ግሎባል ፋኖ ሚዲያ/ዓፋሚ/Global Fano Media/GFM
1.34K subscribers
4.16K photos
331 videos
17 files
2.2K links
የፋኖ ድምፅ
Download Telegram
ፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና በአውደ ውጊያ አይሳካለት ሲል ጦር መሳሪያ ያልታጠቁ ንፁሃኖችን ኢላማ ያደረገ የከባድ መሳሪያ ድብደባ እየፈፀመ ቀጥሏል::

የፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና ሰራዊት ደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ 08 ቀበሌ ልዩ ስሙ ጣምሬ የተባለ ቦታ ላይ ተደጋጋሚ የመድፍና የሞርተር 120 mm ድብደባ በመፈፀም በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል:: በዚህም በተጠቀሰው የመቅደላ ወረዳ በተንቀሳቃሽ ምስል በሚታየው መልኩ ህዝብ በብዛት ወደሚኖርበት ቀበሌ ከባድ መሳሪያ በማስወንጨፍ ጉዳት አድርሷል::

በዚህም ፋሽስቱ አገዛዝ የአብይ አህመዱ ብልፅግና ሰራዊቱ በአውደ ውጊያ የፋኖን ክንድ መቋቋም ሲያቅተው የከባድ መሳሪያ ሽፋንና ድጋፍ በሚያገኝበት ሁኔታ በአስተኳሽቹ በኩል ወደ ገጠር መንደሮችና ታዳጊ የገጠር ከተሞች ጭምር በተደጋጋሚ እንዲወነጨፍ በማድረግ የንፁሃኖችን ህይወት በጅምላ እየቀጠፈና አካል እያጎደለ እንስሳቶችንም እያስጨፈጨፈ ቤትና ንብረትም እያወደመ ይገኛል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
የካቲት 13/2018 ዓ.ም
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የበላይ ዕዝ አመራሮች አስቸጋሪ መልካምድሮችን ራብና ጥም ብርድና ውችንፍር ተቋቁሞ ጠላትን እየተዋጋና እያዋጋ በትጋት ተልዕኮውን እየተወጣ ይገኛል።

የህዝብ ትግል አደራ በላብና በደም ዋጋ ይጠበቃል!!

ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ
🙏9
አፋብን| ቴዎድሮስ ዕዝ
_______፩
የካቲት 14/2018 ዓ/ም የምህርት አዋጁን የተቀበሉ የአገዛዙ የአድማ ብተና አባላት ዛሬም እንደትናንቱ ከጠላት ካፕ በመኮብለል 105ኛ ኮር የ55ኛ ክ/ጦር የፋኖ አባላትን እየተቀላቀሉ ነው።
የምህረት አዋጁን የተቀበሉ አባላት፦

1ኛ ረዳት ሳጅን ሀብቴ ላቀው
2ኛ ኮንስታብል ወርቅየ አበበ
3ኛ ኮንስታብል ሰኢድ ሁሴን የተባሉ የአድማ ብተና አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው ሻውራ አካባቢ ከሚንቀሳቀሰው የጠላት ሀይል በመውጣት የ105ኛ ኮር የ55ኛ ክ/ጦር የፋኖ አባላት ተቀላቅለዋል።

_____፪
የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም የቆመውና በቋሪት ወረዳ የመሸገው 76ኛ ክፍለ-ጦር አባላት የነበሩ ሦስት ሚሊሻዎች፣ የአገዛዙን ሰንሰለት በመበጠስ ትጥቃቸውን ሙሉ በሙሉ ይዘው የዐማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄን (አፋብን) በክብር ተቀላቅለዋል።

1.እንዳላማው ድረስ
2. የቻለ በለጠ እና
3. ስሜነህ ታፈረ የተባሉ የሚሊሻ አባላት 102ኛ ኮር 33ኛ ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል።
የምህረት አዋጁ አማራን የሚባል ሕዝብ ለማዳን ነውና ሁሉም ሊጠቀምበት ይገባል። አማራ እርስበርሱ መጋደል የለበትም ሊጠፋ የተፈረደበት ሕዝብ ልጆችነንና ኑ ተቀላቀሉን።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
አፋብን| ቴወድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የካቲት 14/2018 ዓ.ም
👍2
የአደረጃጀት/የሪፎርም ዜና

አፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር አድዋ ክ/ጦ ለ7 ቀናት ያክል ከቀጠናው የዕዙ ግብረ-ሀይል ማለትም አርበኛ ዮሀንስ ንጉሱ፣ አርበኛ ስጦታው ዳኛው(ባሻ)፣ አርበኛ ታደሰ ወርቁ ፣አርበኛ መቶ አለቃ ቢራራ፣ አርበኛ ኢንጅነር በየነ አለማው፣ አርበኛ ሚኒያስ አለማየሁ፤ ከኮሩ ከፍተኛ አመራር ጋር በመሆን ጥልቅ ግምገማና ውይይት በማድረግ፣ የስራ ተግዳሮቶችን እና መልካም አጋጣሚዎችን በመለየት ለቀጣይ ክ/ጦሯን በሁሉም ዘርፍ ሁለንተናዊ የድርጅት መርህን በተከተለ መልኩ ስራዎችን ተደራሽ ማድረግና ለውጤት መታተር እንደሚገባ የጋራ መግባባት ላይ መድረስ ተችሏል።ከዚህ በተጨማሪ በማንኛውም አይነት የስራ ዘርፍ መርህን ባማከለ መልኩ በኃላፊነት ተግባራትን ከመከዎን ባሻገር በመርህ እዝ እና ሰንሰለትን ጠብቆ መልካም የስራ ውጤቶችን እውቅና መስጠት እንደሚገባ ሁሉ መጠየቅም እንዳለ በአፅኖት ተገልጿል ተፈፃሚም ሆኗል።

በዚህ ጥልቅ ግምገማ የአድዋ ክ/ጦ መልካም ስራዎችንና ተሞክሮዎችን በማድነቅ እንዲሁም እውቅና በመስጠት አድናቆትን ያገኙ ሲሆን በሁለንተናዊው የስራ ዘርፍ ተግዳሮት ሆነው የማያሰሩ እንቅፋቶችን በመለየት የቀጣይ ድርጅታዊ አቅጣጫ በማስቀመጥ ችሎታንና አቅምን ባማከለ እና ለተሻለ ግዳጅ በሚያመች መልኩ የመሪዎች ሪፎርም ሊሰራ ችሏል። ከዚህ በተጨማሪ የአድዋ ክ/ር ካሉት ብርጌዶች መካከል በሁለቱ ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ የብርጌድ ሪፎርም በተሳካ ሁኔታ መስራት ተችሏል።

👉የክ/ር ሪፎርም:
1. የክ/ር ወታደራዊ ዋና አዛዥ.....................አርበኛ ተመስገን ወለላው
2. ም/ወ/አዛዥ.................................አርበኛ ገብረማርያም በየነ
3. የክ/ር ዘመቻ................................አርበኛ ጌጤ ደሳለኝ
4. የክ/ር ም/ዘመቻ............................አርበኛ ቻሌ መኩ
5. የክ/ሩ ልዩ ኦፕሬሽን ኃላፊ..................አርበኛ ገበያው አቤ
6. የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ......................አርበኛ ተስፋ ጌታሁን
7.የፅ/ቤት ኃላፊ.............................አርበኛ ጌታቸው ማንደፍሮ
8. የህ/ግንኙነት ኃላፊ.....................አርበኛ ዳንኤል አቡሀይ
9.ህዝብ አስተዳደር.........................አርበኛ አዳም ውበት
10.አደረጃጀት...................................አርበኛ ተዋቸው አንመው
11. የሰው ሀይል አስተዳደር................አርበኛ ኤፍሬም መዝገቡ
12. ሎጀስቲክ..................................አርበኛ ሀብታሙ ደምለው
13.ትምህርትና ስልጠና.......................አርበኛ ብርሌው አበባው
14.ፋይናንስ........................................አርበኛ አየሁ አለሙ

