እውነት ሄድሽ በቃ?
(እዮብ ዘ ማርያም)
-
ምትወጃት ጨረቃ
ከሰማይ ሰሌዳ ሳትጠፋ ጠልቃ
ነብሴም እንቺን ለምዳ፣
ልክ እንደ ህፃን ልጅ ሳይበቃት ፈንድቃ
እውነት ሄድሽ በቃ?
ለቅሶ ይሰማኛል፣
የሚያነቡ ሰዎች ከፊቴ አያለሁ
አፈር ቡንን ይላል፣
መቃብር ሲቆፈር እመለከታለሁ
ምን እያረጉ ነው?
ምን እንደሚያደርጉ እኔ ምን አውቃለሁ
ድንዝዝ ብያለሁ!
መደንዝዝ ታውቂያለሽ፣
ሳይነቃነቁ ዝም ብሎ መገተር
ምንም ስሜት አልባ፣
በጥፊ ቢመታ ወይም ቢገፈተር
ደንዝዝ ብያለሁ አዎ ልክ እንደዛ
እንዲሁ እንደ ወዛ!
ፎቶሽን የያዙ፣
አሮጊት ሴትዮ ደረት ይመታሉ
እንዳንዶች በዕንባ፣
እህህ እያሉ ይንከራተታሉ
የማልቀስ
የማንባት
እነዚህ ስሜቶች እኔ ጋ የታሉ?
ፍርጃ
ፍዝዝ ብያለሁ ያላንዳች እርምጃ
ድንዝዝ ብያለሁ የነካኝን እንጃ!
በቆምኩበት ቦታ፣
እንደተገተርኩኝ ዕንባ ሳላወጣ
የለቅሶ የዋይታ፣
አሰቃቂ ድምፀት እየተጠጋኝ መጣ!
ድንገት ብንን አልኩኝ፣
ይደልቅ ጀመረ ልቤ በሀይል መምታት
ለሁለት ተከፈልኩኝ አነቃኝ ማመንታት!
በዚህ...፣
ዘላለማዊ ናት አትሞትም እሷ
በዚያ...፣
እመን
እመን
እመን
ከንግዲህ አትመጣም አፈር ሆኗል ልብሷ!
በጥርጥር መሀል
በማመንም መሀል ልቤ እየዋለለ
ዕንባዬ ጠብ አለ!
ጉም ዙሪያዬን ሞላው ጨለማ ከለለኝ
መሄድ መሞትሽን አመንኩኝ መሰለኝ!
ለራሴ አዘንኩኝ ባዘን ሆዴ ባባ
አምርሬ አለቀስሁ ታጠብኩኝ በዕንባ!
አይመስለኝም ነበር
በግዜ ምትከፍቺው የማቃብርን በር!
መውደድ ሳይዳብሰኝ ፍቅር ሳይነካካኝ
አልቀርብሽም ነበር፣
መሆንሽን ባውቀው እዚህ ድረስ ጨካኝ::
ላትመጪ ነገር
ላትመለሽ ነገር
ወዴት ሄጄ ልበድ፣
የልቤን ትኩሳት ምን ብዬ ልናገር?
ምትወጃት ጨረቃ
ከሰማይ ሰሌዳ ሳትጠፋ ጠልቃ
ነብሴም እንቺን ለምዳ፣
ልክ እንደ ህፃን ልጅ ሳይበቃት ፈንድቃ
እውነት ሄድሽ በቃ?
ለሌሎች ምርጥ ምርጥ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
(እዮብ ዘ ማርያም)
-
ምትወጃት ጨረቃ
ከሰማይ ሰሌዳ ሳትጠፋ ጠልቃ
ነብሴም እንቺን ለምዳ፣
ልክ እንደ ህፃን ልጅ ሳይበቃት ፈንድቃ
እውነት ሄድሽ በቃ?
ለቅሶ ይሰማኛል፣
የሚያነቡ ሰዎች ከፊቴ አያለሁ
አፈር ቡንን ይላል፣
መቃብር ሲቆፈር እመለከታለሁ
ምን እያረጉ ነው?
ምን እንደሚያደርጉ እኔ ምን አውቃለሁ
ድንዝዝ ብያለሁ!
መደንዝዝ ታውቂያለሽ፣
ሳይነቃነቁ ዝም ብሎ መገተር
ምንም ስሜት አልባ፣
በጥፊ ቢመታ ወይም ቢገፈተር
ደንዝዝ ብያለሁ አዎ ልክ እንደዛ
እንዲሁ እንደ ወዛ!
ፎቶሽን የያዙ፣
አሮጊት ሴትዮ ደረት ይመታሉ
እንዳንዶች በዕንባ፣
እህህ እያሉ ይንከራተታሉ
የማልቀስ
የማንባት
እነዚህ ስሜቶች እኔ ጋ የታሉ?
ፍርጃ
ፍዝዝ ብያለሁ ያላንዳች እርምጃ
ድንዝዝ ብያለሁ የነካኝን እንጃ!
በቆምኩበት ቦታ፣
እንደተገተርኩኝ ዕንባ ሳላወጣ
የለቅሶ የዋይታ፣
አሰቃቂ ድምፀት እየተጠጋኝ መጣ!
ድንገት ብንን አልኩኝ፣
ይደልቅ ጀመረ ልቤ በሀይል መምታት
ለሁለት ተከፈልኩኝ አነቃኝ ማመንታት!
በዚህ...፣
ዘላለማዊ ናት አትሞትም እሷ
በዚያ...፣
እመን
እመን
እመን
ከንግዲህ አትመጣም አፈር ሆኗል ልብሷ!
በጥርጥር መሀል
በማመንም መሀል ልቤ እየዋለለ
ዕንባዬ ጠብ አለ!
ጉም ዙሪያዬን ሞላው ጨለማ ከለለኝ
መሄድ መሞትሽን አመንኩኝ መሰለኝ!
ለራሴ አዘንኩኝ ባዘን ሆዴ ባባ
አምርሬ አለቀስሁ ታጠብኩኝ በዕንባ!
አይመስለኝም ነበር
በግዜ ምትከፍቺው የማቃብርን በር!
መውደድ ሳይዳብሰኝ ፍቅር ሳይነካካኝ
አልቀርብሽም ነበር፣
መሆንሽን ባውቀው እዚህ ድረስ ጨካኝ::
ላትመጪ ነገር
ላትመለሽ ነገር
ወዴት ሄጄ ልበድ፣
የልቤን ትኩሳት ምን ብዬ ልናገር?
ምትወጃት ጨረቃ
ከሰማይ ሰሌዳ ሳትጠፋ ጠልቃ
ነብሴም እንቺን ለምዳ፣
ልክ እንደ ህፃን ልጅ ሳይበቃት ፈንድቃ
እውነት ሄድሽ በቃ?
ለሌሎች ምርጥ ምርጥ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሳልነግርሽ…
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
አፍቅሬ እንዳጣሁሽ…
በነብያቶች አፍ፣
ፍልስፍና ሚመስል ፣ ትንቢት ተነገረ
ታምር የሚሰራ…
ጎትቶ ጎትቶ ፣
በመርፌ ቀዳዳ ፣ ግመል አሻገረ
ግመሉ ሲሻገር ፣ መርፌው ተሰበረ፡፡
በሰባራ መርፌ….
ፍቅርሽን ከፍቅሬ ፣ ባንድነት ልሰፋ
ይኸው እደክማለሁ…
ክር ሆነሽ እያጠርሽ ፣ ኖራለሁ ስለፋ፡፡
………………………………….
ሳልነግርሽ…
የኔ አለም ያላንቺ ፣እንደሆነ ራቁት
ባንቺ እንደነበር ፤ ቀንና ሌሊቴ የሚፈራረቁት፡፡
እንደተለየሽኝ …
አለም ባዶ ሆና ፣ መኖር እንዳስጠላኝ
ፍቅርሽ እከክ ሆኖ…
በልቤ ተተክሎ ፣ ነፍሴን እንደበላኝ፡፡
…………………………………
ሳልነግርሽ….
የነብያት ትንቢት ፣ በኔ መፈፀሙን
‹‹ታምሪያለሽ ›› እያልሁኝ ፣ ‹‹ተአምር ›› ማክተሙን
የተለየሽኝ ለት…
ምፅአት መምጣቱን ፣ የኔ አለም መቆሙን፡፡
…………………………………………
ሳልነግርሽ….
ካጣሁሽ በኋላ….
ባለፍኩት ጭንቅ ዓለም ፣ የስቃዬን መአት
አፍቅሮ ማጣት ነው…
በሰባራ መርፌ፣
እውነትን መስፋት ነው ፣ ለካንስ ምፅአት፡፡
ለሌሎች ምርጥ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
አፍቅሬ እንዳጣሁሽ…
በነብያቶች አፍ፣
ፍልስፍና ሚመስል ፣ ትንቢት ተነገረ
ታምር የሚሰራ…
ጎትቶ ጎትቶ ፣
በመርፌ ቀዳዳ ፣ ግመል አሻገረ
ግመሉ ሲሻገር ፣ መርፌው ተሰበረ፡፡
በሰባራ መርፌ….
