✤✣ይታይሽ የኔ አለም✣✤
ይታይሽ የኔ አለም
አዎን ተመልከቺ
አስተውይ እናቴ....
የእህቶቼን ሳቅ
የልጆችሽን ድምፅ
ሳጣው ከሰፈሬ።
፨፨፨፨፨፨
አዎን ኢትዮጵያዬ
በወንዞች በሳርሽ
በእርሻ ባፈርሽ
ቦርቀው ያደጉት
እነዛ ልጆችሽ......
ዛሬ ምነው ጠፉ
ደብዛ ተሠወረ
ማን ቀማሽ ከእጆችሽ።
፨፨፨፨፨፨፨
አዎን የኔ ልእልት
የሉም ከቤታቸው
ቀዬ መንደራቸው
ብቻውን ይጮሃል..
እናትም ተጨንቃ
አይኗ አንባን ያነባል።
ህፃናት አጥተዋል
ጡትን ከአፋቸው....
የእናታቸው መጥፋት
እንባ እያስነባቸው።
ያልተዘጋው ማጀት
ዛሬም አፉን ከፍቷል ....
እምዬ ከሌለች
እታአለም ካልመጣች
አሻፈረኝ ብሏል።
፨፨፨፨
እናም እታለሜ
አዎን አስተውዪ
የህዝቦችሽን ግፍ
የአጥፊዎችሽን ደባ ...
የእህቴን በደል
የቀሚሷን እንባ።
አዎን ተመልከቺ
መፍትሔ የሌለው
ጩኸቴን አድምጪ
✣✣✣✣✣
እናም ኢትዮጵያዬ
እስኪ ጠይቂያቸው
ወንዘና ተራራ
አእዋፍ ዛፎቹን ..
ጋራ ሸንተረሩን
መስካመስክ ዋሻውን ..
አይቻለሁ ያለ
ካለ..
የሲቃን ድምፅ
ያደመጠ ...
የሀዘንን እንባ
የጠረገ...
የእምዬን ፍርሀት ተመልክቶ
ለእህቶቹ ተቆርቁሮ
አንደራሱ የታገለ
እስኪ ጠይቂ ካለ !!!!!!
✍ተፃፈ @Mak_bale
23.5.2012
@getem
@getem
@getem
ይታይሽ የኔ አለም
አዎን ተመልከቺ
አስተውይ እናቴ....
የእህቶቼን ሳቅ
የልጆችሽን ድምፅ
ሳጣው ከሰፈሬ።
፨፨፨፨፨፨
አዎን ኢትዮጵያዬ
በወንዞች በሳርሽ
በእርሻ ባፈርሽ
ቦርቀው ያደጉት
እነዛ ልጆችሽ......
ዛሬ ምነው ጠፉ
ደብዛ ተሠወረ
ማን ቀማሽ ከእጆችሽ።
፨፨፨፨፨፨፨
አዎን የኔ ልእልት
የሉም ከቤታቸው
ቀዬ መንደራቸው
ብቻውን ይጮሃል..
እናትም ተጨንቃ
አይኗ አንባን ያነባል።
ህፃናት አጥተዋል
ጡትን ከአፋቸው....
የእናታቸው መጥፋት
እንባ እያስነባቸው።
ያልተዘጋው ማጀት
ዛሬም አፉን ከፍቷል ....
እምዬ ከሌለች
እታአለም ካልመጣች
አሻፈረኝ ብሏል።
፨፨፨፨
እናም እታለሜ
አዎን አስተውዪ
የህዝቦችሽን ግፍ
የአጥፊዎችሽን ደባ ...
የእህቴን በደል
የቀሚሷን እንባ።
አዎን ተመልከቺ
መፍትሔ የሌለው
ጩኸቴን አድምጪ
✣✣✣✣✣
እናም ኢትዮጵያዬ
እስኪ ጠይቂያቸው
ወንዘና ተራራ
አእዋፍ ዛፎቹን ..
ጋራ ሸንተረሩን
መስካመስክ ዋሻውን ..
አይቻለሁ ያለ
ካለ..
የሲቃን ድምፅ
ያደመጠ ...
የሀዘንን እንባ
የጠረገ...
የእምዬን ፍርሀት ተመልክቶ
ለእህቶቹ ተቆርቁሮ
አንደራሱ የታገለ
እስኪ ጠይቂ ካለ !!!!!!
✍ተፃፈ @Mak_bale
23.5.2012
@getem
@getem
@getem
~~የመሔዷ መምጣት~~
"""""""""""""""""""""""""""
በ👉መኮንን አልማው ✍ ተፃፈ👈
''""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ቅርብ ሳለ ፍቅሯ
ሩቅ ሆኖ አዳሯ
የአይኗን ብርሃን በአይኔ ለማየት ጓጉቼ
ገላዋን በጣቴ መዳበስ ሰስቼ
ናፍቆቷን አውርቼ
ነይ ስላት... ነይ ስላት
የመፈለግ ኩራት
ልቧን ስለሞቀው ዝና እየመሠላት
ቆማ ስትወላውል
ጊዜዋን ስትገድል
እንደ ኤሳው በኩር ዕድሏን ለውጣው
መምጣቷን ገድሎ ነው መሔዷ የመጣው!
