ግጥም ብቻ 📘
64.3K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
ከፍቅር ደሴት ዳር
©ሲራክ
ሰኔ ሰላሳ ነው ያገኘውሽ እለት
ፍቅርሽን በልቤ ያነጋገስኩበት
አንቺ የኔ ውሃ
የኔ ድንቅ አምሃ
ከዶቅማው ዛፍ ስር
የከተብነው ፍቅር
ከመስኩ ቦርቀን ያሸትነው ትዝታ
ከወንዙ ዳርዳርታ በውኃው ድንፋታ
የቀማመርንበት
ጅምሩ ፍቅራችን ህይወት የዘራበት
ዛሬ ነው ቀናችን
አሁን ነው ጊዜያችን
ዘመናትን አልፎ ጅምሩን ያፀናው
እንደ ንስር በሮ ከልብሽ ያረፈው
አንቺ የኔ ውሃ
የኔ ድንቅ አምሃ
ከክፉ እንቅልፉ ያነቃሽው ልቤ
በአስኳላው ወኔ ያገኘሽ ምናቤ
ነይ እንሂድ ብሏል ከሀይቁ ዳርዳርታ
ብቅ በይ ይልሻል ሲመሽ ወደ ማታ
ሀይቁን ዳር አፅድቼ
መንፈሴን አፅንቼ
እጠብቅሻለሁ ስጋጃ ዘርግቼ
ሻማዬን አብርቼ
ከፍቅር ደሴት ዳር
በሀሴት ተሳክረን ስንበር እንድናድር
__________°°°°°°______________
ሲራክ @siraaq
መልካም የፍቅረኛሞች ቀን
መልካም ቫላንታይን
መልካም ባላንጣይን

@getem
@getem
@getem
@getem
Audio
እንዴት ነህ ፈጣሪ
(በረከት በላይነህ)

@getem
@getem
@getem
#እኖርልሻለሁ !
(© በርናባስ ከበደ)
-
ኢትዮጵያ ሀገሬ ፡ እኔ እወድሻለሁ
እንኳን መሞት ቀርቶ ፡ እኖርልሻለሁ፡፡

እንደ ጥዑም ቡና ፡ እንደሚያውድ እጣን
እንደ ትሁት ምላስ ፡ አባራሪ ሰይጣን፣
እንደ ዋሽንት ድምፅ ፡ እንደሚሰጥ ሀሴት
ሥነ-ሥርዐት እንዳላት ፡ አመለ-ሸጋ ሴት፣
እንደሚያምር ሸማ ፡ በሰዎች ገላ ላይ
እንደነዚ ሁሉ ፡ ከነዚህም በላይ፣
ኢትዮጵያ ሀገሬ ፡ እኔ እወድሻለሁ
እንኳን መሞት ቀርቶ ፡ እኖርልሻለሁ፡፡

ላንቺ ያለኝን ፍቅር -
ቃሌን ከሰማሽው ፡ ካየሽው መውደዴን
በይ አድምጭኝ ደሞ -
የበላኝን ነገር ፡ ያንጀቴን የሆዴን ፡፡

ሸሽቶ ካልበረረ -
ታጥቆ ካልዘመተ ፡ ዱር ወድቆ ካልቀረ
ጀግና አይባልም ወይ?
ቃል አልበላም ብሎ : ጦሙን ውሎ ያደረ?!
አይባልም ወይ ጀግና : እያለች ህይወቱ
ነፋስ ጎርፉን ችሎ : የፀናው በ’ምነቱ፡፡

እውነቴን እኮ ነው! …
እንዲያውም… እንዲያውም… ሞትማ ረፍት ነው!!
እረፍት እኮ ነው ሞት -
እርግፍ አርጎ መተው : ላንድዬው ግልግል
መኖር ግና ውጊያ : ከራስ ጋራ ትግል!
ከራስ አቋም ሙግት : ከራስ ሃሳብ ግጥሚያ
ተኩስ አቁም የሌለው : የዘላለም ፍልሚያ፡፡