👉የብርጌድ ሪፎርም:
1ኛ.የንጋት ጮራ ብርጌድ
አርበኛ መኳንንት አንዳርጌ.........ዋና ብርጌድ መሪ
አርበኛ ምረቴ አወቀ....................ምክትል ብርጌድ መሪ
አርበኛ እሸቴ ይስማው.................የብርጌድ ዘመቻ
👉የነብሮ ብርጌድ ሪፎርም
አርበኛ መኳንንት ተገኘ.................ዋና ብርጌድ መሪ
አርበኛ ፍቅሩ ..................ምክትል ብርጌድ መሪ
አርበኛ ደሴ ባየ............................የብርጌድ ዘመቻ

የተሰራውን የመሪዎች ሪፎርም ሁሉም የሰራዊት አባላት በሙሉ ድምፅ ከማፅደቃቸው በተጨማሪ ሁሉም የክ/ጦ አመራሮች በሰራዊቱ ፊት እንዲሁም የአፋብን ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሳሙኤል ባለድል፣ የዕዙና የኮር አመራር ባሉበት በታማኝነት፣ በፍታዊነት፣ በቅንነት፣ እዝ እና ሰንሰለትን በመጠበቅ ከትናንት ተግዳሮቶቻችን ተምረን፣ ጠንካራ ጎኖቻችን የበለጠ አጠንክረን በተሻለ የስራ አፈፃፀም የአማራን የህልውና ትግል አሸናፊ ሆኖ የድል ችቦ ለማብራት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳንል አማራዊ ግዴታችን እንወጣለን ሲሉ ቃል ኪዳን ገብተዋል።

በመጨረሻም የዕዝ ግብረሀይሉና የኮሩ አመራር የአድዋን ክ/ጦ አመራሮች በጋራ በመሆን ድርጅታዊ መርህንና አሰራርን ተከትሎ መስራት፣ በየዘርፉ በተጠያቂነትና በኃላፊነት ስራዎችን መከወን፣ በግምገማ ተግዳሮቶችን መለየትና አቅጣጫ ማስቀመጥ፣ የተሻለ የስራ አፈፃፀምን ማስቀጠልና ለታሪክ መሰነድ እንደሚገባ በጋራ መክረዋል። ለቀጣይ የስራ ጉድለቶችን በስልጠና ማስተካከልና በዕውቀት ማማ ስር ሆኖ ትግሉን በፍጥነት ተሻጋሪ እንዲሆን ከማድረግ አንፃር አፅኖት የተሰጠው ጉዳይ ሆኗል።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
አፋብን ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር የህ/ግ
የካቲት 14/2018
👍21🙏1
የአደረጃጀት/የሪፎርም ዜና

አፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር አድዋ ክ/ጦ ለ7 ቀናት ያክል ከቀጠናው የዕዙ ግብረ-ሀይል ማለትም አርበኛ ዮሀንስ ንጉሱ፣ አርበኛ ኢንጅነር በየነ አለማየሁ፣ አርበኛ የሻንበል አምሳሉ ማዘንጊያ፣አርበኛ ስጦታው ዳኛው(ባሻ)፣ አርበኛ ታደሰ ወርቁ ፣አርበኛ መቶ አለቃ ቢራራ፣ አርበኛ ሚኒያስ አለማየሁ ፤ ከኮሩ ከፍተኛ አመራር ጋር በመሆን ጥልቅ ግምገማና ውይይት በማድረግ፣ የስራ ተግዳሮቶችን እና መልካም አጋጣሚዎችን በመለየት ለቀጣይ ክ/ጦሯን በሁሉም ዘርፍ ሁለንተናዊ የድርጅት መርህን በተከተለ መልኩ ስራዎችን ተደራሽ ማድረግና ለውጤት መታተር እንደሚገባ የጋራ መግባባት ላይ መድረስ ተችሏል።ከዚህ በተጨማሪ በማንኛውም አይነት የስራ ዘርፍ መርህን ባማከለ መልኩ በኃላፊነት ተግባራትን ከመከዎን ባሻገር በመርህ እዝ እና ሰንሰለትን ጠብቆ መልካም የስራ ውጤቶችን እውቅና መስጠት እንደሚገባ ሁሉ መጠየቅም እንዳለ በአፅኖት ተገልጿል ተፈፃሚም ሆኗል።

