ለቅዳሚታችን ጭማሪ ጀባታ!
❤
የላይኛው!!!!!!
ከነ መምሬ አሊ፤
ከሸህ በላይ ሃገር ፤ ተሰርቶ እትብታችን፤
በሰውነት ልኬት፤
ሰው በመሆን ሚዛን ፤ ተሰፍሮ ልባችን፤
ከሰውነት መንበር፤
እንግፋችሁ ሲሉን፤
እንለያችሁ ሲሉን ፤
ያንቀጠቅጠናል ያንገሸግሸናል አይወድም ቀልባችን።
እነ ቦተሊካ፤
ላይሳካላቸው፤
የእምነት ለምድ ለብሰው፥ የተንኮልን ኩታ፤
በታችኛው መንደር ፤
ታቹን እያሰቡ ፤
መስጂዲና ደብሩን ፤ ተለያይ እያሉት ቢገፉት ጧት ማታ፤
ህልማቸው ከንቱ ነው፤
ይኸው ዛሬ ድረስ፤
ታቹን ንቀን ትተን፤
ከላይ ተቃቅፈናል ተቃቀፉ ብሎን የላይኛው ጌታ።
((( ጃ ኖ ))💚💛❤
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!❤
@getem
@getem
@Nagayta
❤
የላይኛው!!!!!!
ከነ መምሬ አሊ፤
ከሸህ በላይ ሃገር ፤ ተሰርቶ እትብታችን፤
በሰውነት ልኬት፤
ሰው በመሆን ሚዛን ፤ ተሰፍሮ ልባችን፤
ከሰውነት መንበር፤
እንግፋችሁ ሲሉን፤
እንለያችሁ ሲሉን ፤
ያንቀጠቅጠናል ያንገሸግሸናል አይወድም ቀልባችን።
እነ ቦተሊካ፤
ላይሳካላቸው፤
የእምነት ለምድ ለብሰው፥ የተንኮልን ኩታ፤
በታችኛው መንደር ፤
ታቹን እያሰቡ ፤
መስጂዲና ደብሩን ፤ ተለያይ እያሉት ቢገፉት ጧት ማታ፤
ህልማቸው ከንቱ ነው፤
ይኸው ዛሬ ድረስ፤
ታቹን ንቀን ትተን፤
ከላይ ተቃቅፈናል ተቃቀፉ ብሎን የላይኛው ጌታ።
((( ጃ ኖ ))💚💛❤
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!❤
@getem
@getem
@Nagayta
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የጊዜሽ እውነታ! !
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።
የፎቶ ዓለም ነው!
የብልጭታ ዘመን...
ታይታ የሞላው ፥ መታበይ የሰራው
አዋቂው ብዙ ነው !
በራሱ ዛቢያ ላይ ፥ መንገድ 'ሚያቀናው።
ጎዳናው አንድ ነው!
የለም የተለየ...
ጠርጣሪው እልፍ ነው!
ገለባ ሸንትሮ ፥ ሽንብራ ያለየ።
መቅረዝ ተሸካሚው.. .
አትሮኖሱን ዘርጊው...
ባለ ጧፉ ብዙ
ባለ መጣፍ ብዙ
መድረኩ ላይ ቆሞ ፥ እኔን ስሙ 'ሚለው
እሪያው አሸን ነው!
ያሉትን አድምጦ ፥ በመንጋ 'ሚጎርፈው
#ይኸው ተመልከቺ!
ስንደዶው መች ጠፋ?
አክርማው መች ጠፋ?
ባለሙያው ብዙ
ባለ ወስፌው ብዙ
እንዴት ቢሰፋ ነው?
መሶቡ ሳያምር ፥ የሚታይ ሰበዙ?
#አየሽ!
በዚህች በጉድ ሀገር...
ቱባውን አፍታቶ ፥ ክሮቹን ወድሮ
ጋቢ ልስፋ 'ሚለው ፥ ሸማኔው ቢበዛም
ሁሉም እርቃኑን ነው!
የሞቀው ሰው የለም ፥ ውርጩም አልተረታም።
@getem
@getem
@paappii
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።
የፎቶ ዓለም ነው!
