#አያስታውቅም_ወይ ❓❓❓
በከረረ ጥፊ ፥ ጆሮዬ ሲናጋ
በቡጢና ጡጫ ፥ ገላዬ ሲለጋ
በበላዬ ሰፍረሽ ፥ ልክ እንደ ግመሬ
መላወሻ ባጣ ፥ መሬት ተዘርሬ
#ኡ.... #ኡ.....ብዬ ጮኬ
ጎረቤት አውኬ
በሰለለ ድምፄ የተደናገጡ
#ተግተልትለው መጡ
ከወረደው መአት ፥ ከጭን ሰው ሊያወጡ
ከመቅፅበት ግና ፥ ቤታችን ሲደርሱ
ገላዬን አሳፍሮ ፥ገላሽ መገንደሱ
ከበላይሽ ሆኜ ፥ ቢማትሩ ግዜ
#በእግዜር ተዋት አሉኝ
#ማሪው እንደማለት
ተራዱኝ ያልኳቸው ፥ ቦታዬን በማየት
ዳሩ...ምን ያድርጉ
ባይገባቸው እንጂ ፥ ቦታዬና ቦታሽ
ያስታውቅ ነበር ፥ አንቺ እንዳልተመታሽ ።
#ተበላው ( 😔😔😔 )
#አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
✍ @Abr_sh
@getem
@getem
በከረረ ጥፊ ፥ ጆሮዬ ሲናጋ
በቡጢና ጡጫ ፥ ገላዬ ሲለጋ
በበላዬ ሰፍረሽ ፥ ልክ እንደ ግመሬ
መላወሻ ባጣ ፥ መሬት ተዘርሬ
#ኡ.... #ኡ.....ብዬ ጮኬ
ጎረቤት አውኬ
በሰለለ ድምፄ የተደናገጡ
#ተግተልትለው መጡ
ከወረደው መአት ፥ ከጭን ሰው ሊያወጡ
ከመቅፅበት ግና ፥ ቤታችን ሲደርሱ
ገላዬን አሳፍሮ ፥ገላሽ መገንደሱ
ከበላይሽ ሆኜ ፥ ቢማትሩ ግዜ
#በእግዜር ተዋት አሉኝ
#ማሪው እንደማለት
ተራዱኝ ያልኳቸው ፥ ቦታዬን በማየት
ዳሩ...ምን ያድርጉ
ባይገባቸው እንጂ ፥ ቦታዬና ቦታሽ
ያስታውቅ ነበር ፥ አንቺ እንዳልተመታሽ ።
#ተበላው ( 😔😔😔 )
#አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
✍ @Abr_sh
@getem
@getem
#የስሌት #ጋብቻ
#አንቺ
ሽማግሌ አዘጋጅ ብለሽ ተናግረሻል
ምን አለው ይሉኛል ብለሽ ተጨንቀሻል
#እኔ
ከቀየው መርጬ
በቂ ሽማግሌ አዘጋጅቻለሁ
የሌለኝ ነገር
ለራሴ አለኝ ብዬ በቃል ሸምድጃለሁ
#እነሱ
ቤተዘመድ መጥቶ
ምን አለው ለማለት ማልዶ ይሰለፋል
ሽማግሌ ከቦ
ምን አለው ለሚባል
የወላጅ ጥያቄ የሐሰት መልስ ይፅፋል
#ውዴ #አትጨነቂ
ያንቺ ብቻ አይደለም የሀገር ነው ችግሩ
እኛም ቤት ብትመጪ ይሔው ነው ነገሩ
#አምና
የታናሽ እህቴ
የልጅነት ፍቅሯ አመት በአል አስታኮ
በፍቅር መርቀን
ፈቅደን እንድንሰጠው ሽማግሌ ልኮ
#መልስ #ሲጠባበቅ
በዚህ ወገን ሆኜ እኔም ጠይቄያለሁ
ማይደርስብኝ መስሎኝ ምን አለው ብያለሁ
በሴት ወገን ስንሆን የወንዱን ባናውቅም
ምን አለው ተብሎ ሰው አይጠየቅም
ሀቅ ተዟዙሮ
ቦታ ተቀያይሮ
የትናንት ተቀባይ ከነገ ወዲያ ይልካል
በሴቷ ጠይቆ በወንድ ይጠየቃል
ሸፋፍነነው እንጂ
ደፍረን ከጠራነው ነገሩ ያሳስባል
በንግድ አጠያየቅ
ምን አለው አይደለም ስንት አለው ነው ሚባል
ባንክ ቤት ስንት አለው በጥሬው ያኖረው
ስንት መኪና አለው የሚያሽከረክረው
ስንት ካሬ መሬት ካርታ የወጣለት
ስንት ክፍል ቪላ የተንጣለለለት
በልጅ የደም ቀለም የሌለንን ስንስል
ልጅ የምንድር ሳይሆን ገዢ ነው ምንመስል
የመመኘት ቀመር
የማዟዟር ብዜት በዘመን ሲጣፋ
ምን አለው ነው እንጂ
ከዬት አመጣው የሚል ሽማግሌ ጠፋ
#እኔ #ምለው ?
