ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.32K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.23K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር 49ኛ ክፍለ ጦር የሰራዊት ተሃድሶና የአልባሳት መረሀ-ግብር በደማቅ ሁኔታ አካሔደ።

የ102ኛ ኮር አካል የሆነው የ49ኛ ክ/ጦር ከግዳጅ ጎን ለጎን የሰራዊት ተሀድሶና የአልባሳት ፕሮግራም በማድረግ ለወደ ፊት ለሚደረጉ ግዳጆች ዝግጁ መሆናቸውን የክፍለጦር አመራሮች ገልፀዋል።

በመርሀ ግብሩ ከተከናውኑት ሁነቶች መካከል በ49ኛ ክ/ጦር የሰልፍ ትሪኢት፣ በግዳጅ የተሻለ አፈፃፀም የነበራቸውን የሻለቃ አመራር፣ የክ/ጦር አመራር፣ የድርጅት አመራርን በመሸለምና ተወዳጅ የሆነውን የአማራ ፋኖ መዝሙር በጣዕመ ዜማ ቀርቧል።

የተሀድሶ ፕሮግራሙን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የ102ኛ ኮር ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ቀኝ አዝማች ረዳ ውበቱ ሲሆን ለ49ኛ ክ/ጦር የሰራዊት አባላት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሰብሳቢው አያይዘው እንደገለፁት የአማራን ህዝብ በሀይል ለማንበርከክ የመጣውን ነውረኛ አገዛዝ ለማስወገድ ከመቸውም ጊዜ በላይ ሰራዊቱ ዝግጁ እንድሆን ገለፁ።

በምርጫ ስም በህዝባችን ላይ ህገ-መንግስታዊና መዋቅራዊ በደል ለማስቀጠል እንድሁም የዳር ተመልካች ለማድረግ የመጣውን የብልፅግና አገዛዝ በቀላሉ ለማስወገድ በሰሞኑ በወሰድንበት ጠንካራ ምት የተብረከረከ በመሆኑ በኮራችን ለሚገኙ ክፍለጦሮች ከመቸውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እንዲሆኑ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የ102ኛ ኮር ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ጌታቸው መልኩ ለ49ኛ ክፍለ ጦር የሰራዊት አባላት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አሰተላልፈዋል።

ወታደራዊ አዛዡ አያይዘው እንደተናገሩት ከሆነ የአብይ አህመድን ጨፍጫፊ አገዛዝ በአጭር ጊዜ ለማስወገድ ከመቸውም ጊዜ በላይ የሰራዊታቸውን ወትሮ ዝግጁነት እንደሚተማመኑበት ጠንከር ያለ ሀሳብ አስተላልፈዋል።

በተጨማሪም ንግግር ያደረጉት የአሁኑ 49ኛ ክ/ጦር የቀድሞው የከላኮርማ ክፍለ ጦር መስራችና የ102ኛ ኮር ም/ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ዘውዱ ዳርጌ ለሰራዊት አባሉ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ወታደራዊ አዛዡ ለሰራዊቱ ካስተላለፉት መካከል ስለ አላማ ፅናትና የትግል ባህሪያት በመግለፅ ማንም የአማራ ፋኖ ታጋይ የአማራ ብሔርተኝነትን ተላብሶ በህዝባችን ላይ በግደታ የተጫነበትን ቀንበር ከትክሻው ለማስወገድ ዝግጁ እንድሆን መልዕክት አስተላልፈዋል።

እንድሁም የ102ኛ ኮር የስልጠና መምሪያ ሀላፊ መቶ አለቃ ሲሳይ መንግስቴና የኮሩ የሰው ሀይልና የመስክ ስልጠና መምሪያ ሃላፊ አምሳ አለቃ ያብቃል ቢተው የተሀድሶውን የሰልፍ ትሪኢትና የአልባሳት ፕሮግራም በመምራት ዝግጅቱ እንድያምር የራሳቸውን አሻራ ጥለዋል።

በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ወሎ ቤተ-አማራ ም/የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አርበኛ አሰፋ መሰለ /አሳምነው/ በዝግጅቱ በመገኘት ለ49ኛ ክፍለ ጦር አመራርና የሰራዊት አባላት እንኳን ደስ ያላችሁ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የአረጃጀት ዘርፍ ሀላፊው አያይዘው ለሰራዊቱ ጨፍጫፊውንና አምባገነኑን አገዛዝ ለመፋለምና ህዝባቸውን ከገባበት ቅርቃር ውስጥ ለማውጣት ዝግጁ እንድሆን መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም 102ኛ ኮር ዋና የፖለቲካ መምሪያ ሀላፊ አርበኛ ሻምበል አሌ ለ49ኛ ክፍለ ጦር አመራር የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አያይዘው እንደተናገሩት የአማራ ህዝብ የፍትህ፣ የነፃነትና የህገ-መንግስት ጥያቄ ስላለው በወርድና በቁመቱ ልክ የፖለቲካ ውክልና እስኪኖረው ድረስ ጠንካራ ታጋይ እንድፈጠር ሲሉ አበክረው ገልፀዋል።

