"ትዝታ ፣ ናፍቆት ፣ ህመም"
ያምናው በሽታዬን
ያምናው ትዝታዬን ማነው የቀሰቀሰው
ትናፍቀኝ ጀመር የማልናፍቃት ሰው።
ክራሬን አነሳሁ ደሞ ጀማመረኝ
በትዝታ ቅኝት ለናፈቀኝ ልቀኝ ፤
ነካካሁት ክሩን
ገረፍኩት ክራሩን
ያቃስት ጀመረ እንደታመመ ሰው
ነፍሴን አሳቀቃት ልቤን አላወሰው
እህ ብቻ ሆነ የናፍቆት ህመሙ
ሲቃ ብቻ ሆነ ዜማዉና ግጥሙ ፤
ህመም ተለወጠ ነገር ተቀየረ
ከታች አምናው ባሰ መልኩን ቀያየረ
እህ ብቻ ሆኖ ነፍስ ማድማት ጀመረ ፤
እህ ትዝታዬ
እህ በሽታዬ እህ የኔ ህመም
አንችን እያሰቡ
መሞትም ውበት ነው እንኳንስ መታመም።
abu
╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗
@geyone
@geyone
╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝
❥❥________⚘_______❥❥
ያምናው በሽታዬን
ያምናው ትዝታዬን ማነው የቀሰቀሰው
ትናፍቀኝ ጀመር የማልናፍቃት ሰው።
ክራሬን አነሳሁ ደሞ ጀማመረኝ
በትዝታ ቅኝት ለናፈቀኝ ልቀኝ ፤
ነካካሁት ክሩን
ገረፍኩት ክራሩን
ያቃስት ጀመረ እንደታመመ ሰው
ነፍሴን አሳቀቃት ልቤን አላወሰው
እህ ብቻ ሆነ የናፍቆት ህመሙ
ሲቃ ብቻ ሆነ ዜማዉና ግጥሙ ፤
ህመም ተለወጠ ነገር ተቀየረ
ከታች አምናው ባሰ መልኩን ቀያየረ
እህ ብቻ ሆኖ ነፍስ ማድማት ጀመረ ፤
እህ ትዝታዬ
እህ በሽታዬ እህ የኔ ህመም
አንችን እያሰቡ
መሞትም ውበት ነው እንኳንስ መታመም።
abu
╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗
@geyone
@geyone
╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝
❥❥________⚘_______❥❥
_
Vergine Tube ድንግል ቱዩብ
ሴና ክፍል አሥራ ስምንት ❤️
. . . ቅናት ይሁን ንዴት ብቻ አላውቅም ውስጤ በጣም ተረበሸ እንዴ ግን ምንድነው እንደዚ ሚያደርገኝ ሳምንት ላወኩት ልጅ? አላውቅም የተወሳሰበ ስሜት ነው ሚሰማኝ እንዲህ ነው ብዬ ማልናገረው፡፡
ዴቭ አዲሷ አሮጌዋ አሮጊቷ እያለ ለፍሬ ሚስት መረጣ ጀመረ፡፡ "እውነት አግብቷል?" አልኩት ዴቭን አይን አይኑን እየተመለከትኩ፡፡ "ያው ቀለበት አላሰረላትም እንጂ ሚስቱ በያት፡፡ደሞ ላልተዋት ቃል ገብቻለው ምናምን ሲል ነበር" አለኝ ወደኔ እየተመለከተ፡፡ ደግሜ አልጠየኩትም፡፡ ቀኑን በጣም ከብዶኝ ዋልኩ፡፡ ዶርም እንደገባው ልብሴን እንኳን ሳልቀይር ነው አልጋዬላይ ወጥቼ ጋደም አልኩ፡፡ ማንንም አላናገርኩም፡፡ ልቤ ድንግጥ ድንግጥ ይላል፡፡ አልጋዬላይ ጋደም እንዳልኩ ስልኬን አስር ግዜ አየዋለው ፍሬ ከደወለ ወይም መልእክት ከላከ ብዬ፡፡ ምንም አዲስ ነገር የለም፡፡ ፍሬን ሳላገኝ ዋልኩ አደርኩ፡፡
ጥዋት እንደተነሳው ልደውልለት አስቤ ነገር ግን ለምን እሱ አይደውልም ስል መልሼ ተውኩት፡፡ ክፍል ገብቼም ቡዙም ደስተኛ አልነበርኩም፡፡ ቆይ ምን ነካኝ እንዴ ፍሬ አይደለም ፍቅረኛ ልጅ ቢኖረው እኔ ምን ቸገረኝ ስል ከራሴ ጋር መሟገት ጀመርኩ፡፡ አስተማሪው ምን እንዳለ በቅጡ ሳልሰማ ከክፍል ወጣን፡፡ ድብርብር ነው ያለኝ፡፡
ምሳ ሰአት ላይ ፍሬን አገኘውት፡፡ ተጠምጥሜበት ነው ሰላም ያልኩት፡፡ ሌላ ግን ምንም ያወራሁለት ነገር የለም፡፡ አብረን ምሳ በልተን የለመድንበት ቦታ ቁጭ ብለን ስንጨዋወት ዋልን፡፡ ፍሬን ስለፍቅረኛው ልጠይቀው እያልኩ ፈራና ተወዋለው፡፡ እነሚጣንም ካወራዋቸው ሌላ ነገር ይመስላል በዬ በማሰብ ተውኩኝ፡፡ ታዲያ ማንን ላውራ? ትንሽ ካሰቡኩ ቡሀላ ለምን ለቹቹ አልነግራትም ስል አሰብኩ፡፡ ምናልባት እሷ ከነ ሚጣ ጋር ስለማትገናኝ ሚስጥሬ የተጠበቀ ይሆናል ብዬ አሰብኩ፡፡ ሳልውል ሳላድር ላነጋግራት ፈለኩ፡፡
ማታ ዶርም ስገባ እሷም ጉዋደኞቿም የሉም፡፡ ጥዋት ወደ ክፍል ሲሄዱ ግን ያየዋቸው መሰለኝ፡፡ ለማንኛውም አምሽተውም ቢሆን መምጣታቸው አይቀርም ብቻ ውጪ እንዳያድሩ እንጂ እያልኩ በሆዴ አወራ ጀመር፡
ማታ ከፍሬ ጋር ፅሁፍ እያወራው አልጋላይ ቁጭ ብዬ የነቹቹን መምጣት እጠባበቅ ጀመር፡፡ 'ወይ ታሪክ ዛሬ ደሞ ቹቹ ናፈቀችኝ' አልኩ በሆዴ ፡፡ ነገሮችን አስቤያቸው ሳቄን ለከኩት፡፡ ብቻዬን ስስቅ እነሚጣ በየ አልጋቸው ላይ እንደሆኑ የየራሳቸውን ስራ እየሰሩ"ሆሆሆ የዛሬው ደሞ ጫን ያለው ነው፡፡" ሲሉ ሰማለው፡፡ አልታወቀኝም እንጂ ብዙ ግዜ ነው ለካ የሳኩት፡፡
ቁጭ እንዳልኩ ትንሽ ቆይተው እነ ቹቹ በር ማንኳኳት ጀመሩ፡፡ ከአልጋዬ ላይ እንዴት ወርጄ በሩን እንደከፈትኩላቸው፡፡ እነ ሚጣ ገርሞአቸው ያዩኛል፡፡ እነ ቹቹን ሰላም ብዬ ወደ አልጋዬ ተመለስኩ፡፡ እንደለመዱት ሰክረዋል፡፡ አሁን ልታናግረኝ ስማትችል ያለኝ አማራጭ ነገ ነው፡፡ ከፍሬ ጋር ተሰነባብቼ ተኛው፡፡ ጥዋት ክፍል እንድሄድ ሲቀሰቅሱኝ ትንሽ ራሴን አመም አድርጎኛል አልሄድም ብያቸው ቀረው፡፡ እነሱ ከወጡ ቡሀላ ቹቹ ከእንቅልፏ እስክትነቃ ቁጭ ብዬ መጠበቅ ጀመርኩ፡፡
ብዙ ከጠበኳት ብሀላ አልነሳ ብትለኝ ትእግስት ስላጣው ቀሰቀስኳት፡፡ ቹቹ የግዷን ተነሳች፡፡ ላናግራት እንደምፈልግ ነግሬያት በዛውም ቁርስ ልጋብዛት ይዥት ወጣው፡፡
ካፌ እንደደረስን ምግብ አዘን እየተመገብን ከምን እንደምጀምርላት ግራ ገባኝ፡፡ "እኔ ምልሽ እእእእ . . . . " እያልኩኝ ስንተባተብ "አቦ ንገሪኛ ልቤን ሰቀልሽው እኮ" አለችኝ ጮክ ብላ፡፡" አረ ድምፅሽን ዝቅ አድርጊ እሺ ነግርሻለው "አልኳት፡፡ ከወንበሬ ተመቻችቼ ከተቀመጥኩ ቡሀላ . . .
#ክፍል_አስራዘጠኝን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
. . . ቅናት ይሁን ንዴት ብቻ አላውቅም ውስጤ በጣም ተረበሸ እንዴ ግን ምንድነው እንደዚ ሚያደርገኝ ሳምንት ላወኩት ልጅ? አላውቅም የተወሳሰበ ስሜት ነው ሚሰማኝ እንዲህ ነው ብዬ ማልናገረው፡፡
ዴቭ አዲሷ አሮጌዋ አሮጊቷ እያለ ለፍሬ ሚስት መረጣ ጀመረ፡፡ "እውነት አግብቷል?" አልኩት ዴቭን አይን አይኑን እየተመለከትኩ፡፡ "ያው ቀለበት አላሰረላትም እንጂ ሚስቱ በያት፡፡ደሞ ላልተዋት ቃል ገብቻለው ምናምን ሲል ነበር" አለኝ ወደኔ እየተመለከተ፡፡ ደግሜ አልጠየኩትም፡፡ ቀኑን በጣም ከብዶኝ ዋልኩ፡፡ ዶርም እንደገባው ልብሴን እንኳን ሳልቀይር ነው አልጋዬላይ ወጥቼ ጋደም አልኩ፡፡ ማንንም አላናገርኩም፡፡ ልቤ ድንግጥ ድንግጥ ይላል፡፡ አልጋዬላይ ጋደም እንዳልኩ ስልኬን አስር ግዜ አየዋለው ፍሬ ከደወለ ወይም መልእክት ከላከ ብዬ፡፡ ምንም አዲስ ነገር የለም፡፡ ፍሬን ሳላገኝ ዋልኩ አደርኩ፡፡
ጥዋት እንደተነሳው ልደውልለት አስቤ ነገር ግን ለምን እሱ አይደውልም ስል መልሼ ተውኩት፡፡ ክፍል ገብቼም ቡዙም ደስተኛ አልነበርኩም፡፡ ቆይ ምን ነካኝ እንዴ ፍሬ አይደለም ፍቅረኛ ልጅ ቢኖረው እኔ ምን ቸገረኝ ስል ከራሴ ጋር መሟገት ጀመርኩ፡፡ አስተማሪው ምን እንዳለ በቅጡ ሳልሰማ ከክፍል ወጣን፡፡ ድብርብር ነው ያለኝ፡፡
ምሳ ሰአት ላይ ፍሬን አገኘውት፡፡ ተጠምጥሜበት ነው ሰላም ያልኩት፡፡ ሌላ ግን ምንም ያወራሁለት ነገር የለም፡፡ አብረን ምሳ በልተን የለመድንበት ቦታ ቁጭ ብለን ስንጨዋወት ዋልን፡፡ ፍሬን ስለፍቅረኛው ልጠይቀው እያልኩ ፈራና ተወዋለው፡፡ እነሚጣንም ካወራዋቸው ሌላ ነገር ይመስላል በዬ በማሰብ ተውኩኝ፡፡ ታዲያ ማንን ላውራ? ትንሽ ካሰቡኩ ቡሀላ ለምን ለቹቹ አልነግራትም ስል አሰብኩ፡፡ ምናልባት እሷ ከነ ሚጣ ጋር ስለማትገናኝ ሚስጥሬ የተጠበቀ ይሆናል ብዬ አሰብኩ፡፡ ሳልውል ሳላድር ላነጋግራት ፈለኩ፡፡
ማታ ዶርም ስገባ እሷም ጉዋደኞቿም የሉም፡፡ ጥዋት ወደ ክፍል ሲሄዱ ግን ያየዋቸው መሰለኝ፡፡ ለማንኛውም አምሽተውም ቢሆን መምጣታቸው አይቀርም ብቻ ውጪ እንዳያድሩ እንጂ እያልኩ በሆዴ አወራ ጀመር፡
ማታ ከፍሬ ጋር ፅሁፍ እያወራው አልጋላይ ቁጭ ብዬ የነቹቹን መምጣት እጠባበቅ ጀመር፡፡ 'ወይ ታሪክ ዛሬ ደሞ ቹቹ ናፈቀችኝ' አልኩ በሆዴ ፡፡ ነገሮችን አስቤያቸው ሳቄን ለከኩት፡፡ ብቻዬን ስስቅ እነሚጣ በየ አልጋቸው ላይ እንደሆኑ የየራሳቸውን ስራ እየሰሩ"ሆሆሆ የዛሬው ደሞ ጫን ያለው ነው፡፡" ሲሉ ሰማለው፡፡ አልታወቀኝም እንጂ ብዙ ግዜ ነው ለካ የሳኩት፡፡
ቁጭ እንዳልኩ ትንሽ ቆይተው እነ ቹቹ በር ማንኳኳት ጀመሩ፡፡ ከአልጋዬ ላይ እንዴት ወርጄ በሩን እንደከፈትኩላቸው፡፡ እነ ሚጣ ገርሞአቸው ያዩኛል፡፡ እነ ቹቹን ሰላም ብዬ ወደ አልጋዬ ተመለስኩ፡፡ እንደለመዱት ሰክረዋል፡፡ አሁን ልታናግረኝ ስማትችል ያለኝ አማራጭ ነገ ነው፡፡ ከፍሬ ጋር ተሰነባብቼ ተኛው፡፡ ጥዋት ክፍል እንድሄድ ሲቀሰቅሱኝ ትንሽ ራሴን አመም አድርጎኛል አልሄድም ብያቸው ቀረው፡፡ እነሱ ከወጡ ቡሀላ ቹቹ ከእንቅልፏ እስክትነቃ ቁጭ ብዬ መጠበቅ ጀመርኩ፡፡
ብዙ ከጠበኳት ብሀላ አልነሳ ብትለኝ ትእግስት ስላጣው ቀሰቀስኳት፡፡ ቹቹ የግዷን ተነሳች፡፡ ላናግራት እንደምፈልግ ነግሬያት በዛውም ቁርስ ልጋብዛት ይዥት ወጣው፡፡
ካፌ እንደደረስን ምግብ አዘን እየተመገብን ከምን እንደምጀምርላት ግራ ገባኝ፡፡ "እኔ ምልሽ እእእእ . . . . " እያልኩኝ ስንተባተብ "አቦ ንገሪኛ ልቤን ሰቀልሽው እኮ" አለችኝ ጮክ ብላ፡፡" አረ ድምፅሽን ዝቅ አድርጊ እሺ ነግርሻለው "አልኳት፡፡ ከወንበሬ ተመቻችቼ ከተቀመጥኩ ቡሀላ . . .