የብልጭታ ዘመን...
ታይታ የሞላው ፥ መታበይ የሰራው
አዋቂው ብዙ ነው !
በራሱ ዛቢያ ላይ ፥ መንገድ 'ሚያቀናው።
ጎዳናው አንድ ነው!
የለም የተለየ...
ጠርጣሪው እልፍ ነው!
ገለባ ሸንትሮ ፥ ሽንብራ ያለየ።
መቅረዝ ተሸካሚው.. .
አትሮኖሱን ዘርጊው...
ባለ ጧፉ ብዙ
ባለ መጣፍ ብዙ
መድረኩ ላይ ቆሞ ፥ እኔን ስሙ 'ሚለው
እሪያው አሸን ነው!
ያሉትን አድምጦ ፥ በመንጋ 'ሚጎርፈው
#ይኸው ተመልከቺ!
ስንደዶው መች ጠፋ?
አክርማው መች ጠፋ?
ባለሙያው ብዙ
ባለ ወስፌው ብዙ
እንዴት ቢሰፋ ነው?
መሶቡ ሳያምር ፥ የሚታይ ሰበዙ?
#አየሽ!
በዚህች በጉድ ሀገር...
ቱባውን አፍታቶ ፥ ክሮቹን ወድሮ
ጋቢ ልስፋ 'ሚለው ፥ ሸማኔው ቢበዛም
ሁሉም እርቃኑን ነው!
የሞቀው ሰው የለም ፥ ውርጩም አልተረታም።
@getem
@getem
@paappii
Miki ebalalew ye gonder university ye 3gna amet temari negn kelay yelakulachu ehitachin tsigereda tibalalech egna betechalen akim lemasebaseb mokirenal enantem yetechalachun adirgulat.
1 be silk. ye enatua silk new( +251 96 143 1288) weyim beakal bemeteyek tikur anbesa hospital bemehed
2 be accountbkutrua bemasgebat be ajal weyim *886# be mobile banking ke 5 birr eske chalachut
3 keguadegnochachu ga bemehon bemasebaseb
4 be telegram be facebook endihum beteleyayu social midiawoch share bemadreg
Endihum andand gudayochin keslbetesebochua ga bemehon mascheres yechalachutin bemadreg alenilish beluat.
Melkamin bemadreg yetebarekewun ye edme zemenachinin melsen enbarkew.
Lerechemari mereja @mikihaile bemegbat mawarat tichilalachu.
Egziabher ethiopian ena hizbochuan yibark amen amen amen 🙏🙏🙏
1 be silk. ye enatua silk new( +251 96 143 1288) weyim beakal bemeteyek tikur anbesa hospital bemehed
2 be accountbkutrua bemasgebat be ajal weyim *886# be mobile banking ke 5 birr eske chalachut
3 keguadegnochachu ga bemehon bemasebaseb
4 be telegram be facebook endihum beteleyayu social midiawoch share bemadreg
Endihum andand gudayochin keslbetesebochua ga bemehon mascheres yechalachutin bemadreg alenilish beluat.
Melkamin bemadreg yetebarekewun ye edme zemenachinin melsen enbarkew.
Lerechemari mereja @mikihaile bemegbat mawarat tichilalachu.