""""""""""""""""""""/""""'/""""""""'/""""""""""""""""""
..............23/05/2012/ዓ.ም~ሀዋሣ
@getem
@getem
@getem
"""""""""""""""""""""""""""
በ👉መኮንን አልማው ✍ ተፃፈ👈
''""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ቅርብ ሳለ ፍቅሯ
ሩቅ ሆኖ አዳሯ
የአይኗን ብርሃን በአይኔ ለማየት ጓጉቼ
ገላዋን በጣቴ መዳበስ ሰስቼ
ናፍቆቷን አውርቼ
ነይ ስላት... ነይ ስላት
የመፈለግ ኩራት
ልቧን ስለሞቀው ዝና እየመሠላት
ቆማ ስትወላውል
ጊዜዋን ስትገድል
እንደ ኤሳው በኩር ዕድሏን ለውጣው
መምጣቷን ገድሎ ነው መሔዷ የመጣው!
""""""""""""""""""""/""""'/""""""""'/""""""""""""""""""
..............23/05/2012/ዓ.ም~ሀዋሣ
@getem
@getem
@getem
የውጊያ ስልት
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ሙሴ በበትሩ
ፈርኦን በጦሩ
ኤርትራ ባሕር ላይ ፣ ጦርነት ጀመሩ፡፡
።።።።
ሙሴ በበትሩ…
ግዙፍ ባህር ከፍሎ ፣ ህዝቡን አሻገረ
ፈርኦን በጦሩ
ከነ ወታደሩ
ባሕር ሰጥሞ ቀረ፡፡
።።፣፣
ውጊያ የማይችል ሕዝብ
ግዙፍ ባሕር ከፍሎ ፣ በተዓምር ሲሻገር
ሌላ የውጊያ ስልት
ቀይሮ ይመጣል ፣ ቢሰምጥም ወታደር፡፡
እ
ን
ደ
ዚ
ህ
።
የተሻገረ ህዝብ
ለቀሪ መንገዱ
አሳ እያጠመደ ፣ ከባህር ሲያወጣ
የፈርኦን ወታደር
ሞቶ ለመዋጋት
በአሳ ገላ ላይ ፣ እሾህ ሆኖ መጣ!!!
።።።።
።።።፣
"አሳን መብላት
እንዳይወጋህ ፣ በብልሃት!"
@getem
@getem
#jeko
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ሙሴ በበትሩ
ፈርኦን በጦሩ
ኤርትራ ባሕር ላይ ፣ ጦርነት ጀመሩ፡፡
።።።።
ሙሴ በበትሩ…
ግዙፍ ባህር ከፍሎ ፣ ህዝቡን አሻገረ
ፈርኦን በጦሩ
ከነ ወታደሩ
ባሕር ሰጥሞ ቀረ፡፡
።።፣፣
ውጊያ የማይችል ሕዝብ
ግዙፍ ባሕር ከፍሎ ፣ በተዓምር ሲሻገር
ሌላ የውጊያ ስልት
ቀይሮ ይመጣል ፣ ቢሰምጥም ወታደር፡፡
እ
ን
ደ
ዚ
ህ
።
የተሻገረ ህዝብ
ለቀሪ መንገዱ
አሳ እያጠመደ ፣ ከባህር ሲያወጣ
የፈርኦን ወታደር
ሞቶ ለመዋጋት
በአሳ ገላ ላይ ፣ እሾህ ሆኖ መጣ!!!
።።።።
።።።፣
"አሳን መብላት
እንዳይወጋህ ፣ በብልሃት!"
@getem
@getem
#jeko
❤2
IMG_3490.jpg
172 KB
"የወንድ ምጥ ያማል!"
"የወንድ ምጥ ያማል" ብሎ ሲፅፍ አንዱ
"የሴት ልጅ ይብሳል" ብለው ሌሎች ካዱ!
ፃፊውም 'ካጅውም ያው አዳም ነው ወንዱ
በበለስ ፍሬና በሷ የወረዱ, ከዛ የተዋረዱ::
እርሱስ ቀጥ ያለ ነው የርሷ ግን ጠማበት
ግራ ጎን አጥንቷ ቆልመም ያለችበት
ሊያቀናት ቢሞክር 'ምትሰበርበት!
ግን እንዴት ሆኖ ነው የወንድ ምጥ 'ሚብስ?
በየወሩ አበባው ከማጀቱ 'ሚፈስ?
ነፍስ ጡሮ አንጀቱ እስኪወልድ 'ሚያለቅስ?!
.........እናስ? ደሞ ከዚያስ?!
ግን እንዴት ሆኖ ነው የወንድ ልጅ ጫንቃው
በዘመኑ ላንዴ ዝንተዓለም አፍቅሮ ሁሉን 'ሚንቀው
ይከዳው የሷ ልብ ወንድነቱን ነጥቆት የሚሆን አለቃው
የሚጫወትበት ሲያነሳ ሲጥለው ልቡን ሲነርተው
እንግዲያስ.....
በልቧ ጭካኔ በወሳኝነቷ እሷን የሚያስመልጥ
አንተን የሚያስላዝን ካንተ ዘንድ የማይቆርጥ
ከእግዜር የተቸራት ደሞዟ ነው የርሷ ምጥ!
ስለዚህ አዳም ሆይ.....