ስለዚ’ ምክንያት : እነሆተ ቅኔ
አንድም ለዘመኔ፣ አንድም ለወገኔ፡፡
‹‹ኢትዮጵያ ሀገሬ ፡ እኔ እወድሻለሁ
እንኳን መሞት ቀርቶ ፡ እኖርልሻለሁ!!››
-
-
-
የሌሎች አገልጋይ : ብሆንም ምንደኛ
ወረቀት ያሰረኝ : የወር ደሞዝተኛ፣
የኮርኒስ አይጥና : ባለግዜ አለቃ
የሚጨፍሩብኝ : በመንታ ፈረቃ፣
ሀገር የምቀልብ : ላቤን ጥጄ በድስት
ሶስት ጨቅላ ልጆች : አንድ ትልቅ መንግስት፣…
ሳልሰስት እውቀቴን
ሳልቆጥብ ጉልበቴን፣
ካመት እስከ ዓመት : በትጋት በመዝለቅ
ደረጃና ደሞዝ : እድገት ስጠባበቅ፣…
ዛሬን እንዳይርበኝ : ቤሳቤስቲን ጥለው
ለነገ እንዳይተርፈኝ : በእርከን ከልለው፣
በትዝብት እያዩኝ
መፅውተው ሲሸኙኝ፣….
ሐዘኔ ቢመርም
ቅስሜ ቢሰበርም፣
ዘንድሮም እናዳምናው
ያው እንደካቻምናው …
ከእለት እንጀራ ጋር ፡ ቀጥላለች ህይወት
ግን ኣላማርርም -
ይሁን ተመስገን ነው ፡ እሱስ ማን አየበት?!
እላለሁ ‹ተመስገን!› -
ፀሎት እና ትጋት : ተስፋ ሲያመረቃኝ
አሜን!... ይሁን አሜን! ...
እኔም ሰው ቀጥሬ : ለመታማት ያብቃኝ|!!!
-
-
-
እንደ ጥዑም ቡና ፡ እንደሚያውድ እጣን
እንደ ትሁት ምላስ ፡ አባራሪ ሰይጣን፣
እንደ ዋሽንት ድምፅ ፡ እንደሚሰጥ ሀሴት
ሥነ-ሥርዐት እንዳላት ፡ አመለ-ሸጋ ሴት፣
እንደሚያምር ሸማ ፡ በሰዎች ገላ ላይ
እንደነዚ ሁሉ ፡ ከነዚህም በላይ፣
ኢትዮጵያ ሀገሬ ፡ እኔ እወድሻለሁ
እንኳን መሞት ቀርቶ ፡ እኖርልሻለሁ፡፡
-
-
-
አፈሯን ቢቅሙት ፡ ስኳር ጣፋጭ ነገር
ሳትሰስት በምትቸር ፡ በዚች ለምለም ሀገር፣
ብልጥግና እንዲሆን -
ኢንዱስትሪ እንዲያብብ ፡ በሚል ቃል ከለላ
ገበሬው ተገፍቶ ፡ ፊት ሲቆም ደላላ፣…
ወረት ፋሽን ጠልፎት -
ሰው ህልሙን እረስቶ ፡ ከቅዠት ሲፋቀር
ደመና ብርቅ ሆኖ -
ሰማይ ከንፈር ሳይገጥም ፡ እንደሳቀ ሲቀር፣…
ንፋስ እንዳጣፋው : የጎረምሳ ከንፈር
መሬት ሲሰነጠቅ : አለት ሲፈረፈር፣…
መጤ ነህ ተብሎ : ወገን ዱር ሲሰደድ
ከምርጥ ሰው ይልቅ : ምርጥ ዘር ሲወደድ፣…
ከሰማይ በራሪ : ከአንበጣ በቀር
ተዘዋውሮ መብላት : ዘበት ሆኖ ሲቀር፣…
ወተት አልሰጥ ብለው : ላሞች ሲለግሙ
ጥጆቹም እንደሰው : ‘አርብ-ሮብ’ ሲፆሙ፣…
ይህ ሁሉ ሲደረግ ፡ በብርሃን በግላጭ
ቢሰነጥቀኝም ፡ ቁጭት እንደ ምላጭ፣
“ዘራፍ ወንዱ!” ብዬ
ሞፈር ጅራፍ ጥዬ፣
ቁራሽ ዳቦ አልጎርስም ፡ ነጥቄ እንደ ሽፍታ
እርሜን ከምበላ -
ትብያ ሆኜ ልቅር ፡ ልሙት ዛሬ ማታ !!!