ፍቅርሽን ከፍቅሬ ፣ ባንድነት ልሰፋ
ይኸው እደክማለሁ…
ክር ሆነሽ እያጠርሽ ፣ ኖራለሁ ስለፋ፡፡
………………………………….
ሳልነግርሽ…
የኔ አለም ያላንቺ ፣እንደሆነ ራቁት
ባንቺ እንደነበር ፤ ቀንና ሌሊቴ የሚፈራረቁት፡፡
እንደተለየሽኝ …
አለም ባዶ ሆና ፣ መኖር እንዳስጠላኝ
ፍቅርሽ እከክ ሆኖ…
በልቤ ተተክሎ ፣ ነፍሴን እንደበላኝ፡፡
…………………………………
ሳልነግርሽ….
የነብያት ትንቢት ፣ በኔ መፈፀሙን
‹‹ታምሪያለሽ ›› እያልሁኝ ፣ ‹‹ተአምር ›› ማክተሙን
የተለየሽኝ ለት…
ምፅአት መምጣቱን ፣ የኔ አለም መቆሙን፡፡
…………………………………………
ሳልነግርሽ….
ካጣሁሽ በኋላ….
ባለፍኩት ጭንቅ ዓለም ፣ የስቃዬን መአት
አፍቅሮ ማጣት ነው…
በሰባራ መርፌ፣
እውነትን መስፋት ነው ፣ ለካንስ ምፅአት፡፡
ለሌሎች ምርጥ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
( ሰቆቃወ ጴጥሮስ )
አዬ ...ምነው እመብርሃን ኢትዮጵያን ጨከንሽባት ፣
ምነው ቀኝሽን እረሳሻት ፣
እስከመቼ ድረስ እንዲህ መቀነትሽን ታጠብቂባት ፣
ልቦናሽን ታዞሪባት ፣
ፈተናዋን ሰቀቀኗን ጣሯን ይበቃል ሳትያት፣
አላንቺኮ ማንም የላት።
[ ጴጥሮስ ያቺን ሰዓት _ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን
@getemTheII
አዬ ...ምነው እመብርሃን ኢትዮጵያን ጨከንሽባት ፣
ምነው ቀኝሽን እረሳሻት ፣
እስከመቼ ድረስ እንዲህ መቀነትሽን ታጠብቂባት ፣
ልቦናሽን ታዞሪባት ፣
ፈተናዋን ሰቀቀኗን ጣሯን ይበቃል ሳትያት፣
አላንቺኮ ማንም የላት።
[ ጴጥሮስ ያቺን ሰዓት _ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን
@getemTheII
............
እንደነገርኩሽ ነው
አፍሽም ለብቻው ስሙን እያወጣ
ጆሮሽም ለብቻው ስሙን እያወጣ
ወየው ወየው እንጂ ወዬ የሚል ታጣ
.
አምላክም እንደ ሰው
ባለመስጠት ሞላ ከመስጠት ጎደለ
ብጠራው ብጠራው አቤት አልል አለ
ማለትሽን ሰምቼ ምስኪን አመልሽን
ከመልክሽ አዛምደሽ ከምትጠረጥሪው
እስቲ ቅፅሉን ተይና በዋና ስም ጥሪው
.
ሰሚን ሲበድሉ ጠሪን ሲበድሉ
ለጌታም ቅፅል ስም አወጡለት አሉ
በልጥፍጥፍ መአት ዋናው ገፅ ፈረሰ
ስም አውጪው ሲበዛ አቤት ባይ አነሰ
አመሌን አመልሽን ለማያውቁ ሁሉ
ጠርቼው አልመጣም ትዪኛለሽ አሉ
.
እሷ የስም ሀብታም
ትጠራው አታጣ ትሸኘው አታጣ
እኔ ባለ አንድ ስም ምን ሰምቼ ልምጣ?
ሰሚን ሲያናንቁ ጠሪን ሲያቃልሉ
የስም ፋብሪካ ነው ጉራንጉሩ ሁሉ
....
እንደነገርኩሽ ነው
የላክሽው ፎቶ አንሺ
በጥላሽ ከልሎ ባንቺ ብርሃን ኩሎ
ፎቶ ነስቶኝ ሄደ ፎቶ አነሳሁ ብሎ
ፓ! ፓ! ፓ! ካሜራ ኧረረ !! ካሜራ
በሌሉበት ሁሉ ማንሳት የማይራራ
ሊያውም በክት ልብስ ጥለት አዛንቄ
ሊያውም በጀግና ልብስ በኒሻን ደምቄ
.....
እያገላበጠ
ተዟዟርር እያለ ሲያነሳኝ ሰንብቶ
በትኖልኝ ሄደ ልብስ የሌለው ፎቶ
ካሜራሽ ስልጡኑ ካንቺ እኩል ያወቀ
ፎቶ ያነሳል አሉኝ ልብስ እያወለቀ
.
እንደነገርኩሽ ነው
የማንም ያልሆነን ያንተ ነው ተብዬ
በመሠለኝ ፋንታ ፍሬምሽን ሰቅዬ
ግራ የገባው አይን ከዕርቃን ይፋጠጣል
የጀግና ፎቶዬ የበዓል ፎቶዬ ከሱቅሽ ይሸጣል
..
አንቺ የመልክ ሀብታም ቀለም የተረፈሽ
አንቺ የልክ ሀብታም መስመር የተረፈሽ
የተኩላዎች ክፋት በበጎች ስም ፅፈሽ
መጥቀሻል ይሉኛል በምኞት መሠላል
ግድየለም ምጠቂ
ቅዠት ሲደጋገም ከህልም ይማሰላል
.
እንደነገርኩሽ ነው
ቧልተኛው ዶክተርሽ በስላቁ ፈዞ
አከምኩ ይለኛል
የራሱን መዳኒት ለመምተኛው አዞ
.
የመምተኛሽ ጉዳይ
የመምተኛው ደሞ
ከዶክተርሽ ባሰ ሁለቴ ገደለኝ
ተመረመርኩልህ ይቺን ዋጣት አለኝ
በታመመ ልኩ ጤና ሲሰፍርልኝ
በሽተኛ ልጅሽ ተመረመረልኝ
..
መድሃኒት ከሰረ
ጤና ተቃወሰ በሽታ ተስፋፋ
ግብረ ገብ ጎደለን ስነ ምግባር ጠፋ
ጉባኤ ሰብስበው ሰበብ ሲያዳምቁ
እኔን የገደለኝ
ከበሽታው ይልቅ በሽተኛው በውል አለመታወቁ
•
ያንቺዬማ አይነቱ
ማድማቱን ደብቆ
መድማቱን ለብቻ እያስመረመረ
ፈውስ በስም ብቻ ተድበስብሶ ቀረ
.
በኔ ና አንቺ አለም
ከማዘን ማሳዘን ከመሳት ማሳሳት
ከደም ማነስ ደም ማሳነስ
ከመርሳት ማስረሳት በእጥፍ ይቀድማል
ከህመሙ በላይ ህመምተኛው ያማል
..
ኧረ ያንቺስ ነገር
ትንሽ እየሰፋ ብዙ መቅደድ ያውቃል
ክርሽ ሳይነካ መርፌሽ ብቻ ያልቃል
ኧረ ያንቺስ አራጅ ቅርጫውን ሳንበላው
ያልቅብሻል አሉ ሞረድ እና ቢላው
ጎዳናው ሳይጠበን አመል እያጋፋን
እንኳን አካሄዱ አቋቋሙ ጠፋን
ለሌሎች ምርጥ ምርጥ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII @getemTheII
@getemTheII @getemTheII
@getemTheII
እንደነገርኩሽ ነው
አፍሽም ለብቻው ስሙን እያወጣ
ጆሮሽም ለብቻው ስሙን እያወጣ
ወየው ወየው እንጂ ወዬ የሚል ታጣ
.
አምላክም እንደ ሰው
ባለመስጠት ሞላ ከመስጠት ጎደለ
ብጠራው ብጠራው አቤት አልል አለ
ማለትሽን ሰምቼ ምስኪን አመልሽን
ከመልክሽ አዛምደሽ ከምትጠረጥሪው
እስቲ ቅፅሉን ተይና በዋና ስም ጥሪው
.
ሰሚን ሲበድሉ ጠሪን ሲበድሉ
ለጌታም ቅፅል ስም አወጡለት አሉ
በልጥፍጥፍ መአት ዋናው ገፅ ፈረሰ
ስም አውጪው ሲበዛ አቤት ባይ አነሰ
አመሌን አመልሽን ለማያውቁ ሁሉ
ጠርቼው አልመጣም ትዪኛለሽ አሉ
.
እሷ የስም ሀብታም
ትጠራው አታጣ ትሸኘው አታጣ
እኔ ባለ አንድ ስም ምን ሰምቼ ልምጣ?
ሰሚን ሲያናንቁ ጠሪን ሲያቃልሉ
የስም ፋብሪካ ነው ጉራንጉሩ ሁሉ
....