የማካፈል ስሌት ዞሮ የመጣ ‘ለት
ምን ያህል ይዘናል ምን አለው ለማለት
#ይልቅ
እግዚአብሔር አድሎት
በጥላቻ ዘመን የሰው ልጅ ሲፋቀር
አፍቃሪ ልብና
ሁሉም ነገር አለው ከሀብት በስተቀር
ሀቁን እያወቅነው ውጠን ከማባበል
ምን አለውን ትተን ምን የለውም እንበል
=====||=====
✍ከሙሉቀን ሰ•
@getem
@getem
@beppa_19
#አንቺ
ሽማግሌ አዘጋጅ ብለሽ ተናግረሻል
ምን አለው ይሉኛል ብለሽ ተጨንቀሻል
#እኔ
ከቀየው መርጬ
በቂ ሽማግሌ አዘጋጅቻለሁ
የሌለኝ ነገር
ለራሴ አለኝ ብዬ በቃል ሸምድጃለሁ
#እነሱ
ቤተዘመድ መጥቶ
ምን አለው ለማለት ማልዶ ይሰለፋል
ሽማግሌ ከቦ
ምን አለው ለሚባል
የወላጅ ጥያቄ የሐሰት መልስ ይፅፋል
#ውዴ #አትጨነቂ
ያንቺ ብቻ አይደለም የሀገር ነው ችግሩ
እኛም ቤት ብትመጪ ይሔው ነው ነገሩ
#አምና
የታናሽ እህቴ
የልጅነት ፍቅሯ አመት በአል አስታኮ
በፍቅር መርቀን
ፈቅደን እንድንሰጠው ሽማግሌ ልኮ
#መልስ #ሲጠባበቅ
በዚህ ወገን ሆኜ እኔም ጠይቄያለሁ
ማይደርስብኝ መስሎኝ ምን አለው ብያለሁ
በሴት ወገን ስንሆን የወንዱን ባናውቅም
ምን አለው ተብሎ ሰው አይጠየቅም
ሀቅ ተዟዙሮ
ቦታ ተቀያይሮ
የትናንት ተቀባይ ከነገ ወዲያ ይልካል
በሴቷ ጠይቆ በወንድ ይጠየቃል
ሸፋፍነነው እንጂ
ደፍረን ከጠራነው ነገሩ ያሳስባል
በንግድ አጠያየቅ
ምን አለው አይደለም ስንት አለው ነው ሚባል
ባንክ ቤት ስንት አለው በጥሬው ያኖረው
ስንት መኪና አለው የሚያሽከረክረው
ስንት ካሬ መሬት ካርታ የወጣለት
ስንት ክፍል ቪላ የተንጣለለለት
በልጅ የደም ቀለም የሌለንን ስንስል
ልጅ የምንድር ሳይሆን ገዢ ነው ምንመስል
የመመኘት ቀመር
የማዟዟር ብዜት በዘመን ሲጣፋ
ምን አለው ነው እንጂ
ከዬት አመጣው የሚል ሽማግሌ ጠፋ
#እኔ #ምለው ?
የማካፈል ስሌት ዞሮ የመጣ ‘ለት
ምን ያህል ይዘናል ምን አለው ለማለት
#ይልቅ
እግዚአብሔር አድሎት
በጥላቻ ዘመን የሰው ልጅ ሲፋቀር
አፍቃሪ ልብና
ሁሉም ነገር አለው ከሀብት በስተቀር
ሀቁን እያወቅነው ውጠን ከማባበል
ምን አለውን ትተን ምን የለውም እንበል
=====||=====
✍ከሙሉቀን ሰ•
@getem
@getem
@beppa_19
❤1
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
(በjo)
በፀጥታ ላይ ትዝታ
በትዝታ ላይ መኝታ...