#ክፍል_አስራዘጠኝን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
❤️የፍቅር ሚዛን
💛የፍቅርን እውነተኛ ጣዕም ለማወቅ ሁለት ሰዎች እኩል መንገድ መምጣት መቻል አለባቸው። እኩል መምጣት ቢያቅታቸው እንኳን ተቀራራቢ መንገድ መጓዝ ግድ ይላቸዋል። አንዱ ብቻ መንገዱን ገስግሶ ቢመጣና ሌላው ከቆመበት ሳይንቀሳቀስ ቢጠብቅ የፍቅር ሚዛን ይዳፋል።
❤️ፍቅር ጤናማ የምትሆነው ሚዛናዊ ስትሆን ብቻ ነው። ፍቅር በየጊዜው ዘንበል ቀና ብትልም ፈጽሞ ወደ አንዱ ብቻ መውደቅ የለባትም። ወደ አንዱ ከወደቀች፤ አንዱ ተሸካሚ ሌላው ተጫዋች ይሆናል። ተሸካሚው የፍቅርን አበሳ፤ ተጫዋቹ የፍቅርን ጨዋታ ብቻ ይመለከታሉ። እይታቸው የተለያየ ስለሚሆን፤ ፍቅርን በአንድ አቅጣጫ አይመለከቷትም። ታዲያ እንዴት ሊግባቡ ይቻላል? በፍጹም አይግባቡም።
💜በሰው ስሜት እንዳንጫወት፤ የፍቅርን መንገድ ከመጀመራችን በፊት፤ ምን ያህል እርቀት መጓዝ እንደምንችል እናስብ። ከሚወደን ሰው ጋር መኖር በተጫዋቹ ቦታ መቀመጥ ፤ ከምንወደው ሰው ጋር መሆን በተሸካሚው ቦታ መሆን እንዳይሆንብን።
💛 የፍቅርን ሚዛናዊነት አይቶ ጨዋታውን ለማጣጣም አፍቃሪ እና ተፈቃሪ ሆነን ሳይሆን፤ ሁለት አፍቃሪዎች ሆነን መቅረብ አለብን። እንደ ሚዛን ጨዋታ፤ ጨዋታውን ለማጣጣም አንዴ እላይ አንዴ እታች ቦታ እየተለዋወጥን የፍቅርን ሚዛን መጠበቅ ግድ ይለናል።ፍቅር የባላይ ልሁን ለሚል ሰው አትሆንም፤ ከላይ ብቻ ተሰቅሎ ሚዛኑን ሌላው ላይ ማዳፋት ከፍቅር ጨዋታ የራቀ ነው።
💜ፍቅር እኔ ብቻ ልሸከማት ለሚልም አትሆነም፤ ምክንያቱም ጣዕሟን ለማጣጣም ስለሚከብደው። ምናልባት በፍቅር ሚዛን ላይ ከሆንን ፤ ግንኙነታችን እንቃኘው፤ ማነው ሸክሙን የተሸከመው፤ ማነው ጨዋታውን እያጣጠመ ያለው? በሰው ስሜት እንዳንቀልድ ለፍቅር ሚዛናዊ ለመሆን እንሞክር። የሚወዱን ሰዎች ሊወደዱ ይገባቸዋል፤ እኛ ሚዛኑን መጠብቅ ካልቻልን ከፍ ሊያደርጋቸው ለሚችል ለሌላ ሰው ቦታውን እንልቀቅላቸው። የምንወዳቸው ሰዎችም ሚዛኑን መጠበቅ ካቃታቸው፤ ፍቅር ለሚገባው፤ ዝቅ ካልንበት ከፍ ለሚያደርገን ሰው ቦታውን ቢለቁልን መልካም ነው።
ውብ ምሽት❤️
✍ሚስጥረ አደራው
💛የፍቅርን እውነተኛ ጣዕም ለማወቅ ሁለት ሰዎች እኩል መንገድ መምጣት መቻል አለባቸው። እኩል መምጣት ቢያቅታቸው እንኳን ተቀራራቢ መንገድ መጓዝ ግድ ይላቸዋል። አንዱ ብቻ መንገዱን ገስግሶ ቢመጣና ሌላው ከቆመበት ሳይንቀሳቀስ ቢጠብቅ የፍቅር ሚዛን ይዳፋል።
❤️ፍቅር ጤናማ የምትሆነው ሚዛናዊ ስትሆን ብቻ ነው። ፍቅር በየጊዜው ዘንበል ቀና ብትልም ፈጽሞ ወደ አንዱ ብቻ መውደቅ የለባትም። ወደ አንዱ ከወደቀች፤ አንዱ ተሸካሚ ሌላው ተጫዋች ይሆናል። ተሸካሚው የፍቅርን አበሳ፤ ተጫዋቹ የፍቅርን ጨዋታ ብቻ ይመለከታሉ። እይታቸው የተለያየ ስለሚሆን፤ ፍቅርን በአንድ አቅጣጫ አይመለከቷትም። ታዲያ እንዴት ሊግባቡ ይቻላል? በፍጹም አይግባቡም።
💜በሰው ስሜት እንዳንጫወት፤ የፍቅርን መንገድ ከመጀመራችን በፊት፤ ምን ያህል እርቀት መጓዝ እንደምንችል እናስብ። ከሚወደን ሰው ጋር መኖር በተጫዋቹ ቦታ መቀመጥ ፤ ከምንወደው ሰው ጋር መሆን በተሸካሚው ቦታ መሆን እንዳይሆንብን።
💛 የፍቅርን ሚዛናዊነት አይቶ ጨዋታውን ለማጣጣም አፍቃሪ እና ተፈቃሪ ሆነን ሳይሆን፤ ሁለት አፍቃሪዎች ሆነን መቅረብ አለብን። እንደ ሚዛን ጨዋታ፤ ጨዋታውን ለማጣጣም አንዴ እላይ አንዴ እታች ቦታ እየተለዋወጥን የፍቅርን ሚዛን መጠበቅ ግድ ይለናል።ፍቅር የባላይ ልሁን ለሚል ሰው አትሆንም፤ ከላይ ብቻ ተሰቅሎ ሚዛኑን ሌላው ላይ ማዳፋት ከፍቅር ጨዋታ የራቀ ነው።
💜ፍቅር እኔ ብቻ ልሸከማት ለሚልም አትሆነም፤ ምክንያቱም ጣዕሟን ለማጣጣም ስለሚከብደው። ምናልባት በፍቅር ሚዛን ላይ ከሆንን ፤ ግንኙነታችን እንቃኘው፤ ማነው ሸክሙን የተሸከመው፤ ማነው ጨዋታውን እያጣጠመ ያለው? በሰው ስሜት እንዳንቀልድ ለፍቅር ሚዛናዊ ለመሆን እንሞክር። የሚወዱን ሰዎች ሊወደዱ ይገባቸዋል፤ እኛ ሚዛኑን መጠብቅ ካልቻልን ከፍ ሊያደርጋቸው ለሚችል ለሌላ ሰው ቦታውን እንልቀቅላቸው። የምንወዳቸው ሰዎችም ሚዛኑን መጠበቅ ካቃታቸው፤ ፍቅር ለሚገባው፤ ዝቅ ካልንበት ከፍ ለሚያደርገን ሰው ቦታውን ቢለቁልን መልካም ነው።
ውብ ምሽት❤️
✍ሚስጥረ አደራው
እንደገና
Mohammud ahmud
Title ➲ እንደገና
Song ➲ Mehammud Ahmed
Size ➲ 1.1 mb
https://telegram.me/geyone
https://telegram.me/geyone
ሼር 🙏🙏
Song ➲ Mehammud Ahmed
Size ➲ 1.1 mb
https://telegram.me/geyone
https://telegram.me/geyone
ሼር 🙏🙏
💕ሰኞን እንዲህ ብንጀምርስ?💕
🇪🇹በመጀመሪያ ለዛሬዋ እለት ላደረሰን ለቸሩ ፈጣሪያችን 👏ክብር ምስጋና ይገባዋል 🙇♀
እለታትን እያፈራረቀ በእድሜያችን ላይ እድሜ እየጨመረ ዛሬ ላይ አድርሶናል ነገንም በሱ ቸርነት እናያለን
ሁሉም እንደአቅሙ ለሰው ልጅ የሚበጅ መልካም ስራ ሰርቶ መዋል በቅን ልቦና በመነሳሳት እራስና ወገንን በመርዳት እየሰራን ብናልፍ ለራሳችን ክብር ለሀገር ኩራት በሆንን ነበር ነገር ግን ግዜው አልፈቀደም የፊጢኝ ወደሗላ አስሮ እየጎተተን ነው
በፈጣሪ ያችን ቸርነት ሁሉም በግዜው ያልፋልና በግዜያችንም በተሰጠን እለት ያቅማችንን መልካም አድርገን እንለፍ ።
እንኳን ለዛሬዋ እልት በሰላም በጤና አደረሰን እያልኩ ሳምንቱ የታመመ የሚድንበት ያጣ የሚያገኝበት ያዘነ የሚፅናነበት የተራበ የሚጠግብበት የተጠማ ጠጥቶ የሚረካበት ፍቅር ያጣ ፍቅር የሚያገኝበት የታሰረ የሚፈታበት ፍትህ ያጣ ትክክለኛ ፍርድ የሚያገኝበት መልካም የስራ ሳምንት እንዲሆንልን እመኛለሁ እግዚአብሔር ይጠብቀን
ፈጣሪ ሀገራችንን ይባርክ መልካም ቀን
🇪🇹በመጀመሪያ ለዛሬዋ እለት ላደረሰን ለቸሩ ፈጣሪያችን 👏ክብር ምስጋና ይገባዋል 🙇♀
እለታትን እያፈራረቀ በእድሜያችን ላይ እድሜ እየጨመረ ዛሬ ላይ አድርሶናል ነገንም በሱ ቸርነት እናያለን
ሁሉም እንደአቅሙ ለሰው ልጅ የሚበጅ መልካም ስራ ሰርቶ መዋል በቅን ልቦና በመነሳሳት እራስና ወገንን በመርዳት እየሰራን ብናልፍ ለራሳችን ክብር ለሀገር ኩራት በሆንን ነበር ነገር ግን ግዜው አልፈቀደም የፊጢኝ ወደሗላ አስሮ እየጎተተን ነው
በፈጣሪ ያችን ቸርነት ሁሉም በግዜው ያልፋልና በግዜያችንም በተሰጠን እለት ያቅማችንን መልካም አድርገን እንለፍ ።
እንኳን ለዛሬዋ እልት በሰላም በጤና አደረሰን እያልኩ ሳምንቱ የታመመ የሚድንበት ያጣ የሚያገኝበት ያዘነ የሚፅናነበት የተራበ የሚጠግብበት የተጠማ ጠጥቶ የሚረካበት ፍቅር ያጣ ፍቅር የሚያገኝበት የታሰረ የሚፈታበት ፍትህ ያጣ ትክክለኛ ፍርድ የሚያገኝበት መልካም የስራ ሳምንት እንዲሆንልን እመኛለሁ እግዚአብሔር ይጠብቀን
ፈጣሪ ሀገራችንን ይባርክ መልካም ቀን
ሴና ክፍል አሥራ ዘጠኝ ❤️
. . . ከወንበሬ ተመቻችቼ ከተቀመጥኩ ቡሀላ ግቢ ከገባው ቀን ጀምሮ ያለውን ሁኔታ በሙሉ ሳምንት ያጋጠመኝን ያደረኩዋቸውን ነገሮች ማወቅ ያለባትን ያህል አጫወትኳት፡፡"እኔ በአንድ ሙሉ ሴሚስተር ያላሰለፍኩትን ላይፍ አንቺ በአንድ ሳምንት ኮመኮምሽዋ?" ብላ ሳቀችብኝ፡፡ እኔም አብሬያት ሳኩኝ፡፡"እኔ ምልሽ ግን ለምንድነው ታዲያ እንደዚ ሚሰማኝ? አንድ ሳምንት ማውቀው ልጅ ከይደለም ሚስት ፍቅረኛ ምናምን ቀርቶ ልጅ ቢኖረው ምን አገባኝ? ለምንድነው ውስጤ የሚረበሸው? ለምንድነው ልቤ ሚደነግጠው? በናትሽ ቹቹ ንገሪኝ?" አልኳት ሳቋን እስክትጨርስ እንኳን ሳልጠብቃት አይን አይኗን እያየው፡፡
"የውልሽ ሴና" ሴና አለች በወንበሯ ተመቻችታ እየተቀመጠች "የውልሽ ሴና ምናልባት አንቺ ወንድ እንደዚ ስትቀርቢ ይህ የመጀመሪያሽ ስለሆነም ሊሆን ይችላል እንደዚ የተሰማሽ፡፡ ሳታስቢው ፍቅር እየያዘሽ . . .." "ምን?! ፍቅር?" አቋረጥኳት፡፡ ደነገጥኩ "ምንድነው ምትይው? እንዴት በአንድ ሳምንት ውስጥ. . . ማለቴ . . .ደሞ የፍቅር ፅሁፎች ብዙ አንብቤያለው እነዴት . . . እኔ ምልሽ ቆይ ስታስቢው . . . " ተንተባተብኩ ፊቴን ላብ አሰመጠኝ ፤የምናገረው ግራ ገባኝ 'እንዴት ነው ፍቅር ቆይ እንደዚ ነው እንዴ?' ከራሴጋር መጨቃጨቅ ጀመርኩ፡፡"የውልሽ ሴና አዳምጪኝ" አለች ቹቹ ረጋ ባለ መንፈስ፡፡"እኔም ለመጀመሪያ ግዜ እንዳንቺው ነበር የሆንኩት እመኚኝ በቃ የቡሀላውን ባናውቅም ለግዜው ግን ፍቅር ይዞሻል፡፡" ደገመችልኝ "እንዴት ነው በዚህ ቀን ውስጥ ፍቅር? ፍቅር እንደዚ ነው እንዴ?ምን አይነት ፍቅር ነው ይሄ?" አፈጠጥኩባት ፤ጥያቄ ላይ ጥያቄ አከታተልኩባት፡፡ ቹቹ ዝም ብላ ስትመለከተኝ ከቆየች ብሀላ "ቆይ ለልጁ ምንም ስሜት የለሽም?