የልቧን ቅመም ቋት ላትስተካከለው ላትሰፍረው አትሩጥ
ማጀቷን ላትኖር የሷን ልብ አትመኝ አርግዘህ ላታምጥ
ለአፍቃሪ ልብህ ምጥህ ጭንቀትህ ነው በል አርፈህ ተቀመጥ!!!
©️አቤንኤዘር ጥላሁን/papi
Feb. 1, 2020
@getem
@getem
"የወንድ ምጥ ያማል" ብሎ ሲፅፍ አንዱ
"የሴት ልጅ ይብሳል" ብለው ሌሎች ካዱ!
ፃፊውም 'ካጅውም ያው አዳም ነው ወንዱ
በበለስ ፍሬና በሷ የወረዱ, ከዛ የተዋረዱ::
እርሱስ ቀጥ ያለ ነው የርሷ ግን ጠማበት
ግራ ጎን አጥንቷ ቆልመም ያለችበት
ሊያቀናት ቢሞክር 'ምትሰበርበት!
ግን እንዴት ሆኖ ነው የወንድ ምጥ 'ሚብስ?
በየወሩ አበባው ከማጀቱ 'ሚፈስ?
ነፍስ ጡሮ አንጀቱ እስኪወልድ 'ሚያለቅስ?!
.........እናስ? ደሞ ከዚያስ?!
ግን እንዴት ሆኖ ነው የወንድ ልጅ ጫንቃው
በዘመኑ ላንዴ ዝንተዓለም አፍቅሮ ሁሉን 'ሚንቀው
ይከዳው የሷ ልብ ወንድነቱን ነጥቆት የሚሆን አለቃው
የሚጫወትበት ሲያነሳ ሲጥለው ልቡን ሲነርተው
እንግዲያስ.....
በልቧ ጭካኔ በወሳኝነቷ እሷን የሚያስመልጥ
አንተን የሚያስላዝን ካንተ ዘንድ የማይቆርጥ
ከእግዜር የተቸራት ደሞዟ ነው የርሷ ምጥ!
ስለዚህ አዳም ሆይ.....
የልቧን ቅመም ቋት ላትስተካከለው ላትሰፍረው አትሩጥ
ማጀቷን ላትኖር የሷን ልብ አትመኝ አርግዘህ ላታምጥ
ለአፍቃሪ ልብህ ምጥህ ጭንቀትህ ነው በል አርፈህ ተቀመጥ!!!
©️አቤንኤዘር ጥላሁን/papi
Feb. 1, 2020
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
እንዲህ እንደዛሬ...
በመሀከላችን
ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር
በኔና አንቺ መሀል...
የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር።
አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!!
............................................
በዚህ ስንዝር መሀል....
እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ
እነዚህ ሰዎችም....
ቅርብ ላለች ሰማይ
የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ።
"ምድር ዘማዊ ነው
ምድር ሀጣዊ ነው
ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው"
እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ
ሰማይ ፊኛ ሆና...
ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይታ
በሰዎች እስትንፋስ...
ወደ ላይ ተነፍታ
ወደጎንም ሰፍታ።
.......................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
................................................
እንደውም እንደውም...
በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ
እዛሬ ላይ ሆነው..
"ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ
እድሜ የሰጣቸው
ጥቂት ሰዎች አሉ
የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ።
.............................................
እንደውም እንደውም....
ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር
ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር
እንዲህ እንደዛሬው...
ነፋስ አቀጣጥሎት
ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር
የሰው ልጆች ሁሉ
በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር።
.............................................
ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው
ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው።
ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ
ቀኑ ጨለማ ነው...
ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ።
...........................................
መቼ ነው ሚነጋው?
ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው
መርዙ መድሀኒትሽ...
በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው
ካፈቀሩት ጋራ....
እንኳን ላንድ ለሊት
ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው።
.............................................
መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል
ንጋት ላይ የሚሸሽ..
ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል
አንቺ የሌለሽበት...
ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል።
ለራስ ምታት ህመም..
መድሀኒት እንዲሆን
በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም።
...................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ.
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
#belay bekele weya
@getem
@getem
@beppa_19
.
.
እንዲህ እንደዛሬ...
በመሀከላችን
ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር
በኔና አንቺ መሀል...
የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር።
አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!!
............................................
በዚህ ስንዝር መሀል....
እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ
እነዚህ ሰዎችም....
ቅርብ ላለች ሰማይ
የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ።
"ምድር ዘማዊ ነው
ምድር ሀጣዊ ነው
ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው"
እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ
ሰማይ ፊኛ ሆና...
ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይታ
በሰዎች እስትንፋስ...
ወደ ላይ ተነፍታ
ወደጎንም ሰፍታ።
.......................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
................................................
እንደውም እንደውም...
በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ
እዛሬ ላይ ሆነው..
"ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ
እድሜ የሰጣቸው
ጥቂት ሰዎች አሉ
የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ።
.............................................
እንደውም እንደውም....
ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር
ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር
እንዲህ እንደዛሬው...
ነፋስ አቀጣጥሎት
ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር
የሰው ልጆች ሁሉ
በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር።
.............................................
ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው
ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው።
ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ
ቀኑ ጨለማ ነው...
ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ።
...........................................
መቼ ነው ሚነጋው?
ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው
መርዙ መድሀኒትሽ...
በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው
ካፈቀሩት ጋራ....
