዛውን ጠላት ተጋፍጦ፣ህመም ስሜትን ተቋቁሞ እጅግ ፈታኝ 24 ዓመታትን አሳልፎ በማተቡ ፀንቶ ህይወቱን ለወገኑ የሰጠ ክቡር ሰማዕት አርበኛ አበራ ጎባው...

24 ዓመታት ፅናት ሳይጓደል ስንቱን መከራ ብቻውን በጠላት በተከበበ ቀጠና ተቋቁሞ የታገለና ያታገለ ጀግና 2009 ዓ.ም በአርማጭሆ አሸሬ አካባቢ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ውጊያ ጠላትን እንደ ቅጠል አርግፎ በጀግንነት ተሰውቷል።

አርበኛ ጎቤ አጋሩ አበራ ሲሰዋ በእልህ ሰራዊቱን አሰባስቦ ያለማቋረጥ ማጥቃት በማድረግ አፀፋ መልሷል።

ፋኖ ማለት የአያት የቅድመ አያቶቻችን ማህበረሰባዊ ታማኝ የኃይል አማራጭ ነው ማለት እንደ አበራ ጎባው አይነቶቹ ጠብቀው ያሻገሩት መሆኑን መዋጥ በራሱ ክብር ነው።

የአዲሱ ትውልድ የአርበኝነት አደራ አውራሾች ለዛሬው ትውልድ አርበኝነታዊ የፋኖ ትግል ዱላ አቀባይ ባለመብቶችም ናቸው።

ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ
🙏42🤯2
አፋብኃ ሠሜን አማራ ቀጠና/በላይ ዘለቀ ዕዝ
ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር
ጉና ክፍለ ጦር
ሠኔ 5/2017ዓ.ም

ገብረ መሥቀል ብርጌድ/ጣይቱ ሻለቃ የአገዛዙ አራዊት ሠራዊትን ከወርቄን እሥከ ገና መ መጫወቻ ሥትገርፈው ውላለች። የነበረው የጠላት ጦር ኃይል ይጨመርልኝ ባለው መሠረት ዙ-23 መሣሪያን የያዘ ተጨማሪ ኃይል ታክሎለት በአንዲት ሻለቃ ሢጨነቅ ውሏል። የአማራ ፋኖ ከፍ ያለ ልዕልና ላይ ተቀምጧል። በየትኛውም መንገድ ጠላት ቁሣዊ፣ አካላዊና ሥነልቦናዊ ኪሣራን እየተከናነበ ነው የሚገኘው።

ድላችን በተባበረ ክንዳችን
ዝንተዓለም አምሐራ

ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ኮር ሕዝብ ግንኙነት
ኃቅአለው ፀጋ
6🙏2
አሁናዊ መረጃ ቡሬ ዳሞት 

የአማራ ፋኖ በጎጃም 5ኛ ክ/ጦር ቡሬ ዳሞት ብርጌድ ዘመነ ካሴ ሻለቃ ፣ አሳምነው ሻለቃ ፣ መርከብ ሻለቃ ፣ ሰፊ ሻለቃ ፣ አባይ ሻለቃ በመጣመር ቡሬ ከተማ ላይ ከፍተኛ ጀብዱ ፈፀሙ። ውጊያውን የጦር ጠበብቶቹ ሃምሳ አለቃ ጌታቸው ታረቀኝ የብርጌዱ ሰብሳቢ እና የብርጌዱ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ ኮማንዶ ይበልጣል ጋር በመጣመር በአራት አቅጣጫ ውጊያ በመክፈት ቡሬ ከተማን በመቆጣጠር ከፍተኛ ጀብዱ ፈፅመዋል።

➽ የጠላት ሰራዊት ተደምስሷል።
➽ የቡሬ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት የመሳሪያ መካዝን በቁጥጥር ስር ውሎ ከ50 በላይ የጦር መሳሪያ እና ብዛት ያለዉ ተተኳሽ ተማርኳል።
➽ የቡሬ ከንቲባ ፅ/ቤት በቁጥጥር ስር ውሏል።
➽ ከፍተኛ ቁጥር የጠላት ሰራዊት ቁስለኛ ሁኗል።
➽ የጠላት ካምፕ በድሽቃ እና በሞርተር ከጥቅም ውጭ ሁኗል።

ጠላት በዚህ ሰዓት ቡሬ ኢንዱስትሪ ፓርክ ገብቶ መሽጓል የጠላት ፍላጎት ኢንዱስትሪ ፓርኩ እንዲወድም ነው ፓርኩን ፋኖ ላለመደብደብ ጥረት እያደረገ በኮማንዶዎች የከተማ ውጊያ እየመራ ይገኛል።
👍3👎1
➤ የጎንደሬ በጋሻው ክ/ጦር ብርጌዶችና የታድሎ ብርሃን ክ/ጦር ትንሳኤ ሻለቃ በጋራ ከጠላት ጋር ውጊያ አካሄዱ ።