"አረ ምንም ስሜት የለኝም በቃ እናወራለን እንጫወታለን አለቀ ከዛ ውጪ ምምም ማስበው ነገር የለም፡፡"እንደመናደድ ብያለው፡፡"እና ብታጪውም ምንም አይመስልሽማ?" አለችኝ ቹቹ አይኔን ትኩር ብላ እየተመለከተች"አዎ እንዴ ምን አይመስለኝም"አልኳት አይኔን እያርገበገብኩ፡፡ "እሺ በአንድ ነገር እንስማማ"አለችኝ፡፡ ምንድነው እንኳን አላልኳትም ወዲያው እሺ አልኩኝ፡፡ "ፍቅር ይዞሻል ብቻ አትበይኝ ሌላ ነገር እስማማለው "አልኳት፡፡ "ለልጁ ምንም ስሜት ከሌለሽ እስከዛሬ ሳምንት በስልክም በአካልም እንዳታገኚው፡፡እውነት ምንም ስሜት ከሌለሽ አይደለም አንድ ሳምንት እስከመጨረሻሽ እንኳን ባትገናኙ ምንም አይመስልሽም ማለት ነው" አለችኝ ፡፡ ደነገጥኩ! ግን ፍቅር እንዳልያዘኝ ለራሴም ለቹቹም ማሳየት ፈልጋለው፡፡ ተስማማው ፤እሺ አልኳት፡፡ "አንድ ሳምንት ፍሬ ሚባል ሰው እንኳን አልገናኝም፡፡" አልኳት፡፡ በውስጤ ግን አንድ ነገር አሰብኩ፡፡ 'እንዴ ከነሚጣ ጋር ከሆንኩ እኮ ፍሬን መገናኘቴ አይቀርም፡፡ ከቹቹ ጋር ደሞ መዋል አልችልም፡፡ እና ብቻዬን ልሆን ነው?' ምን ማድረግ እንዳለብኝ ከራሴ ጋር ማሰላሰል ጀመርኩ፡፡
እንዴት ነው ይሄንን አንድ ሳምንት ማሳልፈው? አንድ ሀሳብ መጣልኝ ወንድሜ 'አግኚያት የመስራቤታችን ሰውዬ ልጅ ናት ያለኝ ትዝ አለኝ፡፡ አዎ ከሷጋር ሆናለው የዛኔ ማንንም አላገኝም ማለት ነው፡፡'በዚህ ሀሳብ ከራሴ ጋር ተስማማው፡፡'ግን እኮ አላውቃት አታውቀኝ አባቱዋና ወንድሜ አንድ ቦታ ሰሩና እኔና እሱዋ እንግባባለን ማለት ነው?' ስል ደሞ ሌላ ነገር ማሰብም ጀመርኩ፡፡ በቃ ላይብረሪ ውላለው ወይም ዶርም ተኝቼ ውላለው፡፡ ብዙ ብዙ ነገር አሰብኩ፡፡ እንዴት እንደማደርግ ሳወጣ ሳወርድ በሀሳብ ሄድኩ፡፡
"ሴና ! ምን ሆነሻል?" ከወሰደኝ ሀሳብ የቹቹ ጥሪ መለሰኝ፡፡ እንዲሁ ነው ብያት ከቹቹ ጋር ከተስማማን ብሀላ ጨዋታ ቀይረን ስለሌላ ነገር ማውራት ጀመርን፡፡ በዚህ መሀል ስልኬ ጠራ ፡፡ፍሬ ነው . . .
#ክፍል_ሀያን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
@fiker_markiye
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
. . . ከወንበሬ ተመቻችቼ ከተቀመጥኩ ቡሀላ ግቢ ከገባው ቀን ጀምሮ ያለውን ሁኔታ በሙሉ ሳምንት ያጋጠመኝን ያደረኩዋቸውን ነገሮች ማወቅ ያለባትን ያህል አጫወትኳት፡፡"እኔ በአንድ ሙሉ ሴሚስተር ያላሰለፍኩትን ላይፍ አንቺ በአንድ ሳምንት ኮመኮምሽዋ?" ብላ ሳቀችብኝ፡፡ እኔም አብሬያት ሳኩኝ፡፡"እኔ ምልሽ ግን ለምንድነው ታዲያ እንደዚ ሚሰማኝ? አንድ ሳምንት ማውቀው ልጅ ከይደለም ሚስት ፍቅረኛ ምናምን ቀርቶ ልጅ ቢኖረው ምን አገባኝ? ለምንድነው ውስጤ የሚረበሸው? ለምንድነው ልቤ ሚደነግጠው? በናትሽ ቹቹ ንገሪኝ?" አልኳት ሳቋን እስክትጨርስ እንኳን ሳልጠብቃት አይን አይኗን እያየው፡፡
"የውልሽ ሴና" ሴና አለች በወንበሯ ተመቻችታ እየተቀመጠች "የውልሽ ሴና ምናልባት አንቺ ወንድ እንደዚ ስትቀርቢ ይህ የመጀመሪያሽ ስለሆነም ሊሆን ይችላል እንደዚ የተሰማሽ፡፡ ሳታስቢው ፍቅር እየያዘሽ . . .." "ምን?! ፍቅር?" አቋረጥኳት፡፡ ደነገጥኩ "ምንድነው ምትይው? እንዴት በአንድ ሳምንት ውስጥ. . . ማለቴ . . .ደሞ የፍቅር ፅሁፎች ብዙ አንብቤያለው እነዴት . . . እኔ ምልሽ ቆይ ስታስቢው . . . " ተንተባተብኩ ፊቴን ላብ አሰመጠኝ ፤የምናገረው ግራ ገባኝ 'እንዴት ነው ፍቅር ቆይ እንደዚ ነው እንዴ?' ከራሴጋር መጨቃጨቅ ጀመርኩ፡፡"የውልሽ ሴና አዳምጪኝ" አለች ቹቹ ረጋ ባለ መንፈስ፡፡"እኔም ለመጀመሪያ ግዜ እንዳንቺው ነበር የሆንኩት እመኚኝ በቃ የቡሀላውን ባናውቅም ለግዜው ግን ፍቅር ይዞሻል፡፡" ደገመችልኝ "እንዴት ነው በዚህ ቀን ውስጥ ፍቅር? ፍቅር እንደዚ ነው እንዴ?ምን አይነት ፍቅር ነው ይሄ?" አፈጠጥኩባት ፤ጥያቄ ላይ ጥያቄ አከታተልኩባት፡፡ ቹቹ ዝም ብላ ስትመለከተኝ ከቆየች ብሀላ "ቆይ ለልጁ ምንም ስሜት የለሽም?
"አረ ምንም ስሜት የለኝም በቃ እናወራለን እንጫወታለን አለቀ ከዛ ውጪ ምምም ማስበው ነገር የለም፡፡"እንደመናደድ ብያለው፡፡"እና ብታጪውም ምንም አይመስልሽማ?" አለችኝ ቹቹ አይኔን ትኩር ብላ እየተመለከተች"አዎ እንዴ ምን አይመስለኝም"አልኳት አይኔን እያርገበገብኩ፡፡ "እሺ በአንድ ነገር እንስማማ"አለችኝ፡፡ ምንድነው እንኳን አላልኳትም ወዲያው እሺ አልኩኝ፡፡ "ፍቅር ይዞሻል ብቻ አትበይኝ ሌላ ነገር እስማማለው "አልኳት፡፡ "ለልጁ ምንም ስሜት ከሌለሽ እስከዛሬ ሳምንት በስልክም በአካልም እንዳታገኚው፡፡እውነት ምንም ስሜት ከሌለሽ አይደለም አንድ ሳምንት እስከመጨረሻሽ እንኳን ባትገናኙ ምንም አይመስልሽም ማለት ነው" አለችኝ ፡፡ ደነገጥኩ! ግን ፍቅር እንዳልያዘኝ ለራሴም ለቹቹም ማሳየት ፈልጋለው፡፡ ተስማማው ፤እሺ አልኳት፡፡ "አንድ ሳምንት ፍሬ ሚባል ሰው እንኳን አልገናኝም፡፡" አልኳት፡፡ በውስጤ ግን አንድ ነገር አሰብኩ፡፡ 'እንዴ ከነሚጣ ጋር ከሆንኩ እኮ ፍሬን መገናኘቴ አይቀርም፡፡ ከቹቹ ጋር ደሞ መዋል አልችልም፡፡ እና ብቻዬን ልሆን ነው?' ምን ማድረግ እንዳለብኝ ከራሴ ጋር ማሰላሰል ጀመርኩ፡፡
እንዴት ነው ይሄንን አንድ ሳምንት ማሳልፈው? አንድ ሀሳብ መጣልኝ ወንድሜ 'አግኚያት የመስራቤታችን ሰውዬ ልጅ ናት ያለኝ ትዝ አለኝ፡፡ አዎ ከሷጋር ሆናለው የዛኔ ማንንም አላገኝም ማለት ነው፡፡'በዚህ ሀሳብ ከራሴ ጋር ተስማማው፡፡'ግን እኮ አላውቃት አታውቀኝ አባቱዋና ወንድሜ አንድ ቦታ ሰሩና እኔና እሱዋ እንግባባለን ማለት ነው?' ስል ደሞ ሌላ ነገር ማሰብም ጀመርኩ፡፡ በቃ ላይብረሪ ውላለው ወይም ዶርም ተኝቼ ውላለው፡፡ ብዙ ብዙ ነገር አሰብኩ፡፡ እንዴት እንደማደርግ ሳወጣ ሳወርድ በሀሳብ ሄድኩ፡፡
"ሴና ! ምን ሆነሻል?" ከወሰደኝ ሀሳብ የቹቹ ጥሪ መለሰኝ፡፡ እንዲሁ ነው ብያት ከቹቹ ጋር ከተስማማን ብሀላ ጨዋታ ቀይረን ስለሌላ ነገር ማውራት ጀመርን፡፡ በዚህ መሀል ስልኬ ጠራ ፡፡ፍሬ ነው . . .