በዚህ ጥልቅ ግምገማ የአድዋ ክ/ጦ መልካም ስራዎችንና ተሞክሮዎችን በማድነቅ እንዲሁም እውቅና በመስጠት አድናቆትን ያገኙ ሲሆን በሁለንተናዊው የስራ ዘርፍ ተግዳሮት ሆነው የማያሰሩ እንቅፋቶችን በመለየት የቀጣይ ድርጅታዊ አቅጣጫ በማስቀመጥ ችሎታንና አቅምን ባማከለ እና ለተሻለ ግዳጅ በሚያመች መልኩ የመሪዎች ሪፎርም ሊሰራ ችሏል። ከዚህ በተጨማሪ የአድዋ ክ/ር ካሉት ብርጌዶች መካከል በሁለቱ ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ የብርጌድ ሪፎርም በተሳካ ሁኔታ መስራት ተችሏል።

👉የክ/ር ሪፎርም:
1. የክ/ር ወታደራዊ ዋና አዛዥ.....................አርበኛ ተመስገን ወለላው
2. ም/ወ/አዛዥ.................................አርበኛ ገብረማርያም በየነ
3. የክ/ር ዘመቻ................................አርበኛ ጌጤ ደሳለኝ
4. የክ/ር ም/ዘመቻ............................አርበኛ ቻሌ መኩ
5. የክ/ሩ ልዩ ኦፕሬሽን ኃላፊ..................አርበኛ ገበያው አቤ
6.. የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ......................አርበኛ ተስፋ ጌታሁን
7.የፅ/ቤት ኃላፊ.............................አርበኛ ጌታቸው ማንደፍሮ
8. የህ/ግንኙነት ኃላፊ.....................አርበኛ ዳንኤል አቡሀይ
9..ህዝብ አስተዳደር.........................አርበኛ አዳም ውበት
10አደረጃጀት...................................አርበኛ ተዋቸው አንመው
11. የሰው ሀይል አስተዳደር................አርበኛ ኤፍሬም መዝገቡ
12.ሎጀስቲክ..................................አርበኛ ሀብታሙ ደምለው
13.ትምህርትና ስልጠና.......................አርበኛ ብርሌው አበባው
14.ፋይናንስ........................................አርበኛ አየሁ አለሙ

👉የብርጌድ ሪፎርም:
1ኛ.የንጋት ጮራ ብርጌድ
አርበኛ መኳንንት አንዳርጌ.........ዋና ብርጌድ መሪ
አርበኛ ምረቴ አወቀ....................ምክትል ብርጌድ መሪ
አርበኛ እሸቴ ይስማው.................የብርጌድ ዘመቻ
👉የነብሮ ብርጌድ ሪፎርም
አርበኛ መኳንንት ተገኘ.................ዋና ብርጌድ መሪ
አርበኛ ፍቅሩ ..................ምክትል ብርጌድ መሪ
አርበኛ ደሴ ባየ............................የብርጌድ ዘመቻ

የተሰራውን የመሪዎች ሪፎርም ሁሉም የሰራዊት አባላት በሙሉ ድምፅ ከማፅደቃቸው በተጨማሪ ሁሉም የክ/ጦ አመራሮች በሰራዊቱ ፊት እንዲሁም የአፋብን ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሳሙኤል ባለድል፣ የዕዙና የኮር አመራር ባሉበት በታማኝነት፣ በፍታዊነት፣ በቅንነት፣ እዝ እና ሰንሰለትን በመጠበቅ ከትናንት ተግዳሮቶቻችን ተምረን፣ ጠንካራ ጎኖቻችን የበለጠ አጠንክረን በተሻለ የስራ አፈፃፀም የአማራን የህልውና ትግል አሸናፊ ሆኖ የድል ችቦ ለማብራት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳንል አማራዊ ግዴታችን እንወጣለን ሲሉ ቃል ኪዳን ገብተዋል።