እንደነገርኩሽ ነው
የላክሽው ፎቶ አንሺ
በጥላሽ ከልሎ ባንቺ ብርሃን ኩሎ
ፎቶ ነስቶኝ ሄደ ፎቶ አነሳሁ ብሎ
ፓ! ፓ! ፓ! ካሜራ ኧረረ !! ካሜራ
በሌሉበት ሁሉ ማንሳት የማይራራ
ሊያውም በክት ልብስ ጥለት አዛንቄ
ሊያውም በጀግና ልብስ በኒሻን ደምቄ
.....
እያገላበጠ
ተዟዟርር እያለ ሲያነሳኝ ሰንብቶ
በትኖልኝ ሄደ ልብስ የሌለው ፎቶ
ካሜራሽ ስልጡኑ ካንቺ እኩል ያወቀ
ፎቶ ያነሳል አሉኝ ልብስ እያወለቀ
.
እንደነገርኩሽ ነው
የማንም ያልሆነን ያንተ ነው ተብዬ
በመሠለኝ ፋንታ ፍሬምሽን ሰቅዬ
ግራ የገባው አይን ከዕርቃን ይፋጠጣል
የጀግና ፎቶዬ የበዓል ፎቶዬ ከሱቅሽ ይሸጣል
..
አንቺ የመልክ ሀብታም ቀለም የተረፈሽ
አንቺ የልክ ሀብታም መስመር የተረፈሽ
የተኩላዎች ክፋት በበጎች ስም ፅፈሽ
መጥቀሻል ይሉኛል በምኞት መሠላል
ግድየለም ምጠቂ
ቅዠት ሲደጋገም ከህልም ይማሰላል
.
እንደነገርኩሽ ነው
ቧልተኛው ዶክተርሽ በስላቁ ፈዞ
አከምኩ ይለኛል
የራሱን መዳኒት ለመምተኛው አዞ
.
የመምተኛሽ ጉዳይ
የመምተኛው ደሞ
ከዶክተርሽ ባሰ ሁለቴ ገደለኝ
ተመረመርኩልህ ይቺን ዋጣት አለኝ
በታመመ ልኩ ጤና ሲሰፍርልኝ
በሽተኛ ልጅሽ ተመረመረልኝ
..
መድሃኒት ከሰረ
ጤና ተቃወሰ በሽታ ተስፋፋ
ግብረ ገብ ጎደለን ስነ ምግባር ጠፋ
ጉባኤ ሰብስበው ሰበብ ሲያዳምቁ
እኔን የገደለኝ
ከበሽታው ይልቅ በሽተኛው በውል አለመታወቁ
•
ያንቺዬማ አይነቱ
ማድማቱን ደብቆ
መድማቱን ለብቻ እያስመረመረ
ፈውስ በስም ብቻ ተድበስብሶ ቀረ
.
በኔ ና አንቺ አለም
ከማዘን ማሳዘን ከመሳት ማሳሳት
ከደም ማነስ ደም ማሳነስ
ከመርሳት ማስረሳት በእጥፍ ይቀድማል
ከህመሙ በላይ ህመምተኛው ያማል
..
ኧረ ያንቺስ ነገር
ትንሽ እየሰፋ ብዙ መቅደድ ያውቃል
ክርሽ ሳይነካ መርፌሽ ብቻ ያልቃል
ኧረ ያንቺስ አራጅ ቅርጫውን ሳንበላው
ያልቅብሻል አሉ ሞረድ እና ቢላው
ጎዳናው ሳይጠበን አመል እያጋፋን
እንኳን አካሄዱ አቋቋሙ ጠፋን
ለሌሎች ምርጥ ምርጥ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII @getemTheII
@getemTheII @getemTheII
@getemTheII
Forwarded from Deleted Account via @Yared_buttons_bot
ዛሬ ለናንተ አሪፍ አሪፍ እና ብዙ ተከታዮች ያሏቸውን ቻናሎች ላስተዋውቃችሁ።
።ፍቅር- ፈራን:ጠላን።
ሌሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
ለሌሎች ምርጥ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
ሌሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
ለሌሎች ምርጥ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
ዕንባና ቃል
.
.
በላክሽው ደብዳቤ
የመግቢያ መስመር ላይ 'ይድረስ' የሚል ሳጣ፤
ገባኝ ተስፋ እንዳጣሽ
እንደማታገኚኝ ዞሬ እንደማልመጣ፤
ከቃልሽ መካከል
ቢደርቅም ይታያል የዕንባ ጠብታሽ፤
መልዕክትሽን ትቼ
ዕንባሽን አንብቤ ገባኝ ምን እንዳጣሽ፤
.
አውቃለሁ!..
የኢያሪኮ ቅጥር
የሚያህል ሕመምሽን በእልልታ ያፈረሠ፤
ጎልያድ የሚያህል
ያንቺን ብቸኝነት በወንጭፍ የጣሠ፤
የኔ ደንዳና ልብ
በእምነት በፍቅሩ የማይደራደር፤
ላፍታ መጥቶ ነበር
ከደብርሽ መንኖ በልብሽ ለማደር፤
ግን በቃ!...
ከዕለታት ባንዱ ቀን
ከገዳምሽ መሐል ክህደትሽ ነገሠ፤
ልቤም እምነት አጣ
ቆቡን ጥሎ ሸሸ ክህነት አፈረሠ፤
.
ይኸው ከዚያ ወዲያ
አልዞረም አልመጣም አንቺ ወዳለሽበት፤
ያንቺም ልብ ደንድኖ
ሌላ አማኝ መንኩሶ በእምነት ሠፈረበት፤
ይህ ሁሉ እያለፈ
ሲሾም ሲሻርበት የልብሽ ንግስና፤
እያየሁ ቢያመኝም
ዘወትር ባስብሽም መች ፈለግኩሽና፤
አንቺም ይሄን አውቀሽ
በፃፍሽው ደብዳቤ አጥተሽ ጭላጭ ተስፋ፤
'ይድረስ' የሚል የለም...
መድረሻ መንገዱ ፍቅሬ ስለጠፋ፤
.
መደምደሚያውም ላይ
የመሠናበቻሽ 'ቻው!' የሚል ቃል ሳጣ፤
ገባኝ ተስፋ እንዳለሽ
እንደምታገኚኝ ዞሬ እንደምመጣ፤
.
.
በሁለት ምኞትሽ
መካከል ሠፍሬ ቃልሽን አነበብኩት፤
'ይድረስ' እና 'ቻው'ን
ያላሠፈርሽበት ምክንያትሽን አሠብኩት፤
.
አስቤ!
አስቤ!
አስቤ!
.
መልስ ይሁንሽ ብዬ!...
ደብዳቤሽን ላክኩት አንድም ቃል ሳልነካ፤
'ይደርስ'ም አልልም
'ቻው'ም አልልሽም
የዕንባሽን ጥልቀት ሕመምሽን ሳልለካ፤
.
ከተደረደረው
ከቃላትሽ በላይ ዕንባሽ ጉልበት አለው፤
ለዚህ ነው አሁን ላይ ምንም የማልለው፤
ለሌሎች ምርጥ ምርጥ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
.
.
በላክሽው ደብዳቤ
የመግቢያ መስመር ላይ 'ይድረስ' የሚል ሳጣ፤
ገባኝ ተስፋ እንዳጣሽ
እንደማታገኚኝ ዞሬ እንደማልመጣ፤
ከቃልሽ መካከል
ቢደርቅም ይታያል የዕንባ ጠብታሽ፤
መልዕክትሽን ትቼ
ዕንባሽን አንብቤ ገባኝ ምን እንዳጣሽ፤
.
አውቃለሁ!..
የኢያሪኮ ቅጥር
የሚያህል ሕመምሽን በእልልታ ያፈረሠ፤
ጎልያድ የሚያህል
ያንቺን ብቸኝነት በወንጭፍ የጣሠ፤
የኔ ደንዳና ልብ
በእምነት በፍቅሩ የማይደራደር፤
ላፍታ መጥቶ ነበር
ከደብርሽ መንኖ በልብሽ ለማደር፤
ግን በቃ!...
ከዕለታት ባንዱ ቀን
ከገዳምሽ መሐል ክህደትሽ ነገሠ፤
ልቤም እምነት አጣ
ቆቡን ጥሎ ሸሸ ክህነት አፈረሠ፤
.
ይኸው ከዚያ ወዲያ
አልዞረም አልመጣም አንቺ ወዳለሽበት፤
ያንቺም ልብ ደንድኖ
ሌላ አማኝ መንኩሶ በእምነት ሠፈረበት፤
ይህ ሁሉ እያለፈ
ሲሾም ሲሻርበት የልብሽ ንግስና፤
እያየሁ ቢያመኝም
ዘወትር ባስብሽም መች ፈለግኩሽና፤
አንቺም ይሄን አውቀሽ
በፃፍሽው ደብዳቤ አጥተሽ ጭላጭ ተስፋ፤
'ይድረስ' የሚል የለም...
መድረሻ መንገዱ ፍቅሬ ስለጠፋ፤
.