#ክፍል_ሀያን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
@fiker_markiye
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
ሴና ክፍል ሀያ ❤️
. . . "ሴና ምን ሆነሻል?" ከወሰደኝ ሀሳብ የቹቹ ጥሪ መለሰኝ፡፡ እንዲሁ ነው ብያት ከቹቹ ጋር ከተስማማን ብሀላ ጨዋታ ቀይረን ስለሌላ ነገር ማውራት ጀመርን፡፡በዚህ መሀል ስልኬ ጠራ ፡፡ፍሬ ነውስልኬን አይቼ ቀና ብዬ ቹቹን እየተመለከትኳት "ፍሬ ደወለ" አልኩ እንደመደንገጥ ብዬ፡፡"እና ይደውላ ምነው ልታነሽው ባልሆነ፡፡"ስትለኝ ምንም መልስ ሳልሰጣት ስልኬን አስቀምጬ ጨዋታችንን ቀጠልን፡፡ ብዙ ከተጨዋወትን ቡሀላ ቹቹ ምትሄድበት እንዳለ ነግራኝ ካፌ ትታኝ ወጣች፡፡
ትንሽ ብቻዬን እንደተቀመጥኩ ለነ ሚጣ ልደውል አስቤ ደግሞ ፍሬ ቢኖርስ ብዬ ተዉኩት፡፡ ወንድሜ አግኛት ላለኝ ልጅ ልደውል አልደውል ስል ብዙ አመነታው፡፡በመጨረሻም ደወልኩላት፡፡ ረጋ ያለች ልጅ ትመስላለች ትንሽ አናግሬያት ከተዋወቅን ብሃላ ከቻለች እንድንገናኝ ስጠይቃት "ዛሬ ክላስ የለኝም ቤት ነኝ ጥዋት ነው ምመጣው"አለችኝ፡፡ 'ጎሽ ከኔም የባሰ አለ ማለት ነው' አልኩ በሆዴ፡፡ነገ ላገኛት ተቀጣጥረን ስልኩን ዘግቼ ቁጭ ብዬ ቲቪ ላይ ማፍጠጥ ጀመርኩ፡፡ ብቻዬን ነው የተቀመጥኩት፡፡ አይኔ ቲቪ ያያል እንጂ ሀሳቤ ሌላ ቦታ ነው፡፡
"አረ ቆንጆ ብቻሽን ምነው? ከገባው ጀምሮ ሳይሽ ብቻሽን ነሽ የማን ፋራ ነው አስደግፎሽ የቀረው?" እያለ ከፊትለፊቴ ያለ ወንበር ስቦ ተቀመጠ አንድ ፀጉረ ጨበሬ ወንድ፡፡ምንም መልስ አልሰጠውትም፡፡ ከተቀመጠ ቡሃላ "ወንበሩ ግን ሰው አለው?" አለኝ መልስ አልሰጠውትም ወደ ወንበሬ መደገፊያ ደገፍ ብዬ እጄን በደረቴ አድርጌ ተቀመጥኩ፡፡ "ፆም ገባ እንዴ?" አለኝ ፡፡ 'የምን ፆም?' ስለው "ተመስገን አልገባም ማለት ነው፡፡ምነው ብቻሽን እዚ ማንን እየጠበቅሽ ነው?" አለ፡፡ከመጣ ሰአት ጀም ሌላም ያላስታወስኮቸው ብዙ ነገሮች አወራ ፣ሊቀልድ ማከረ ፣ሊያስገርመኝ ሞከረ፡፡ እኔ በራሴ ሀሳብ ውስጥ ነኝ፡፡ ወሬው ቢያቅተኝ ለሚጣ ደውዬ ቀጥሮ እንደሚጠብቅ ሰው'የት ናቹ ቆየው እኮ ከመጣው የት ልምጣ' አልኩኝ እንደመቆጣት ብዬ፡፡ሚጣ ያልኳት ግራ ቢገባትም ያሉበትን ነገረችኝ፡፡ እዛው ጠብቁኝ ብዬ ተነሳው፡፡ ልጁ አብሮኝ ተነሳ"እኔም ወደዛው ስለሆንኩ ልሸኝሽ?" አለኝ፡፡ 'ምሄድበትን እንዴት አወክ?' ብዬ ስጠይቀው "እሱን ስትደርሺ ነዋ ማውቀው"አለኝ፡፡ 'ውይ በናትክ ወንድሜ ተወኝ'ብዬ ወደነሚጣ ገሰገስኩ፡፡
ከነሚጣ ጋር ስገናኝ ረጅም ቀን ያጣዋቸው ያህል ነበር የናፈቁኝ፡፡ ሁሉንም ሰላም ብዬ "ምነው ቅድም ፍሬ እየደወለልሽ አታነሺም አብረን ነበርን" አሉኝ፡፡ ከሰው ጋር እንደነበርኩ ነግሬያቸው ካፌ ውስጥ ያጋጠመኝን ልጅ ነግሬያቸው መሳሳቅ ጀመርን፡፡
ማታ ዶርም ገብቼ ልብሴን ከቀያየርኩ ቡሀላ ክፍል ገብተው ከፃፉት ማስታወሻ ላይ መገልበጥ ስጀምር የፍሬ መልእክት በስልኬ ገባ"ምነው ጠፋሽ በሰላም ነው?" ሚል ነበር፡፡ አንበቤ ብቻ ስልኬን መልሼ አስቀምጬ መፃፌን ቀጠልኩ፡፡ ዶርም ውስጥ እያወራን እየተሳሳቅን ስለነበር ለፍሬ መልእክት አለመመለሴ ብዙም ቅር አላለኝም፡፡
ጥዋት ወደ ክፍል ስንሄድ ፍሬን ባላገኘው ብዬ በውስጤ ተመኘው፡፡ ጠልቼው አይደለም ግን ደሞ . . . በቃ ብቻ ላገኘው አልፈለኩም፡፡ ብዙ ቀን ወደክፍል ስንሄድ ፍሬና ዴቭን እናገኛቸዋለን፡፡ ዛሬ አላገኘናቸውም የሆዴን ሰማኝ መሰለኝ፡፡
ቀን ከክፍል ስንወጣ ምሳ ካፌ እንግባ ወይስ ውጪ እንብላ ብዬ ጠየኩዋቸው፡፡ "አረ ዴቭ ዛሬ ምሳ በኔ ነው ብሎአል ልደውልለት እንደውም ብላ ስልኳን መነካካት ጀመረች፡፡ ደነገጥኩ 'ወይኔ ጉዴ ፍሬም ይመጣል ማለት ነው እኮ' አልኩኝ ለራሴ፡፡ በዚህ መሀል የወንድሜ ባልደረባ ልጅ ደወለች፡፡ ከተመቸኝ አሁን እንዳገኛት ጠየቀችኝ፡፡ እንደሚመቸኝ ነግሬያት ለነሚጣ 'በጣም ይቅርታ ረስቼው ነው ወንድሜ እንዳገኛት የነገረኝ ልጅ አለች አሁን ነበር ቀጠሮዋችን፡፡ረስቼው ነው በጣም ይቅርታ ጉዋደኞቼ ቡሀላ አገኛቹሀለው ብዬ ጉንጫቸውን ስሜያቸው ተሰናበትከበቸው፡፡በመሄዴ ደስ ባይላቸውም በእሺታ ራሳቸውን እየነቀነቁ ተቀበሉኝ፡፡ ትቻቸው ሄድኩ፡፡
ግን እስከመቼ? ለአንድ ሳምንት ወይስ እስከመጨረሻው? ቆይ ዛሬን እንዲ አለፍኩ ነገስ? ምን እያደረኩ ነው? ምን እየሆንኩ ነው? ውስጤ ብዙ ጥያቄ ይመላለሳል፡፡ እየተወዛገብኩ እርምጃዬ ወደ ቀጠሮዬ እያመራኝ ነው . . .
#ክፍል_ሀያአንድን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
https://telegram.me/geyone
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
. . . "ሴና ምን ሆነሻል?" ከወሰደኝ ሀሳብ የቹቹ ጥሪ መለሰኝ፡፡ እንዲሁ ነው ብያት ከቹቹ ጋር ከተስማማን ብሀላ ጨዋታ ቀይረን ስለሌላ ነገር ማውራት ጀመርን፡፡በዚህ መሀል ስልኬ ጠራ ፡፡ፍሬ ነውስልኬን አይቼ ቀና ብዬ ቹቹን እየተመለከትኳት "ፍሬ ደወለ" አልኩ እንደመደንገጥ ብዬ፡፡"እና ይደውላ ምነው ልታነሽው ባልሆነ፡፡"ስትለኝ ምንም መልስ ሳልሰጣት ስልኬን አስቀምጬ ጨዋታችንን ቀጠልን፡፡ ብዙ ከተጨዋወትን ቡሀላ ቹቹ ምትሄድበት እንዳለ ነግራኝ ካፌ ትታኝ ወጣች፡፡
ትንሽ ብቻዬን እንደተቀመጥኩ ለነ ሚጣ ልደውል አስቤ ደግሞ ፍሬ ቢኖርስ ብዬ ተዉኩት፡፡ ወንድሜ አግኛት ላለኝ ልጅ ልደውል አልደውል ስል ብዙ አመነታው፡፡በመጨረሻም ደወልኩላት፡፡ ረጋ ያለች ልጅ ትመስላለች ትንሽ አናግሬያት ከተዋወቅን ብሃላ ከቻለች እንድንገናኝ ስጠይቃት "ዛሬ ክላስ የለኝም ቤት ነኝ ጥዋት ነው ምመጣው"አለችኝ፡፡ 'ጎሽ ከኔም የባሰ አለ ማለት ነው' አልኩ በሆዴ፡፡ነገ ላገኛት ተቀጣጥረን ስልኩን ዘግቼ ቁጭ ብዬ ቲቪ ላይ ማፍጠጥ ጀመርኩ፡፡ ብቻዬን ነው የተቀመጥኩት፡፡ አይኔ ቲቪ ያያል እንጂ ሀሳቤ ሌላ ቦታ ነው፡፡
"አረ ቆንጆ ብቻሽን ምነው? ከገባው ጀምሮ ሳይሽ ብቻሽን ነሽ የማን ፋራ ነው አስደግፎሽ የቀረው?" እያለ ከፊትለፊቴ ያለ ወንበር ስቦ ተቀመጠ አንድ ፀጉረ ጨበሬ ወንድ፡፡ምንም መልስ አልሰጠውትም፡፡ ከተቀመጠ ቡሃላ "ወንበሩ ግን ሰው አለው?" አለኝ መልስ አልሰጠውትም ወደ ወንበሬ መደገፊያ ደገፍ ብዬ እጄን በደረቴ አድርጌ ተቀመጥኩ፡፡ "ፆም ገባ እንዴ?" አለኝ ፡፡ 'የምን ፆም?' ስለው "ተመስገን አልገባም ማለት ነው፡፡ምነው ብቻሽን እዚ ማንን እየጠበቅሽ ነው?" አለ፡፡ከመጣ ሰአት ጀም ሌላም ያላስታወስኮቸው ብዙ ነገሮች አወራ ፣ሊቀልድ ማከረ ፣ሊያስገርመኝ ሞከረ፡፡ እኔ በራሴ ሀሳብ ውስጥ ነኝ፡፡ ወሬው ቢያቅተኝ ለሚጣ ደውዬ ቀጥሮ እንደሚጠብቅ ሰው'የት ናቹ ቆየው እኮ ከመጣው የት ልምጣ' አልኩኝ እንደመቆጣት ብዬ፡፡ሚጣ ያልኳት ግራ ቢገባትም ያሉበትን ነገረችኝ፡፡ እዛው ጠብቁኝ ብዬ ተነሳው፡፡ ልጁ አብሮኝ ተነሳ"እኔም ወደዛው ስለሆንኩ ልሸኝሽ?" አለኝ፡፡ 'ምሄድበትን እንዴት አወክ?' ብዬ ስጠይቀው "እሱን ስትደርሺ ነዋ ማውቀው"አለኝ፡፡ 'ውይ በናትክ ወንድሜ ተወኝ'ብዬ ወደነሚጣ ገሰገስኩ፡፡
ከነሚጣ ጋር ስገናኝ ረጅም ቀን ያጣዋቸው ያህል ነበር የናፈቁኝ፡፡ ሁሉንም ሰላም ብዬ "ምነው ቅድም ፍሬ እየደወለልሽ አታነሺም አብረን ነበርን" አሉኝ፡፡ ከሰው ጋር እንደነበርኩ ነግሬያቸው ካፌ ውስጥ ያጋጠመኝን ልጅ ነግሬያቸው መሳሳቅ ጀመርን፡፡
ማታ ዶርም ገብቼ ልብሴን ከቀያየርኩ ቡሀላ ክፍል ገብተው ከፃፉት ማስታወሻ ላይ መገልበጥ ስጀምር የፍሬ መልእክት በስልኬ ገባ"ምነው ጠፋሽ በሰላም ነው?" ሚል ነበር፡፡ አንበቤ ብቻ ስልኬን መልሼ አስቀምጬ መፃፌን ቀጠልኩ፡፡ ዶርም ውስጥ እያወራን እየተሳሳቅን ስለነበር ለፍሬ መልእክት አለመመለሴ ብዙም ቅር አላለኝም፡፡
ጥዋት ወደ ክፍል ስንሄድ ፍሬን ባላገኘው ብዬ በውስጤ ተመኘው፡፡ ጠልቼው አይደለም ግን ደሞ . . . በቃ ብቻ ላገኘው አልፈለኩም፡፡ ብዙ ቀን ወደክፍል ስንሄድ ፍሬና ዴቭን እናገኛቸዋለን፡፡ ዛሬ አላገኘናቸውም የሆዴን ሰማኝ መሰለኝ፡፡
ቀን ከክፍል ስንወጣ ምሳ ካፌ እንግባ ወይስ ውጪ እንብላ ብዬ ጠየኩዋቸው፡፡ "አረ ዴቭ ዛሬ ምሳ በኔ ነው ብሎአል ልደውልለት እንደውም ብላ ስልኳን መነካካት ጀመረች፡፡ ደነገጥኩ 'ወይኔ ጉዴ ፍሬም ይመጣል ማለት ነው እኮ' አልኩኝ ለራሴ፡፡ በዚህ መሀል የወንድሜ ባልደረባ ልጅ ደወለች፡፡ ከተመቸኝ አሁን እንዳገኛት ጠየቀችኝ፡፡ እንደሚመቸኝ ነግሬያት ለነሚጣ 'በጣም ይቅርታ ረስቼው ነው ወንድሜ እንዳገኛት የነገረኝ ልጅ አለች አሁን ነበር ቀጠሮዋችን፡፡ረስቼው ነው በጣም ይቅርታ ጉዋደኞቼ ቡሀላ አገኛቹሀለው ብዬ ጉንጫቸውን ስሜያቸው ተሰናበትከበቸው፡፡በመሄዴ ደስ ባይላቸውም በእሺታ ራሳቸውን እየነቀነቁ ተቀበሉኝ፡፡ ትቻቸው ሄድኩ፡፡
ግን እስከመቼ? ለአንድ ሳምንት ወይስ እስከመጨረሻው? ቆይ ዛሬን እንዲ አለፍኩ ነገስ? ምን እያደረኩ ነው? ምን እየሆንኩ ነው? ውስጤ ብዙ ጥያቄ ይመላለሳል፡፡ እየተወዛገብኩ እርምጃዬ ወደ ቀጠሮዬ እያመራኝ ነው . . .