በመጨረሻም የዕዝ ግብረሀይሉና የኮሩ አመራር የአድዋን ክ/ጦ አመራሮች በጋራ በመሆን ድርጅታዊ መርህንና አሰራርን ተከትሎ መስራት፣ በየዘርፉ በተጠያቂነትና በኃላፊነት ስራዎችን መከወን፣ በግምገማ ተግዳሮቶችን መለየትና አቅጣጫ ማስቀመጥ፣ የተሻለ የስራ አፈፃፀምን ማስቀጠልና ለታሪክ መሰነድ እንደሚገባ በጋራ መክረዋል። ለቀጣይ የስራ ጉድለቶችን በስልጠና ማስተካከልና በዕውቀት ማማ ስር ሆኖ ትግሉን በፍጥነት ተሻጋሪ እንዲሆን ከማድረግ አንፃር አፅኖት የተሰጠው ጉዳይ ሆኗል።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
አፋብን ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር የህ/ግ
የካቲት 14/2018
6🙏1
አፋብን ሰ/አ/ቀ በላይ ዕዝ
ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር
ጉና ክፍለ ጦር ሁሉም ብርጌድ በተሳተፋበት ውጊያ ትልቅ ድል ተገኘ

========================
አፋብን ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ሜ/ጀ ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር፦
ጉና ክፍለ ጦር ሙሉ ስራ አስፈፃሜ፣
የሜ/ጀ ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ስራ አሰፈፃሜ፣
የጉና ክፍለ ጦር 5ቱም ብርጌዶች(እሥቴ ዴንሳ ብርጌድ፣ ገ/መሥቀል ብርጌድ፣ ሐገረ ቢዘን ብርጌድ፣ አንዳቤት ብርጌድና መቅደላ አምባ ብርጌድ
ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር እና
የጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ፦
ተራራው ራሥ ጉና ክፍለ ጦር በጥምረት በሰሩት አኩሪ መቀናጀት ትልቅ ድል ተመዝግቧል።

የብርሃኑ ጁላ አራዊት ሰራዊት ጥምር ጦር መነሻውን ደብረታቦር ከተማ አድርጎ ሌሊት ጀምሮ ወደ ክምር ድንጋይ አቅጣጫ የወጣው የጠላት ሃይል አርሴማ፣ ጋሳይ ፣ ዘበራ እና ክምር ድንጋይ በተባሉ ቦታዎች በተደረገ አውደ ውጊያ የጀግኖች ምድር ክንደ ነበልባሎች ወሳኝ ቦታዎችን ቀድመው በመያዝ ከጠዋቱ 2:25 ጀምሮ እስከ ምሽት 12:30 ድርስ በተደረገ አውደ ውጊያ የአገዛዙ ወንበር ጠባቂ ሁለት ፖትሮለ ቁስለኛ መጠኑ በውል ያልታወቀ ሙት በየ መንገዱ ሲያንጠባጥብ ውሏል።
በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ የደረሰ ሲሆን ለጊዜው 2 ብሬን እና 2 M14 የቡድን መሣሪያዎች ከጠላት በምርኮ ሲገኙ፣ 1 ዙ-23 ከጥቅም ውጭ ተደርጎ ተመትቷል። ክላሽና ሌሎች የምርኮና የተተኳሽ መሣሪያዎች እንደደረሱን እናቀርባለን። ሌሎች መረጃዎችም በተመሣሣይ ይደርሳሉ።

በዚህ ውጊያ ጉና ክፍለ ጦርና ተራራው ራሥ ጉና ክ/ጦር የአንበሳውን ድርሻ ወስደዋል።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን👊
አፋብን ሰ/አ/ቀ በላይ ዕዝ
ሜ/ጀ ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር
ጉና ክ/ጦር ሕ/ግ ክፍል
ፋኖ መምሕር ያሬድ ገደፋው
7🙏1
አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ታላቅ ጀብድ በመፈጸም ላይ ነው።