ዋጥ አርጌው እንጅ ፡ ቢቸግረኝ መላው
ንገረኝ ካልሽማ -
ብሶት መች ይጠፋል ፡ በሆድ የማብላላው፡፡

ይኸው በኛ ቀዬ -
መሬቱም እንደ ሰው ፡ እጅ መንሻ ለምዶ
አለማዳበርያ : ሣር አይበቅልም ሰርዶ !!
ይሁን!... ምንም አይደል -
ምርቱ ተትረፍርፎ : ጎተራ ከሞላ
ግን ውለታ አያውቅም -
ደሞ ለከርሞውም ፡ ይጠብቃል ሌላ!

ከገብሱ፣ ከስንዴው፣
ከጤፍ፣ ከሽምብራው ፡ እኩሉ ተሽጦ
እሽግ ማዳበርያ ፡ ኹኖ ተለውጦ፣
ስልቅጥ ያረገዋል ፡ አፈር ላንድ ‘ራቱ
ሰው “ጭሰኛ” ሆነ ፡ የገዛ መሬቱ !!!

አየሽልኝ አይደል?
እንዲ ነው ኑሮዬ ፡ ነገር አኳኋኔ
መተከዝ ምን ሊበጅ -
ችግሬ ላይ ስስቅ ፡ ፈክቶ ያልፋል ቀኔ፡፡
አኮቴት ነው ለአፌ -
ስተኛም ‹ተመስገን!› : ስነቃም ‹ተመስገን!›
የነገን የከርሞን : እርሱ ያውቃል መገን!!

አይጨክን አንድዬ : ባይዘልቅም ከጓዳ
ራዕይ ያሳየኛል : በሕልሜ ሰሌዳ!
አያለሁ በሕልሜ -
“ኩልል ያለ ውሃ : ከቧንቧ ስቀዳ
ሞፈር ወድያ ጥዬ : ትራክተር ስነዳ፣…
ግልገል አውሮፕላን -
ማሳዬ ገላ ላይ : ፀረ-ተባይ ሲረጭ
አረም እና ችጋር : በአጭሩ ሲቀጭ፣…
ፈረንጅ አሰልፌ : ስሸጥ ዳማከሴ
አንቱታ እና አክብሮት : ሲሆን ቡና ቁርሴ፣ …”
ኣያለሁ ዘለለት -
ሲባትል የዋለ : ጎኔን ሳሳርፈው
ምናል ለልጄ ሲል -
ሕልሜን እውን አርጎት : በስምሽ በፃፈው፡፡
-
-
-
እንደ ጥዑም ቡና ፡ እንደሚያውድ እጣን
እንደ ትሁት ምላስ ፡ አባራሪ ሰይጣን፣
እንደ ዋሽንት ድምፅ ፡ እንደሚሰጥ ሀሴት
ሥነ-ሥርዐት እንዳላት ፡ አመለ-ሸጋ ሴት፣
እንደሚያምር ሸማ ፡ በሰዎች ገላ ላይ
እንደነዚ ሁሉ ፡ ከነዚህም በላይ፣
ኢትዮጵያ ሀገሬ ፡ እኔ እወድሻለሁ
እንኳን መሞት ቀርቶ ፡ እኖርልሻለሁ፡፡
-
-
-
በክርስቶስ በኩል : ከዛም በሃዋርያት
በተሰጠው ሹመት : ቅዱስ ስነ-ሥርዓት፣
ካህኑ ሲያስተምር : ወንጌል መፅሃፍ ገልጦ
ምእመኑ እየሰማ : ፊት ለፊት ተቀምጦ፣
“አንድ ሰው ወደቀ…”
“ተቀሰፈ” ሲባል : በሃጥያት ተረታ
ሁሉም በአንድነት
እልልታን ያሰማል : በመተከዝ ፈንታ!

አሁን አሁንማ …
ይህን ሰሞንማ : ጭራሽ ብሶበታል
በአንድ እግር ያስቻለው : ተመስጦውን አቷል
ማንጎላጀት ቀርቶ ፡ አንጥፎ ተኝቷል!!

በአንቀጽ፣ በምዕራፍ
በየፀሎቱ ጫፍ
ጎሸም የሚያረገው ፡ ቀስቃሽ ይፈልጋል
በ‹አባት ሆይ!› ጀምሮ ፡ በ‹አሜን!› እስኪያሳርግ : አሥር ግዜ ያዛጋል፡፡