የአብይ ወንበር አስጠባቂ ሃይል መነሻውን ከአዘዞ ወታደራዊ ካምኘ በማድረግ የተለያዩ ቁሳቁሶችን የጫኑ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን በማጀብ ወደ ባህር ዳር አቅጣጫ በመጓዝ ላይ እያለ የዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ጎ/ በጋሻው ክ/ጦር አካሎች
ቃኘው ብርጌድ
ጎንደር ብርጌድ
ፋሲለደስ ብርጌድ ና
የታድሎ ብርሃን ክ/ጦር ጣሰው ብርጌድ ትንሳኤ ሻለቃ በጥምረት
በጎንደሬ በጋሻው ም/ወታደራዊ አዛዥ በአርበኛ ደመላሽ ስመኝ መሪነት ከአርሴማ እስከ ምንዝሮ ያለውን ቀጠና በመሸፈን ውጊያ አካሂደዋል።
በውጊያውም የተገኘውን ድል በአሁኑ ሰዓት በእውን ማወቅ ባይቻልም የጠላት ሃይል የሚያጅበውን ወታደራዊ ተሽከርካሪ ይዞ እግር አውጭኝ ብሎ ፈርጥጧል።
ከዚህ በፊት በዚህ ቀጠና ላይ ተከታታይነት ያለው አውደ ውጊያዎችን በማድረግ የመቶ አለቃነት ማዕረግ ያለው የስርዓቱ አገልጋይ ወታደር ግድያን ጨምሮ የቁሳቁስ ምርዠ መገኘቱን መዘገባችን የቅርብ ትውስታ ነው።

➤ አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ የዳግ/ቴዎ/5ኛ ኮር ህ/ግን/ኃላፊ
አብነትሞላ
ሃምሌ 06/2017 ዓ.ም
👍64
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ በልጅ እያሱ ኮር ስር ያለችው ቤተ አምሐራ ክፍለ ጦር በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ በቆጋት ሚካኤል እና ሐሙሲት በሚባሉ አካባቢዎች ሐምሌ 02 እና 03 2017ዓ.ም በተደረገ የደፈጣ ውጊያ 11 የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ ሰራዊት ሲቆስሉ አንድ የአስር አለቃ ማዕረግ ያለው ወታደር እና አምስት እግረኛ ወታደሮች ተገለዋል።

ደፈጣው ግሽን ላለው ወንበር አስጠባቂ ወታደር ቀለብ ለመስፈር ለሚጓዝ ሌላ ወንበር አስጠባቂ የመከላከያ ሰራዊት ላይ እንደሆነ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል።

የተኩስ ልውውጡን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም አንድ የመከላከያ አባል ቤተ አምሐራ ክፍለ ጦርን ተቀላቅሏል የመከላከያ አባሉም ክፍለ ጦሯን ከተቀላቀለ በሗላ እንደተናገረው አጋጣሚዎችን በመጠቀም ከመከላከያ ሰራዊት ለመውጣት የሚጠባበቀው ብዙ ነው ብሏል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ሐምሌ 6/2017 ዓ.ም
👍91
ሰበር ዜና!
ላሊበላ ፋኖ ወደ ከተማው ዘልቆ የገባ ሲሆን በአሸተን በሺምሽሃ በአየር ማረፊያ በአቦ መሳለሚያና ጣረስታ በሚባሉ 5 ቦታዎች ከጥዋቱ 12 ስአት የጀመረ ውጊያ በመካሄድላይ ላይ እንደሆነ በውስጥ መረጃ ደርሶናል።
ድል ለፋኖ💪
5
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ

አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ልጅ እያሱ ኮር ቤተ አምሐራ ክፍለ ጦር ድል ተጎናተፈች::

ዛሬ ሃምሌ 6/2017ዓ.ም ከጠዋቱ 11:00 ጀምሮ እስከ ቀኑ 6:00 በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ በ021 እና በ022 ቀበሌ ጠረግማን እና ጅብ ጎዶ በተባሉ ቦታዎች በተደረገ ውጊያ የቤተ አምሐራ ክፍለ ጦርን ለመግጠም በ46ኛ ክፍለ ጦር ስር ያሉ ከ1ኛ ሬጅመንት እስከ 5ኛ ሬጅመንት ያሰለፈ ሲሆን በዚህም ውጊያ መከላከያ በሁለት አይሱዙ እና በሶስት አምቡላስ ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ወደ መጣበት እንድፈረጥጥ ተደርጓል።

በተጨማሪም ሁለት የመከላከያ አመራሮች በሞትና በህይወት መካከል ሲሆኑ የአመራሮቹን ማንነት መረጃ እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።

በሌላ በኩል የብልፅግናው መከላከያ የፋኖን ምት መቋቋም ሲያቅተው ውጊያው በተካሂደባቸው አካባቢዎች ህዝብ ላይ በመተኮስ ሁለት አርሶደሮችን ሲገድል አስራ ሶስት አርሶደሮች ደግሞ ታግተው እንደተወሰዱ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
ሐምሌ 7/2017 ዓ.ም
👍5💔1
የአማራ ወጣት ሆይ የምትፈራት ሞት በዚህ ልክ የሞት አሟሟትክንና መከራህን አብስታ እየመጣች የዉርዴት ሞት ከምትሞት ወደወንድሞችሁ ጫካዉ ቤቴ ብለህ ጠላትክን ጉረሮ ለጉረሮ ተናንቀህ እልክህን እየተወጣህ ብትሞትና ለቀረዉ ወገንህ እንደሻማ ቀልጠህ ታሪክ ብታፅፍ ይሻልካል አልረፈደብህም በያቅጣጫህ ትክክለኛዉን ታጋይ እየመረጥኩ ተከላቀል።