Egziabher ethiopian ena hizbochuan yibark amen amen amen 🙏🙏🙏
🔥1
እቴ
(በውቀቱ ስዩም)
ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ
ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ
ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ
ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤
ይስጥሽ ከጸጉሮቼ ከአናቴ ላይ ዘግኖ
ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ
አወይ ጸጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ
ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ፤
... እቴ
ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ
ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ
ከአይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ
እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ።
እቴ
እጄን ብትፈልጊ
እግሬን ብትፈልጊ
አንገቴን ደረቴን
ተሰጥኦ ሀሳቤን
ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ
እግዜር ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ
ያስቀርልኝ አይኔን
አንቺን ማየት ብቻ ያኖረኛል እኔን
@getem
@getem
(በውቀቱ ስዩም)
ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ
ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ
ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ
ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤
ይስጥሽ ከጸጉሮቼ ከአናቴ ላይ ዘግኖ
ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ
አወይ ጸጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ
ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ፤
... እቴ
ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ
ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ
ከአይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ
እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ።
እቴ
እጄን ብትፈልጊ
እግሬን ብትፈልጊ
አንገቴን ደረቴን
ተሰጥኦ ሀሳቤን
ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ
እግዜር ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ
ያስቀርልኝ አይኔን
አንቺን ማየት ብቻ ያኖረኛል እኔን
@getem
@getem
👍3❤2
እግዚዎ አዳማ
በጨለማ
አቦ ናዝሬት በኩለሊት
(ነብይ መኮንን )
ሺ ኮከብ ካናትሽ ፈጦ
ስንት አምፖል አይኑን አጉርጦ
አስፋልትሽ በብርሀን አጊጦ
ጉድሽ በጭለማ ፈርጦ
ቡና ቤቱ ደጃፍ በሩ....
ባንኮኒው ከሰው ተፋጦ
ሙቀት ትነት
ዳንስ ጩኸት
ሴት ወንዱን ሳይወድ አስምጦ
ያራውጠዋል አዳሜን
ሞራ እድሉን ለሊት ገልጦ፡፡
እግዚዎ አዳማ
በጨለማ
አቦ ናዝሬት
በኩለሊት
አልጋ ፍለጋ የሚሮጠው
ሴት አዳር የሚያካልለው
ሰክሮ በድጋፍ የሚቆመው
ግብግብ ገጥሞ የሚጮኸው
ይራወጣል ዳር እስከዳር
ይራወጣል ሰፈር መንደር
ሽቅብ ቀጨማ ድንበር
እስከ አሮጌ አዳማ ዳር ዳር
ቁልቁል እስከ እሩቅ ጮሬ በር
ጎኑን እስከ ቦይ ማዶ አጥር
ላዩን ሀዲዱን ታኮ
ታቹን አቡስቶ ቡሉኮ
መሀል ከእርግብግቢትሽ ላይ
የማርያም ሰፈር አዋይ
የገዳም ሰፈር አዋዋይ
የቁርቁራ አድባር ሲሳይ
ሳር ሰፈር ነፃነት ሜዳ.....
መስጊድ አራዳ ፍሙ ላይ
ምንጃር ጎዳናን አካሎ.....
በየ ቀዬው የማታ አዋይ
ስንቱ ሲነድ ስንቱ ሲጋይ
አይኑ ከመብራት ሲተያይ
አምፖሉም ቀይ
ብሌኑም ቀይ
ቤት ምድሩም ቀይ
የአዳም ዘር ቀይ
አንዱ ሀይ ሀይ
አንዷ ውይ ውይ
ሌላው ዳይ ዳይ
እግዚዎ አዳማ
በጭለማ
አቦ ናዝሬት
በኩለሊት፡፡
ዙርያሽ በተራራ ክበብ
ጥግሽ በጋራ አለት ድባብ
የልምለየሜሽን ንባብ
ቁልቁል ለረባዳሽ ሲያነብ
ኮርኒስሽ የሰማይ ኮከብ
ምድርሽ የአዋራ ቅቤ ቅብ
ፍሬሽ የዋንዛ እንኮይ ጥጋብ
ገፅሽ የባህር ዛፍ ክብካብ
ዋርካሽ የቁርቁራ መሶብ
በጨለማሽ ሁሉ ጥቁር
በኮከብሽ ሁሉ ፍቅር
.
እያለ ይቀጥላል...
ሸጋ ሰንበት!💚💛❤
@getem
@getem
@Nagayta
በጨለማ
አቦ ናዝሬት በኩለሊት
(ነብይ መኮንን )
```````````````
ሺ ኮከብ ካናትሽ ፈጦ
ስንት አምፖል አይኑን አጉርጦ
አስፋልትሽ በብርሀን አጊጦ
ጉድሽ በጭለማ ፈርጦ
ቡና ቤቱ ደጃፍ በሩ....