የካቲት14/2018 ዓ.ም ከደብረ ታቦር ወደ ክምር ድንጋይ በእንቅስቃሴ ላይ የነበረን የአገዛዙ ሰራዊት በተራራው ራስ ጉና ክፍለ ጦር አይቀጡ ቅጣት እየተቀጣ ነው። ከዲሽቃ እስከ ከዙ-23 የታጠቀው የጠላት ኃይል ክምር ድንጋይን የቀመጫ ማኢከል ለማድረግ እና ንፋስ መውጫ ካለው ኃይል ጋር በጥምረት ቀጠናውን እቆጣጠራለው የሚል የህልም አለም ቅዠት ቢኖረውም ሳይሳካለት እተቀጠቀጠ ይገኛል።
ከጋሳይ እስከ ዘበራ ባለው የአውደ ውጊያ ውሎ ከ30 በላይ ሙት አስተናግዶ አስከሬኑን እያዝረከረከ በማፈግፈግ ላይ የሚገኝ ሲሆን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ቁስለኛ ደግሞ ወደ ደብረታ ቦር ሆስፒታል ሸኝቷል። እስካሁን ገቢ የሆኑ በምርኮዎች:-
## 1==ብሬን
## 1===m14
## 15===ክላሽ ኮፕ
በሌላኛው አውደ ውጊያ ደግሞ አፋብን ጎጠግዕ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ከንፋስ መውጫ ከተማ ተነስቶ ወደ ክምር ድንጋይ ከደብረ ታቦር ለሚንቀሳቀሰው ኃይል ለመድረስ እና ሽፋን ለመስጠት ወደ ጎብጎብ በመንቀሳቀስ ላይ እያለ የጀግኖቹን ብርቱ ክንድ አስተናግዶ ሙትና ቁስለኛውን ታቅፎ ወደ ተነሳበት ንፋስ መውጫ ከተማ መልሶ እንዲገባ ተደርጓል ።

በዚህ አውደ ውጊያ ከፍተኛ ቀጠናዊ ትስስር የተጋመደበት ወታደራዊ ግዳጅ የነበር ሲሆን አንበሳው ጋይንት ክፍለ ጦር መኳቢያ ፣ኡራኤል ፣ማደያ ፣ጣሪያ ጊዬዎርጊስ አካባቢ ትንቅንቅ ሲያደርግ ገብርዬ ክፍለ ጦር ደግሞ ከየደሮ አቅጣጫ እና ክሬቸር አካባቢ የጠላትን ኃይል ከፍተኛ ኪሳራ እንዲያስተናግድ ሲያደርገው በሌላኛው የአውደ ውጊያ ግንባር ደግሞ አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ሚኒሊክ ዕዝ ደጋው መብረቅ ኮር ከሦስት ክፍለ ጦር የተውጣጣ ኃይል እና ሌሎች በቀጠናው እሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት ደግሞ በአምባ ማርያም አቅጣጫ የተናበበ ምትን አሳርፈውበት ከፍተኛ ጉዳት አስተናግዷል ።
በነዚህ የአውደ ውጊያ ግንባሮች:-

## ከ20 በላይ ክላሽ ኮፕ
## በርካታ የዲሽቃና የክላሽ ኳፕ ተተኳሾች
## 10 የሚሊሻ እና ፖሊስ ምርኮ
## ከ35 በላይ ሙት
## 55 ቁስለኛ ታቅፎ ንፋስ መውጫን የሙጥኝ ብሏል።


ድል ለአማራ ፋኖ!!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!!
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ህዝብ ግንኙነት !!!
የካቲት 14/ 2018 ዓ.ም
4🙏1
የደብረ ታቦር ከተማ ብልጽግና፣ የደቡብ ጎንደር ዞን ብልጽግና እና አጠቃላይ የአቢይ አሕመድ ኮርቻ አማሮች ዋይታ
[የካቲት 15/2018ዓ.ም]