እንድሁም የ102ኛ ኮር የፖለቲካ መሪው እንደገለፁት ያለጦርነት መኖር ከማይፈልገው የአብይ አህመድ አገዛዝ የአማራን ህዝብ ነፃ ለማውጣት አመራራችንና የሰራዊት አባላችን በሙሉ በምናስተዳድራቸውና አድስ በተቆጣጠርናቸው አካባቢዎች ለህግና ስርዓት ተገዥ እንድሆን ጠንካራ መልዕክት አስተላልፈዋል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ-ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ
ሚያዚያ 16/2018 ዓ.ም
🙏2
ሰበር ዜና!!!

አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር 49ኛ ክፍለ ጦር የሰራዊት ተሃድሶና የአልባሳት መረሀ-ግብር በደማቅ ሁኔታ አካሔደ።

የ102ኛ ኮር አካል የሆነው የ49ኛ ክ/ጦር ከግዳጅ ጎን ለጎን የሰራዊት ተሀድሶና የአልባሳት ፕሮግራም በማድረግ ለወደ ፊት ለሚደረጉ ግዳጆች ዝግጁ መሆናቸውን የክፍለጦር አመራሮች ገልፀዋል።

በመርሀ ግብሩ ከተከናውኑት ሁነቶች መካከል በ49ኛ ክ/ጦር የሰልፍ ትሪኢት፣ በግዳጅ የተሻለ አፈፃፀም የነበራቸውን የሻለቃ አመራር፣ የክ/ጦር አመራር፣ የድርጅት አመራርን በመሸለምና ተወዳጅ የሆነውን የአማራ ፋኖ መዝሙር በጣዕመ ዜማ ቀርቧል።

የተሀድሶ ፕሮግራሙን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የ102ኛ ኮር ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ቀኝ አዝማች ረዳ ውበቱ ሲሆን ለ49ኛ ክ/ጦር የሰራዊት አባላት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሰብሳቢው አያይዘው እንደገለፁት የአማራን ህዝብ በሀይል ለማንበርከክ የመጣውን ነውረኛ አገዛዝ ለማስወገድ ከመቸውም ጊዜ በላይ ሰራዊቱ ዝግጁ እንድሆን ገለፁ።

በምርጫ ስም በህዝባችን ላይ ህገ-መንግስታዊና መዋቅራዊ በደል ለማስቀጠል እንድሁም የዳር ተመልካች ለማድረግ የመጣውን የብልፅግና አገዛዝ በቀላሉ ለማስወገድ በሰሞኑ በወሰድንበት ጠንካራ ምት የተብረከረከ በመሆኑ በኮራችን ለሚገኙ ክፍለጦሮች ከመቸውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እንዲሆኑ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የ102ኛ ኮር ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ጌታቸው መልኩ ለ49ኛ ክፍለ ጦር የሰራዊት አባላት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አሰተላልፈዋል።

ወታደራዊ አዛዡ አያይዘው እንደተናገሩት ከሆነ የአብይ አህመድን ጨፍጫፊ አገዛዝ በአጭር ጊዜ ለማስወገድ ከመቸውም ጊዜ በላይ የሰራዊታቸውን ወትሮ ዝግጁነት እንደሚተማመኑበት ጠንከር ያለ ሀሳብ አስተላልፈዋል።

በተጨማሪም ንግግር ያደረጉት የአሁኑ 49ኛ ክ/ጦር የቀድሞው የከላኮርማ ክፍለ ጦር መስራችና የ102ኛ ኮር ም/ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ዘውዱ ዳርጌ ለሰራዊት አባሉ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ወታደራዊ አዛዡ ለሰራዊቱ ካስተላለፉት መካከል ስለ አላማ ፅናትና የትግል ባህሪያት በመግለፅ ማንም የአማራ ፋኖ ታጋይ የአማራ ብሔርተኝነትን ተላብሶ በህዝባችን ላይ በግደታ የተጫነበትን ቀንበር ከትክሻው ለማስወገድ ዝግጁ እንድሆን መልዕክት አስተላልፈዋል።