እንኳን ላንድ ለሊት
ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው።
.............................................
መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል
ንጋት ላይ የሚሸሽ..
ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል
አንቺ የሌለሽበት...
ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል።
ለራስ ምታት ህመም..
መድሀኒት እንዲሆን
በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም።
...................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ.
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
#belay bekele weya
@getem
@getem
@beppa_19
እየሔዱ መጠበቅ
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
‹‹እየሄድክ ጠብቀኝ›› - ስትይኝ ሄጃለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ….
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ…
አክሱምን እንዳየሽ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ጠራቢው እኔ ነኝ!
ያለፍኩት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ሰማይ ጠቀስ ሐውልት - የተፈለፈለ፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
አክሱም ሐውልት ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ጥበብ አለ!!
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ - ላሊበላን አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ፈልፋዩ እኔ ነኝ፤…
ያለፍሁት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ህንፃ ቤተ-መቅደስ ፤ የተፈለፈለ፡፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
በላሊበላ ውስጥ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ፅናት አለ፡፡
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ - ትክል ድንጋይ አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
የኔው መቃብር ነው!
ውድቀቴም እዛው ነው! ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ባባራ ዘመኑ፤
የራሱን መቃብር - ለመትከል የቻለ፤
መኖር የሚመስል - መሞትም ያይደለ፤
በጢያ ድንጋይ ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ውድቀት አለ፡፡
ከውድቀቴ ኃላ - ባይንሽ የምታዪው፤
ታምር የሚመስል - ታሪክ የምትይው፤
ምልክት የሚሆን - መንገድ ስላልተውኩኝ፤
ከመሞቴ በፊት..
ውድቀቴን፤
ሽንፈቴን፤
ከመቃብሬ ላይ - እንዲህ ብዬ ፃፍሁኝ፡፡
ሩጫዬን ጨረስኩ፤
ሰው ነኝ - ተሸነፍኩ!!!
እናምልሽ ውዴ….
‹‹እየሔድህ ጠብቀኝ›› - ያልሽው ቃል ስህተት
ነው፤
ቃሉም ገብቶሽ እንደው…
መራመድ መሄድ ነው፤
መሮጥም መሄድ ነው፤
መብረርም መሄድ ነው፤
አንቺ እንድትደርሺብኝ …
እኔ እየሞትሁ - እጠብቅሻለው!!!
****************
@getem
@getem
#jeko
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
‹‹እየሄድክ ጠብቀኝ›› - ስትይኝ ሄጃለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ….
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ…
አክሱምን እንዳየሽ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ጠራቢው እኔ ነኝ!
ያለፍኩት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ሰማይ ጠቀስ ሐውልት - የተፈለፈለ፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
አክሱም ሐውልት ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ጥበብ አለ!!
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ - ላሊበላን አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ፈልፋዩ እኔ ነኝ፤…
ያለፍሁት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ህንፃ ቤተ-መቅደስ ፤ የተፈለፈለ፡፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
በላሊበላ ውስጥ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ፅናት አለ፡፡
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ - ትክል ድንጋይ አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
የኔው መቃብር ነው!
ውድቀቴም እዛው ነው! ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ባባራ ዘመኑ፤
የራሱን መቃብር - ለመትከል የቻለ፤
መኖር የሚመስል - መሞትም ያይደለ፤
በጢያ ድንጋይ ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ውድቀት አለ፡፡
ከውድቀቴ ኃላ - ባይንሽ የምታዪው፤
ታምር የሚመስል - ታሪክ የምትይው፤
ምልክት የሚሆን - መንገድ ስላልተውኩኝ፤
ከመሞቴ በፊት..
ውድቀቴን፤
ሽንፈቴን፤
ከመቃብሬ ላይ - እንዲህ ብዬ ፃፍሁኝ፡፡
ሩጫዬን ጨረስኩ፤
ሰው ነኝ - ተሸነፍኩ!!!
እናምልሽ ውዴ….
‹‹እየሔድህ ጠብቀኝ›› - ያልሽው ቃል ስህተት
ነው፤
ቃሉም ገብቶሽ እንደው…
መራመድ መሄድ ነው፤
መሮጥም መሄድ ነው፤
መብረርም መሄድ ነው፤
አንቺ እንድትደርሺብኝ …
እኔ እየሞትሁ - እጠብቅሻለው!!!
****************
@getem
@getem
#jeko
❤1
ኑ ደም በመለገስ በክቡሩ ስጦታ ክቡሩን የሰው ልጅ ሕይወት ከሞት እንታደግ...!
የካቲት 1፣2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በመገናኛ ቦሌ ክፍለ ከተማው አጠገብ!
ቤተሰብ ወዳጅ ዘመድዎን ይዘው ይመጡ!
ጉራማይሌ የበጎ አድራጎት ድርጅት!!!
@Guramayelie
+251955431015
@GURAMAYLIE
የካቲት 1፣2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በመገናኛ ቦሌ ክፍለ ከተማው አጠገብ!
ቤተሰብ ወዳጅ ዘመድዎን ይዘው ይመጡ!
ጉራማይሌ የበጎ አድራጎት ድርጅት!!!