#ክፍል_ሀያአንድን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
https://telegram.me/geyone
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
ሴና ክፍል ሀያአንድ
. . . ከቀጠሮዬ ቦታ ደስደርስ ስልክ ደውዬ ተገናኘን፡፡ እንደጠበኳት ግን አይደለችም፡፡ዝንጥ ያለች ቆንጅዬ ልጅ ነች፡፡ ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ ተዋውቀን ተቀመጥኩ፡፡ ፌቨን ነው ስሟ፡፡ ትንሽ እንዳወራን ተግባባን ፡፡ ፌቨን ቀለል ያለች ተጫዋች ልጅ ነች፡፡ ቡዙ ተጨዋወትን በዚህ መሀል ስልኬ ሶስት ግዜ ተደውሎአል፡፡ ፍሬ ነው አላነሳውትም፡፡ ቀኔን ከፌቨን ጋር አሳለፍኩ፡፡
ወደ አመሻሽ ላይ እና ሚጣ ደውለው እራት አብሬያቸው እንድበላ ጠየቁኝ፡፡ አብሬያቸው መሆንን ፈልጌያለው፡፡ ግን ፍሬ ሊኖር ይችላል ብዬ ስላሰብኩ ሰበብ ፈጥሬ መቅረትን መረጥኩ፡፡"ትንሽ አመም አድርጎኝ ወደ ዶርም እየሄድኩ ነው፡፡ ባይሆን ስትመጡ እራት ይዛቹልኝ ኑ" ብያቸው ወደ ዶርሜ አቀናው፡፡
ዶርሜ ስገባ ያቺን ባለ መነፅር አልጋዋላይ ተኝታ ኮምፒውተሯን እየጎረጎረች አገኘዋት፡፡ ሰላም ተባብለን ለምን ብቻዬን እንደመጣው ስትጠይቀኝ ትንሽ ራሴን አመም አድርጎኝ እንደሆነ ነግሬያት ልብሴን ቀይሬ ተጣጥቤ አልጋዬላይ ወጥቼ ተኛው፡፡ ከእንቅልፌ የባነንኩት በሚጣ ጥሪ ነው፡፡ "ምን ሆነሽ ነው? በጣም አመመሽ እንዴ?" አለችኝ ግንባሬን በእጇ እየዳበሰች፡፡ "የት ውለሽ ነው? ምን ሆነሽ ነው? የጥያቄ መአት እያከታተሉ ይጠይቁኝ ጀመር፡፡ ብዙም አላወራውም ያመጡልኝን እራት ከበላሁ ቡሀላ ተመልሼ አልጋዬላይ ወጣሁ፡፡ ስለውሎዋቸው ያጫውቱኝ ጀመር፡፡ እያወራን ስልኬ መልእክት ገባ ፡፡ ፍሬ ነው አነብቤው ተውኩት፡፡ ጨዋታችን ቀጠለ፡፡
እንዲ እንዲያ እያልኩ ቀናት ተቆጠሩ ፣ሳምንቱም አለቀ ፣ቤት ደርሼ ተመለስኩ፡፡ ለቹቹ ቃል እንደገባውላት ፍሬን አንድ ሳምንት ሳላገኘው፡፡ በቀጠሮዋችን ቀን ከቹቹ ጋር የተለመደው ቦታ ተቀምጠን ስላለፈው ነገር ማውራት ጀመርን፡፡ "ይኸው ፍቅር እንዳልያዘኝ እወቂ፡፡ አንድ ሳምንት አላገኘውትም ግን ምንም አልተሰማኝም ፣ምንም አልሆንኩም" አልኳት ግዳጁን እንደተወጣ መልእክተኛ ፡፡ "ስለዚህ በዚሁ ትቀጥያለሽ ማለት ነው" አለችኝ ቹቹ፡፡ አልገባኝም ፤ደነገጥኩ "ማለት ከዚህ ቡሀላ ፍሬን ላላገኘው?" አልኳት፡፡ "እንደዛ ማለቴ አይደለም ከዚህ ቡሀላም ስለፍሬ አታስቢም ፣ብዙ ግዜሽን ከፍሬ ጋር አታሳልፊም፡፡ በቃ እንደማንኛውም ተራ ጉዋደኛ ብቻ ይሆናል ምትቀራረቢው" አለችኝ፡፡
" 'ለምንድነው?' ብለሽ እንደምታስቢ አውቃለው፡፡ አንቺ በዚህ ግዜ ስለ ፍቅር ምንም ማሰብም ፣ፍቅረኛ እንዲኖርሽ አትፈልጊም፡፡ ፍሬ ደሞ በአጭር ቀን ውስጥ በጣም የቀረብሽው ወንድ ነው፡፡ በዚህ ከቀጠልሽ ደሞ ወደ ፍቅር ማይቀየርበት ምክንያት አይኖርም፡፡ስለዚህ ግንኙነታቹን ትቀንሻለሽ፡፡ ይሄንን ደሞ ምመክርሽ ላንቺው ብዬ ነው፡፡" አለችኝ ቹቹ፡፡ ዝም ብዬ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ ምንም ሳልናገር ከ አስር ደቂቃ በላይ አሳለፍኩ፡፡ ብዙ አወጣው አወረድኩ፡፡ "እውነቷን ነው? አይ ምንም ችግር የለውም . . . "ቹቹም ዝም ብላ ታየኝ ጀመር፡፡ እንደመጀመሪያው ቀን ዛሬ ወዲያው ልስማማ አልቻልኩም፡፡ "እሺ" የማለት ድፍረት አጣው፡፡ "ይሄንን ግዜ ወስደሽ በደንብ አስቢበት፡፡ የምርጫ ጉዳይ አይደለም፡፡ እሺ ወይ እንቢ እንድትይኝ አይደለም፡፡ ራስሽ እንድታስቢው ፤ራስሽን በራስሽ እንድትመረምሪበት ነው የነገርኩሽ" አለችኝ ቹቹ አይኔን እያየች፡፡ እንማስብበት ነግሬያት በተለመደው ሰአት ተለያየን፡፡
ወደሚጣ ስልክ ስደውል ፍሬ አነሳው፡፡ "ሴና ግን ምን አድርጌሽ ነው? እንደዚ ሚያስከፋ ነገር አደረኩሽ ግን? . . ."ገና እያወራኝ ስልኩን ዘጋውት፡፡ ደነገጥኩኝ፡፡ 'እውነት ምን አድርጎኝ ነው ግን?' ብዬ አሰብኩ፡፡ 'እንዴት ግን የሚጣን ስልክ አነሳው?ምናልባት አብረው ሆነው ይሆናል፡፡' እነሚጣ የት እንዳሉ ለማወቅ ነበር የደወልኩት፡፡
ትንሽ ቆይቶ ፍሬ በራሱ ስልክ መልእክት ላከልኝ፡፡ በቆምኩበት ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩ፡፡ እያነበብኩ ወደመሀል ስደርስ ሳላስበው እንባዬ መጣ፡፡ ማንበቤን ቀጠልኩ፡፡ እንባዬ አይኔን ሸፎኖኝ ስልኬላይ መንጠባጠብ ጀመረ፡፡ የላከልኝ መልእክት እንዲህ የሚል ነው . . .
#ክፍል_ሀያሁለትን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
. . . ከቀጠሮዬ ቦታ ደስደርስ ስልክ ደውዬ ተገናኘን፡፡ እንደጠበኳት ግን አይደለችም፡፡ዝንጥ ያለች ቆንጅዬ ልጅ ነች፡፡ ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ ተዋውቀን ተቀመጥኩ፡፡ ፌቨን ነው ስሟ፡፡ ትንሽ እንዳወራን ተግባባን ፡፡ ፌቨን ቀለል ያለች ተጫዋች ልጅ ነች፡፡ ቡዙ ተጨዋወትን በዚህ መሀል ስልኬ ሶስት ግዜ ተደውሎአል፡፡ ፍሬ ነው አላነሳውትም፡፡ ቀኔን ከፌቨን ጋር አሳለፍኩ፡፡
ወደ አመሻሽ ላይ እና ሚጣ ደውለው እራት አብሬያቸው እንድበላ ጠየቁኝ፡፡ አብሬያቸው መሆንን ፈልጌያለው፡፡ ግን ፍሬ ሊኖር ይችላል ብዬ ስላሰብኩ ሰበብ ፈጥሬ መቅረትን መረጥኩ፡፡"ትንሽ አመም አድርጎኝ ወደ ዶርም እየሄድኩ ነው፡፡ ባይሆን ስትመጡ እራት ይዛቹልኝ ኑ" ብያቸው ወደ ዶርሜ አቀናው፡፡
ዶርሜ ስገባ ያቺን ባለ መነፅር አልጋዋላይ ተኝታ ኮምፒውተሯን እየጎረጎረች አገኘዋት፡፡ ሰላም ተባብለን ለምን ብቻዬን እንደመጣው ስትጠይቀኝ ትንሽ ራሴን አመም አድርጎኝ እንደሆነ ነግሬያት ልብሴን ቀይሬ ተጣጥቤ አልጋዬላይ ወጥቼ ተኛው፡፡ ከእንቅልፌ የባነንኩት በሚጣ ጥሪ ነው፡፡ "ምን ሆነሽ ነው? በጣም አመመሽ እንዴ?" አለችኝ ግንባሬን በእጇ እየዳበሰች፡፡ "የት ውለሽ ነው? ምን ሆነሽ ነው? የጥያቄ መአት እያከታተሉ ይጠይቁኝ ጀመር፡፡ ብዙም አላወራውም ያመጡልኝን እራት ከበላሁ ቡሀላ ተመልሼ አልጋዬላይ ወጣሁ፡፡ ስለውሎዋቸው ያጫውቱኝ ጀመር፡፡ እያወራን ስልኬ መልእክት ገባ ፡፡ ፍሬ ነው አነብቤው ተውኩት፡፡ ጨዋታችን ቀጠለ፡፡
እንዲ እንዲያ እያልኩ ቀናት ተቆጠሩ ፣ሳምንቱም አለቀ ፣ቤት ደርሼ ተመለስኩ፡፡ ለቹቹ ቃል እንደገባውላት ፍሬን አንድ ሳምንት ሳላገኘው፡፡ በቀጠሮዋችን ቀን ከቹቹ ጋር የተለመደው ቦታ ተቀምጠን ስላለፈው ነገር ማውራት ጀመርን፡፡ "ይኸው ፍቅር እንዳልያዘኝ እወቂ፡፡ አንድ ሳምንት አላገኘውትም ግን ምንም አልተሰማኝም ፣ምንም አልሆንኩም" አልኳት ግዳጁን እንደተወጣ መልእክተኛ ፡፡ "ስለዚህ በዚሁ ትቀጥያለሽ ማለት ነው" አለችኝ ቹቹ፡፡ አልገባኝም ፤ደነገጥኩ "ማለት ከዚህ ቡሀላ ፍሬን ላላገኘው?" አልኳት፡፡ "እንደዛ ማለቴ አይደለም ከዚህ ቡሀላም ስለፍሬ አታስቢም ፣ብዙ ግዜሽን ከፍሬ ጋር አታሳልፊም፡፡ በቃ እንደማንኛውም ተራ ጉዋደኛ ብቻ ይሆናል ምትቀራረቢው" አለችኝ፡፡
" 'ለምንድነው?' ብለሽ እንደምታስቢ አውቃለው፡፡ አንቺ በዚህ ግዜ ስለ ፍቅር ምንም ማሰብም ፣ፍቅረኛ እንዲኖርሽ አትፈልጊም፡፡ ፍሬ ደሞ በአጭር ቀን ውስጥ በጣም የቀረብሽው ወንድ ነው፡፡ በዚህ ከቀጠልሽ ደሞ ወደ ፍቅር ማይቀየርበት ምክንያት አይኖርም፡፡ስለዚህ ግንኙነታቹን ትቀንሻለሽ፡፡ ይሄንን ደሞ ምመክርሽ ላንቺው ብዬ ነው፡፡" አለችኝ ቹቹ፡፡ ዝም ብዬ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ ምንም ሳልናገር ከ አስር ደቂቃ በላይ አሳለፍኩ፡፡ ብዙ አወጣው አወረድኩ፡፡ "እውነቷን ነው? አይ ምንም ችግር የለውም . . . "ቹቹም ዝም ብላ ታየኝ ጀመር፡፡ እንደመጀመሪያው ቀን ዛሬ ወዲያው ልስማማ አልቻልኩም፡፡ "እሺ" የማለት ድፍረት አጣው፡፡ "ይሄንን ግዜ ወስደሽ በደንብ አስቢበት፡፡ የምርጫ ጉዳይ አይደለም፡፡ እሺ ወይ እንቢ እንድትይኝ አይደለም፡፡ ራስሽ እንድታስቢው ፤ራስሽን በራስሽ እንድትመረምሪበት ነው የነገርኩሽ" አለችኝ ቹቹ አይኔን እያየች፡፡ እንማስብበት ነግሬያት በተለመደው ሰአት ተለያየን፡፡
ወደሚጣ ስልክ ስደውል ፍሬ አነሳው፡፡ "ሴና ግን ምን አድርጌሽ ነው? እንደዚ ሚያስከፋ ነገር አደረኩሽ ግን? . . ."ገና እያወራኝ ስልኩን ዘጋውት፡፡ ደነገጥኩኝ፡፡ 'እውነት ምን አድርጎኝ ነው ግን?' ብዬ አሰብኩ፡፡ 'እንዴት ግን የሚጣን ስልክ አነሳው?ምናልባት አብረው ሆነው ይሆናል፡፡' እነሚጣ የት እንዳሉ ለማወቅ ነበር የደወልኩት፡፡
ትንሽ ቆይቶ ፍሬ በራሱ ስልክ መልእክት ላከልኝ፡፡ በቆምኩበት ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩ፡፡ እያነበብኩ ወደመሀል ስደርስ ሳላስበው እንባዬ መጣ፡፡ ማንበቤን ቀጠልኩ፡፡ እንባዬ አይኔን ሸፎኖኝ ስልኬላይ መንጠባጠብ ጀመረ፡፡ የላከልኝ መልእክት እንዲህ የሚል ነው . . .