ባንኮኒው ከሰው ተፋጦ
ሙቀት ትነት
ዳንስ ጩኸት
ሴት ወንዱን ሳይወድ አስምጦ
ያራውጠዋል አዳሜን
ሞራ እድሉን ለሊት ገልጦ፡፡
እግዚዎ አዳማ
በጨለማ
አቦ ናዝሬት
በኩለሊት
አልጋ ፍለጋ የሚሮጠው
ሴት አዳር የሚያካልለው
ሰክሮ በድጋፍ የሚቆመው
ግብግብ ገጥሞ የሚጮኸው
ይራወጣል ዳር እስከዳር
ይራወጣል ሰፈር መንደር
ሽቅብ ቀጨማ ድንበር
እስከ አሮጌ አዳማ ዳር ዳር
ቁልቁል እስከ እሩቅ ጮሬ በር
ጎኑን እስከ ቦይ ማዶ አጥር
ላዩን ሀዲዱን ታኮ
ታቹን አቡስቶ ቡሉኮ
መሀል ከእርግብግቢትሽ ላይ
የማርያም ሰፈር አዋይ
የገዳም ሰፈር አዋዋይ
የቁርቁራ አድባር ሲሳይ
ሳር ሰፈር ነፃነት ሜዳ.....
መስጊድ አራዳ ፍሙ ላይ
ምንጃር ጎዳናን አካሎ.....
በየ ቀዬው የማታ አዋይ
ስንቱ ሲነድ ስንቱ ሲጋይ
አይኑ ከመብራት ሲተያይ
አምፖሉም ቀይ
ብሌኑም ቀይ
ቤት ምድሩም ቀይ
የአዳም ዘር ቀይ
አንዱ ሀይ ሀይ
አንዷ ውይ ውይ
ሌላው ዳይ ዳይ
እግዚዎ አዳማ
በጭለማ
አቦ ናዝሬት
በኩለሊት፡፡
ዙርያሽ በተራራ ክበብ
ጥግሽ በጋራ አለት ድባብ
የልምለየሜሽን ንባብ
ቁልቁል ለረባዳሽ ሲያነብ
ኮርኒስሽ የሰማይ ኮከብ
ምድርሽ የአዋራ ቅቤ ቅብ
ፍሬሽ የዋንዛ እንኮይ ጥጋብ
ገፅሽ የባህር ዛፍ ክብካብ
ዋርካሽ የቁርቁራ መሶብ
በጨለማሽ ሁሉ ጥቁር
በኮከብሽ ሁሉ ፍቅር
.
እያለ ይቀጥላል...
ሸጋ ሰንበት!💚💛❤
@getem
@getem
@Nagayta
ቀረሽ እንደዋዛ፣
እንደ ድመቶቹ፤
የትም እንደሚያድሩት፣
እንደ ስልክ እንጨቶች፤
እንደ ዛፍ ሀረጎች፣
እንደ ቤት ክዳኖች፤
ብርድ አቆራመደኝ?
ስጠብቅ ስጠብቅ
˝ትመጫለሽ ብዬ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ፤
የልጅነት አይኔ ሟሟ እንደ በረዶ፤
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር፤
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር፤
ትመጫለሽ ብዬ ባዝን ባንጎራጉር፤
ትወጫለሽ ብዬ በበራፍሽ ብዞር፤
ብርድ አቆራመደኝ፤
የመንገድ መብራቶች አይተው አፌዙብኝ፤
ውርጩ ቀለደብኝ፤
ጨለማው ሳቀብኝ፤
አለመምጣትሽን አውቀዋል ያውቃሉ?
መስኮቶች ጨልመው፤
ቤቶች ተቆልፈው፤
ከተማው ሲተኛ፣
አይተዋል ያያሉ፤
አለመምጣትሽን
አውቀዋል ያውቃሉ፤
✍ገብረ ክርስቶስ ደስታ
@getem
@getem
@beppa_19
እንደ ድመቶቹ፤
የትም እንደሚያድሩት፣
እንደ ስልክ እንጨቶች፤
እንደ ዛፍ ሀረጎች፣
እንደ ቤት ክዳኖች፤
ብርድ አቆራመደኝ?