አዝማምያውን አይተን
ይህን ተመልክተን ፡ ለነገው ስንፈራ
ደሞ አዲሶች መጡ -
ተሸክመው ወስደው ፡ ሊያደርጉት ጭፍራ!!
ተስፋ የሚሸጡ ፡ ቅብዓት ነጋዴዎች
ሃሰተኛ ነብያት ፡ “የእግዚአብሔር ሰዎች”፣
በየመንገዱ ዳር -
የፈውስ የታምራት ፡ ድንኳን እየጣሉ
ይህ ምስኪን ህዝብሽን -
ቀኑን ይሰርቁታል ፡ “ይነጋል” እያሉ፡፡
“ይነጋል” እያሉ ፡ ይሰርቁታል ዓይኑን
“ይነጋል” እያሉ ፡ ይሰርቁታል ልቡን …
እስኪ እግዜር ይሁነው ፡ ይመልሰው ቀልቡን
እኔም ልቅሶው ይብቃኝ ፡ ስጭኝ መሃረቡን፡፡

ኢትዮጵያዬ እናቴ
ባፈርሽ ላይ ኑሬ : ካለቀረ መሞቴ
እነሆ ምኞቴ ፡ የዘመን ፀሎቴ!

ከትላንት እስከ ጥንት -
ሲሻው በሎሌው ላይ ፡ ሲሻው በመኳንንት
አድሮ ሚያስጨንቅሽ ፡ የአየር አጋንንት
ሰላሳ ክንድ ይራቅ -
ይውደቅ ይንፈራፈር ፡ ይሙት ትንፋሽ ይጣ
ሶስት ጊዜ ጩሆ ፡ ከግዛትሽ ይውጣ !!!
-
-
-
እንደ ጥዑም ቡና ፡ እንደሚያውድ እጣን
እንደ ትሁት ምላስ ፡ አባራሪ ሰይጣን፣
እንደ ዋሽንት ድምፅ ፡ እንደሚሰጥ ሀሴት
ሥነ-ሥርዐት እንዳላት ፡ አመለ-ሸጋ ሴት፣
እንደሚያምር ሸማ ፡ በሰዎች ገላ ላይ
እንደነዚ ሁሉ ፡ ከነዚህም በላይ፣
ኢትዮጵያ ሀገሬ ፡ እኔ እወድሻለሁ
እንኳን መሞት ቀርቶ ፡ እኖርልሻለሁ፡፡
-
-
-
እንደ ለውዝ ቆሎ : እንደ ጦር ማስቲካ
የመንገድ ዳር ሸቀጥ : ሲሆን ፖለቲካ፣
“ቀኝ ዘመም” ያልነው : አ
1
ድሮ ሲሆን ግራ
ከሊቅ እስከ ደቂቅ : ሲተነትን ሴራ፣…
ሹመት በዘር ገመድ -
በጎሳ በነገድ፣ ሲዋረስ እንደ ርስት
“ሙሴያችሁ ነኝ’’ ሲለን -
በትሩን የያዘው : ባለጊዜው መንግሥት፣…
ቀን ሰው እያነሳ : ቀን ሰው እየጣለ
ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ …
እኔ ኩሩው ልጅሽ : በጣት የማይዘግኑኝ
ትንታግ የሳት ቋያ : እማያዳፍኑኝ፣
ባይኖረኝም ፓርቲ : የለት ውሎ መግቢያ
ምርጫ ምልክቱ : አርማው ማራገብያ፣
ቼ! ብዬ ማዘምተው : ባልመለምል ቡድን
አንዱን ረግጦ ሚገል : አንዱን ወድቆ እሚያድን፣
ጭቁኑ ላይ ቆሜ -
ጭንቁን አፋፍሜ : ድልን ባልጎነጭ
ግንባሬ ላብ እንጂ : ስልጣን ባያመነጭ፣
እንዴት ዝም ልበል -
ጆሮ ዳባ ብዬ : እስከመቼ ልዝለቅ
ፊት ለፊቴ እያየሁ -
በታሪክ ውትፍትፍ : ወገን ሲተላለቅ!