#ክፍል_ሀያሁለትን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
ሴና ክፍል ሀያ ሁለት ❤️
. . . የላከልኝ መልእክት እንዲህ የሚል ነው"ሴና ይሄንን መልእክት ማታ ነበር ልልክልሽ የነበረው፡፡ ግን ምናልባት ሳይመቻት ይሆናል ስልም መልሼ አሰብኩ፡፡ አሁን ገን ጥርጣሬዬ እውነት መሆኑን አሳየሽኝ፡፡
ሴና በዚች አንድ ሳምንት ያሳለፍነው ግዜ ለብዙ ግዜያት አብሬያቸው የቆየው ሌሎች ሴቶች ጋር ያሳለፍኩትን ግዜ በእጥፍ የሚበልጥ ነው፡፡ ምን እንዳስቀየምኩሽ ፣ምን እንዳጠፋው ወይ ያልተመቸሽ ነገር ምን እንደሆነ ራሱ ሳትናገሪ በድንገት ጠፋሽ፡፡ 'አንድ ሳምንት ለምታውቃት ልጅ ምንድነው እንደዚ ሙጭጭ ማለት፡፡' እስኪሉኝ የዶርም ልጆች ስላንቺ ሳስብ ስጨነቅ ነበር፡፡አንቺ ግን ትክክል አልሰራሽም፡፡ በእውነት እልሻለው ትክክል አልሰራሽም፡፡ አንቺ ምክንያት ሊኖርሽ ይችላል፡፡ ግን ምንም ሆነ ምን ከኔጋር ሚገናኝ ምክንያት የሚኖርሽ አይመስለኝም፡፡ መጀመሪያ ያገኘውሽ ቀን የሆነ ነገር ነበር የተሰማኝ፡፡ያለፈውን መጥፎ ግዜ አስታወሽኝ አሁን ፡፡ ምን እንደሆነ ልነግርሽ አልችልም፡፡ እና ሴናዬ በቃ አንቺ ያመንሽበት ነገር ከሆነ ችግር የለውም አልደውልም ፣ መልእክትም አልክም፡፡ እኔ ሴት ምናምን ወዲያ ወዲ ማደርግ መስሎሽም ከሆነ ተሳስተሻል፡፡ እንደዛ ቢሆን አንድ ሳምንት ላወኩሽ ይሄንን ሁሉ ባለፈለፍኩ በሁለተኛው ቀን ነበር ምረሳሽ፡፡ እና በቃ እኔን ሽሽት ከ ጉዋደኞችሽ አትራቂ፡፡ እኔ አልደርስብሽም፡፡ መንገድ ላስ ስንገናኝ 'ሰላም' በይኝ ግን እሺ፡፡ ደና ሁኚ፡፡"
አንብቤው እንደጨረስኩ ባለሁበት አካባቢ መቀመጫ ፈልጌ ቁጭ አልኩ፡፡ ሳላስበው በጉንጬ ላይ የወረደውን እንባዬን አብሼ መልሼ መልእክቱን ማየት ጀመርኩ፡፡ አላውቅም ብቻ የሆነ ነገር ረበሸኝ፡፡ ልቤ ድንግጥ ድንግጥ ይላል፡፡ የማላውቀው የጭንቀት ስሜት ተሰማኝ፡፡ እንደምንም ራሴን አረጋግቼ ወደ ዶርም ሄድኩኝ፡፡
ዶርሜ አልጋዬላይ ጋደም እንዳልኩ ፊቴ ላይ ሚመጣው ፍሬ ነው፡፡ ብገላበጥም ፣ጥቅልል ብዬ ብተኛም ፍሬን ብቻ ማሰብ ሆነ ስራዬ፡፡ ስልኬን አውጥቼ ከመጀመሪያ ቀን ጀምሮ ከፍሬ ጋር የተላላክናቸውን መልእክቶች ማንበብ ጀመርኩኝ፡፡ እነዛን ቀናት በውስጤ እያሰብኳቸው ብቻዬን ፈገግ እላለው፡፡ ዛሬ የላከልኝን መልእክት ደግሜ ሳነበው እንባዬ ይመጣል፡፡
እውነቱን ነው እኮ ግን ምን አደረገኝ ቆይ? ከኔጋር ግዜውን ስላጠፋ ነው? አብሮኝ ስለሆነ ነው? ስለቀረበኝ ነው? የራሴን ስሜት ብቻ ለምን ተከተልኩ? ሳላስበው እንባዬ ይፈሳል፡፡ የሆነ ቅር ቅር ሚል ነገር ይሰማኛል፡፡ አልጋዬላይ ጋደም በዬ በትዝታ ከፍሬ ጋር እየተጫወትኩ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡
ከእንቅልፌ ስነሳ እኩለ ለሊት አልፎአል፡፡ ራሴን በጣም አሞኛል፡፡ አልጋዬ ላይ እንዳለው ቀና ብዬ ዶርሙን በአይኔ ቃኘው፡፡ ሁሉም ተኝተዋል፡፡ ጠረቤዛ ላይ የፕላስቲክ ምሪንዳ እና ብስኩት ተቀምጦአል፡፡ ምናልባት ለኔ ይሆናል ብዬ አሰብኩ፡፡ ስልኬን ስመለከት 16 ግዜ ተደውሎአል፡፡ደነገጥኩ ወንድሜ እና አባቴ ናቸው፡፡ አሁን እንዳልደውል ወረበሽ ይሆናል፡፡ የፍሬን መልእክት ስላጣው ቅር አለኝ፡፡ተመልሼ ተኛሁ ግን እንቅልፍ አልወስድ አለኝ፡፡ እንዲሁ ስገላበጥ አነጋው፡፡
ጥዋት የዶርሜ ልጆች ሲነሱ ሁሉም በየተራ "ሴና ማታ ምን ሆነሽ ነው?" ይሉኝ ጀመር፡፡መልሼ ጠየኳቸው"ምን ሆንኩኝ?" ስል፡፡ "እንዴ ማታ ብንጠራሽ አትሰሚ ደሙ አልቅሰሽ ነበር? ስልክሽም ያንን ሁሉ ግዜ እንደዛ እየጠራ መጨረሻ እንዳይጨነቁ ብዬ 'ትንሽ ራሱዋን አመም አድርጎዋት ተኝታ ነው'አልኩልሽ፡፡ ቆይ ግን ምን ሆነሽ ነው?" አለችኝ እኑካ፡፡'አይ ተመስገን ስልኬን ካነሳቹ ሌላው ቀላል ነው' አልኩኝ በሆዴ፡፡
"ሜምናልባት እራት ካልበላሽ ብለን ነው ያመጣንልሽ እኮ ፆምሽን ነዋ ያደርሽው?" አለችኝ ሚጣ እንደመቆጣት ብላ፡፡ "እሺ አሁን ቁርስ በላዋለው "ብያቸው ልተጣጠብ ወጣው፡፡ ተጣጥቤ ስመለስ ራስምታቴ ባሰብኝ፡፡ አልጋዬ ላይ ተመልሼ ተኛው፡፡ ቢጠይቁኝም መልስ የለኝም፡፡ "የክፍል ሰአት እየደረሰ ስለሆነ እናንተ ሂዱ በቃ እኔ እዚ አለው" አለች ቹቹ፡፡ አሁን ድምፁዋን ስሰማ ነው መኖሩዋን ያወኩት፡፡ "አይ እኔ አለው እናንተ ሂዱ" አለች ሚጣ፡፡ ከቹቹ ጋር ተቃራኒ እንደሆኑ አውቃለው፡፡ "ካልሽ እንዳልሽ ይሁን "ስትል ቹቹና ጉዋደኞቹዋ ተያይዘው ወጡ፡፡ እነ እኑካም ተከታትለው ወጡ፡፡ በመጨረሻም ባለ መነፅሯ ወጣች፡፡ እኔና ሚጣ ብቻ ቀረን፡፡ አልጋዬላይ ተጠቅልዬ ጋደም እንዳልኩ ነኝ፡፡
"ምን ሆነሽ ነው ግን? ሰሞኑን እኮ ልክ አይደለሽም" አለችኝ ሚጣ፡፡ "ምንም አልሆንኩም" አልኳት እንባ እየተናነቀኝ፡፡"የሆነ ነገርማ ሆነሻል ፤ግድ የለሽም ንገሪኝ" ስትል በጥያቄ አስጨነቀችኝ፡፡" እኔም ግራ ገብቶኛል ሚጣ ፡፡ እኔ ራሴ አላውቅም! እንዲነው ምልሽ ! ተረድቼ ማስረዳሽ ! የሆንኩትን ማውቀው ነገር የለኝም! እኔም ግራ ገብቶኛል እኮ! ምን ሆንኩ ልበልሽ!? እንዴት ላስረዳሽ!? " እንባዬ እየወረደ ሀይለቃል የተቀላቀለበት መልስ መለስኩላት፡፡ ራስምታቴ ጨመረ . . .
#ክፍል_ሀያሶስትን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
https://telegram.me/geyone
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
. . . የላከልኝ መልእክት እንዲህ የሚል ነው"ሴና ይሄንን መልእክት ማታ ነበር ልልክልሽ የነበረው፡፡ ግን ምናልባት ሳይመቻት ይሆናል ስልም መልሼ አሰብኩ፡፡ አሁን ገን ጥርጣሬዬ እውነት መሆኑን አሳየሽኝ፡፡
ሴና በዚች አንድ ሳምንት ያሳለፍነው ግዜ ለብዙ ግዜያት አብሬያቸው የቆየው ሌሎች ሴቶች ጋር ያሳለፍኩትን ግዜ በእጥፍ የሚበልጥ ነው፡፡ ምን እንዳስቀየምኩሽ ፣ምን እንዳጠፋው ወይ ያልተመቸሽ ነገር ምን እንደሆነ ራሱ ሳትናገሪ በድንገት ጠፋሽ፡፡ 'አንድ ሳምንት ለምታውቃት ልጅ ምንድነው እንደዚ ሙጭጭ ማለት፡፡' እስኪሉኝ የዶርም ልጆች ስላንቺ ሳስብ ስጨነቅ ነበር፡፡አንቺ ግን ትክክል አልሰራሽም፡፡ በእውነት እልሻለው ትክክል አልሰራሽም፡፡ አንቺ ምክንያት ሊኖርሽ ይችላል፡፡ ግን ምንም ሆነ ምን ከኔጋር ሚገናኝ ምክንያት የሚኖርሽ አይመስለኝም፡፡ መጀመሪያ ያገኘውሽ ቀን የሆነ ነገር ነበር የተሰማኝ፡፡ያለፈውን መጥፎ ግዜ አስታወሽኝ አሁን ፡፡ ምን እንደሆነ ልነግርሽ አልችልም፡፡ እና ሴናዬ በቃ አንቺ ያመንሽበት ነገር ከሆነ ችግር የለውም አልደውልም ፣ መልእክትም አልክም፡፡ እኔ ሴት ምናምን ወዲያ ወዲ ማደርግ መስሎሽም ከሆነ ተሳስተሻል፡፡ እንደዛ ቢሆን አንድ ሳምንት ላወኩሽ ይሄንን ሁሉ ባለፈለፍኩ በሁለተኛው ቀን ነበር ምረሳሽ፡፡ እና በቃ እኔን ሽሽት ከ ጉዋደኞችሽ አትራቂ፡፡ እኔ አልደርስብሽም፡፡ መንገድ ላስ ስንገናኝ 'ሰላም' በይኝ ግን እሺ፡፡ ደና ሁኚ፡፡"
አንብቤው እንደጨረስኩ ባለሁበት አካባቢ መቀመጫ ፈልጌ ቁጭ አልኩ፡፡ ሳላስበው በጉንጬ ላይ የወረደውን እንባዬን አብሼ መልሼ መልእክቱን ማየት ጀመርኩ፡፡ አላውቅም ብቻ የሆነ ነገር ረበሸኝ፡፡ ልቤ ድንግጥ ድንግጥ ይላል፡፡ የማላውቀው የጭንቀት ስሜት ተሰማኝ፡፡ እንደምንም ራሴን አረጋግቼ ወደ ዶርም ሄድኩኝ፡፡
ዶርሜ አልጋዬላይ ጋደም እንዳልኩ ፊቴ ላይ ሚመጣው ፍሬ ነው፡፡ ብገላበጥም ፣ጥቅልል ብዬ ብተኛም ፍሬን ብቻ ማሰብ ሆነ ስራዬ፡፡ ስልኬን አውጥቼ ከመጀመሪያ ቀን ጀምሮ ከፍሬ ጋር የተላላክናቸውን መልእክቶች ማንበብ ጀመርኩኝ፡፡ እነዛን ቀናት በውስጤ እያሰብኳቸው ብቻዬን ፈገግ እላለው፡፡ ዛሬ የላከልኝን መልእክት ደግሜ ሳነበው እንባዬ ይመጣል፡፡
እውነቱን ነው እኮ ግን ምን አደረገኝ ቆይ? ከኔጋር ግዜውን ስላጠፋ ነው? አብሮኝ ስለሆነ ነው? ስለቀረበኝ ነው? የራሴን ስሜት ብቻ ለምን ተከተልኩ? ሳላስበው እንባዬ ይፈሳል፡፡ የሆነ ቅር ቅር ሚል ነገር ይሰማኛል፡፡ አልጋዬላይ ጋደም በዬ በትዝታ ከፍሬ ጋር እየተጫወትኩ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡
ከእንቅልፌ ስነሳ እኩለ ለሊት አልፎአል፡፡ ራሴን በጣም አሞኛል፡፡ አልጋዬ ላይ እንዳለው ቀና ብዬ ዶርሙን በአይኔ ቃኘው፡፡ ሁሉም ተኝተዋል፡፡ ጠረቤዛ ላይ የፕላስቲክ ምሪንዳ እና ብስኩት ተቀምጦአል፡፡ ምናልባት ለኔ ይሆናል ብዬ አሰብኩ፡፡ ስልኬን ስመለከት 16 ግዜ ተደውሎአል፡፡ደነገጥኩ ወንድሜ እና አባቴ ናቸው፡፡ አሁን እንዳልደውል ወረበሽ ይሆናል፡፡ የፍሬን መልእክት ስላጣው ቅር አለኝ፡፡ተመልሼ ተኛሁ ግን እንቅልፍ አልወስድ አለኝ፡፡ እንዲሁ ስገላበጥ አነጋው፡፡
ጥዋት የዶርሜ ልጆች ሲነሱ ሁሉም በየተራ "ሴና ማታ ምን ሆነሽ ነው?" ይሉኝ ጀመር፡፡መልሼ ጠየኳቸው"ምን ሆንኩኝ?" ስል፡፡ "እንዴ ማታ ብንጠራሽ አትሰሚ ደሙ አልቅሰሽ ነበር? ስልክሽም ያንን ሁሉ ግዜ እንደዛ እየጠራ መጨረሻ እንዳይጨነቁ ብዬ 'ትንሽ ራሱዋን አመም አድርጎዋት ተኝታ ነው'አልኩልሽ፡፡ ቆይ ግን ምን ሆነሽ ነው?" አለችኝ እኑካ፡፡'አይ ተመስገን ስልኬን ካነሳቹ ሌላው ቀላል ነው' አልኩኝ በሆዴ፡፡
"ሜምናልባት እራት ካልበላሽ ብለን ነው ያመጣንልሽ እኮ ፆምሽን ነዋ ያደርሽው?" አለችኝ ሚጣ እንደመቆጣት ብላ፡፡ "እሺ አሁን ቁርስ በላዋለው "ብያቸው ልተጣጠብ ወጣው፡፡ ተጣጥቤ ስመለስ ራስምታቴ ባሰብኝ፡፡ አልጋዬ ላይ ተመልሼ ተኛው፡፡ ቢጠይቁኝም መልስ የለኝም፡፡ "የክፍል ሰአት እየደረሰ ስለሆነ እናንተ ሂዱ በቃ እኔ እዚ አለው" አለች ቹቹ፡፡ አሁን ድምፁዋን ስሰማ ነው መኖሩዋን ያወኩት፡፡ "አይ እኔ አለው እናንተ ሂዱ" አለች ሚጣ፡፡ ከቹቹ ጋር ተቃራኒ እንደሆኑ አውቃለው፡፡ "ካልሽ እንዳልሽ ይሁን "ስትል ቹቹና ጉዋደኞቹዋ ተያይዘው ወጡ፡፡ እነ እኑካም ተከታትለው ወጡ፡፡ በመጨረሻም ባለ መነፅሯ ወጣች፡፡ እኔና ሚጣ ብቻ ቀረን፡፡ አልጋዬላይ ተጠቅልዬ ጋደም እንዳልኩ ነኝ፡፡
"ምን ሆነሽ ነው ግን? ሰሞኑን እኮ ልክ አይደለሽም" አለችኝ ሚጣ፡፡ "ምንም አልሆንኩም" አልኳት እንባ እየተናነቀኝ፡፡"የሆነ ነገርማ ሆነሻል ፤ግድ የለሽም ንገሪኝ" ስትል በጥያቄ አስጨነቀችኝ፡፡" እኔም ግራ ገብቶኛል ሚጣ ፡፡ እኔ ራሴ አላውቅም! እንዲነው ምልሽ ! ተረድቼ ማስረዳሽ ! የሆንኩትን ማውቀው ነገር የለኝም! እኔም ግራ ገብቶኛል እኮ! ምን ሆንኩ ልበልሽ!? እንዴት ላስረዳሽ!? " እንባዬ እየወረደ ሀይለቃል የተቀላቀለበት መልስ መለስኩላት፡፡ ራስምታቴ ጨመረ . . .