ስጠብቅ ስጠብቅ
˝ትመጫለሽ ብዬ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ፤
የልጅነት አይኔ ሟሟ እንደ በረዶ፤
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር፤
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር፤
ትመጫለሽ ብዬ ባዝን ባንጎራጉር፤
ትወጫለሽ ብዬ በበራፍሽ ብዞር፤
ብርድ አቆራመደኝ፤
የመንገድ መብራቶች አይተው አፌዙብኝ፤
ውርጩ ቀለደብኝ፤
ጨለማው ሳቀብኝ፤
አለመምጣትሽን አውቀዋል ያውቃሉ?
መስኮቶች ጨልመው፤
ቤቶች ተቆልፈው፤
ከተማው ሲተኛ፣
አይተዋል ያያሉ፤
አለመምጣትሽን
አውቀዋል ያውቃሉ፤
✍ገብረ ክርስቶስ ደስታ
@getem
@getem
@beppa_19
👍1
➬ ያልተፈታ ቅኔ ➪
©ሲራክ
ዳዊቴን ደግሜ ከማክዳሽ ምድር
ቅኔን ተግቻለሁ
በታሰረ አካሌ ያሰርሽው ልብሽን
ሳስፈታ ኑሬያለሁ
ቅኔሽን ተግቼ አጥቼሽ እያለሁ ....
ካሰረኝ ልብሽ ዳር በማይፈታኝ ወኔ
ምን ልሆን መጣለሁ?
አየሽ አንቺ አካሌ
እኔ ማለት በቃ የመሄድ ፅዋ ነኝ
የተገፊ ማሪ
እኔ ማለት በቃ ጎደሎ አክርማ
በሞላ ሀገር ኗሪ
ዳዊቴ ተደግሞ ከማክዳሽ ምድር ቅኔሽ ተጠጥቶ
በታሰረ አካሌ በጠፈርሽው ልብሽ
ሲከፋ ይኖራል እምባ ባይኑ አግቶ
➪➪➪➪ሲራክ ➮➮➮➮
ጥር 2 ሺህ ፲፪
@siraaq
#
@getem
@getem
@getem
@getem
©ሲራክ
ዳዊቴን ደግሜ ከማክዳሽ ምድር
ቅኔን ተግቻለሁ
በታሰረ አካሌ ያሰርሽው ልብሽን
ሳስፈታ ኑሬያለሁ
ቅኔሽን ተግቼ አጥቼሽ እያለሁ ....
ካሰረኝ ልብሽ ዳር በማይፈታኝ ወኔ
ምን ልሆን መጣለሁ?
አየሽ አንቺ አካሌ
እኔ ማለት በቃ የመሄድ ፅዋ ነኝ
የተገፊ ማሪ
እኔ ማለት በቃ ጎደሎ አክርማ
በሞላ ሀገር ኗሪ
ዳዊቴ ተደግሞ ከማክዳሽ ምድር ቅኔሽ ተጠጥቶ
በታሰረ አካሌ በጠፈርሽው ልብሽ
ሲከፋ ይኖራል እምባ ባይኑ አግቶ
➪➪➪➪ሲራክ ➮➮➮➮
ጥር 2 ሺህ ፲፪
@siraaq
#
@getem
@getem
@getem
@getem
✤✣ይታይሽ የኔ አለም✣✤
ይታይሽ የኔ አለም
አዎን ተመልከቺ
አስተውይ እናቴ....
የእህቶቼን ሳቅ
የልጆችሽን ድምፅ
ሳጣው ከሰፈሬ።
፨፨፨፨፨፨
አዎን ኢትዮጵያዬ
በወንዞች በሳርሽ
በእርሻ ባፈርሽ
ቦርቀው ያደጉት
እነዛ ልጆችሽ......
ዛሬ ምነው ጠፉ
ደብዛ ተሠወረ
ማን ቀማሽ ከእጆችሽ።
፨፨፨፨፨፨፨
አዎን የኔ ልእልት
የሉም ከቤታቸው
ቀዬ መንደራቸው
ብቻውን ይጮሃል..