እናማ …
የቤትሽ ቅናት ቢበላኝ : ልቤ በሃዘን ቢደማ…
ጠቅል ብራና ይዤ : ወጣሁኝና ከማማ፣
ገድልሽን አንቀፅ በአንቀፅ : ከዳር እስከ ዳር ነዛሁት
እንኳንስ አፈር መሬቱን : ሰማዩን ጭምር ገዛሁት፡፡
በዘመን ጀርባ ታክኬ
የኋሊት ኋሊት ተጉዤ
ከዮቶር ሃረግ መዝዤ፣…
የዋሾ ምላሱ እስቲያንቀው : ነገርኩት ገናናው ሥሜን
ወአክሱም ወላሊበላ : አሀዱ ኢትዮጵያ አሜን!!!!
-
-
-
ኢትዮጵያ ሀገሬ ፡ እኔ እወድሻለሁ
እንኳን መሞት ቀርቶ ፡ እኖርልሻለሁ፡፡
-
ሞትማ ረፍት ነው -
እርግፍ አርጎ መተው : ላንድዬው ግልግል
መኖር ግና ውጊያ : ከራስ ጋራ ትግል!
ከራስ አቋም ሙግት : ከራስ ሃሳብ ግጥሚያ
ተኩስ አቁም የሌለው : የዘላለም ፍልሚያ፡፡
-
-
-
እንደ ጥዑም ቡና
እንደሚያውድ እጣን
እንደ ትሁት ምላስ : አባራሪ ሰይጣን፣
እንደ ዋሽንት ድምፅ ፡ እንደሚሰጥ ሀሴት
ሥነ-ሥርዐት እንዳላት ፡ አመለ-ሸጋ ሴት፣
እንደሚያምር ሸማ ፡ በሰዎች ገላ ላይ
እንደነዚ ሁሉ ፡ ከነዚህም በላይ፣
ኢትዮጵያ ሀገሬ ፡ እኔ እ ወ ድ ሻ ለ ሁ
እንኳን መሞት ቀርቶ ፡ እ ኖ ር ል ሻ ለ ሁ!!!
------------------//------------------------
(© በርናባስ ከበደ)

@getem
@getem
@getem
1
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ጋሞ!!!!!


ከቃጫው ገመድ ላይ ፤ ውብ ፍቅሩን ጠምጥሞ፤
በሰፊ ትከሻው፤
ጦቢያ የምትባል ያባቶቹን ኪዳን ሃገር ተሸክሞ፤
ሩቅ ነው ምናቡ፤
ሩቅ ነው መንገዱ፣ ዳርቻ የለውም እንደ አባያ ጫሞ፤
ወዘናው ሙሉ ነው፤
አፉ ይጣፍጣል፤
ብእሩ ይሰላል እንደ ጨንቻው ሰንደቅ እንደ አሰፋ ጫቦ፤
ጨንቻ ሚካኤል ላይ፤
ሳየው ደስ ይለኛል በአረንጓዴ አፈር ላይ በአዝመራ ታጅቦ፤
ልክ እንደተራራው፤
እንደ ጨንቻ ዳገት ወደ ላይ ወደ ላይ ከፍ ብሎ ተሹሞ፤
ቃሉን የማይሽረው፤
የባንዲራው ጌታ ፤
የጦቢያ ባለሟል እንደምነው ዶርዜ እንደምነው ጋሞ???

(( ጃ ኖ ))💚💛

@getem
@getem
ከእኔነት ያመጸ ፤ ክብርን የሚያስረሳ ፤ ፍቅር ባንች ሞልቶ፤
በጀምበር መግቢያ ላይ፤
በጥርጊያው መንገድ ላይ፤
መንገዱ ሲከዳኝ የጉልበቴ ስፍር መቀነቱ ላልቶ፤
እምወድሽዋ፤
የመንገዴን ጥመት ፤ ጎንበስ ብሎ ማቅናት አትሰለችም ከቶ።

((( ጃ ኖ ))💚💛

@getem
@getem
@Nagayta
""""የሴት ህልም""""
.......መኮንን አልማው ገበይ.....
..............
በሃካል እርቀሽኝ
በሰው አሳማሽኝ!
ኑሮዬን ለብቻ ስገፋው እያዩ
"ብቸኛው" ይሉኛል ከሰው እየለዩ!
እውነት ከተባለ
ብቻነት የት አለ?
'ያሣብ ሰረገላ ከስንቱ እያዋለ!
በርግጥ
በፍቅር ለመዋደቅ
ግድ ቢልም መተዋወቅ
ግን የትኛውም ወንድ
ሳታውቀው ሳያውቃት
በልቡ የሚሥላት
በአዕምሮው የሚያሥባት
ከነፍሱ የማትሾልክ
አለች የሴት መላክ!
"
አሁን እኔ እንኳን
ከዓለም ህዝብ መሃል ፣ ሰው 'ብቸኛው'ሚለኝ
ኮሮና እንዳለበት ፣ ደፍሮ ሠው ባይቀርበኝ
ብመሥልም ብቸኛ...
ገልጠው ባያዩኝ እንጂ ፣ እንደ እትም ደብዳቤ
ቢፈትሹኝ ኖሮ ፣ እንደተጎዘጎዝሽ አንቺ አለሽ በልቤ!