#ክፍል_ሀያሶስትን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
https://telegram.me/geyone
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
ሴና ክፍልሀያሶስት ❤️
. . . ራስ ምታቴ ጨመረ በጣም ጭንቅንቅ ሚያደርግ ስሜት ይሰማኛል፡፡እንደምንም ራሴን ለማረጋጋት እየሞከርኩ ነው፡፡ሚጣ በተደጋጋሚ ብትጠይቀኝም ምክንያቴን እኔ ራሱ እንደማላውቀው ነገርኳት፡፡
ቀናት ተቆጠሩ የሆዴን በሆዴ ይዤ ቀጠልኩ፡፡ቅዳሜና እሁድ ቤት ስሄድ ከበፊቱ ይበልጥ ይጨንቀኝ ጀመር፡፡ ትምህርቱም እየቀጠለ ፣እኔም ተማሪዎችን እየተግባባው ግቢውንም በደንብ እየለመድኩት ፣ዶርም ውስጥም ሁላችንም እየተግባባን መጣን፡፡ የኛ ዶርም ውስጥ የተመደብነው 8ብንሆንም አንደኛዋ ግን መጥታም አታውቅም የቀረነው ግን ከቀን ወደቀን የዶርም አንድነታችን እየጠነከረ መጣ፡፡ እነ ቹቹ ሚያመሹ ቀን እንጠብቃቸው ጀመርን፡፡ ዶርማችንን እየወደድኩት መጣው፡፡ወር አለፈ ቀናት ተቆጠሩ፡፡ይሄንን ሁሉ ግዜ ግን በውስጤ ያለውን ነገር ለማንም አልተናገርኩም፡፡ ዛሬም ድረስ ስልኬ ላይ የፍሬን መልእክቶች አነባቸዋለው፡፡ እነዛ ወክ ያደረግንባቸው ምሽቶች የመጀመሪያዎቼም ስለሆኑ መሰለኝ ዛሬም ድረስ ውስጤ አሉ፡፡
በዚህ ሁሉ ግዜ ፍሬን በአካል አግኝቼው አላውቅም፡፡ አንድ ግቢውስጥ ሁነን አለመገናኘታችን አስገርሞኛል፡፡እኔ ከነሚጣጋር ስሆን ፍሬ አይመጣም፤እንዳጋጣሚ እኔ የሌለው ቀን ፍሬ እንደመጣ ይነግሩኛል፡፡አለመገጣጠም ይሁን ፍሬ ከኔ እየራቀ አልገባኝም፡፡ስለሱ ወሬ ሲነሳ ደስ ይለኛል ፣ናፍቀዋለው ለሱ የሆነ ስሜት ይሰማኛል፡፡"ምን እየሆንኩ ነው ግን?"ስል ራሴን ጠይቃለው፡፡ ዴቭን ሳገኘው ስለፍሬ ልጠይቅ እያልኩ ተወዋለው፡፡ ሽንፈት መስሎ ይታየኛል፡፡ "ግን ምኑን ነው ምሸነፈው?" የተደበላለቀ ነገር ውስጥ ነኝ፡፡ አሁንም ድረስ ውስጤ አልተረጋጋም ፣የሆነ ነገር የጎደለ ያህል ቅር ቅር ይለኛል፡፡
ዛሬ የዶርም ልጆች ተሰብስበን እራት አንድ ላይ ልንበላ ተቀጣጥረናል፡፡ ሀሳቡን ያመጣችው ቹቹ ነች፡፡ ሁላችንም ምሽት ላይ ግቢውስጥ በአንዱ ካፌ ተሰብስበን እራት ከበላን ብሀላ ቹቹ አንድ ልታሳየን ምትፈልገው ነገር እንዳለ ነግራን ሁላችንም ተያይዘን ወደ ምትወስደን ቦታ እንከተላት ጀመር፡፡
ከአንድ ተማሪዎች ከማይበዙበት ቦታ እንደደረስን እዚ እንድንቀመጥ ነገረችን፡፡ እኔ ውስጤ ተጨነቀ፡፡ ይሄ ቦታ ከፍሬጋር ማታ መታ እንቀመጥበት ነበር፡፡ ሁላችንም ቦታ ቦታ ይዘን ተቀመጥን፡፡ ቹቹ ከመሀከላችን ቆማ ንግግር ታደርግ ጀመር "እህቶቼ እንደምን አመሻቹ፡፡ ያው እንግዲ ዛሬ እንዲ እንድንሰባሰብ ያደረኩዋቹ እኛ አንድ ክፍል ውስጥ ምንኖር ልጆች ነን፡፡ ያ' ማለት ደሞ ልክ እንደ አንድ ወላጅ ልጆች ነን ማለት ነው፡፡ እዚ ሆነን የሆነ ነገር ቢደርስብን ከወላጆቻችንም ሆነ ከማንም ቀድመን አንዳኝን ነን ለአንዳችን ምንደርሰው፡፡ በዶርም ውስጥ ስንኖኖር አንዳች የሌላውን ደስታም ሆነ ሀዘን እንጋራለን፡፡ አብረን ስንሆን በጋራ ምናሳልፋቸው ነገሮች ደሞ ብዙ ናቸው፡፡ዛሬ እንደመጀመሪያ በዶርማችን የተፈጠረ አንድ ነገር አለ እሱን እናስተካክላለን፡፡እና ብዙ እንዳለፈልፍባቹ ሴና ተነሺ "አለች፡፡
እኔን እንድነሳ ካደረገችን ቡሀላ በአንድ ጨርቅ አይኔን ልታስረኝ እንደሆነ ነገረችኝ፡፡ፈራው ምን ሊፈጠር እንደሚችል ልገምትም አልቻልኩም፡፡"እንግዲ ሴና ዛሬ ላንቺ አንድ ደስ ሚል ነገር አለ" አለች ቹቹ አይኔን አስራ ስታበቃ፡፡'ምን ይሆን?' አልኩኝ ፤አይኔ እስኪፈታ ቸኮልኩ ፤የተዘጋጀልኝ ነገር ምን እንደሆነ ለማየት በጣም ጓጓው . . .
#ክፍል\ሀያአራትን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
@geyone
@geyone
@geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
. . . ራስ ምታቴ ጨመረ በጣም ጭንቅንቅ ሚያደርግ ስሜት ይሰማኛል፡፡እንደምንም ራሴን ለማረጋጋት እየሞከርኩ ነው፡፡ሚጣ በተደጋጋሚ ብትጠይቀኝም ምክንያቴን እኔ ራሱ እንደማላውቀው ነገርኳት፡፡
ቀናት ተቆጠሩ የሆዴን በሆዴ ይዤ ቀጠልኩ፡፡ቅዳሜና እሁድ ቤት ስሄድ ከበፊቱ ይበልጥ ይጨንቀኝ ጀመር፡፡ ትምህርቱም እየቀጠለ ፣እኔም ተማሪዎችን እየተግባባው ግቢውንም በደንብ እየለመድኩት ፣ዶርም ውስጥም ሁላችንም እየተግባባን መጣን፡፡ የኛ ዶርም ውስጥ የተመደብነው 8ብንሆንም አንደኛዋ ግን መጥታም አታውቅም የቀረነው ግን ከቀን ወደቀን የዶርም አንድነታችን እየጠነከረ መጣ፡፡ እነ ቹቹ ሚያመሹ ቀን እንጠብቃቸው ጀመርን፡፡ ዶርማችንን እየወደድኩት መጣው፡፡ወር አለፈ ቀናት ተቆጠሩ፡፡ይሄንን ሁሉ ግዜ ግን በውስጤ ያለውን ነገር ለማንም አልተናገርኩም፡፡ ዛሬም ድረስ ስልኬ ላይ የፍሬን መልእክቶች አነባቸዋለው፡፡ እነዛ ወክ ያደረግንባቸው ምሽቶች የመጀመሪያዎቼም ስለሆኑ መሰለኝ ዛሬም ድረስ ውስጤ አሉ፡፡
በዚህ ሁሉ ግዜ ፍሬን በአካል አግኝቼው አላውቅም፡፡ አንድ ግቢውስጥ ሁነን አለመገናኘታችን አስገርሞኛል፡፡እኔ ከነሚጣጋር ስሆን ፍሬ አይመጣም፤እንዳጋጣሚ እኔ የሌለው ቀን ፍሬ እንደመጣ ይነግሩኛል፡፡አለመገጣጠም ይሁን ፍሬ ከኔ እየራቀ አልገባኝም፡፡ስለሱ ወሬ ሲነሳ ደስ ይለኛል ፣ናፍቀዋለው ለሱ የሆነ ስሜት ይሰማኛል፡፡"ምን እየሆንኩ ነው ግን?"ስል ራሴን ጠይቃለው፡፡ ዴቭን ሳገኘው ስለፍሬ ልጠይቅ እያልኩ ተወዋለው፡፡ ሽንፈት መስሎ ይታየኛል፡፡ "ግን ምኑን ነው ምሸነፈው?" የተደበላለቀ ነገር ውስጥ ነኝ፡፡ አሁንም ድረስ ውስጤ አልተረጋጋም ፣የሆነ ነገር የጎደለ ያህል ቅር ቅር ይለኛል፡፡
ዛሬ የዶርም ልጆች ተሰብስበን እራት አንድ ላይ ልንበላ ተቀጣጥረናል፡፡ ሀሳቡን ያመጣችው ቹቹ ነች፡፡ ሁላችንም ምሽት ላይ ግቢውስጥ በአንዱ ካፌ ተሰብስበን እራት ከበላን ብሀላ ቹቹ አንድ ልታሳየን ምትፈልገው ነገር እንዳለ ነግራን ሁላችንም ተያይዘን ወደ ምትወስደን ቦታ እንከተላት ጀመር፡፡
ከአንድ ተማሪዎች ከማይበዙበት ቦታ እንደደረስን እዚ እንድንቀመጥ ነገረችን፡፡ እኔ ውስጤ ተጨነቀ፡፡ ይሄ ቦታ ከፍሬጋር ማታ መታ እንቀመጥበት ነበር፡፡ ሁላችንም ቦታ ቦታ ይዘን ተቀመጥን፡፡ ቹቹ ከመሀከላችን ቆማ ንግግር ታደርግ ጀመር "እህቶቼ እንደምን አመሻቹ፡፡ ያው እንግዲ ዛሬ እንዲ እንድንሰባሰብ ያደረኩዋቹ እኛ አንድ ክፍል ውስጥ ምንኖር ልጆች ነን፡፡ ያ' ማለት ደሞ ልክ እንደ አንድ ወላጅ ልጆች ነን ማለት ነው፡፡ እዚ ሆነን የሆነ ነገር ቢደርስብን ከወላጆቻችንም ሆነ ከማንም ቀድመን አንዳኝን ነን ለአንዳችን ምንደርሰው፡፡ በዶርም ውስጥ ስንኖኖር አንዳች የሌላውን ደስታም ሆነ ሀዘን እንጋራለን፡፡ አብረን ስንሆን በጋራ ምናሳልፋቸው ነገሮች ደሞ ብዙ ናቸው፡፡ዛሬ እንደመጀመሪያ በዶርማችን የተፈጠረ አንድ ነገር አለ እሱን እናስተካክላለን፡፡እና ብዙ እንዳለፈልፍባቹ ሴና ተነሺ "አለች፡፡
እኔን እንድነሳ ካደረገችን ቡሀላ በአንድ ጨርቅ አይኔን ልታስረኝ እንደሆነ ነገረችኝ፡፡ፈራው ምን ሊፈጠር እንደሚችል ልገምትም አልቻልኩም፡፡"እንግዲ ሴና ዛሬ ላንቺ አንድ ደስ ሚል ነገር አለ" አለች ቹቹ አይኔን አስራ ስታበቃ፡፡'ምን ይሆን?' አልኩኝ ፤አይኔ እስኪፈታ ቸኮልኩ ፤የተዘጋጀልኝ ነገር ምን እንደሆነ ለማየት በጣም ጓጓው . . .
#ክፍል\ሀያአራትን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
@geyone
@geyone
@geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
🎁ኢትዮ-ቴሌኮም ትርፉን በማስመልከት ለህዝቡ ለ3 ቀናት የሚቆይ የ1GB ኢንተርኔት እና የ303 Flexi Unit ነፃ አገልግሎት አቀረበ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://telegram.me/geyone
https://telegram.me/geyone
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://telegram.me/geyone
https://telegram.me/geyone
,,,,አይ እሷ
እንደ እናት አንደ አባት፣
እንደ ባል ሁኘ አገለገልኳት፣
እኔ ለሷ ብየ አንገቴን ብደፋላት፣
እሷ እዳትደክም ብየ እኔ ስሰራላት፣
በለለኝ አንደበት ፍቅሬን በሰጠዋት፣
ወገቤን አጥፌ እሷን ባነገስኳት፣
እዚ እኔን ሚስት አርጋ፣
ለካ እዛ ባል አላት።
$$$$$$$=Job
✍eyoba
https://telegram.me/geyone
እንደ እናት አንደ አባት፣
እንደ ባል ሁኘ አገለገልኳት፣
እኔ ለሷ ብየ አንገቴን ብደፋላት፣
እሷ እዳትደክም ብየ እኔ ስሰራላት፣
በለለኝ አንደበት ፍቅሬን በሰጠዋት፣
ወገቤን አጥፌ እሷን ባነገስኳት፣
እዚ እኔን ሚስት አርጋ፣
ለካ እዛ ባል አላት።
$$$$$$$=Job
✍eyoba
https://telegram.me/geyone
ሴና ክፍል ሀያ አራት ❤️
. . . የተዘጋጀልኝ ነገር ምን እንደሆነ ለማየት ጓጓው፡፡ "ይሄንን ያደረኩት በብዙ መልኩ አመዛዝኜ ነው፡፡ በዶርማችን ውስጥ የሴና የሰሞኑ ጭንቀቱዋ ሁላችንንም ያስጨነቀን ነገር ነው፡፡ እናም ዛሬ . . ."