እናትም ተጨንቃ
አይኗ አንባን ያነባል።
ህፃናት አጥተዋል
ጡትን ከአፋቸው....
የእናታቸው መጥፋት
እንባ እያስነባቸው።
ያልተዘጋው ማጀት
ዛሬም አፉን ከፍቷል ....
እምዬ ከሌለች
እታአለም ካልመጣች
አሻፈረኝ ብሏል።
፨፨፨፨
እናም እታለሜ
አዎን አስተውዪ
የህዝቦችሽን ግፍ
የአጥፊዎችሽን ደባ ...
የእህቴን በደል
የቀሚሷን እንባ።
አዎን ተመልከቺ
መፍትሔ የሌለው
ጩኸቴን አድምጪ
✣✣✣✣✣
እናም ኢትዮጵያዬ
እስኪ ጠይቂያቸው
ወንዘና ተራራ
አእዋፍ ዛፎቹን ..
ጋራ ሸንተረሩን
መስካመስክ ዋሻውን ..
አይቻለሁ ያለ
ካለ..
የሲቃን ድምፅ
ያደመጠ ...
የሀዘንን እንባ
የጠረገ...
የእምዬን ፍርሀት ተመልክቶ
ለእህቶቹ ተቆርቁሮ
አንደራሱ የታገለ
እስኪ ጠይቂ ካለ !!!!!!
✍ተፃፈ @Mak_bale
23.5.2012
@getem
@getem
@getem
ይታይሽ የኔ አለም
አዎን ተመልከቺ
አስተውይ እናቴ....
የእህቶቼን ሳቅ
የልጆችሽን ድምፅ
ሳጣው ከሰፈሬ።
፨፨፨፨፨፨
አዎን ኢትዮጵያዬ
በወንዞች በሳርሽ
በእርሻ ባፈርሽ
ቦርቀው ያደጉት
እነዛ ልጆችሽ......
ዛሬ ምነው ጠፉ
ደብዛ ተሠወረ
ማን ቀማሽ ከእጆችሽ።
፨፨፨፨፨፨፨
አዎን የኔ ልእልት
የሉም ከቤታቸው
ቀዬ መንደራቸው
ብቻውን ይጮሃል..
እናትም ተጨንቃ
አይኗ አንባን ያነባል።
ህፃናት አጥተዋል
ጡትን ከአፋቸው....
የእናታቸው መጥፋት
እንባ እያስነባቸው።
ያልተዘጋው ማጀት
ዛሬም አፉን ከፍቷል ....
እምዬ ከሌለች
እታአለም ካልመጣች
አሻፈረኝ ብሏል።
፨፨፨፨
እናም እታለሜ
አዎን አስተውዪ
የህዝቦችሽን ግፍ
የአጥፊዎችሽን ደባ ...
የእህቴን በደል
የቀሚሷን እንባ።
አዎን ተመልከቺ
መፍትሔ የሌለው
ጩኸቴን አድምጪ
✣✣✣✣✣
እናም ኢትዮጵያዬ
እስኪ ጠይቂያቸው
ወንዘና ተራራ
አእዋፍ ዛፎቹን ..
ጋራ ሸንተረሩን
መስካመስክ ዋሻውን ..
አይቻለሁ ያለ
ካለ..
የሲቃን ድምፅ
ያደመጠ ...
የሀዘንን እንባ
የጠረገ...
የእምዬን ፍርሀት ተመልክቶ
ለእህቶቹ ተቆርቁሮ
አንደራሱ የታገለ
እስኪ ጠይቂ ካለ !!!!!!
✍ተፃፈ @Mak_bale
23.5.2012
@getem
@getem
@getem
~~የመሔዷ መምጣት~~
"""""""""""""""""""""""""""
በ👉መኮንን አልማው ✍ ተፃፈ👈
''""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ቅርብ ሳለ ፍቅሯ
ሩቅ ሆኖ አዳሯ
የአይኗን ብርሃን በአይኔ ለማየት ጓጉቼ
ገላዋን በጣቴ መዳበስ ሰስቼ
ናፍቆቷን አውርቼ
ነይ ስላት... ነይ ስላት
የመፈለግ ኩራት
ልቧን ስለሞቀው ዝና እየመሠላት
ቆማ ስትወላውል
ጊዜዋን ስትገድል
እንደ ኤሳው በኩር ዕድሏን ለውጣው
መምጣቷን ገድሎ ነው መሔዷ የመጣው!