መደምደሚያውም ላይ
የመሠናበቻሽ 'ቻው!' የሚል ቃል ሳጣ፤
ገባኝ ተስፋ እንዳለሽ
እንደምታገኚኝ ዞሬ እንደምመጣ፤
.
.
በሁለት ምኞትሽ
መካከል ሠፍሬ ቃልሽን አነበብኩት፤
'ይድረስ' እና 'ቻው'ን
ያላሠፈርሽበት ምክንያትሽን አሠብኩት፤
.
አስቤ!
አስቤ!
አስቤ!
.
መልስ ይሁንሽ ብዬ!...
ደብዳቤሽን ላክኩት አንድም ቃል ሳልነካ፤
'ይደርስ'ም አልልም
'ቻው'ም አልልሽም
የዕንባሽን ጥልቀት ሕመምሽን ሳልለካ፤
.
ከተደረደረው
ከቃላትሽ በላይ ዕንባሽ ጉልበት አለው፤
ለዚህ ነው አሁን ላይ ምንም የማልለው፤
ለሌሎች ምርጥ ምርጥ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
❤️Fkracin😍😘😘😘😘😘
Yefkre balabet fkracin gn aleg😍😘😘😘😘😘😘😘😘😘
Bante aftatre weste gn temtata.
Betamun teleyeh kalug kemakacew...
Yne navew biyem kemitbikacew😍😘😘😘😘😘😘❤️❤️❤️
✍ & 🎙 @Nihutina_Amen
Join fo more....ewntoce🥺😘
@yefkr_kalatoce_kekalat
Yefkre balabet fkracin gn aleg😍😘😘😘😘😘😘😘😘😘
Bante aftatre weste gn temtata.
Betamun teleyeh kalug kemakacew...
Yne navew biyem kemitbikacew😍😘😘😘😘😘😘❤️❤️❤️
✍ & 🎙 @Nihutina_Amen
Join fo more....ewntoce🥺😘
@yefkr_kalatoce_kekalat
ለማንበብ 15 ደቅቃ ብቻ ስጥ ህይወትን ይቀየራል አትሳሳት
share አድርገው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዓለም ወዴት እየሄደች ነው? 1. - መጽሐፍ ቅዱስን ማቃጠል በኡጋንዳ በይፋ ተረጋግጦአል
* በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ፣ ወንድ ወይም ሴት በዝሙት ምክንያት ሌላውን የመክሰስ መብት የለውም
*በአሜሪካ እየታየ ያለው የወንድ ለወንድና የሴት ለሴት ጋብቻ
*ጀርመን ወንድም እህቱን ማግባት እንደሚችል ፣ አባት ልጁን:እናት ልጆአን የማግባት ፍቃድን መስጠቱ ፡፡
*የmiami ከተማበመንገድ ላይ ፣ በቤተ ክርስቲያን ፣ በገቢያ ፣ በእግር ኳስ ሜዳ ወዘተ ውስጥ ወሲባዊ ግንኙነት በማንኛውም መንገድ ማግኘት እንዲችሉ መፍቀዶአ
.*ካናዳ (ከእንስሳት ጋር የ sexታ ግንኙነትን መፍቀዶአ
* በስፔን ውስጥ-የወሲብ ፊልሞች በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና በዩኒቨርሲቲዎች መፈቀዱ *- ለአካለ መጠን ያልደረሱ ዝሙት አዳሪዎች ፈቃድ ማሪ ሉክ በህግ መፈቀዱ *በመጨረሻም ዩኤስ አሜሪካ የሰይጣንን ቤተ ክርስቲያን ከፍታለች ፡፡ በይፋ።
የተከበራችሁ ወንድሞች እና እህቶች ፣ መጨረሻው ተቃርቧል ፣ ጌታ ኢየሱስ በቅርቡ ይመጣል! ማርታናታ!!!
ክርስትያኖች ትኩረታቸው እየተከፋፈሉ ሲሆን ዲያቢሎስ መለኮታዊውን ምህረት ለማስቆም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ነፍሳት ከእርሱ ጋር ሊወስድ ይፈልጋል ፡፡ ደቂቃ ካለዎት ... ይህንን መልእክት ያጋሩ ፡፡ ለምን በቤተክርስቲያን ውስጥ እንተኛለን ? ስለ እግዚአብሔር ማውራት ከባድ የሆነው ለምንድነው ሐሜት ለመናገር በጣም ቀላል የሆነው ለምንድነው? የእግዚአብሔርን መልእክት ችላ ማለት ለምን ቀላል ሆነ?
ይህንን መልእክት ለጓደኞችዎ ይልካሉ ወይም ችላ ይላሉ? ኢየሱስ “በጓደኞችህ ብትክዱኝ በአባቴ ፊት እክድሃለሁ” አለ ፡፡ ኢየሱስን ከወደዱ ይህንን መልእክት ለምርጥ ጓደኞችዎ እና በቡድን በ 60 ሴኮንድ ውስጥ ያጋሩ ፡፡ እግዚአብሔር ይባርኮት. ኣሜን
የአለም መጨረሻ ተቃርቧል አትዘናጉ
አሁን ያለንበት 2012 ዓም + 5500 ዘመን=7512 ስለዚህ ከ 8ኛው ሽ ላይ ከንሱት ።
8000 – 7512= 488 ዓም ይቀራል።
ነገር ግን ሰምታችሁ ከሆነ ዘንዶ 400 ዓመት ገዝቷል ይባላል እስኪ ጠይቁ።
እና የዘንዶው ሲቆጠር 488 – 400 =88 አመት ቀረው።ትንቢቱም እየተፈፀመ ነው። ሌላው ይህ በንዲህ እንዳለ ደሞ
666 አሁን እዚህ በደጃችን ነው፡፡ አጠንክረን እንፀልይ፡፡ የአውሬው
ቁጥር 6 6 6 የሚፈፀምበት የትንቢት ጊዜ አልቋል/ተፈፅሟል፡፡
የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት ባስተላለፈው የኦባማን የጤና
ሽፋን ረቂቅ በህግ እንዲካተት ተደርጓል፡፡ የህግ ተግባሩ በቅርቡ
ይጀምራል፡፡ ይህን የጤና ሽፋን ረቂቅ በእያንዳንዱ የአሜሪካ ዜጋ
የሰውነት ክፍል ላይ ግላዊ የሬዲዬ ፍሪኩዌንሲ ቺፕስ መልክ (RFID
CHIPS) እንዲተከል ታዟል፡፡ ይህ ቺፕስ በግንባር ወይም በክንድ ላይ
ይደረጋል፡፡ ይህ ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደሚናገረው በራዕይ 13 :
15 -18 የተቀመጠውን የአውሬው ምልክት ይፈፀም ዘንድ ነው፡፡ እና
አሁንም ስለ ፍፃሜው ትጠራጠራለህ? ታውቃለህ ለኦባማ የተለየ
መኪና እንደተሰራ አውሬው የሚባል? ተዘጋጅ ንጥቀት አሁን
ይጀምራል፡፡ ራዕይ 13ን ቀድመው ተጫውተውታል፡፡ ብዙዎች ግን
ይህን አልተገነዘቡትም፡፡ 1. ለምንድን ነው ይህ ችፕስ ከባንክ
አካውንት ጋር የተቆራኘው ወይም የተገናኘው? አስታውሱ መጽሐፍ
ቅዱስ እንደሚለው ካለ አውሬው ቁጥር 666 ልትገዙም ወይም
ልትሸጡም አትችሉም ስለሚል፡፡ እስኪ ገምቱ ይህ ቺፕስ ከገንዘብ
ዝርዝር መረጃ ጋር ለምን ተገናኘ? እንዲያውም በጣም ያሳዘነኝ
በቤተክርስቲያን ያሉ ብዙዎች ሰዎች ጌታ ሲመጣ ይህን ሁኔታ
ሊያልፉት አይችሉም፡፡ ደግሞም ብዙዎቹ መጨረሻው እንደቀረበ
አያውቁም፡፡ የቴክኖሎጂ በጣም መራቀቅ ምክንያት ነው ብላችሁ
መልስ እንዳትሰጡኝ፡፡ በማንኛውም የህይወት ጎዳናችሁ
ከእግዚአብሔር ጋር ካልተስማማ አሁኑኑ ንሰሀ ግቡና ተለወጡ፡፡
ካለበለዚያ መንግስተ ሰማያትን ካጣችሁት ገሀነምን አታጡትም፡፡
ስለዚህ አስቡበት፡፡ ገሀነም መልካም ስፍራ አይደለም በጣም
አስከፊው ክፍሉ እንደ መንግስተ ሰማያት ዘላለማዊነት እንዳለበት
እዚህም እንደዛው ነው፡፡ ጆሮ ያለው ይስማ መንፈስ ለአብያተ
ክርስቲያናት የሚለውን ይስማ፡፡ ጠቃሚ ያልሆነ ነገር ከምትልኩ ይህን
ለሌላው ብታስተላልፉ መልካም ነው፡፡ ለምታውቋቸው ቅርብ
ለሆኗችሁ ሰዎች ላኩላቸው፡፡ እስኪ የወንጌላዊ ስራ እንስራ፡፡
እባካችሁ ለምታውቋቸው ለእያንዳንዳቸው በየስማቸው ላኩላቸው፡፡
ለሞባይል እንደምንጠነቀቅ ያክል ለእግዚአብሔር ቃል ብንጠነቀቅ
ምን እንደሚሆን ልትገምቱ ትችላላችሁ፡፡ ከዚህ ደግሞ በጭራሽ
ልንላቀቅ ነፃ ልንሆን አንችል፡፡ ስለዚህ የቻልነውን ያክል እንትጋ
እንጋደል፡፡ 7% የሚሆኑቱ ናቸው መልዕክቱን የላኩት በድጋሚ 93%ቱ
ግን አልላኩም አላወቁም ስለዚህ ጠንክረን እንስራ፡፡ ሰይጣን
እንዲህ ይላል፡- " የሚገርመኝ ሰው እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ
አይታዘዝም እኔን ይጠላኛል ግን ይታዘዘኛል፡፡" ይህን መልዕክት በኋላ
እንዳትልኩት አሁኑኑ ላኩት!!!