@Guramayelie
+251955431015
@GURAMAYLIE
ትሑት ምህላ
=========
አቤቱ ጌታ ሆይ ፣
የኢትዮጵያውያንን እምነት
የግሪክን ጥበብ መሻት
የአይሁድን ምልክት ጥማት
የፈሪሳውያንን የአመክንዮ ሙግት-
ልክፍት
የሱፊን ተደሞ
የዜንን አርምሞ
የተመሥጦ መገለጥን ምትሐት ፣
......አጣምረህ ለነብሴ ሥጣት!
በዚህ፣ኃይሏ ግርማ
እንደ ጨለማ ፣ ቀለም ድንበርን ታሥማማ.....።
አሜን።
ዲበኩሉ ጌታ
ሰኔ ፳ ፳፻፰ ዓ.ም
-----------//----------
የምድር ዘላለም ድንቅ መፅሀፍ ነው በተገኘበት ይነበብ!! ያነበበ ብዙ ያተርፋል
#
@getem
@getem
@getem
=========
አቤቱ ጌታ ሆይ ፣
የኢትዮጵያውያንን እምነት
የግሪክን ጥበብ መሻት
የአይሁድን ምልክት ጥማት
የፈሪሳውያንን የአመክንዮ ሙግት-
ልክፍት
የሱፊን ተደሞ
የዜንን አርምሞ
የተመሥጦ መገለጥን ምትሐት ፣
......አጣምረህ ለነብሴ ሥጣት!
በዚህ፣ኃይሏ ግርማ
እንደ ጨለማ ፣ ቀለም ድንበርን ታሥማማ.....።
አሜን።
ዲበኩሉ ጌታ
ሰኔ ፳ ፳፻፰ ዓ.ም
-----------//----------
የምድር ዘላለም ድንቅ መፅሀፍ ነው በተገኘበት ይነበብ!! ያነበበ ብዙ ያተርፋል
#
@getem
@getem
@getem
ኑ ደም በመለገስ በክቡሩ ስጦታ ክቡሩን የሰው ልጅ ሕይወት ከሞት እንታደግ...!
የካቲት 1፣2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በመገናኛ ቦሌ ክፍለ ከተማው አጠገብ!
ቤተሰብ ወዳጅ ዘመድዎን ይዘው ይመጡ!
ጉራማይሌ የበጎ አድራጎት ድርጅት!!!
@Guramayelie
+251955431015
@GURAMAYLIE
የካቲት 1፣2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በመገናኛ ቦሌ ክፍለ ከተማው አጠገብ!
ቤተሰብ ወዳጅ ዘመድዎን ይዘው ይመጡ!
ጉራማይሌ የበጎ አድራጎት ድርጅት!!!
@Guramayelie
+251955431015
@GURAMAYLIE
ማህሌተ ገንቦ
(በእውቀቱ ስዩም)
"ባጭር ቀረን" ስንል ፣ እድሜ ላበደሩን
ቀርፀው ላሳመሩን
ለኩሰው ላበሩን
ቺርስ!!
።።።
ፊታችንን ዐይተው እንደተቸገርን ፣
ካይናችን ላወቁ
"ስለማርያም" ብለን
እስክንለምናቸው ፣ ቆመው ላልጠበቁ
ቺርስ!!!
።።።
ወድቀው ለማይጥሉ ፣
ነግሰው ለሚያነግሱ
ነውራችንን ዐይተው ልክ እንደ ድመት ኩስ ፣ ለሚያለባብሱ
ብድር አበድረው ፣ ፈጥነው ለሚረሱ
ቺርስ!!!!
።።፣
ላባ ላረጉልን ፣ የመከራ ሸክሙን
ቀልደው ላሳቁን ፣ተጫውተው ላከሙን
በቸከ ዘመን ላይ ስጋ ለበስ ትንግርት ፣ ሆነው ላስደመሙን
ቺርስ!!!!!
@getem
@getem
#jeko
(በእውቀቱ ስዩም)
"ባጭር ቀረን" ስንል ፣ እድሜ ላበደሩን
ቀርፀው ላሳመሩን
ለኩሰው ላበሩን
ቺርስ!!
።።።
ፊታችንን ዐይተው እንደተቸገርን ፣
ካይናችን ላወቁ
"ስለማርያም" ብለን
እስክንለምናቸው ፣ ቆመው ላልጠበቁ
ቺርስ!!!
።።።
ወድቀው ለማይጥሉ ፣
ነግሰው ለሚያነግሱ
ነውራችንን ዐይተው ልክ እንደ ድመት ኩስ ፣ ለሚያለባብሱ
ብድር አበድረው ፣ ፈጥነው ለሚረሱ
ቺርስ!!!!
።።፣
ላባ ላረጉልን ፣ የመከራ ሸክሙን
ቀልደው ላሳቁን ፣ተጫውተው ላከሙን
በቸከ ዘመን ላይ ስጋ ለበስ ትንግርት ፣ ሆነው ላስደመሙን
ቺርስ!!!!!
@getem
@getem
#jeko
❤2
#አዎ ~ባላ'ገር~ነህ!!!