በነበር ላይ እንሆናለን
በባዶ ሜዳ እንከብራለን።
አይ እኛ........
ፀጥ ብሎ መኝታ
ከዛም ተስፋ ማድረግ፤
እረብሻን ቀስቅሶ
በአንዱ እንባ ላይ ማደግ፤
ነበር እንጂ ያለን
መች ደረሰ ላሁን፤
ቀደምት ታሪካችን
መች ጠቀመን አሁን፤
አዎን መች ጠፍቶናል.........
ደግሞም ተስፋ ማድረግ
አልጋ ላይ ተኝቶ፤
የህልም እንጀራን ማኘክ።
ግና ከዚህ ሁሉ......
ነበር ሳይሆን ለሁን፣
ግዜው ክፉ ሳይሆን፣
ፀሀይቱም ሳትጠልቅ፣
ጨረቃም ሳትለቅ........
በድቅድቅ ጨለማ
እንደሚበራ ኮከብ
አሁን ነው መፈንጠቅ.......
✍ተፃፈ በ @Mak_bale
29.5.2012
@getem
@getem
@getem
(በjo)
በፀጥታ ላይ ትዝታ
በትዝታ ላይ መኝታ...
በነበር ላይ እንሆናለን
በባዶ ሜዳ እንከብራለን።
አይ እኛ........
ፀጥ ብሎ መኝታ
ከዛም ተስፋ ማድረግ፤
እረብሻን ቀስቅሶ
በአንዱ እንባ ላይ ማደግ፤
ነበር እንጂ ያለን
መች ደረሰ ላሁን፤
ቀደምት ታሪካችን
መች ጠቀመን አሁን፤
አዎን መች ጠፍቶናል.........
ደግሞም ተስፋ ማድረግ
አልጋ ላይ ተኝቶ፤
የህልም እንጀራን ማኘክ።
ግና ከዚህ ሁሉ......
ነበር ሳይሆን ለሁን፣
ግዜው ክፉ ሳይሆን፣
ፀሀይቱም ሳትጠልቅ፣
ጨረቃም ሳትለቅ........
በድቅድቅ ጨለማ
እንደሚበራ ኮከብ
አሁን ነው መፈንጠቅ.......
✍ተፃፈ በ @Mak_bale
29.5.2012
@getem
@getem
@getem
👍1
#ሹ ክ ሹ ክ ታ
እንቺ
የኔ ኮልታፋ
በለሌሊቱ ሰማይ
ከፀጥታው በላይ
በመሸው አለም ላይ
የኛ ሹክሹክታ ነው ሚሰማው ባለም ላይ
በጣፋጭ አንደበት
በኮልታፋው አፍሽ ስትንሾካሾኪ
#አፈቅልሀለሁ ብለሽ ፍቅርሽን ስትሰብኪ
ሌሊቴን በኮልታፋው አፍሽ ከቶ ስታፈኪ
ሰይጣን ተላካፊው ከቶ ግርም ሲለው
ደግሞ በዚ ምሽት ደሞ የምን ፍቅር ነው
ጥያቄ ሲያበዛ መግቢያ መውጫው
ሰይጣንስ ቢጠፋው
ሚለክፈውን ጉብል አንቺ ስታስቆሚው
#አፈቅልሀለሁ ስትይኝ
ከቶ ሚቃጠለው
ከፀበል ቀጥሎ የኔ ኮልተረፋ ናት ለሰይጣን መፍትሄው
አቦ ተኮላተፊልኝ
አፍሽ ሲኮላተፍ
የኔ ልብ ይመታል
ቃል ስታጣምሚ
ሀሴቴ ይመጣል
ወልከፍ ስትይልኝ
ጥርሴ ይፈለቀለቃል
የማላቀው ስሜት እንዲህ ሹክ በላት ይለኛል
ፍቅሌ
አቅልሻለሁ ሁሌ
ተኮላተፍኩ እንዴ
አወየው እድሌ
አንደበትሽ
ከኔ ስለሆነ ነው
አሁንማ
ትናጋሽ የኔም ነው
✍ተፃፈ በብላቴናው ብዕር
@getem
@getem
@getem
@getem
እንቺ
የኔ ኮልታፋ
በለሌሊቱ ሰማይ
ከፀጥታው በላይ
በመሸው አለም ላይ
የኛ ሹክሹክታ ነው ሚሰማው ባለም ላይ
በጣፋጭ አንደበት
በኮልታፋው አፍሽ ስትንሾካሾኪ
#አፈቅልሀለሁ ብለሽ ፍቅርሽን ስትሰብኪ
ሌሊቴን በኮልታፋው አፍሽ ከቶ ስታፈኪ
ሰይጣን ተላካፊው ከቶ ግርም ሲለው
ደግሞ በዚ ምሽት ደሞ የምን ፍቅር ነው
ጥያቄ ሲያበዛ መግቢያ መውጫው
ሰይጣንስ ቢጠፋው