እንድሁም የ102ኛ ኮር የስልጠና መምሪያ ሀላፊ መቶ አለቃ ሲሳይ መንግስቴና የኮሩ የሰው ሀይልና የመስክ ስልጠና መምሪያ ሃላፊ አምሳ አለቃ ያብቃል ቢተው የተሀድሶውን የሰልፍ ትሪኢትና የአልባሳት ፕሮግራም በመምራት ዝግጅቱ እንድያምር የራሳቸውን አሻራ ጥለዋል።

በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ወሎ ቤተ-አማራ ም/የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አርበኛ አሰፋ መሰለ /አሳምነው/ በዝግጅቱ በመገኘት ለ49ኛ ክፍለ ጦር አመራርና የሰራዊት አባላት እንኳን ደስ ያላችሁ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የአረጃጀት ዘርፍ ሀላፊው አያይዘው ለሰራዊቱ ጨፍጫፊውንና አምባገነኑን አገዛዝ ለመፋለምና ህዝባቸውን ከገባበት ቅርቃር ውስጥ ለማውጣት ዝግጁ እንድሆን መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም 102ኛ ኮር ዋና የፖለቲካ መምሪያ ሀላፊ አርበኛ ሻምበል አሌ ለ49ኛ ክፍለ ጦር አመራር የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አያይዘው እንደተናገሩት የአማራ ህዝብ የፍትህ፣ የነፃነትና የህገ-መንግስት ጥያቄ ስላለው በወርድና በቁመቱ ልክ የፖለቲካ ውክልና እስኪኖረው ድረስ ጠንካራ ታጋይ እንድፈጠር ሲሉ አበክረው ገልፀዋል።

እንድሁም የ102ኛ ኮር የፖለቲካ መሪው እንደገለፁት ያለጦርነት መኖር ከማይፈልገው የአብይ አህመድ አገዛዝ የአማራን ህዝብ ነፃ ለማውጣት አመራራችንና የሰራዊት አባላችን በሙሉ በምናስተዳድራቸውና አድስ በተቆጣጠርናቸው አካባቢዎች ለህግና ስርዓት ተገዥ እንድሆን ጠንካራ መልዕክት አስተላልፈዋል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ-ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 16/2018 ዓ.ም
🙏2
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር 34ኛ ክፍለ ጦር በጋዞ ወረዳ የጥላትን ሰራዊት ዶግ አመድ በማድረግ ድል አስመዘገቡ::

ከሚያዚያ 15/2018 ዓ/ም እስከ ሚያዚያ 16/2018 ዓ/ም ለተከታታይ ሁለት ቀናቶችን ያስቆጠረው አውደ ውጊያ በ34ኛ ክፍለ ጦር አናብስቶች የአገዛዙ ሰራዊት ከፍተኛ ምት ተፈፅሞበታል። ውጊያው ቀጥሎ ያለ ሲሆን ጥላት እስካሁን ሙትና ቁስለኛውን እያነሳ ላይዋጋበት የቆፈረውን ምሽጉን እየለቀቀ እየፈረጠጠ ይገኛል።

የፋኖዎች የድል ግስጋሴ የጋዞ ወረዳ ዋና ከተማ የእስታይሽ ከተማን ግማሽ አካልና ፖሊስ ጣቢያ በፋኖዎች ቁጥጥር ስር ውሏል። በዚህ የድል ግስጋሴ በብዙ ደርዘን የሁለት ቀን ቁስለኛና ሙቱን አገዛዙ ተሸክሞ ወደ ኋላ እግሬ አውጭኝ እያለ እየፈረጠጠ ይገኛል።

በዚህ ሰዓት የእስታይሽ ሆስፒታል በቁስለኞች የተሞሉ ሲሆን የጤና ጣቢያ እና የጤና ኬላን ባለሞያዎችን አገዛዙ በግድ ካላከማችሁ እየተባሉ በየ ስራ ቦታቸው እየታፈሱ መወሰዳቸውን የአይን እማኞች ገልፀዋል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል
ሚያዚያ 16/2018 ዓ.ም
🙏2
የብልፅግናው ወታደሮች አገዛዙን በመክዳት ዛሬም ጀግናው የአማራ ፋኖን ሲቀላቀሉ ሰራዊታችን ድል ተቀዳጅቷል።

ሚያዚያ 16/2018ዓ.ም

በአማራ ህዝብ ላይ የተደቀነውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ እንደ ህዝብ እያታገለ በፊትአውራሪነት የተሰለፈውን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) አታጋይ ድርጅት መመስረቱን ተከትሎ በርካታ የአገዛዙ ወታደሮች በሁሉም የአማራ ግዛቶች በየቀኑ ፋኖን እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።