ቢያንስ ለ #15 ሰው
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
✥ 💚 @yetwahedolijoch💚 ✥
✥ 💛 @yetwahedolijoch 💛 ✥
✥ ❤️ @yetwahedolijoch ❤️ ✥
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
share አድርገው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዓለም ወዴት እየሄደች ነው? 1. - መጽሐፍ ቅዱስን ማቃጠል በኡጋንዳ በይፋ ተረጋግጦአል
* በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ፣ ወንድ ወይም ሴት በዝሙት ምክንያት ሌላውን የመክሰስ መብት የለውም
*በአሜሪካ እየታየ ያለው የወንድ ለወንድና የሴት ለሴት ጋብቻ
*ጀርመን ወንድም እህቱን ማግባት እንደሚችል ፣ አባት ልጁን:እናት ልጆአን የማግባት ፍቃድን መስጠቱ ፡፡
*የmiami ከተማበመንገድ ላይ ፣ በቤተ ክርስቲያን ፣ በገቢያ ፣ በእግር ኳስ ሜዳ ወዘተ ውስጥ ወሲባዊ ግንኙነት በማንኛውም መንገድ ማግኘት እንዲችሉ መፍቀዶአ
.*ካናዳ (ከእንስሳት ጋር የ sexታ ግንኙነትን መፍቀዶአ
* በስፔን ውስጥ-የወሲብ ፊልሞች በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና በዩኒቨርሲቲዎች መፈቀዱ *- ለአካለ መጠን ያልደረሱ ዝሙት አዳሪዎች ፈቃድ ማሪ ሉክ በህግ መፈቀዱ *በመጨረሻም ዩኤስ አሜሪካ የሰይጣንን ቤተ ክርስቲያን ከፍታለች ፡፡ በይፋ።
የተከበራችሁ ወንድሞች እና እህቶች ፣ መጨረሻው ተቃርቧል ፣ ጌታ ኢየሱስ በቅርቡ ይመጣል! ማርታናታ!!!
ክርስትያኖች ትኩረታቸው እየተከፋፈሉ ሲሆን ዲያቢሎስ መለኮታዊውን ምህረት ለማስቆም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ነፍሳት ከእርሱ ጋር ሊወስድ ይፈልጋል ፡፡ ደቂቃ ካለዎት ... ይህንን መልእክት ያጋሩ ፡፡ ለምን በቤተክርስቲያን ውስጥ እንተኛለን ? ስለ እግዚአብሔር ማውራት ከባድ የሆነው ለምንድነው ሐሜት ለመናገር በጣም ቀላል የሆነው ለምንድነው? የእግዚአብሔርን መልእክት ችላ ማለት ለምን ቀላል ሆነ?
ይህንን መልእክት ለጓደኞችዎ ይልካሉ ወይም ችላ ይላሉ? ኢየሱስ “በጓደኞችህ ብትክዱኝ በአባቴ ፊት እክድሃለሁ” አለ ፡፡ ኢየሱስን ከወደዱ ይህንን መልእክት ለምርጥ ጓደኞችዎ እና በቡድን በ 60 ሴኮንድ ውስጥ ያጋሩ ፡፡ እግዚአብሔር ይባርኮት. ኣሜን
የአለም መጨረሻ ተቃርቧል አትዘናጉ
አሁን ያለንበት 2012 ዓም + 5500 ዘመን=7512 ስለዚህ ከ 8ኛው ሽ ላይ ከንሱት ።
8000 – 7512= 488 ዓም ይቀራል።
ነገር ግን ሰምታችሁ ከሆነ ዘንዶ 400 ዓመት ገዝቷል ይባላል እስኪ ጠይቁ።
እና የዘንዶው ሲቆጠር 488 – 400 =88 አመት ቀረው።ትንቢቱም እየተፈፀመ ነው። ሌላው ይህ በንዲህ እንዳለ ደሞ
666 አሁን እዚህ በደጃችን ነው፡፡ አጠንክረን እንፀልይ፡፡ የአውሬው
ቁጥር 6 6 6 የሚፈፀምበት የትንቢት ጊዜ አልቋል/ተፈፅሟል፡፡
የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት ባስተላለፈው የኦባማን የጤና
ሽፋን ረቂቅ በህግ እንዲካተት ተደርጓል፡፡ የህግ ተግባሩ በቅርቡ
ይጀምራል፡፡ ይህን የጤና ሽፋን ረቂቅ በእያንዳንዱ የአሜሪካ ዜጋ
የሰውነት ክፍል ላይ ግላዊ የሬዲዬ ፍሪኩዌንሲ ቺፕስ መልክ (RFID
CHIPS) እንዲተከል ታዟል፡፡ ይህ ቺፕስ በግንባር ወይም በክንድ ላይ
ይደረጋል፡፡ ይህ ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደሚናገረው በራዕይ 13 :
15 -18 የተቀመጠውን የአውሬው ምልክት ይፈፀም ዘንድ ነው፡፡ እና
አሁንም ስለ ፍፃሜው ትጠራጠራለህ? ታውቃለህ ለኦባማ የተለየ
መኪና እንደተሰራ አውሬው የሚባል? ተዘጋጅ ንጥቀት አሁን
ይጀምራል፡፡ ራዕይ 13ን ቀድመው ተጫውተውታል፡፡ ብዙዎች ግን
ይህን አልተገነዘቡትም፡፡ 1. ለምንድን ነው ይህ ችፕስ ከባንክ
አካውንት ጋር የተቆራኘው ወይም የተገናኘው? አስታውሱ መጽሐፍ
ቅዱስ እንደሚለው ካለ አውሬው ቁጥር 666 ልትገዙም ወይም
ልትሸጡም አትችሉም ስለሚል፡፡ እስኪ ገምቱ ይህ ቺፕስ ከገንዘብ
ዝርዝር መረጃ ጋር ለምን ተገናኘ? እንዲያውም በጣም ያሳዘነኝ
በቤተክርስቲያን ያሉ ብዙዎች ሰዎች ጌታ ሲመጣ ይህን ሁኔታ
ሊያልፉት አይችሉም፡፡ ደግሞም ብዙዎቹ መጨረሻው እንደቀረበ
አያውቁም፡፡ የቴክኖሎጂ በጣም መራቀቅ ምክንያት ነው ብላችሁ
መልስ እንዳትሰጡኝ፡፡ በማንኛውም የህይወት ጎዳናችሁ
ከእግዚአብሔር ጋር ካልተስማማ አሁኑኑ ንሰሀ ግቡና ተለወጡ፡፡
ካለበለዚያ መንግስተ ሰማያትን ካጣችሁት ገሀነምን አታጡትም፡፡
ስለዚህ አስቡበት፡፡ ገሀነም መልካም ስፍራ አይደለም በጣም
አስከፊው ክፍሉ እንደ መንግስተ ሰማያት ዘላለማዊነት እንዳለበት
እዚህም እንደዛው ነው፡፡ ጆሮ ያለው ይስማ መንፈስ ለአብያተ
ክርስቲያናት የሚለውን ይስማ፡፡ ጠቃሚ ያልሆነ ነገር ከምትልኩ ይህን
ለሌላው ብታስተላልፉ መልካም ነው፡፡ ለምታውቋቸው ቅርብ
ለሆኗችሁ ሰዎች ላኩላቸው፡፡ እስኪ የወንጌላዊ ስራ እንስራ፡፡
እባካችሁ ለምታውቋቸው ለእያንዳንዳቸው በየስማቸው ላኩላቸው፡፡
ለሞባይል እንደምንጠነቀቅ ያክል ለእግዚአብሔር ቃል ብንጠነቀቅ
ምን እንደሚሆን ልትገምቱ ትችላላችሁ፡፡ ከዚህ ደግሞ በጭራሽ
ልንላቀቅ ነፃ ልንሆን አንችል፡፡ ስለዚህ የቻልነውን ያክል እንትጋ
እንጋደል፡፡ 7% የሚሆኑቱ ናቸው መልዕክቱን የላኩት በድጋሚ 93%ቱ
ግን አልላኩም አላወቁም ስለዚህ ጠንክረን እንስራ፡፡ ሰይጣን
እንዲህ ይላል፡- " የሚገርመኝ ሰው እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ
አይታዘዝም እኔን ይጠላኛል ግን ይታዘዘኛል፡፡" ይህን መልዕክት በኋላ
እንዳትልኩት አሁኑኑ ላኩት!!!