ሚለክፈውን ጉብል አንቺ ስታስቆሚው
#አፈቅልሀለሁ ስትይኝ
ከቶ ሚቃጠለው
ከፀበል ቀጥሎ የኔ ኮልተረፋ ናት ለሰይጣን መፍትሄው
አቦ ተኮላተፊልኝ
አፍሽ ሲኮላተፍ
የኔ ልብ ይመታል
ቃል ስታጣምሚ
ሀሴቴ ይመጣል
ወልከፍ ስትይልኝ
ጥርሴ ይፈለቀለቃል
የማላቀው ስሜት እንዲህ ሹክ በላት ይለኛል
ፍቅሌ
አቅልሻለሁ ሁሌ
ተኮላተፍኩ እንዴ
አወየው እድሌ
አንደበትሽ
ከኔ ስለሆነ ነው
አሁንማ
ትናጋሽ የኔም ነው
✍ተፃፈ በብላቴናው ብዕር
@getem
@getem
@getem
@getem
አጥብቆ ተመልካች
/በዕውቀቱ ስዩም/
*--------------*
አይሽ አይሽና
አበባ ከንፈሯ
አበባ ከንፈሯ
ከንፈሯ እንዴት ያምራል!
እንኳን የኔን ገላ ንቦችን ይጠራል
እያልኩ አስባልሁ
ከንፈርሽን አያለሁ።
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አበባ ከንፈሯ
አበባ ከንፈሯ
ትንሽ አብጧል መሰል
ማነው የቀጠፋት?
ተስማ ነውንጂ መቼም ንብ አይነድፋት
እያልኩ አስባለሁ
ከንፈርሽን አያለሁ።
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይደለም ከንፈሯ
አይኔ ነው ያበጠው
አይቶ ያታለለ
ከንፈሯን ያሳየኝ ቅል እያሳከለ
እያልኩ አስባለሁ
ከንፈርሽን አያለሁ።
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይኔን እንቃለሁ
ከፊቴ የማየው
ከንፈር ይሁን ግንባር
እንዴት ብዬ አውቃለሁ?
እያልኩ አስባለሁ።
~~~~~~~~~~~
@getem
@getem
@beppa_19
/በዕውቀቱ ስዩም/
*--------------*
አይሽ አይሽና
አበባ ከንፈሯ
አበባ ከንፈሯ
ከንፈሯ እንዴት ያምራል!
እንኳን የኔን ገላ ንቦችን ይጠራል
እያልኩ አስባልሁ
ከንፈርሽን አያለሁ።
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አበባ ከንፈሯ
አበባ ከንፈሯ
ትንሽ አብጧል መሰል
ማነው የቀጠፋት?
ተስማ ነውንጂ መቼም ንብ አይነድፋት
እያልኩ አስባለሁ
ከንፈርሽን አያለሁ።
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይደለም ከንፈሯ
አይኔ ነው ያበጠው
አይቶ ያታለለ
ከንፈሯን ያሳየኝ ቅል እያሳከለ
እያልኩ አስባለሁ
ከንፈርሽን አያለሁ።
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይሽ አይሽና
አይኔን እንቃለሁ
ከፊቴ የማየው
ከንፈር ይሁን ግንባር
እንዴት ብዬ አውቃለሁ?
እያልኩ አስባለሁ።
~~~~~~~~~~~
@getem
@getem
@beppa_19
❤1
በግራሽ -እቀፊኝ
== == == == ጋሻው ለኔ
ውዴ ሆይ ነይልኝ እንኩዋን ደህና መጣሽ
በጣም በርዶኝ ነበር ካጠገቤ ሳጣሽ
በይ እቅፍ አድርጊኝ ግራ እጅሽን ዘርጊ
ባይሆን ቀኝ እጅሽን ትንሽ ወደዛ አርጊ
ኡፍፍ...