ቹቹ ስትናገር እኔ ይበልጥ ጉጉቴ ጨመረ፡፡ ምንድነው ያዘጋጀችልኝ? ጭንቀቴን ሚቀርፈው ነገር ምንድነው? የተጋረደው አይኔን ለመፍታት ከጫፍ ደረስኩ፡፡ 'አረ ማብራሪያው ቡሀላ ይደርሳል!' ብዬ ልጮህ ምንም አልቀረኝም፡፡ በመሀል ዝምታ ሰፈነ፡፡ ጨነቀኝ እየተጫወቱብኝ መሰለኝ፡፡በመቀጠል ቹቹ ከሁዋላዬ ቆማ ጨርቁን ከአይኔ ላይ ልታነሳልኝ ስትሞክር በጣም በመቸኮሌ እኔም አገዝኳት፡፡ በሁለት እጄ አይኔላይ የተሸፈነውን ጨርቅ ገለጥኩት፡፡ ደነገጥኩ! የሆነ ነገር ሰውነቴን ውርር አደረገኝ!
ፍሬ ነው፡፡ አዎ አጠገቤ የቆመው ፍሬ ነው፡፡' አ . . .እ . . . 'ተንተባተብኩ ፡፡ማውራትም አልቻልኩም፡፡ 'ፍ . . . ፍ . . . ፍሬ . . .አን . . ተ' ተንቀጠቀጥኩ ፡፡ምን እንደተሰማኝ እንኳ በቅጡ አላውቀዉም፡፡ ፍሬ ወደኔ ተጠጋ . . . አይኖቼ እንባ አቀረሩ፡፡ እቅፍ አደረገኝእኔም እቅፍ አደረኩት፡፡ ጭምቅ . . .አድርጌ አቀፎኩት፡፡ እንባዬ መውረድ ጀመረ፡፡ አላመንኩም ፍሬን ነው ያቀፍኩት? ቀና ብዬ አይኑን አየውት መልሼ አቀፍኩት፡፡ "እንዴት ግን ይሄንን ሁሉ ቀን ?" አላስጨረሰኝም አንድ ጣቱን ከንፈሬ ላይ አድርጎ "ሁሉንም እርሺው በቃ"አለኝ፡፡ 'እሺ 'አልኩት መልሼ እያቀፍኩት አንገቱ ስር ሽጉጥ ብዬ፡፡ እንባዬ በጉንጬ ላይ ይወርዳል፡፡ "አታልቅሺያ አሁን እኮ አለሁ" አለኝ ፍሬ ጉንጬን በሁለት እጆቹ እየጠረገ፡፡
እኔ የተሰማኝን ደስታ መግለፅ እንኳ አልቻልኩም፡፡ ውስጤ ሰላም አገኘ ፡፡ትልቅ መረጋጋት ነው የተሰማኝ፡፡ ሁሉም ቆመው በደስታ እየተመለከቱን ነበር፡፡ ፍሬ ጉንጬን ከጠረገ ቡሀላ እጄን ይዞኝ ከአንደኛው መቀመጫላይ አብረን ቁጭ አልን፡፡ ሁሉም ተቀመጡ፡፡ የሁሉም ፊት ላይ ደስታ ይነበባል፡፡ እኔም በጣም ነው ደስ ያለኝ፡፡ ያ' ሁሉ ጭንቀቴ ወዴት እንደገባ፡፡ ቅልል ነው ያለኝ፡፡ በተቀመጥንበት መቀመጫ ላይ የፍሬን ትከሻ ድግፍ ብዬ በእጆቼ ወገቡን እና ሆዱን እቅፍ እንዳደረኩ እሱም አንገቴን አቅፎኝ እስሩ ሹግጥ ብዬ ሁሉንም ተራ በተራ እመለከታቸው ጀመር፡፡ የሁሉም ፊት ላይ ደስታ ይነበባል፡፡
ይህ ሁሉ ሲሆን ቆማ ትመለከት የነበረችው ቹቹ አሁንም እንደቆመች ናት፡፡ ሁላችንም ቦታ ቦታ ይዘን ክብ ሰርተን ከተቀመጥን ቡሀላ ንግግሩዋን ቀጠለች፡፡"ያው እንግዲ እህታችን ሴና ሰሞኑን ይረብሻት እና ሰላም ይነሳት የነበረው ነገር አሁን ላይ የተፈታ ይመስለኛል፡፡ ይሄንን ደሞ እንድናደርግ ሀሳብ ያመጣችው ሚጣ ስትሆን ሁላችንም በመተባበር አንድ ነገር እናድርግ ባልነው መሰረት ይኸው እንዲህ ሆነ፡፡ ሁላቹም ፈጣሪ ያክብራቹ፡፡ በጣም ደስ ሚል ምሽት ነበር፡፡ እና በቃ አሁን መሽቶአል ወደ ዶርም" አለች ፡፡ በንግግሩዋ መጨረሻ ላይ ሁሉም አጨበጨቡ፡፡ እየተሳሳቅን እና እየተጨዋወትን ትንሽ ከቆየን ቡሀላ ወደ ዶርም መሄድ ጀመርን፡፡
ወደ ዶርም መግቢያ ስንደርስ ፍሬ ሁሉንም ከተሰናበተ ቡሀላ በመጨረሻ ሁለታችን ቀረን፡፡ እንደከዚ ቀደሙ 'ደና ደር ፣ደና ደሪ' ብቻ ተባብለን መለያየት አልቻልንም፡፡ ሊሄድ ሲል ጠራዋለው ፣ልሄድ ስል ይጠራኛል፡፡ በመጨረሻም "በቃ ግቢ በስልክ እናወራለን ብዙ ካመሸው ዶርም ይቅጡኛል" ካለኝ ቡሀላ አቅፎኝ ተሰናብቶኝ ሄደ፡፡ መንገድ እንደሚሄድ ሰው ትንሽ ቆሜ አየሁት፡፡
ዶርም ስገባ በ ላፕቶፕ ዘፈን ከፍተው እየጨፈሩ ዶርሙን አድምቀውታል፡፡ እንኳን ደስ አለሽ እያሉ ሁሉም በተራ አቀፉኝ፡፡ የዶርማችን ፍቅር እውነት ደስ አለኝ፡፡ "ግን እንዴት እንደዚ ልታደርጉ ቻላቹ?"አልኩኝ ከወደበሩ ከሚገኘው አልጋ ላይ እየተቀመጥኩ፡፡ ጭፈራቸውን አቁመው ዘፈኑን ከዘጉ ቡሀላ ሁሉም ቦታ ቦታ ይዘው መቀመጥ ጀመሩ፡፡ ጥያቄዬን ደገምኩት "ግን እንዴት መጣላቹ ይሄ ሀሳብ?" አልኩኝ በፈገግታ የተሞላ ፊታቸውን መልሼ በፈገግታ እየተመለከትኩ፡፡ "የውልሽ ሴና" አለች ሚጣ ተመቻችታ እየተቀመጠች፡፡ "የውልሽ ሴና . . . ."
#ክፍል_ሀያአምስትን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
https://telegram.me/geyone
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••
. . . የተዘጋጀልኝ ነገር ምን እንደሆነ ለማየት ጓጓው፡፡ "ይሄንን ያደረኩት በብዙ መልኩ አመዛዝኜ ነው፡፡ በዶርማችን ውስጥ የሴና የሰሞኑ ጭንቀቱዋ ሁላችንንም ያስጨነቀን ነገር ነው፡፡ እናም ዛሬ . . ."
ቹቹ ስትናገር እኔ ይበልጥ ጉጉቴ ጨመረ፡፡ ምንድነው ያዘጋጀችልኝ? ጭንቀቴን ሚቀርፈው ነገር ምንድነው? የተጋረደው አይኔን ለመፍታት ከጫፍ ደረስኩ፡፡ 'አረ ማብራሪያው ቡሀላ ይደርሳል!' ብዬ ልጮህ ምንም አልቀረኝም፡፡ በመሀል ዝምታ ሰፈነ፡፡ ጨነቀኝ እየተጫወቱብኝ መሰለኝ፡፡በመቀጠል ቹቹ ከሁዋላዬ ቆማ ጨርቁን ከአይኔ ላይ ልታነሳልኝ ስትሞክር በጣም በመቸኮሌ እኔም አገዝኳት፡፡ በሁለት እጄ አይኔላይ የተሸፈነውን ጨርቅ ገለጥኩት፡፡ ደነገጥኩ! የሆነ ነገር ሰውነቴን ውርር አደረገኝ!
ፍሬ ነው፡፡ አዎ አጠገቤ የቆመው ፍሬ ነው፡፡' አ . . .እ . . . 'ተንተባተብኩ ፡፡ማውራትም አልቻልኩም፡፡ 'ፍ . . . ፍ . . . ፍሬ . . .አን . . ተ' ተንቀጠቀጥኩ ፡፡ምን እንደተሰማኝ እንኳ በቅጡ አላውቀዉም፡፡ ፍሬ ወደኔ ተጠጋ . . . አይኖቼ እንባ አቀረሩ፡፡ እቅፍ አደረገኝእኔም እቅፍ አደረኩት፡፡ ጭምቅ . . .አድርጌ አቀፎኩት፡፡ እንባዬ መውረድ ጀመረ፡፡ አላመንኩም ፍሬን ነው ያቀፍኩት? ቀና ብዬ አይኑን አየውት መልሼ አቀፍኩት፡፡ "እንዴት ግን ይሄንን ሁሉ ቀን ?" አላስጨረሰኝም አንድ ጣቱን ከንፈሬ ላይ አድርጎ "ሁሉንም እርሺው በቃ"አለኝ፡፡ 'እሺ 'አልኩት መልሼ እያቀፍኩት አንገቱ ስር ሽጉጥ ብዬ፡፡ እንባዬ በጉንጬ ላይ ይወርዳል፡፡ "አታልቅሺያ አሁን እኮ አለሁ" አለኝ ፍሬ ጉንጬን በሁለት እጆቹ እየጠረገ፡፡
እኔ የተሰማኝን ደስታ መግለፅ እንኳ አልቻልኩም፡፡ ውስጤ ሰላም አገኘ ፡፡ትልቅ መረጋጋት ነው የተሰማኝ፡፡ ሁሉም ቆመው በደስታ እየተመለከቱን ነበር፡፡ ፍሬ ጉንጬን ከጠረገ ቡሀላ እጄን ይዞኝ ከአንደኛው መቀመጫላይ አብረን ቁጭ አልን፡፡ ሁሉም ተቀመጡ፡፡ የሁሉም ፊት ላይ ደስታ ይነበባል፡፡ እኔም በጣም ነው ደስ ያለኝ፡፡ ያ' ሁሉ ጭንቀቴ ወዴት እንደገባ፡፡ ቅልል ነው ያለኝ፡፡ በተቀመጥንበት መቀመጫ ላይ የፍሬን ትከሻ ድግፍ ብዬ በእጆቼ ወገቡን እና ሆዱን እቅፍ እንዳደረኩ እሱም አንገቴን አቅፎኝ እስሩ ሹግጥ ብዬ ሁሉንም ተራ በተራ እመለከታቸው ጀመር፡፡ የሁሉም ፊት ላይ ደስታ ይነበባል፡፡
ይህ ሁሉ ሲሆን ቆማ ትመለከት የነበረችው ቹቹ አሁንም እንደቆመች ናት፡፡ ሁላችንም ቦታ ቦታ ይዘን ክብ ሰርተን ከተቀመጥን ቡሀላ ንግግሩዋን ቀጠለች፡፡"ያው እንግዲ እህታችን ሴና ሰሞኑን ይረብሻት እና ሰላም ይነሳት የነበረው ነገር አሁን ላይ የተፈታ ይመስለኛል፡፡ ይሄንን ደሞ እንድናደርግ ሀሳብ ያመጣችው ሚጣ ስትሆን ሁላችንም በመተባበር አንድ ነገር እናድርግ ባልነው መሰረት ይኸው እንዲህ ሆነ፡፡ ሁላቹም ፈጣሪ ያክብራቹ፡፡ በጣም ደስ ሚል ምሽት ነበር፡፡ እና በቃ አሁን መሽቶአል ወደ ዶርም" አለች ፡፡ በንግግሩዋ መጨረሻ ላይ ሁሉም አጨበጨቡ፡፡ እየተሳሳቅን እና እየተጨዋወትን ትንሽ ከቆየን ቡሀላ ወደ ዶርም መሄድ ጀመርን፡፡
ወደ ዶርም መግቢያ ስንደርስ ፍሬ ሁሉንም ከተሰናበተ ቡሀላ በመጨረሻ ሁለታችን ቀረን፡፡ እንደከዚ ቀደሙ 'ደና ደር ፣ደና ደሪ' ብቻ ተባብለን መለያየት አልቻልንም፡፡ ሊሄድ ሲል ጠራዋለው ፣ልሄድ ስል ይጠራኛል፡፡ በመጨረሻም "በቃ ግቢ በስልክ እናወራለን ብዙ ካመሸው ዶርም ይቅጡኛል" ካለኝ ቡሀላ አቅፎኝ ተሰናብቶኝ ሄደ፡፡ መንገድ እንደሚሄድ ሰው ትንሽ ቆሜ አየሁት፡፡
ዶርም ስገባ በ ላፕቶፕ ዘፈን ከፍተው እየጨፈሩ ዶርሙን አድምቀውታል፡፡ እንኳን ደስ አለሽ እያሉ ሁሉም በተራ አቀፉኝ፡፡ የዶርማችን ፍቅር እውነት ደስ አለኝ፡፡ "ግን እንዴት እንደዚ ልታደርጉ ቻላቹ?"አልኩኝ ከወደበሩ ከሚገኘው አልጋ ላይ እየተቀመጥኩ፡፡ ጭፈራቸውን አቁመው ዘፈኑን ከዘጉ ቡሀላ ሁሉም ቦታ ቦታ ይዘው መቀመጥ ጀመሩ፡፡ ጥያቄዬን ደገምኩት "ግን እንዴት መጣላቹ ይሄ ሀሳብ?" አልኩኝ በፈገግታ የተሞላ ፊታቸውን መልሼ በፈገግታ እየተመለከትኩ፡፡ "የውልሽ ሴና" አለች ሚጣ ተመቻችታ እየተቀመጠች፡፡ "የውልሽ ሴና . . . ."
#ክፍል_ሀያአምስትን_ለማንበብ_የቸኮለ👉♥️
https://telegram.me/geyone
https://telegram.me/geyone
,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,,
••●◉Join us share◉●••