ቢያንስ ለ #15 ሰው
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
✥ 💚 @yetwahedolijoch💚 ✥
✥ 💛 @yetwahedolijoch 💛 ✥
✥ ❤️ @yetwahedolijoch ❤️ ✥
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
ሰው ከቀየው እንጂ
(በእውቀቱ ስዩም)
.
ወጥቼ ከቀሳው
ለጊዜው ታግየ
ሞትን ድል ብነሳው
መኖር አሸነፈኝ
ቤቴ ተደፍቶብኝ ፤ ሁለት ወር አለፈኝ::
ተፈጥሮየ ከዳኝ፤ ፈሊጡን ቀየረ
አካሌ ሸፈተ ፤ አዲስ ወግ ተማረ
ገላየ በቁሙ ፤ሳር ማብቀል ጀመረ ::
እንዳልቆይ መታከት፤ እንዳልወጣ -ሽብር
ሳይደክመኝ ተኝቼ ፤
እንቅልፍ አንገቴ ላይ ፤ቀንበሩን ሳይሰብር-
-ካልጋ ተነስቼ
እየተደናገርሁ
እየተደናበርሁ
በምሳ ሰአቴ ፤ራት እየጋገርሁ ፤
ኑሮ እንደ ሳር ጉንጉን፤ እያደናቀፈኝ
ሁለት ወር አለፈ ኝ !
ዛሬ ኮበለለ
ትላንትናን ቀድሞት ፤ባምባላይ ፈረሱ
ቀኔና ሌሊቴም ፤ሰልፍ እያፈረሱ
ይተራመሳሉ
ይርመሰመሳሉ፤
አርባም እድሜ ሆና
ያችን ለማሳጠር
ነፋስ በሰው ሲያድም፤ ከሞት ሲመሳጠር
ወዴትስ ይኬዳል
ሰው ከቀየው እንጂ ፤ካለም ይሰደዳል ?
ለሌሎች ደስ የሚሉ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
(በእውቀቱ ስዩም)
.
ወጥቼ ከቀሳው
ለጊዜው ታግየ
ሞትን ድል ብነሳው
መኖር አሸነፈኝ
ቤቴ ተደፍቶብኝ ፤ ሁለት ወር አለፈኝ::
ተፈጥሮየ ከዳኝ፤ ፈሊጡን ቀየረ
አካሌ ሸፈተ ፤ አዲስ ወግ ተማረ
ገላየ በቁሙ ፤ሳር ማብቀል ጀመረ ::
እንዳልቆይ መታከት፤ እንዳልወጣ -ሽብር
ሳይደክመኝ ተኝቼ ፤
እንቅልፍ አንገቴ ላይ ፤ቀንበሩን ሳይሰብር-
-ካልጋ ተነስቼ
እየተደናገርሁ
እየተደናበርሁ
በምሳ ሰአቴ ፤ራት እየጋገርሁ ፤
ኑሮ እንደ ሳር ጉንጉን፤ እያደናቀፈኝ
ሁለት ወር አለፈ ኝ !
ዛሬ ኮበለለ
ትላንትናን ቀድሞት ፤ባምባላይ ፈረሱ
ቀኔና ሌሊቴም ፤ሰልፍ እያፈረሱ
ይተራመሳሉ
ይርመሰመሳሉ፤
አርባም እድሜ ሆና
ያችን ለማሳጠር
ነፋስ በሰው ሲያድም፤ ከሞት ሲመሳጠር
ወዴትስ ይኬዳል
ሰው ከቀየው እንጂ ፤ካለም ይሰደዳል ?
ለሌሎች ደስ የሚሉ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
Forwarded from Liul-Z-ማርያም
የጥበብ አይኖች
መካሪ ሀሳቦች ጥበብ ናቸው
የፈልጉት ሀሳብ በፈለጉት መንገድ
እዚህ ይገኛል ።ሀሳበዎን ለማካፈል በዘህ ሊንክ
ይጠቀሙ @sam2127
https://t.me/TIBEBnegni
መካሪ ሀሳቦች ጥበብ ናቸው
የፈልጉት ሀሳብ በፈለጉት መንገድ
እዚህ ይገኛል ።ሀሳበዎን ለማካፈል በዘህ ሊንክ
ይጠቀሙ @sam2127
https://t.me/TIBEBnegni
Telegram
ሰው መሆን...
ሰው ከመሆን በላይ ምን አለ ?
መልካም እንሁን ፡፡
ሟች መሆናችንን እያሰብን እንኑር
0923983389
@sam2127
መልካም እንሁን ፡፡
ሟች መሆናችንን እያሰብን እንኑር
0923983389
@sam2127
ልጠብቅሽ ፈለኩ
መምጣት አለመምጣት
ሁለት ምርጫ ኑሮሽ፡
አንደኛውን መርጠሽ
ሌላውን ስትሸሽ፡
ፈለኩ.....ቃልሽን መወሰን፡
ሀሳብሽን ማስከን፡
አለመምጣት ይውደቅ
መምጣት እንዲፀድቅ፡
ልክ እንደ ፈጣሪሽ
መምጣትሽን ላርቅቅ፡
ወሳኝም አይጠፋም
ተቀባይ እንደዛው፡
በሀሳብ ቢደናቀር
የሰው ሀሳብ ከሰው፡
ይሉኝታ ቢከፈን
የሀሳብ ጎዶሎ እቃ፡
ጉዳት ያመጣ እንጂ
የመመራት እጣ
አያስተነፍስም የመወሰን ሲቃ፡
በይ መምጣትሽም ይቅር
ተፈለግሽም ቅሪ፡
ባትመጪ እንኳን ከቶ
አደለሁም'ና የጥበቃ ፈሪ፡
የመምጣትሽን ቃል
ውሳኔሽን ጠበኩ፡
ባትመጪ እንኳን ከቶ
ልጠብቅሽ ፈለኩ።
✍✍ሚኪ
መምጣት አለመምጣት
ሁለት ምርጫ ኑሮሽ፡
አንደኛውን መርጠሽ
ሌላውን ስትሸሽ፡
ፈለኩ.....ቃልሽን መወሰን፡
ሀሳብሽን ማስከን፡
አለመምጣት ይውደቅ
መምጣት እንዲፀድቅ፡
ልክ እንደ ፈጣሪሽ
መምጣትሽን ላርቅቅ፡
ወሳኝም አይጠፋም
ተቀባይ እንደዛው፡
በሀሳብ ቢደናቀር
የሰው ሀሳብ ከሰው፡
ይሉኝታ ቢከፈን
የሀሳብ ጎዶሎ እቃ፡
ጉዳት ያመጣ እንጂ
የመመራት እጣ
አያስተነፍስም የመወሰን ሲቃ፡
በይ መምጣትሽም ይቅር
ተፈለግሽም ቅሪ፡
ባትመጪ እንኳን ከቶ
አደለሁም'ና የጥበቃ ፈሪ፡
የመምጣትሽን ቃል
ውሳኔሽን ጠበኩ፡
ባትመጪ እንኳን ከቶ
ልጠብቅሽ ፈለኩ።
✍✍ሚኪ
Forwarded from Liul-Z-ማርያም
በላይ በቀለ ወያ
.
ገላሽ ገላ አይመርጥም ፣ ከሁሉ ይጋደማል
ከንፈርሽ አየር ነው ፣ በሁሉም ይሳማል
ከሴት ክብርሽ ይልቅ ፣ ስሜትሽ ይቀድማል።
።።።
ነግሬሽ ነበረ፡፡
ጭን ከሰማይ ቢገዝፍ ፣ ከጭንቅላት ያንሳል
ምን ተራራ ቢመስል...
ጡትም አቅመ ቢስ ነው ፣ ሲነኩት ይፈርሳል፡፡
ነግሬሽ ነበረ....
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ
የወንድ ልጅን ዐይን..
ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ
ነግሬሽ ነበረ...
ሴት ክብሯ የአምላክ ነው ፣ እንደ እናት ስታስብ!!!
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ክብረቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ ፣ እናቶች አይደሉም
ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት
በክብር ነው እንጂ.
በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡
።።።።።
ነግሬሽ ነበረ
እናትነት ስሟ
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ።
ሴት ክብሯን ስታጣ ፣ እድሜዋ ይሔዳል
የወንድ ልጅ ቤቱ...
የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው
ቁንጅናም ይረክሳል!
ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው!
።።።።
ነግሬሽ ነበረ
ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ
"ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ስሜት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ።
።።።
ሞኝ ሰው ሲመክሩት
ሞኝ ሰው ሲነግሩት
የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ
ግን እነግርሻለሁ!
ነግሪያት ነበር ስል
ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ።
።።።
ግን እነግርሻለሁ
ግን እመክርሻለሁ
ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም
ሁሉም ይተኛታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም!!!