""""""""""""""""""""/""""'/""""""""'/""""""""""""""""""
..............23/05/2012/ዓ.ም~ሀዋሣ
@getem
@getem
@getem
"""""""""""""""""""""""""""
በ👉መኮንን አልማው ✍ ተፃፈ👈
''""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ቅርብ ሳለ ፍቅሯ
ሩቅ ሆኖ አዳሯ
የአይኗን ብርሃን በአይኔ ለማየት ጓጉቼ
ገላዋን በጣቴ መዳበስ ሰስቼ
ናፍቆቷን አውርቼ
ነይ ስላት... ነይ ስላት
የመፈለግ ኩራት
ልቧን ስለሞቀው ዝና እየመሠላት
ቆማ ስትወላውል
ጊዜዋን ስትገድል
እንደ ኤሳው በኩር ዕድሏን ለውጣው
መምጣቷን ገድሎ ነው መሔዷ የመጣው!
""""""""""""""""""""/""""'/""""""""'/""""""""""""""""""
..............23/05/2012/ዓ.ም~ሀዋሣ
@getem
@getem
@getem
የውጊያ ስልት
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ሙሴ በበትሩ
ፈርኦን በጦሩ
ኤርትራ ባሕር ላይ ፣ ጦርነት ጀመሩ፡፡
።።።።
ሙሴ በበትሩ…
ግዙፍ ባህር ከፍሎ ፣ ህዝቡን አሻገረ
ፈርኦን በጦሩ
ከነ ወታደሩ
ባሕር ሰጥሞ ቀረ፡፡
።።፣፣
ውጊያ የማይችል ሕዝብ
ግዙፍ ባሕር ከፍሎ ፣ በተዓምር ሲሻገር
ሌላ የውጊያ ስልት
ቀይሮ ይመጣል ፣ ቢሰምጥም ወታደር፡፡
እ
ን
ደ
ዚ
ህ
።
የተሻገረ ህዝብ
ለቀሪ መንገዱ
አሳ እያጠመደ ፣ ከባህር ሲያወጣ
የፈርኦን ወታደር
ሞቶ ለመዋጋት
በአሳ ገላ ላይ ፣ እሾህ ሆኖ መጣ!!!
።።።።
።።።፣
"አሳን መብላት
እንዳይወጋህ ፣ በብልሃት!"
@getem
@getem
#jeko
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ሙሴ በበትሩ
ፈርኦን በጦሩ
ኤርትራ ባሕር ላይ ፣ ጦርነት ጀመሩ፡፡
።።።።
ሙሴ በበትሩ…
ግዙፍ ባህር ከፍሎ ፣ ህዝቡን አሻገረ
ፈርኦን በጦሩ
ከነ ወታደሩ
ባሕር ሰጥሞ ቀረ፡፡
።።፣፣
ውጊያ የማይችል ሕዝብ
ግዙፍ ባሕር ከፍሎ ፣ በተዓምር ሲሻገር
ሌላ የውጊያ ስልት
ቀይሮ ይመጣል ፣ ቢሰምጥም ወታደር፡፡
እ
ን
ደ
ዚ
ህ
።
የተሻገረ ህዝብ
ለቀሪ መንገዱ
አሳ እያጠመደ ፣ ከባህር ሲያወጣ
የፈርኦን ወታደር
ሞቶ ለመዋጋት
በአሳ ገላ ላይ ፣ እሾህ ሆኖ መጣ!!!
።።።።
።።።፣
"አሳን መብላት
እንዳይወጋህ ፣ በብልሃት!"
@getem
@getem
#jeko
❤2
IMG_3490.jpg
172 KB
"የወንድ ምጥ ያማል!"
"የወንድ ምጥ ያማል" ብሎ ሲፅፍ አንዱ
"የሴት ልጅ ይብሳል" ብለው ሌሎች ካዱ!