በቀኝ መታቀፍ
እንዴት ነው የሚቀፍ?
እባክሽን ውዴ.....ያልኩሽን ሰምተሻል?
ቀኝሽን አርቂው ግራሽ ነው የሚሻል
በቀኝ እጅሽማ
ለስንቱ ጎረምሳ ሰላምታ ሰጥተሻል
የሰው ከጃይ ሁሉ የዘየረሽ መስሎ
ሲያልፍ አይቸዋለሁ ከመዳፍሽ መሃል ምኞት ቀልቡን ጥሎ::
ምን ይህ ብቻ ውዴ?
ከታሪክ ገፅ ላይ ብታተኩሪ አንዴ
ስንት ገራሚ እውነት ታገኝ የለም እንዴ
የያኔው ባለቀን :ለምዶበት ማቀንቀን
በቀኝ እጄ ሳቅፍህ _
መንገድህ ይቀናል እያለ ሲያሞቀኝ:
ውሎ ሳያድር ነው በቀኝ ሽብር መላ በወጠምሻ ክንዱ ጎኔን ያደቀቀኝ:
ይሄኛውስ ቢሆን በእሱ የተተካው
ላክምልህ በሚል ከንቱ ፖለቲካው
ለስንቴ መሰለሽ_
እየተደበቀ ቁስሌን የሚነካው
ታዲያ በዚህ ዘመን_
እነዚህን ሁሉ የቀኝ አቀንቃኞች ከልቡ እያመነ
በተናገሩት ቃል እየተማመነ
ከቤቱ የወጣ ቀኝ አውለኝ እያለ
ከአውላላ ሜዳ ላይ ቀረ እንደዋለለ::
እናልሽ ፍቅሬ ሆይ ይሄ ተሞክሮ
ልቤ ውስጥ ተቁዋጥሮ
እንኩዋንስ በቀኝ እጅ ልቀፍህ ተብዬ
"ቀ" የሚባል ፊደል ሲያልፍ በጆሮዬ
ቀማኛ
ቀበኛ
ቀጣፊ
ቀሳፊ...
የሚል የ"ቀ" ውላጅ
የክፉ አሳብ ጉማጅ
ባሳቤ እየመጣ
ጤናና ሰላሜን ባንዴ ነው የማጣ::
ስለዚህ ህይወቴ ከገባሽ ጭንቀቴ
በግራሽ እቀፊኝ አድምጭኝ በሞቴ
በግራ ጡትሽ ስር ካለው ትንሽ ኮዳ
ልብ የሚሉት ጉዋዳ:
እኔ ጠጋ ስልሽ ነፍሴ ከነፍስሽ ጋር
ሽርክና መፍጠርዋን በድንገት ሲረዳ:
ምን ያህል ጋሎን ደም ባንዴ እንደሚቀዳ:
የፍቅሬ ማእበል የልብሽን ባህር ስንቴ እንደሚንጠው:
ሽጉጥ ልበልና በደንብ ላዳምጠው:
ከግራ አጥንቶችሽ እስኪ ልበል ልክክ
ለመቁጠር እንድችል የትርታሽን ልክ!!
ትር… ትር… ትር ……………
@getem
@getem
@beppa_19
== == == == ጋሻው ለኔ
ውዴ ሆይ ነይልኝ እንኩዋን ደህና መጣሽ
በጣም በርዶኝ ነበር ካጠገቤ ሳጣሽ
በይ እቅፍ አድርጊኝ ግራ እጅሽን ዘርጊ
ባይሆን ቀኝ እጅሽን ትንሽ ወደዛ አርጊ
ኡፍፍ...
በቀኝ መታቀፍ
እንዴት ነው የሚቀፍ?
እባክሽን ውዴ.....ያልኩሽን ሰምተሻል?
ቀኝሽን አርቂው ግራሽ ነው የሚሻል
በቀኝ እጅሽማ
ለስንቱ ጎረምሳ ሰላምታ ሰጥተሻል
የሰው ከጃይ ሁሉ የዘየረሽ መስሎ
ሲያልፍ አይቸዋለሁ ከመዳፍሽ መሃል ምኞት ቀልቡን ጥሎ::
ምን ይህ ብቻ ውዴ?