ለሌሎች አሪፍ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
.
ገላሽ ገላ አይመርጥም ፣ ከሁሉ ይጋደማል
ከንፈርሽ አየር ነው ፣ በሁሉም ይሳማል
ከሴት ክብርሽ ይልቅ ፣ ስሜትሽ ይቀድማል።
።።።
ነግሬሽ ነበረ፡፡
ጭን ከሰማይ ቢገዝፍ ፣ ከጭንቅላት ያንሳል
ምን ተራራ ቢመስል...
ጡትም አቅመ ቢስ ነው ፣ ሲነኩት ይፈርሳል፡፡
ነግሬሽ ነበረ....
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ
የወንድ ልጅን ዐይን..
ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ
ነግሬሽ ነበረ...
ሴት ክብሯ የአምላክ ነው ፣ እንደ እናት ስታስብ!!!
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ክብረቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ ፣ እናቶች አይደሉም
ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት
በክብር ነው እንጂ.
በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡
።።።።።
ነግሬሽ ነበረ
እናትነት ስሟ
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ።
ሴት ክብሯን ስታጣ ፣ እድሜዋ ይሔዳል
የወንድ ልጅ ቤቱ...
የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው
ቁንጅናም ይረክሳል!
ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው!
።።።።
ነግሬሽ ነበረ
ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ
"ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ስሜት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ።
።።።
ሞኝ ሰው ሲመክሩት
ሞኝ ሰው ሲነግሩት
የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ
ግን እነግርሻለሁ!
ነግሪያት ነበር ስል
ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ።
።።።
ግን እነግርሻለሁ
ግን እመክርሻለሁ
ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም
ሁሉም ይተኛታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም!!!
ለሌሎች አሪፍ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
ለምን አስፈለገ??🤔🤔🤔
SantaYe✍
......&......
🎤Santa¥e
😍😍😍😜
.
ብሩህ ውብ አይኖችህ እኔኑ እያስተዋሉ
የመጀመሪያህ መሆኔን ሌሎች እንደሌሉ
ስትነግረኝ አምኜህ ልቤ ራሴን ታርቆት
ውሸት እንደምጠላ እንደማቶድ ስርቆት......
07/07/2012
#Really_I_want_to_hear_his_answer
(whyyy?)
@Axelym
@Axelym
@Axelym
SantaYe✍
......&......
🎤Santa¥e
😍😍😍😜
.
ብሩህ ውብ አይኖችህ እኔኑ እያስተዋሉ
የመጀመሪያህ መሆኔን ሌሎች እንደሌሉ
ስትነግረኝ አምኜህ ልቤ ራሴን ታርቆት
ውሸት እንደምጠላ እንደማቶድ ስርቆት......
07/07/2012
#Really_I_want_to_hear_his_answer
(whyyy?)
@Axelym
@Axelym
@Axelym
ፀሐይ ያሸንፋል
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ተይ ይነጋል ስልሽ ፣ አይነጋም ብለሽኝ
በጨለማዬ ላይ ፣ ጨለማ ሆነሽኝ
እንደተለየሽኝ
የምኖርለትን ፣ አንድ ምክንያት ሳጣ
ተስፋዬ ተሟጣ
ወይ ታንቄ ልሞት ፣ ወይ መርዝ ልጠጣ
ወይ መርዝ ልገዛ ፣ ወይ ገመድ ላመጣ
ከቤት እንደወጣሁ ፣ በሀገር ፀሐይ ወጣ ።
ጨለማ ተነነ ፣ ፅልመት ረገፈ
ጊዜ ተአምረኛው
እርግብና እባብ ፣ እያስተቃቀፈ
ያሳየኝ ጀመረ ፣ መኖር እስኪያሳሳኝ
ተአምር ስመለከት
ሞቴ ተዘነጋኝ ፣ መሔድሽ ተረሳኝ።
።።።
ተይ ይነጋል ስልሽ ፣ አይነጋም ብለሽኝ
በጨለማዬ ላይ ፣ ጨለማ አልብሰሽኝ
ተስፋ አስቆርጠሽኝ
እንደተለየሽኝ
ሰማይና ምድሩ ፣ ተሞልቶ በተስፋ
ተስፋ የቆረጠ
ድምፁን ሚያሰማበት ፣ አደባባይ ጠፋ
የተስፋ መፈክር
የለውጥ መፈክር
የሚያሰሙ ህዝቦች ፣ ባደባባይ ሞልተው
መንገዶች በሙሉ ፣ በተስፋ ተዘግተው
ጊዜ ተአምረኛው
አይሆንም ያልሽውን ፣ ሲሆን እያሳየኝ
ለህይወት እስክጓጓ ፣ ከሞት ሊያዘገየኝ
በተስፋ አነሳኝ
መሔድሽ ተረሳኝ።
።።።።
ተይ ይነጋል ስልሽ ፣ አይነጋም ብለሽኝ
በጨለመ ቀን ላይ ፣ ፅልመት አልብሰሽኝ
ስትሔጂ ጥለሽኝ
በሀገር ፀሐይ ወጣ ፣ ፅልመቶች ጠፉ
አይሆኑም ያልሻቸው ፣ እየሆኑ አለፉ
በጎች ከተኩላ ጋር ፣ አብረው ተሰማሩ
የታወሩ አህዮች
በጅቦች ተመርተው ፣ መንገድ ተሻገሩ
ታምርና ትንግርት ፣ በሀገሩ ገነነ
አሸባሪ ያሉት ፣ አሻጋሪ ሆነ
ጊዜ ተአምረኛው
ከቶ አይነጋም ስትይ ፣ ሺህ ፀሀይ ታቅፎ
ከባንዲራው መሀል
ያሉትን ኮከቦች ፣ ከላዩ አራግፎ
በፀሐዮች ተካ
ይገርማል አንችዬ
ፀሐይ ስትወጣ ፣ ኮከብ የለም ለካ።
ለካንስ ለካንስ
ፀሐይን ለማያውቅ ፣ ኮከብ ነው ፀሐዩ
ለካንስ ለካንስ
ፀሐይ የጠፋበት ፣ ኮከብ ነው ወካዩ።
።።
ብቻ ምን አለፋሽ
አይነጋም ብለሽኝ ፣ ከሔድሽ በኋላ
የናፈቀን ፀሐይ ፣ እንደአሸን ፈላ
እንደሾላ ፍሬ ፣ ብርሐን ረገፈ
መንጋቱን ሳልነግርሽ
ተአምር እያየሁ
መሔድሽ ተረስቶኝ ፣ ብዙ ቀን አለፈ።
።።።
እርግጥ ነው
እውነት ነው
ዛሬም ባደባባይ ፣ ሰዎች ይሞታሉ
ሰው ባልሆኑ ሰዎች ፣ እየተገደሉ።
ነገር ግን ነገር ግን
በኗሩ ልብ ውስጥ ፣ ሟች አለ በፀጋ
አንዳንድ ሰው አለ
እራሱን ሚያጨልም ፣ ሀገር እንዲነጋ።
(መስዋትነት ነው ፣ የብርሐን ዋጋ)
።።።።
እርግጥ ነው
እውነት ነው
መብራትና ውሐ ፣ አሁንም ይጠፋል
ነገር ግን
ነገር ግን
ቀን የወጣ ፀሐይ ፣ መሽቶም ያሸንፋል።
ውሃ ባትኖርም
እድፍ አልያዘንም ፣ የለብንም ድካም
የፍቅርን ያህል
አያነፃም ውሐ ፣ ጥም ቆርጦ አያረካም።
ለሌሎች እጅግ ደስ የሚሉ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ተይ ይነጋል ስልሽ ፣ አይነጋም ብለሽኝ