የአገዛዙ አራዊት ሰራዊት በቀን 14/06/2018ዓ.ም ከጋሳኝ እሥከ አርሴማ፣ ከዘበራ እሥከ ክምር ድንጋይ በአምሐራ ፋኖ ዛብሯል፣ ተገርፏል፣ ተማርኳል፣ ተደምስሷል፣ ከቁሳዊ እሥከ አካላዊ እና ከሞራላዊ እሥከ መዋቅራዊ መፈራረሥ ደርሶበታል። በዚህ የተነሳም ብዛት ያለው የአገዛዙ አራዊት ሰራዊት ሙትና ቁሥለኛ ሲሆን ጫካ ወድቀው ከቀሩት ውጭ በጅምላ ሆሥፒታል የተወሰዱት ላይመለሱ ማሸለባቸውን ተከትሎ አገዛዙ ደብረ ታቦር ሆሥፒታል በአቢይ አራዊት ሰራዊት አሥከሬን ሞልቶብኛልና የደብረ ታቦር ከተማ በተለይም የሰኞ ገበያ በጎ ፈቃድ ሰጭ ወጣቶች ኑና አቃብሩኝ፤ ብቻዬን አልቻልኩም ያለበት መልዕክት በውሥጥ የመረጃ ምንጮቻችን መሰረት በዚህ ልክ ደርሶናል።

የጊዜ ጉዳይ ሆኖ ትግሉ ሊረዝም ይችላል እንጅ ፀሐይ በምሥራቅ የመውጣቷን ያክል የዓምሐራ ሕዝብ ትግልም አሸናፊ እንደሚሆን 100% ዕናምናለን እናውቃለን።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ዝንተዓለም ዓምሐራ Forever AMHARA👊

አፋብን ሰ/አ/ቀ በላይ ዕዝ
ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ሕ/ግ መምሪያ
ፋኖ ኢንጅነር ኃቅአለው ፀጋ አለባቸው

ቋሚ ምሥል፦ የአገዛዙ አቃብሩኝ ጥሪ ለሚቀርቡት ወዳጆቹ
🙏1
ፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና ደቡብ ወሎ ዞን በወግዲ ወረዳ ህዝብ ላይ በድሮን ሳይቀር እያደረሰ ያለው ጭፍጨፋ ተጠናክሮ ቀጥሏል!

ፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና በወግዲ ወረዳ ንጹሃን ላይ ያነጣጠረ የድሮን ጥቃትና የከባድ መሳሪያ ድብደባ በመፈፀም በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት አደረሰ::

​በደቡብ ወሎ ዞን ወግዲ ወረዳ የሚገኙ ሰላማዊ አርሶ አደሮች በሰው ህይወትና በእንስሳቶች የከፋ ጥቃትና የንብረት ውድመት እየደረሰባቸው መሆኑን እየገለፁ ይገኛሉ:: ከትናንት ወዲያ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በወረዳው ልዩ ስማቸው 016 እና 017 ተብለው በሚጠሩ ቀበሌዎች ውስጥ በተፈጸመ አምስት ዙር የድሮን ድብደባ በንጹሃን ህይወትና ንብረት እንዲሁም እንስሳቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

​አገዛዙ በፈፀመው የድሮን ድብደባ ንፁሃኖች ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን በርካታ የአርሶ አደሮች እንስሳቶች ተገድለዋል። በተጨማሪም ከጥቃቱ ጎን ለጎን በአካባቢው የተሰማራው 11ኛ ዕዝ እና ሪፐብሊካን ጋርድ የተባለ የብልፅግና ጦር የአርሶ አደሮችን ንብረት የመዝረፍና የማውደም ተግባር በሰፊው እየፈፀመ ይገኛል:: በዚህም ስምንት በሬዎች እና አስራ ስምንት ፍየሎች በአካባቢው በነበረው የብልፅግና ሰራዊት ተዘርፈው ተወስደዋል። በተጨማሪም አርሶ አደሩ ለምግብነትና ለገበያ ያከማቸው አስራ አራት ኩንታል ጤፍ በፋሽስቱ ሰራዊት ተዘርፏል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምኒልክ ዕዝ
የካቲት 15/2018 ዓ.ም
💔1
አፋብን ያወጣውን የምህረት አዋጅ ሳይጠቀሙ ቀርተው የፋሽስቱን አገዛዝ ብልፅግና ተልዕኮ በማስፈፀም ላይ የነበሩ ታጣቂዎች ላይ የማያዳግም አስተማሪ እርምጃ ተወሰደ::