፡
የደመናን እንባ
የናፈቁ አይኖችህ
ሽቅብ ወደ ሰማይ ዘውትር ሲዋትቱ
ከደረቀ መሬት
ትግል የገጠሙ
ሻካራ እጆችህ ሞፈር ሲጎትቱ
ከበሬ ተጣምደህ
አፈር ስትገፋ ቀንበር ስትሸከም
ያኔ ነው የገባኝ
የህይወትህ ምሬት ለኔ ያንተ መድከም፡፡
፡
ግና ከተሜው ሰው
የባላገር ትርጉም ያልገባው ምፃጉ
ለስም አልባ ስሙ
መሆንህን እረስቶ ክብርና ማረጉ
አርሰህ ባጎረስከው
ውለታቢስ ሆዱ ለባእዳን ሰግዶ
ባላገር ይልሀል
በመዘመን ብሂል እርሱ ሀገሩን ክዶ፡፡
፡
አዎ ባላ'ገር ነህ
ሀገር ስላለህ ነው ባላ'ገር ምትባል
እውነትም ይሄ ስም
ከማንም በላቀ ለክብርህ ይገባል፡፡
፡
ስለዚህ ለነሱ
ለከተሜው ጭሶች ባላገር ለናቁ
ሀገር እያላቸው
ሀገር አልባ ሆነው ሀገር ለናፈቁ
ባላ'ገር ነህና
ይበሉህ ባላገር ሀገርን እስኪያውቁ፡፡
((ልብ አልባው ገጣሚ))
((ሸጋ ሐሙስ))
@getem
@getem
@beppa_19
፡
የደመናን እንባ
የናፈቁ አይኖችህ
ሽቅብ ወደ ሰማይ ዘውትር ሲዋትቱ
ከደረቀ መሬት
ትግል የገጠሙ
ሻካራ እጆችህ ሞፈር ሲጎትቱ
ከበሬ ተጣምደህ
አፈር ስትገፋ ቀንበር ስትሸከም
ያኔ ነው የገባኝ
የህይወትህ ምሬት ለኔ ያንተ መድከም፡፡
፡
ግና ከተሜው ሰው
የባላገር ትርጉም ያልገባው ምፃጉ
ለስም አልባ ስሙ
መሆንህን እረስቶ ክብርና ማረጉ
አርሰህ ባጎረስከው
ውለታቢስ ሆዱ ለባእዳን ሰግዶ
ባላገር ይልሀል
በመዘመን ብሂል እርሱ ሀገሩን ክዶ፡፡
፡
አዎ ባላ'ገር ነህ
ሀገር ስላለህ ነው ባላ'ገር ምትባል
እውነትም ይሄ ስም
ከማንም በላቀ ለክብርህ ይገባል፡፡
፡
ስለዚህ ለነሱ
ለከተሜው ጭሶች ባላገር ለናቁ
ሀገር እያላቸው
ሀገር አልባ ሆነው ሀገር ለናፈቁ
ባላ'ገር ነህና
ይበሉህ ባላገር ሀገርን እስኪያውቁ፡፡
((ልብ አልባው ገጣሚ))
((ሸጋ ሐሙስ))
@getem
@getem
@beppa_19
👍1
ልበ ዱሪቆን
-------#በሲራክ----------
አለሜ......
በአፍላነት እድሜ ገና በልጅነት
የደወርነው ፍቅር ደርሰው ያልፈተሉት
የትዝታ መንጋ ልባችን ያዘለው
ማደግ ያልዘነጋው
አርያም ባይሰማው ይህን አይነት ፍቅር
ህቡዕ ነው ልንገርሽ የኔና አንቺስ ነገር
እዚህ ከኛ ልብ ውስጥ ንዴት አሸልቧል
ያልወለድነው ፍቅር ልባችን አርግዟል
የኔም የአንቺ አንደበት ዝምታውን መርጧል
ይሁን ይሁን ልቀበለው
ያ ልባችን አማን አለው
.
ትዝ ይልሻል
በማሪያም ዕለት ከንግስ መልስ
ከሜዳው ላይ ከአፀዱ ስር ምሽት ሳይደርስ
ተቀምጠን ተጠጋግተን በፍንደቃ ስናወጋ
ተሰምቶኛል አንዳች እውነት ከሙቀትሽ የላብ ቀጋ
.
ያ ልብሽ ደጋ ነው በማፍቀር የናኘ
የኔ ልብ ቆላ ነው አንቺን የተመኘ
ምክኒያቱ ይህ ነው የልበ ዱሪቆን
ልባችን ተማምኖ አንደበት ቢከዳን
በቃ ተፈጥረን ነው እሳት ውሃ ሆነን
.
ደግሞ ጊዜው ቢተም
ምሽት ደርሶ ቢጨላልም
ከውብ አይንሽ ቅሬታሽን አነባለው
ክንድሽ ሲያቅፈኝ ጭንቀትሽን እረዳለው
.
በሌላ ቀን ተነፋፍቀን ስንገናኝ
ትንፋሽሽ ነው ማፍቀርሽን የሚያወጋኝ
እርግብ ሆነሽ እኔ ቁራ
ተራርቀን ባንድ ጣራ
እሳት ስሆን አንቺ ውሃ
ያልታደልኩሽ የኔ አምሃ
.
ዱሪቆን ነው በቃ እንቅር
እኔና አንቺ አንናገር
በሀሳብ መንገድ እንሳፈር
በልባችን እንፋቀር
አርግዚኝ በተስፋ ልብሽ ከኔ አይሽሽ
ልታገስሽ እኔም በተስፋ ላርግዝሽ
.