በጨለማዬ ላይ ፣ ጨለማ ሆነሽኝ
እንደተለየሽኝ
የምኖርለትን ፣ አንድ ምክንያት ሳጣ
ተስፋዬ ተሟጣ
ወይ ታንቄ ልሞት ፣ ወይ መርዝ ልጠጣ
ወይ መርዝ ልገዛ ፣ ወይ ገመድ ላመጣ
ከቤት እንደወጣሁ ፣ በሀገር ፀሐይ ወጣ ።
ጨለማ ተነነ ፣ ፅልመት ረገፈ
ጊዜ ተአምረኛው
እርግብና እባብ ፣ እያስተቃቀፈ
ያሳየኝ ጀመረ ፣ መኖር እስኪያሳሳኝ
ተአምር ስመለከት
ሞቴ ተዘነጋኝ ፣ መሔድሽ ተረሳኝ።
።።።
ተይ ይነጋል ስልሽ ፣ አይነጋም ብለሽኝ
በጨለማዬ ላይ ፣ ጨለማ አልብሰሽኝ
ተስፋ አስቆርጠሽኝ
እንደተለየሽኝ
ሰማይና ምድሩ ፣ ተሞልቶ በተስፋ
ተስፋ የቆረጠ
ድምፁን ሚያሰማበት ፣ አደባባይ ጠፋ
የተስፋ መፈክር
የለውጥ መፈክር
የሚያሰሙ ህዝቦች ፣ ባደባባይ ሞልተው
መንገዶች በሙሉ ፣ በተስፋ ተዘግተው
ጊዜ ተአምረኛው
አይሆንም ያልሽውን ፣ ሲሆን እያሳየኝ
ለህይወት እስክጓጓ ፣ ከሞት ሊያዘገየኝ
በተስፋ አነሳኝ
መሔድሽ ተረሳኝ።
።።።።
ተይ ይነጋል ስልሽ ፣ አይነጋም ብለሽኝ
በጨለመ ቀን ላይ ፣ ፅልመት አልብሰሽኝ
ስትሔጂ ጥለሽኝ
በሀገር ፀሐይ ወጣ ፣ ፅልመቶች ጠፉ
አይሆኑም ያልሻቸው ፣ እየሆኑ አለፉ
በጎች ከተኩላ ጋር ፣ አብረው ተሰማሩ
የታወሩ አህዮች
በጅቦች ተመርተው ፣ መንገድ ተሻገሩ
ታምርና ትንግርት ፣ በሀገሩ ገነነ
አሸባሪ ያሉት ፣ አሻጋሪ ሆነ
ጊዜ ተአምረኛው
ከቶ አይነጋም ስትይ ፣ ሺህ ፀሀይ ታቅፎ
ከባንዲራው መሀል
ያሉትን ኮከቦች ፣ ከላዩ አራግፎ
በፀሐዮች ተካ
ይገርማል አንችዬ
ፀሐይ ስትወጣ ፣ ኮከብ የለም ለካ።
ለካንስ ለካንስ
ፀሐይን ለማያውቅ ፣ ኮከብ ነው ፀሐዩ
ለካንስ ለካንስ
ፀሐይ የጠፋበት ፣ ኮከብ ነው ወካዩ።
።።
ብቻ ምን አለፋሽ
አይነጋም ብለሽኝ ፣ ከሔድሽ በኋላ
የናፈቀን ፀሐይ ፣ እንደአሸን ፈላ
እንደሾላ ፍሬ ፣ ብርሐን ረገፈ
መንጋቱን ሳልነግርሽ
ተአምር እያየሁ
መሔድሽ ተረስቶኝ ፣ ብዙ ቀን አለፈ።
።።።
እርግጥ ነው
እውነት ነው
ዛሬም ባደባባይ ፣ ሰዎች ይሞታሉ
ሰው ባልሆኑ ሰዎች ፣ እየተገደሉ።
ነገር ግን ነገር ግን
በኗሩ ልብ ውስጥ ፣ ሟች አለ በፀጋ
አንዳንድ ሰው አለ
እራሱን ሚያጨልም ፣ ሀገር እንዲነጋ።
(መስዋትነት ነው ፣ የብርሐን ዋጋ)
።።።።
እርግጥ ነው
እውነት ነው
መብራትና ውሐ ፣ አሁንም ይጠፋል
ነገር ግን
ነገር ግን
ቀን የወጣ ፀሐይ ፣ መሽቶም ያሸንፋል።
ውሃ ባትኖርም
እድፍ አልያዘንም ፣ የለብንም ድካም
የፍቅርን ያህል
አያነፃም ውሐ ፣ ጥም ቆርጦ አያረካም።
ለሌሎች እጅግ ደስ የሚሉ ግጥሞች ሊንኩን ይጫኑ👇👇👇
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
@getemTheII
እኛነታችንን በደንብ አናውቀውም፡ ግን እኛ እኔ በሚል አጥር ውስጥ ተተብትበናል። መኖር እንመኛለን ግን የሌላው አለመኖር አያሳስበንም፡ መራብ አንፈልግም የሌሎች እርሀብ ግን አያመንም፡ ሰላም እንፈልጋለን ግን የሌሎች ሰላም እናናጋለን፡ መደሰት እንወዳለን
ግን ሌሎች እንዲያለቅሱ ምክኒያቶች ነን። በእውነት ምኑም ነገር አልገባንም፡ ብኩኖች ብቻ ነን ፡ ሸክላነታችን ያልገባን ፡ ነገን ለመኖር ዋስትና የሌለን ከንቱዎች፡ አፈርን ካፈር ለመለየት የምንዳክር ቂሎች ፡
ስጋችን የተለቀ ፣አስተሳሰባችን ያልታረቀ ፣ አካሄዳችን እና ምግባራችን የተናቀ ምስቅልቅሎች፡ ምኑም ነገር አልገባንም። ለክብርና ለዝና ፡ ለሀብትና አድሮ አመድ ለሚሆን ስጋችን ባሪያዎች የሆንን፤ የምንፈልገው አይገባንም ፡ የሚያስፈልገን አይታየንም፡ የውስጣችንን ባዶነት በጩህትና ባለባበስ ለመሸፈን የምንዋትት አሳዛኞች፡ ከፈጣሪ ትዛዝ ይልቅ የፍላጎታችን ባሪያወች ፡ ከፍርቅር ይልቅ የጥላቻ ፈረሶች ፡ የሰውነት ክብራችንን ያጣን፣ ጥጋብ ምንሆነውን ያሳጣን ፣ ከቁጣው መቅሰፍት ያልወጣን
ጅሎች ሆነናል ፡፡ የምንናገረውን አናቅም፡ የምናምነውን እሱን አንሰማውም፡ የቃል ሰዎች ብቻ ነን፡ ፡
ሀጢታችን በፊታችን የተገለጠ ነው፡ ግን ክብራችን ይመስለናል ፡፡ እምናደርገውን አናስተውልም ፣ እየሆነ ያለው ሁሉ አይገባንም፡፡ የፈጣሪ እዳ አለብን ፡ እጃችን ባዶ ነው ፡ ለዛውም የተጨማለቀ ። አልገባንም ሀጢያታችን በዝቷል ፡ ውጤቱንም እያየነው ነው ፡፡ ከሩጫችን ረጋ እንበል፣እናስተውል ፣እንመለስ፣ ሰው እንሁን ፣ አስተሳሰባችንን ከሰውነት ሚዛን አናስወጣው ፡፡ አልረፈደም እንፀልይ ፡ የፈጠረን አምላክ ለይቅርታ የታመነ ነው።
ሰላም፣ ፍቅር፣ ጤንነት ፡ለሰው ልጆች ሁሉ ይሁን !
Samuel Adane
❤️🌿❤️🌿❤️🌿❤️🌿❤️🌿❤️
@TIBEBnegni
@TIBEBnegni
@TIBEBnegni
ግን ሌሎች እንዲያለቅሱ ምክኒያቶች ነን። በእውነት ምኑም ነገር አልገባንም፡ ብኩኖች ብቻ ነን ፡ ሸክላነታችን ያልገባን ፡ ነገን ለመኖር ዋስትና የሌለን ከንቱዎች፡ አፈርን ካፈር ለመለየት የምንዳክር ቂሎች ፡
ስጋችን የተለቀ ፣አስተሳሰባችን ያልታረቀ ፣ አካሄዳችን እና ምግባራችን የተናቀ ምስቅልቅሎች፡ ምኑም ነገር አልገባንም። ለክብርና ለዝና ፡ ለሀብትና አድሮ አመድ ለሚሆን ስጋችን ባሪያዎች የሆንን፤ የምንፈልገው አይገባንም ፡ የሚያስፈልገን አይታየንም፡ የውስጣችንን ባዶነት በጩህትና ባለባበስ ለመሸፈን የምንዋትት አሳዛኞች፡ ከፈጣሪ ትዛዝ ይልቅ የፍላጎታችን ባሪያወች ፡ ከፍርቅር ይልቅ የጥላቻ ፈረሶች ፡ የሰውነት ክብራችንን ያጣን፣ ጥጋብ ምንሆነውን ያሳጣን ፣ ከቁጣው መቅሰፍት ያልወጣን
ጅሎች ሆነናል ፡፡ የምንናገረውን አናቅም፡ የምናምነውን እሱን አንሰማውም፡ የቃል ሰዎች ብቻ ነን፡ ፡
ሀጢታችን በፊታችን የተገለጠ ነው፡ ግን ክብራችን ይመስለናል ፡፡ እምናደርገውን አናስተውልም ፣ እየሆነ ያለው ሁሉ አይገባንም፡፡ የፈጣሪ እዳ አለብን ፡ እጃችን ባዶ ነው ፡ ለዛውም የተጨማለቀ ። አልገባንም ሀጢያታችን በዝቷል ፡ ውጤቱንም እያየነው ነው ፡፡ ከሩጫችን ረጋ እንበል፣እናስተውል ፣እንመለስ፣ ሰው እንሁን ፣ አስተሳሰባችንን ከሰውነት ሚዛን አናስወጣው ፡፡ አልረፈደም እንፀልይ ፡ የፈጠረን አምላክ ለይቅርታ የታመነ ነው።
ሰላም፣ ፍቅር፣ ጤንነት ፡ለሰው ልጆች ሁሉ ይሁን !
Samuel Adane
❤️🌿❤️🌿❤️🌿❤️🌿❤️🌿❤️
@TIBEBnegni
@TIBEBnegni
@TIBEBnegni