በመካነሰላም ዙርያ ማለትም ሙደለላ 031 ቀበሌ ከአምሃራ ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር አትሮንስ ሻለቃ እና ኢንጅነር ደሳለኝ አሰፋ ክፍለ ጦር በተውጣጡ ሻለቃዎች የተናበበና የተቀናጀ ውጊያ በሙደለላ ታዳጊ ከተማ የተቀመጠ ከፓሊስ፣ ከሚኒሻና ከሰላም አስከባሪ ተጣምረው የተቀመጡትን የስርአቱ ወንበር ጠባቂወች ከህዝባቸው ይልቅ አለቃቸውን ያመኑ ከህሊናቸው ይልቅ በሆዳቸው የተገዙ የዘመናችን ደናቁርቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወስዶባቸዋል።

በዚህም የፋኖን የምህረት አዋጅ ያልተቀበሉ የኦሮሞ የብልፅግና አገልጋይ ፖሊስና ሚሊሻ ላይ ዛሬ የካቲት 15/2018 ዓ.ም በተወሰደው የማያዳግም አስተማሪ እርምጃ ከሃያ በላይ ሙትና ቁስለኛ የተደረጉ ሲሆን 11 ክላሽ፣ አንድ ሽጉጥ እንዲሁም በርካታ የደረትና የወገብ ትጥቆች ተማርከዋል::

በተጨማሪም መካነሰላም ዙርያ በሰኞ ገበያ ተዋ መገንጠያ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ውጊያ ፋኖ በወሰደው መብረቃዊ ጥቃት በአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ላይ ግለቱን የጠበቀ ውጊያ ተደርጎ በጠላት ላይ ከባድ ኪሳራ ደርሶበታል። ፋኖም ይዞታውን ያስጠበቀ ሲሆን ጠላት አንድ አንቡላስ ሙትና ቁስለኛውን ጭኖ ወደመጣበት ተመልሷል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምኒልክ ዕዝ
የካቲት 15/2018 ዓ.ም
🙏1
በጥር 6/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ሳሲት ከተማ ላይ በአገዛዙ የአየር ወለድ ኮማንዶ ጨፍጫፊ ሀይል በተደረገባቸው ከበባ እጅ ስጡ ሲባሉ አሻፈረኝ፣ ለጠላት እጅ ሰጥተን ትግላችንን፣ የትግል ጓዶቻችንን፣ አላማችንንና ህዝባችንን አንከዳም በማለት የያዙትን ተተኳሽ እስከሚጨርሱ ከጠላት ጋር ተታኩሰው በመጨረሻም 50 አለቃ ታደሰና ጓዶቹ በራሳቸው ጥይት የክብር መሰዋዕትነትን ከተቀበሉ እነሆ ዛሬ 40 ቀን ሞላቸው።

በዚህም የ40 ቀን መታሰቢያቸውን ምክንያት በማድርግ በተሰውበት አካባቢ ሳሲት ላይ የሳሲት ከተማ ነዋሪዎች፣ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አመራሮችና ሰራዊት በተገኙበት የጧፍ ማብራት ፕሮግራም እንዲሁም በወታደራዊ ሰልፍ ቀኑ ታስቦ ውሏል❗️

የካቲት 15/2018 ዓ.ም

ክብር አስከብረውን ለወደቁ ሰማዕት ጀግኖቻችን 🕯️🕯️🕯️

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ
ድል ለአማራ ህዝብ 🟢🟡🔴

https://t.me/shewafa
👍1