ከታሪክ ገፅ ላይ ብታተኩሪ አንዴ
ስንት ገራሚ እውነት ታገኝ የለም እንዴ
የያኔው ባለቀን :ለምዶበት ማቀንቀን
በቀኝ እጄ ሳቅፍህ _
መንገድህ ይቀናል እያለ ሲያሞቀኝ:
ውሎ ሳያድር ነው በቀኝ ሽብር መላ በወጠምሻ ክንዱ ጎኔን ያደቀቀኝ:
ይሄኛውስ ቢሆን በእሱ የተተካው
ላክምልህ በሚል ከንቱ ፖለቲካው
ለስንቴ መሰለሽ_
እየተደበቀ ቁስሌን የሚነካው
ታዲያ በዚህ ዘመን_
እነዚህን ሁሉ የቀኝ አቀንቃኞች ከልቡ እያመነ
በተናገሩት ቃል እየተማመነ
ከቤቱ የወጣ ቀኝ አውለኝ እያለ
ከአውላላ ሜዳ ላይ ቀረ እንደዋለለ::
እናልሽ ፍቅሬ ሆይ ይሄ ተሞክሮ
ልቤ ውስጥ ተቁዋጥሮ
እንኩዋንስ በቀኝ እጅ ልቀፍህ ተብዬ
"ቀ" የሚባል ፊደል ሲያልፍ በጆሮዬ
ቀማኛ
ቀበኛ
ቀጣፊ
ቀሳፊ...
የሚል የ"ቀ" ውላጅ
የክፉ አሳብ ጉማጅ
ባሳቤ እየመጣ
ጤናና ሰላሜን ባንዴ ነው የማጣ::
ስለዚህ ህይወቴ ከገባሽ ጭንቀቴ
በግራሽ እቀፊኝ አድምጭኝ በሞቴ
በግራ ጡትሽ ስር ካለው ትንሽ ኮዳ
ልብ የሚሉት ጉዋዳ:
እኔ ጠጋ ስልሽ ነፍሴ ከነፍስሽ ጋር
ሽርክና መፍጠርዋን በድንገት ሲረዳ:
ምን ያህል ጋሎን ደም ባንዴ እንደሚቀዳ:
የፍቅሬ ማእበል የልብሽን ባህር ስንቴ እንደሚንጠው:
ሽጉጥ ልበልና በደንብ ላዳምጠው:
ከግራ አጥንቶችሽ እስኪ ልበል ልክክ
ለመቁጠር እንድችል የትርታሽን ልክ!!
ትር… ትር… ትር ……………
@getem
@getem
@beppa_19
👍1
" ብልጡ ፍቅርሽ ሲያጃጅለኝ የጫርኩት"
(መልአኩ ስብሐት ባይህ)
**************************
የውበት ዳርቻ
የአድማሷን መባቻ።
አንቺን የእኔን ጠሀይ
የተድላዬን ሰማይ።
ልስልሽ ፈለጌ
ምስልሽን አጣሁት
ከምስሌ አድርጌ።
ከስብዕናሽ ጠለል ከሀሳብሽ ከፍታ
አየሁኝ በሳቅሽ ጨረቃ ተከፍታ።
ጨረቃ ጨረቃ
ጨረቃ ጨረቃ
ያቺ ድንቡል ቦቃ
አንቺ ስትቦዢ ይሆን ምትነቃ?
አንቺ እንደሁ አትቦዢ
ከቶ አደበዝዢ
በመውደድሽ ሸጠሽ ታደርጊያለሽ ገዢ።
ያውም በሠላሳ
ያውም በሠላሳ
ክደሸ ስታበቂኝ ምንም እማልመስልሽ
በገደልሽኝ ቁጥር ሳትሞች ምሞትልሽ
በገፋሽኝ ቁጥር ሳትወድቂ ማነሳሽ
በሸጥሽኝ መጠን ልክ ለመክሰር ምገዛሽ
ይሁዳ ነሽ አንቺ እኔ ደግሞ ጌታሽ።
.
.
.