በማሪያም ዕለት ከንግስ መልስ
ከሜዳው ላይ ከአፀዱ ስር ምሽት ሳይደርስ
ተቀምጠን ተጠጋግተን በፍንደቃ ስናወጋ
ተሰምቶኛል አንዳች እውነት ከሙቀትሽ የላብ ቀጋ
-------------//---------------
ሲራክ @siraaq
#
@getem
@getem
@getem
-------#በሲራክ----------
አለሜ......
በአፍላነት እድሜ ገና በልጅነት
የደወርነው ፍቅር ደርሰው ያልፈተሉት
የትዝታ መንጋ ልባችን ያዘለው
ማደግ ያልዘነጋው
አርያም ባይሰማው ይህን አይነት ፍቅር
ህቡዕ ነው ልንገርሽ የኔና አንቺስ ነገር
እዚህ ከኛ ልብ ውስጥ ንዴት አሸልቧል
ያልወለድነው ፍቅር ልባችን አርግዟል
የኔም የአንቺ አንደበት ዝምታውን መርጧል
ይሁን ይሁን ልቀበለው
ያ ልባችን አማን አለው
.
ትዝ ይልሻል
በማሪያም ዕለት ከንግስ መልስ
ከሜዳው ላይ ከአፀዱ ስር ምሽት ሳይደርስ
ተቀምጠን ተጠጋግተን በፍንደቃ ስናወጋ
ተሰምቶኛል አንዳች እውነት ከሙቀትሽ የላብ ቀጋ
.
ያ ልብሽ ደጋ ነው በማፍቀር የናኘ
የኔ ልብ ቆላ ነው አንቺን የተመኘ
ምክኒያቱ ይህ ነው የልበ ዱሪቆን
ልባችን ተማምኖ አንደበት ቢከዳን
በቃ ተፈጥረን ነው እሳት ውሃ ሆነን
.
ደግሞ ጊዜው ቢተም
ምሽት ደርሶ ቢጨላልም
ከውብ አይንሽ ቅሬታሽን አነባለው
ክንድሽ ሲያቅፈኝ ጭንቀትሽን እረዳለው
.
በሌላ ቀን ተነፋፍቀን ስንገናኝ
ትንፋሽሽ ነው ማፍቀርሽን የሚያወጋኝ
እርግብ ሆነሽ እኔ ቁራ
ተራርቀን ባንድ ጣራ
እሳት ስሆን አንቺ ውሃ
ያልታደልኩሽ የኔ አምሃ
.
ዱሪቆን ነው በቃ እንቅር
እኔና አንቺ አንናገር
በሀሳብ መንገድ እንሳፈር
በልባችን እንፋቀር
አርግዚኝ በተስፋ ልብሽ ከኔ አይሽሽ
ልታገስሽ እኔም በተስፋ ላርግዝሽ
.
በማሪያም ዕለት ከንግስ መልስ
ከሜዳው ላይ ከአፀዱ ስር ምሽት ሳይደርስ
ተቀምጠን ተጠጋግተን በፍንደቃ ስናወጋ
ተሰምቶኛል አንዳች እውነት ከሙቀትሽ የላብ ቀጋ
-------------//---------------
ሲራክ @siraaq
#
@getem
@getem
@getem
👍1
"ካለፈ በኋላ.."
""""""""""""
((ዮሐንስ ፍቃዴ))
ፀጉር ቆራጮቹ
ፀጉሩን እየተቹ
'ምነው እቴ ፀጉሩን...'
ብለው እያወሩ፤ ሊያሙት ተመቻቹ
የልብስ ነጋዴ...
'ልብሱን ባ'መት እንኳ አይቀይርም እንዴ?'
ብለው በአንድነት፤ ተንጫጩበት አንዴ
ደሞ የገነባው፤ ጫማ አምራች ፋብሪካ
'ምናይነት ነፈዝ ነው ብራንድ የማይለካ
እግሩን ካዲስ ጫማ የማያነካካ
ከዘመኑ ጋራ የማይለካካ
ም'ናይነት አፈር ነው እግሩ አፈር የነካ'
ብሎ ይዘልፈዋል...
ጫማውን ለመሸጥ እግሩን ይሰድበዋል
"""""""""""""""""""
ክብር የማይገባው ፍቅር የማይገባው
እውነት ባየ ቁጥር የሚንገበገበው..
'እዩት ይሄ ከንቱ..
ተሸክሞ ሲዞር ባንዲራ ባንገቱ
እዩት ማስጠላቱ ...
ክንዱ ላይ ያሰረው የሸማ ጥለቱ'
ብሎ ያሳጣዋል፤ ክብር ያልገባው ጅል
አማረብኝ ብሎ፤ የሚያምረውን ሊጥል
'እሱም ብሎ ደሞ፤ ጀግና ባለ ቅኔ
ደሞ እሱን ብሎ ሊቅ፤ አረ ለሱስ መጥኔ..
ዝም ብየ ባወራ... አልበልጠውም እኔ?'
ይሉታል አንዳንዶች
ከባድ የሚያቀሉ የቀለሉ ሰዎች
""""""""""""""""""
'እዩት ያን ከርፋፋ..
ቅኔ ነው እያለ ቅሌቱን ሲተፋ
እዩት ይሄን ክርፍፍ..