የካቲት 06/2012 ዓ.ም
(በፍቅረኛሞች ቀን ብቻቸውን ሢያሣልፉ አይተን ፍቅረኛ አልባ መሥለው እንዳይታዩን)

@getem
@getem
@getem
ፍተቅስርፋ(ልዑል ኃይሌ)
ችንካርሽን አየሁት
በፍቅር መስቀል ላይ የተሠቀልሽበት፤
ሠንበርሽን አየሁት
በአይሁድ አፍቃሪ የተገረፍሽበት፤
ደምሽን አየሁት
ቁስልሽን አየሁት አየሁት ያንቺ ዕንባ፤
ጀምበር አዘቅዝቃ
ሕመምሽ ሊቀበር ቁስልሽ አፈር ገባ፤
በ3ኛው መዓልት
ከመከዳት ፍቅር ከሞት ስትነሺ፤
ትንሳኤሽ ናፋቂ
እየጠበቅኩሽ ነው እስክትመለሺ፤
.
ያለፍሽበት መንገድ
ትዝታው ምን ቢያምም ባይሽርም ጠባሳው፤
አሻግረሽ ተመልከች
ተስፋ ነው ትልቅ ስንቅ ትላንት የሚያስረሳው፤
.
ተራመጅ ወደ'ኔ
እየጠበቅኩሽ ነው በናፍቆት ውብ ተስፋ፤
ወደ ኋላ እትሂጂ
የትላንቱ ዕንባሽ ይዞኝ እንዳይጠፋ፤
ደግሞ እንዳይመልሰኝ
ከተሠቀልኩበት የትላንት ችንካሬ የትላንት ግርፋት፤
ወደ ነገ ምሪኝ
በጥዑም ፍቅራችን ዛሬን እንለፋት፤
.
ተመልከች ዙሪያሽን!
ከከተማው ሁሉ
ከወጪ ወራጁ ካላፊ ካ'ግዳሚው፤
ይበዛል ይበልጣል ቁስል ተሸካሚው፤
ግን ዕድሜ ለጥርሱ
ሸፍኖ ያልፈዋል ሐቅ እንዳላወቀ፤
እንዲህ ነው በኛ ዓለም
ጀምበር እየወጣ ጀምበር የጠለቀ፤
.
ተመልከች ዙሪያሽን!
ከጀምበር ተማሪ
እንደሚፈራረቅ መጥለቅና መንጋት፤
ትላንትሽን ጣዪ ዛሬን ውብ አድርጊያት፤
.
እንፍጠር ውብ ዓለም
እንፍጠር ውብ መንደር፤
ተዋድደን እንዋል
ተዋድደን እንደር፤
.
ይግረመው ዓለሙ
በችንከር በክህደት ሲሰቅለን የኖረ፤
ፍቅር ላሠብንለት
ለምላሽ ስንቅ ብሎ ክህደት ለሠፈረ፤
.
ዙሪያሽን ተመልከች!
ሻማው ይታይሻል?
ይታይሻል ክብሪት? 'ሳት እየለኮሰ፤
ፅልመት ለመግፈፍ ነው
ራሱን አቃጥሎ ከክር የደረሠ፤
ፍቅር እንደዚህ ነው
ፅልመትን ለመግፈፍ
ለሠው ብርሃን ሲሉ ራስን ማቃጠል፤
አንጀትን በጥሰው
ለጨለመበት ሠው ብርሃንን መቀጠል፤
.
እኔም ክብሪት ሆኜ ስደርስ ከልብሽ በር፤
ከክርሽ ላይ ሳልደርስ ስለምን ልሰበር፤
አታጥፊኝ በንፋስ አታጥፊኝ በእሣት፤
ከመጥፋቴ በፊት
ቢያንስ
ያንቺን ብርሃንነት ከፅልመቱ ላንሳት
የካቲት 5, 2012 ዓ.ም.
ትቀመጥ!...
@getem
@getem
@getem
1👍1
(እ............ህ............ህ)
....
(መልአኩ ስብሐት ባይህ)
*************
ሰማሽው ይህን ድምጽ?
ሙታንን ሚጠራ
መርገምትን ሚቀራ።
ሰይጥኖ ከሸይጣን ጽድቅትን የጠላ
ከሲኦል እልፍኝ ላይ ግብር እሚያበላ።