ተጻፈ:-፳፩/፱/፳፻፲፩ ዓ.ም
@getem
@getem
@poem_with_mela
(መልአኩ ስብሐት ባይህ)
**************************
የውበት ዳርቻ
የአድማሷን መባቻ።
አንቺን የእኔን ጠሀይ
የተድላዬን ሰማይ።
ልስልሽ ፈለጌ
ምስልሽን አጣሁት
ከምስሌ አድርጌ።
ከስብዕናሽ ጠለል ከሀሳብሽ ከፍታ
አየሁኝ በሳቅሽ ጨረቃ ተከፍታ።
ጨረቃ ጨረቃ
ጨረቃ ጨረቃ
ያቺ ድንቡል ቦቃ
አንቺ ስትቦዢ ይሆን ምትነቃ?
አንቺ እንደሁ አትቦዢ
ከቶ አደበዝዢ
በመውደድሽ ሸጠሽ ታደርጊያለሽ ገዢ።
ያውም በሠላሳ
ያውም በሠላሳ
ክደሸ ስታበቂኝ ምንም እማልመስልሽ
በገደልሽኝ ቁጥር ሳትሞች ምሞትልሽ
በገፋሽኝ ቁጥር ሳትወድቂ ማነሳሽ
በሸጥሽኝ መጠን ልክ ለመክሰር ምገዛሽ
ይሁዳ ነሽ አንቺ እኔ ደግሞ ጌታሽ።
.
.
.
ተጻፈ:-፳፩/፱/፳፻፲፩ ዓ.ም
@getem
@getem
@poem_with_mela
የውልሽ አለሜ
በህይወት ሰንሰለት፣
ከእለታት በአንድ ቀን
ከድኩም ልቤ ጋር ፣
ከደጅ ተቀምጠን
ጨረቃን እያየን፣
ኮኮብ ስንቆጥር
ከሰማይ ሰሌዳ
የተሳለን ውበት ፣
ድምቀት ስንቀምር
ተገልፃልን ነበር ፣
አንድ ግሩም ታምር
ታምሩ እንዲህ ነበር፣
የወረደው ሚስጥር
ከአፈቃሪ ልቤ ጋር፣
ኩኩብ ስንቀጥር
ደምቃ በወጣችው፣
በጠፏ ጨረቀ፣ ውበት ተደንቄ
ከገሀዱ አለም ፣
በምናቡ ሀሳብ ፣ ወዲያ ተደብቄ
በአንቺ ርሀብ ፉርጎ
በትዝታ ሀዲድ ፣በመናፈቅ ባቡር ፣
ከህላዌው ደጀፍ
ከሰማየ ሰማይ ፣ ከልዕሉ መንበር
ከደመናው በላይ ፣
ከመናፍስቱ ዘንድ ፣ወዲይ ሂጄ ነበር
በአማልክቱ ዓለም
በሰማያት ጉዞ ፣በደመናው ፈረስ
………ታድያ እዛ ስደርስ
ከአርያም እልፍኝ
.
.
.
.
.
.
።
።
።
።
።
።
።
።
።
።
።
።
።
.
በቅርቡ ይጠብቁ በማለዳ ስንኝ የግጥም መድብል
Join and share..........👇👇
@getem
@getem
@getem
@getem
በህይወት ሰንሰለት፣
ከእለታት በአንድ ቀን
ከድኩም ልቤ ጋር ፣
ከደጅ ተቀምጠን
ጨረቃን እያየን፣
ኮኮብ ስንቆጥር
ከሰማይ ሰሌዳ
የተሳለን ውበት ፣
ድምቀት ስንቀምር
ተገልፃልን ነበር ፣
አንድ ግሩም ታምር
ታምሩ እንዲህ ነበር፣
የወረደው ሚስጥር
ከአፈቃሪ ልቤ ጋር፣
ኩኩብ ስንቀጥር
ደምቃ በወጣችው፣
በጠፏ ጨረቀ፣ ውበት ተደንቄ
ከገሀዱ አለም ፣
በምናቡ ሀሳብ ፣ ወዲያ ተደብቄ
በአንቺ ርሀብ ፉርጎ
በትዝታ ሀዲድ ፣በመናፈቅ ባቡር ፣
ከህላዌው ደጀፍ
ከሰማየ ሰማይ ፣ ከልዕሉ መንበር
ከደመናው በላይ ፣
ከመናፍስቱ ዘንድ ፣ወዲይ ሂጄ ነበር
በአማልክቱ ዓለም
በሰማያት ጉዞ ፣በደመናው ፈረስ
………ታድያ እዛ ስደርስ
ከአርያም እልፍኝ
.
.
.
.
.
.