ፃፊውም 'ካጅውም ያው አዳም ነው ወንዱ
በበለስ ፍሬና በሷ የወረዱ, ከዛ የተዋረዱ::
እርሱስ ቀጥ ያለ ነው የርሷ ግን ጠማበት
ግራ ጎን አጥንቷ ቆልመም ያለችበት
ሊያቀናት ቢሞክር 'ምትሰበርበት!
ግን እንዴት ሆኖ ነው የወንድ ምጥ 'ሚብስ?
በየወሩ አበባው ከማጀቱ 'ሚፈስ?
ነፍስ ጡሮ አንጀቱ እስኪወልድ 'ሚያለቅስ?!
.........እናስ? ደሞ ከዚያስ?!
ግን እንዴት ሆኖ ነው የወንድ ልጅ ጫንቃው
በዘመኑ ላንዴ ዝንተዓለም አፍቅሮ ሁሉን 'ሚንቀው
ይከዳው የሷ ልብ ወንድነቱን ነጥቆት የሚሆን አለቃው
የሚጫወትበት ሲያነሳ ሲጥለው ልቡን ሲነርተው
እንግዲያስ.....
በልቧ ጭካኔ በወሳኝነቷ እሷን የሚያስመልጥ
አንተን የሚያስላዝን ካንተ ዘንድ የማይቆርጥ
ከእግዜር የተቸራት ደሞዟ ነው የርሷ ምጥ!
ስለዚህ አዳም ሆይ.....
የልቧን ቅመም ቋት ላትስተካከለው ላትሰፍረው አትሩጥ
ማጀቷን ላትኖር የሷን ልብ አትመኝ አርግዘህ ላታምጥ
ለአፍቃሪ ልብህ ምጥህ ጭንቀትህ ነው በል አርፈህ ተቀመጥ!!!
©️አቤንኤዘር ጥላሁን/papi
Feb. 1, 2020
@getem
@getem
"የወንድ ምጥ ያማል" ብሎ ሲፅፍ አንዱ
"የሴት ልጅ ይብሳል" ብለው ሌሎች ካዱ!
ፃፊውም 'ካጅውም ያው አዳም ነው ወንዱ
በበለስ ፍሬና በሷ የወረዱ, ከዛ የተዋረዱ::
እርሱስ ቀጥ ያለ ነው የርሷ ግን ጠማበት
ግራ ጎን አጥንቷ ቆልመም ያለችበት
ሊያቀናት ቢሞክር 'ምትሰበርበት!
ግን እንዴት ሆኖ ነው የወንድ ምጥ 'ሚብስ?
በየወሩ አበባው ከማጀቱ 'ሚፈስ?
ነፍስ ጡሮ አንጀቱ እስኪወልድ 'ሚያለቅስ?!
.........እናስ? ደሞ ከዚያስ?!
ግን እንዴት ሆኖ ነው የወንድ ልጅ ጫንቃው
በዘመኑ ላንዴ ዝንተዓለም አፍቅሮ ሁሉን 'ሚንቀው
ይከዳው የሷ ልብ ወንድነቱን ነጥቆት የሚሆን አለቃው
የሚጫወትበት ሲያነሳ ሲጥለው ልቡን ሲነርተው
እንግዲያስ.....
በልቧ ጭካኔ በወሳኝነቷ እሷን የሚያስመልጥ
አንተን የሚያስላዝን ካንተ ዘንድ የማይቆርጥ
ከእግዜር የተቸራት ደሞዟ ነው የርሷ ምጥ!
ስለዚህ አዳም ሆይ.....
የልቧን ቅመም ቋት ላትስተካከለው ላትሰፍረው አትሩጥ
ማጀቷን ላትኖር የሷን ልብ አትመኝ አርግዘህ ላታምጥ
ለአፍቃሪ ልብህ ምጥህ ጭንቀትህ ነው በል አርፈህ ተቀመጥ!!!
©️አቤንኤዘር ጥላሁን/papi
Feb. 1, 2020
@getem
@getem