ጥርምስ ክርስስ ጭርስስ
ድፍርስ ትርምስ ግርስስ።
ፍጥረቱ የሆነ
ቅላጼው በአንቺታሽ ላይወድቅ የገነነ።

እርኩሳን ያላቁት
አውሬያት ያነቁት።
በርባኖስ ባልባሱ በጽልመት ያስጌጠው
ጭቃ ያጨቀቀው ጭምሉቁ የዋጠው።
ግርጥት አትሮንስ ላይ
ለመልካ ሣጥናኤል ልሳኔ እሚቀኝ
በእብደትሽ ምታብጂው ድመጸቴ ደነቀኝ።

ድምጸቴ ደነቀኝ

ልዝብ ቅርፍፍ ዝልጉስ
ቅፍድድ ብግር ኩስስ
መጫሚያው የሆነ
ኧረ እንዴት ሁኖ ነው
ኧረ እንዴት ኩኖ ነው
ካንቺነትሽ ሲደርስ
አምሮ የተካነ።

ንገሪኝ እመዋ

ስርጌዋ ስሬዋ
ስሜዋ ውቅሬዋ
ክርሜዋ ግርሜዋ።

በፍቅርሽ አጽዋማት
በይሁን ቁርጥማት
በከንፈርሽ ጥማት

ዝንተ ዓለም ስትለብሺኝ
ምነው ያልጸየፍሽኝ
ምነው ያልገደፍሽኝ

ንገሪኝ ግርሜዋ

ንግርት ልፋፌሽ ምንድ ነው
ሰበብ ምክንያት የትሽ ነው።

አንዳንድ ቀንማ
አንዳንድ ቀንማ
ያሰኛል ውሽማ
ብዬ ባልኩሽ ለታ
አ...ቤ....ት..... ድምጽህ ያልሽኝ እውነት ነው በባታ ።

ንገሪኝ ስሬዋ

አምሳል ምስራቼ
መለኮት ምራቼ
የጎደልኩብሽ ለት
ሙሉ ነህ እያልሽኝ ነፍሴን ምታርሻት
እጅ እጅ ምትል ቀልዴን ሳቅ እምትለውሻት
ካለማመን ማመን ማመንን የቸርሻት ።

ነፍሴን የት አረገሻት
ስሜን መች ገባሻት

ብዬ ሳሰላስል
በሕማምሽ ሳስል
ቀኖና ያጀበው አርሟዊ ቀልብሽ
ድገንቱን ተሰቦኝ በመለኮት ኃይልሽ
ሁሉን ነገር ትቼ ሁሉን ነገር ሆንኩሽ

ለምን እዳትይኝ
ስታብጂኝ አበድኩሽ ።
እ............ህ............ህ
.
.
.
ተጻፈ:-06/06/2012 ዓ.ም

@getem
@getem
@getem
1
..........በትዝታዬ ስም ......
ይህን ህዝብ አውቀዋለው
ያከበረኝ የተቀበለኝ የመገበኝ እና የተንከባከበኝ ነው
ይኛውን አላውቀውም
የናቀኝ ያሳደደኝ ያስራበኝ እና ያንገላታኝ ነው
በማውቃት የልደት እና የትንሳዬ ትዝታዬ እምላለው
ያኛው
ከደጉ አለማደጉን
ከቀናው አለመዋሉን
በማውቃት ሸግዬ ትዝታዬ ስም እምላለው
ደግሞም ሳስታውሰው
የልደት ቀን ድግስ እንግድነቴን
ያከበረልኝ ይህ ህዝብ
የአምላክ ፍቅር ለብሶ
ቋንቋዬን ሊናገር ፍርሀቱን ጥሶ
በቀረበኝ ቁጥር ቀርቤው ወድጄዋለው
ደግሞ በትንሳዬው
ኮሾኮሾታ የገደለብኝን የመዋደድ ጥበብ
በዛ በሀሴት ለት
እንደ እህት አይቶ
ሲያከብረኝ እንደ እናት ለይቶ
ሊቀርበኝ ያቀረበኝን ይህን ህዝብ አውቀዋለው

ልቡ ገራገር ነው
የትኩስ ጥጥ ውበት በላዩ የደፋ
ቃላቱ ቁጥብ ነው
ያልፈራ ያልደፈረ ለማንም ያልከፋ
ሀሳቡ ግልፅ ነው
ሊገፋኝ የጠበበ ሊወደኝ የሰፋ
ይህን ህዝብ አውቀዋለው
እርሱ ጠምጦት እኔን አጠጥቷል
ማዕዱን አብልቶ የሚበላው አቷል
ይህ ህዝብ
የፍቅር ልደት ነው
የሩህሩህ ትንሳኤ
ባለቸኝ ሸግዬ ትዝታ እምላለው
ይህ ይህዝብ
እረፍትን የሚወድ
ከእውነት የሚወለድ
ይህ ህዝብ
ከሰላም ነው።

,,,,,ርብቃ ሲሳይ...