ህይወቱን እንደ ጅል፤ ቅኔ ብሎ ሊዘርፍ
ያውና ያ አስመሳይ...
ደሞ እንደገጣሚ ይዞ ተመሳሳይ
እዩት ይጃጃላል
ሲሉ የሰማውን ቅኔ በሉት ይላል
የሰው ነገር ሰምቶ ሊቀኝ ይከጅላል'
እያሉ ይሉታል..
ይሉታል.. ይሉታል...
ገ'ለው ያድኑታል.. ሰቅለው ያወርዱታል
"""""""""""""""""""
እሱ ግን..
የሚሉትን ሁሉ ሰምቶ እያሳለፈ
እሱ እየረገፈ ቅኔ እየዘረፈ
በመንገዱ አለፈ..
'ብቻ ግን የሱ ልብ፤ አለው መቀነቻ
ቅኔ እየዘረፉ፤ ቅኔ መሆን ብቻ!'
እሱ ግን አለፈ..
እንደተቆለፈ!
""""""""""""""""
ካለፈ በኋላ፤ ሁሉም ገረማቸው
የሄደበት መንገድ፤ ሰው መሰለባቸው
ካለፈ በኋላ፤ ሁሉም ጨነቃቸው
የዘረፈው ቅኔ፤ ሰው ሆኖ ታያቸው
ካለፈ በኋላ፤ ሁሉም ተገረሙ
ወደ ተነሳበት፤ ሄዱ እያዘገሙ
ካረፈ በኋላ፤ ሁሉም ተናደዱ
ላያገኙት ነገር፤ ሊፈልጉት ሄዱ
=+++-+++-+++=
@getem
@getem
@getem
""""""""""""
((ዮሐንስ ፍቃዴ))
ፀጉር ቆራጮቹ
ፀጉሩን እየተቹ
'ምነው እቴ ፀጉሩን...'
ብለው እያወሩ፤ ሊያሙት ተመቻቹ
የልብስ ነጋዴ...
'ልብሱን ባ'መት እንኳ አይቀይርም እንዴ?'
ብለው በአንድነት፤ ተንጫጩበት አንዴ
ደሞ የገነባው፤ ጫማ አምራች ፋብሪካ
'ምናይነት ነፈዝ ነው ብራንድ የማይለካ
እግሩን ካዲስ ጫማ የማያነካካ
ከዘመኑ ጋራ የማይለካካ
ም'ናይነት አፈር ነው እግሩ አፈር የነካ'
ብሎ ይዘልፈዋል...
ጫማውን ለመሸጥ እግሩን ይሰድበዋል
"""""""""""""""""""
ክብር የማይገባው ፍቅር የማይገባው
እውነት ባየ ቁጥር የሚንገበገበው..
'እዩት ይሄ ከንቱ..
ተሸክሞ ሲዞር ባንዲራ ባንገቱ
እዩት ማስጠላቱ ...
ክንዱ ላይ ያሰረው የሸማ ጥለቱ'
ብሎ ያሳጣዋል፤ ክብር ያልገባው ጅል
አማረብኝ ብሎ፤ የሚያምረውን ሊጥል
'እሱም ብሎ ደሞ፤ ጀግና ባለ ቅኔ
ደሞ እሱን ብሎ ሊቅ፤ አረ ለሱስ መጥኔ..
ዝም ብየ ባወራ... አልበልጠውም እኔ?'
ይሉታል አንዳንዶች
ከባድ የሚያቀሉ የቀለሉ ሰዎች
""""""""""""""""""
'እዩት ያን ከርፋፋ..
ቅኔ ነው እያለ ቅሌቱን ሲተፋ
እዩት ይሄን ክርፍፍ..
ህይወቱን እንደ ጅል፤ ቅኔ ብሎ ሊዘርፍ
ያውና ያ አስመሳይ...
ደሞ እንደገጣሚ ይዞ ተመሳሳይ
እዩት ይጃጃላል
ሲሉ የሰማውን ቅኔ በሉት ይላል
የሰው ነገር ሰምቶ ሊቀኝ ይከጅላል'
እያሉ ይሉታል..
ይሉታል.. ይሉታል...
ገ'ለው ያድኑታል.. ሰቅለው ያወርዱታል
"""""""""""""""""""
እሱ ግን..
የሚሉትን ሁሉ ሰምቶ እያሳለፈ
እሱ እየረገፈ ቅኔ እየዘረፈ
በመንገዱ አለፈ..
'ብቻ ግን የሱ ልብ፤ አለው መቀነቻ
ቅኔ እየዘረፉ፤ ቅኔ መሆን ብቻ!'
እሱ ግን አለፈ..
እንደተቆለፈ!
""""""""""""""""
ካለፈ በኋላ፤ ሁሉም ገረማቸው
የሄደበት መንገድ፤ ሰው መሰለባቸው
ካለፈ በኋላ፤ ሁሉም ጨነቃቸው
የዘረፈው ቅኔ፤ ሰው ሆኖ ታያቸው
ካለፈ በኋላ፤ ሁሉም ተገረሙ
ወደ ተነሳበት፤ ሄዱ እያዘገሙ
ካረፈ በኋላ፤ ሁሉም ተናደዱ
ላያገኙት ነገር፤ ሊፈልጉት ሄዱ
=+++-+++-+++=
@getem
@getem
@getem