።
።
።
።
።
።
።
።
።
።
።
።
።
.
በቅርቡ ይጠብቁ በማለዳ ስንኝ የግጥም መድብል
Join and share..........👇👇
@getem
@getem
@getem
@getem
ቴዲ /የጠረፍ
እነሱ /ይላሉ/:- ቃል አዉጣ ....ቃል አዉጣ
.....እኔ ያንቺ ድንጉጥ ከየት ብዬ ላምጣ
እነሱ/ይላሉ/ :- ተናገር ስለ እምነት
እኔ ያንቺ አገልጋይ ቡዙ ሰዉ አያለዉ.
ሳስስ ያንቺን አይነት
እነሱ /ይላሉ/:- አስተምር በመንፈስ
እኔ ተለጉሜ አንቺን አስባለዉ
ካለሁበት ስርቅ ከቆኩምኩበት ስፈርስ
.........
እንዲዉ ሳይገናኝ የአማኙ መንጋ
እነሱ ለጮሁት ዝም ያልኩት ሰዉዬ ልሳኔ ተዘጋ.....
/በጌታ ስም/
🤦♂🤦♂🤦♂🤦♂🤦♂🤦♂
....... ብቻ.........
ያየዉሽን ያህል
ያሰብኩሽን ያህል ልነካሽ ወደ ላይ በተሳብኩኝ ቁጥር
እንጃባቱ ሰይጣን ይወድቃል እግሬ ስር
/ወጋዉት/
........ብቻ .....
የናፍቆቴን ያህል
የፍቅርሽን ያህል እያየዉሽ ስስቅ
የፃድቃን አይነቶች አዳራሹን ጥቅጥቅ
/ አንድ ሰዉ ጮሆ አሜን ይበል እስኪ /
.......................
እዚህ
ከልቤ ክፋይ ዉስጥ ጌታ እንቺን ፅፎ
ድዊ እጥል ጀመር ነገሬ ሁሉ ላይ አይንሽ ተለጥፎ
.......
የአይንሽ አኳኃን .... አነሳስ አጣጣል
እመኚዉ ፀጋ ነዉ ታሪክ ይለዉጣል
እርኩስ መናፍስትን ይገለባብጣል
በእየሱስ ስም
@a0Teddy✍✍✍ ቴዲ/ የጠረፍ
@getem
@getem
@getem
እነሱ /ይላሉ/:- ቃል አዉጣ ....ቃል አዉጣ
.....እኔ ያንቺ ድንጉጥ ከየት ብዬ ላምጣ
እነሱ/ይላሉ/ :- ተናገር ስለ እምነት
እኔ ያንቺ አገልጋይ ቡዙ ሰዉ አያለዉ.
ሳስስ ያንቺን አይነት
እነሱ /ይላሉ/:- አስተምር በመንፈስ
እኔ ተለጉሜ አንቺን አስባለዉ
ካለሁበት ስርቅ ከቆኩምኩበት ስፈርስ
.........
እንዲዉ ሳይገናኝ የአማኙ መንጋ
እነሱ ለጮሁት ዝም ያልኩት ሰዉዬ ልሳኔ ተዘጋ.....
/በጌታ ስም/
🤦♂🤦♂🤦♂🤦♂🤦♂🤦♂
....... ብቻ.........
ያየዉሽን ያህል
ያሰብኩሽን ያህል ልነካሽ ወደ ላይ በተሳብኩኝ ቁጥር
እንጃባቱ ሰይጣን ይወድቃል እግሬ ስር
/ወጋዉት/
........ብቻ .....
የናፍቆቴን ያህል
የፍቅርሽን ያህል እያየዉሽ ስስቅ
የፃድቃን አይነቶች አዳራሹን ጥቅጥቅ
/ አንድ ሰዉ ጮሆ አሜን ይበል እስኪ /
.......................
እዚህ
ከልቤ ክፋይ ዉስጥ ጌታ እንቺን ፅፎ
ድዊ እጥል ጀመር ነገሬ ሁሉ ላይ አይንሽ ተለጥፎ
.......
የአይንሽ አኳኃን .... አነሳስ አጣጣል
እመኚዉ ፀጋ ነዉ ታሪክ ይለዉጣል
እርኩስ መናፍስትን ይገለባብጣል
በእየሱስ ስም
@a0Teddy✍✍✍ ቴዲ/ የጠረፍ
@getem
@getem
@getem