@getem
@getem
@getem
👍1
Audio
# _ያማል
(ገጣሚ ሰለሞን ሳህለ)

@getem
@getem
@getem
👍1
ቀርቼ ከ........

መኖርስ ኖሪያለሁ ሁሉንም አይቼ
ከፅድቁም ከርኩሱም ሄደዋል እግሮቼ
ፍቅርንም ጥላቻን ሁሉንም ጎብኝቼ
በሁለቱም ዛቢያ ሳንዟብብ ከርሜ
ከአንደኛው ስሞላ ከሌላኛው ስጎል
ከጎደለው ስዉል ከሞላዉ ሳቃልል
ከዚህም ከዛም ሳልሆን ቀረሁኝ ከመሀል

(እምነት ዋለልኝ)


@getem
@getem
@getem
👍1
🌹ካገባች በኋላ

ሌላ ወንድ አቀፋት የሚል መርዶ ሽሽት
ሌላ ሴት እያቀፍኩ በያንዳንዷ ምሽት
እሷ ናት እላለሁ
(የኔ እብደት ሲገርመኝ ይባስ የሴቶቹ)
ፍቅር የሰለቻቸው ፍቅርን የሰለቹ
እሷ ናችሁ ስላልኩ "እሷ ነን" እያሉ
እኔ እንዳነሳቸው ራሳቸውን ጣሉ


(አሌክስ አብርሀም)


@getem
@getem
@getem
❤️ለትውስታ

ተላለፉ ሲለን
**

ከመረዋው ውግረት
ከቃጭሉ ዋይታ እኩል ብንሰማም
በአንድ ደውል ድምፅ
ግለ ህሊናችን አንድ ላይ ቢደቃም
ተላለፉ ሲለን
ፊትና ኃላ እንጂ እኩል አንነቃም።

ይስማዕከ ወርቁ
ከ "የወንድ ምጥ" የግጥም መድብል


@getem
@getem
@beppa_19
ከስካሩ ጀርባ

በጌሾና በብቅል ከዛለ ሰውነት
ከደከመ ምላስ በመቆም ለእውነት
ከኮልታፋው አፍ ውስጥ ምራቅ ከመረረው
ከሰከረ ሰው ነው ንፁህ ዕውነት ያለው!

ተረት እንደሆነው ተውሶ ከአበው ቃል
ሆድ ያባውነን ሁሉ ብቅል ያወጣዋል
ከሰካራም ሃሳብ ከስካሩ ማህደር
እኔ የተረዳሁት ኅቡዕ ቁምነገር
በገፈ ይጠጣ ሁሉም በገፋ ይስከር
ለእውነት የምትቆም ሀገር ለመፍጠር!

@Eromaa
የካቲት 2012

@getem
@getem
@getem
የፍቅር ፀብ
( በላይ በቀለ ወያ )

ባብሮነታችን ውስጥ
ጥላቻ ባይኖርም - መናናቅ ነበረ
በመናናቃችን
መለያየት መጣ - አብሮ መኖር ቀረ
አብሮ መብላት ቀረ
አብሮ መዋል ቀረ
አብሮ ማደር ቀረ
ቀረ
ቀረ
ቀረ
ሁሉም ነገር ሲቀር - ናፍቆት ተጀመረ
በናፈቅሽኝ ጊዜ - እንዲህ ስል ነበረ
እንኳን ተለያየን - እንኳን አብረን በላን
እንኳንም ናፈቅሽኝ - ፍቅር ነው ያጣለን፡፡
ባብሮነታችን ልክ
መናናቅ ልብ ላይ - ያኔ የተሰቀለ
አሁን የሚታየኝ
ናፍቆት የምንለው - ናፋቂ ፍቅር አለ፡፡
እንኳን ተለያየን!

( በላይ በቀለ ወያ )

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️

@getem
@getem
@getem
👍1