ዛሬን ጨምሮ በተከታታይ ሁለት ቀናት ውስጥ ስድስት የአገዛዙ ሰራዊት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን ተቀላቅለዋል።
በዚሕ መሰረት አራት (4) የመከላከያ ሰራዊት አባላት የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ከተቀላቀሉት ውስጥ:-

ከ101ኛ አየር ወለድ ክ/ጦር 1 አባል
ከ105ኛ ክፍለጦር 1 አባል
ከ15ኛ ክፍለጦር 2 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ሲሆኑ የኮሩ አሃድ የሆነውን የ7ለ70 ክፍለጦርን አንድ የ103ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር አባል ከነ ሙሉ ትጥቁ ተቀላቅሏል።

በተመሳሳይ መረጃ ከብልፅግናው 104ኛ ልዩ ዘመቻ አየር ወለድ ኮመንዶ ክፍለጦር አንድ የሰራዊቱ አባል የመሐመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴ ጉማ ተራራ ክፍለጦርን ከነ ሙሉ ትጥቁ ተቀላቅሏል።

በሌላ የአውደ ግንባር መረጃ በትላንትናው ዕለት ሬሽን በማቀበል ላይ በነበሩ የአገዛዙ ወታደሮች በነበልባሉ የሰራዊታችን ክንድ ክፉኛ መመታቱን መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን ፣የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር በቡልጋ ክፍለጦር በፋኖ ሰራዊት ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገደው የአገዛዙ ወራሪ ሀይል ከምሽቱ 11:30 ላይ የኮሩ አካል በሆኑት በነበልባል ክፍለጦር ቃኝና መሃንዲስ ነብሮ ሻለቃ ልዩ ቦታው ከሰም ወንዝ ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ በጀግኖቹ በተፈፀመ መብረቃዊ ጥቃት የምርኮኛው ብርሀኑ ጁላ ሰራዊት ከፍተኛ ጉዳት ማስተናገዱን ዕዙ በመረጃው አረጋግጧል።

''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን

የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ

ሚያዚያ 16/2018ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የህዝብ ንቅናቄ መድረኮችን በማከናወን ላይ ይገኛል።

"በተደራጀ የፖለቲካ ስራ የአማራ ህዝብ ብሔራዊ ንቃት ይዳብራል፤ ህልውናውም ይረጋገጣል!" በሚል መሪ ቃል ድርጅታችን በተቆጣጠራቸው ሁሉም ቦታወች እየተካሄደ ባለው የህዝብ መድረክ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

ወጣቶች፣ ሴቶች፣ አርሶ አደሮች፣ የመንግስት ሰራተኞችን ጨምሮ በብዛት በሚያሳትፈው የህዝብ መድረክ ላይ የተለያዩ አጀንዳወች ውይይት እየተደረገባቸው ሲሆን ከመድረኩ የሚገኙ ግብአቶች በተደራጀ መንገድ ለድርጅቱ ሪፖርት ይደረጋሉ።

በመድረኮች የህልውና ትግሉ የደረሰበት ደረጃ፣ በትግላችን ያሳካናቸው ድሎች፣ የትግሉ ሳንካወች፣ ድርጅታዊ ተግባሮቻችን፣ ከማህበረሰቡ ጋር ያለን ግንኙነት፣ የብልፅግናን ምርጫ ወ ጦርነት ፕሮጀክት ጨምሮ በርካታ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ።

የአፋብን ማዕከላዊ አመራር ባወረዳቸው የአሰራር መመሪያወች እና የመወያያ ሰነዶች መሰረት የተጀመረው የህዝብ መድረክ በትላንትናው እለት በምኒልክ እዝ እና ቴወድሮስ እዝ ስር ባሉ ኮሮች በድምቀት ተጀምሯል።

ከህዝብ ጋር የሚደረገው ውይይት አፈፃፀም ሰርክ እየተገመገመ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ማሳተፉን በሚያረጋግጥ መንገድ ተጠናክሮ ይቀጥላል። የህዝባችን ድምፅ እና የውይይቱ ፍሬ ሃሳቦች በሶሻል ሚዲያም ሆነ በመደበኛ የሳተላይት ቴሌቪዥኖች ይተላለፋሉ።

ምስል:- በምኒልክ ዕዝ ቃሊም ክላስተር እና በቴወድሮስ እዝ 206ኛ ኮር ስር ባሉ ማዕከላት የተካሄዱ መድረኮች።
​ምንጭ፦የአፋብን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
🙏3