ግጥም ብቻ 📘
64.2K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
እስቲ ልጠይቅህ?
(ሚካኤል አስጨናቂ)
#ጉልበት በአዕምሮ ላይ ክንዱን ሲያበረታ
የሴትነት ክብር
እንደዋዛ ታይቶ ፣ በነውር ሲረታ
ፅልመት ገሀድ ወጥቶ ብርሀን ሲገታ
ይሄን ሁሉ አይተን
ከዳስ ተቀምጠን
አልሰማንም እያልን በዝምታ እንዳናልፍ
እንባ ባህር ሆኖ ተንጣሏል ከበራፍ ።
አዎን በዚህ ወራት!
የአያት የአባቶቼ ተረት እውን ሆኖ
በዝንጀሮ ዳኛ በገደል ፍትህ ቤት እውነቷ ተዳፍኖ
ከዳር ተቀምጣ ለቅሶ በምትዘራ
በአንዲት ምስኪን ሴት ብዙ እውነታዎች ሀገር ተወጥራ
እንዲሁ እንደዋዛ ፣ እንዲሁ እንደዘበት
ውለታዋን ሽሮ ፣ ክዶ ለመገኘት
እናት እያነባች ...
አልሰማሁም ብሎ ፣ ዋሽቶ ለመቧለት
ይቻላል ወይ እውነት ??

#ፍትህ ለታገቱ ሴት እህቶቻችን

@getem
@getem
@getem
ሰይጣን ቅጣትህ ነው



"ሀጥያቴ" ነው አትበል
ኮሽ ባለ ቁጥር
" በደሌ" ነው አትበይ
ኮሽ ባለ ቁጥር


ሀጥያቴ በደሌ
'ምትሉት ሽንገላ
ከጀርባው ያዘለው

ሰይጣን አሳሳተን
የሚል አንድምታ አለው

እንዲህ ነው እንግዲህ
ሰው ድንቁርናውን
ማመን ሲቸግረው
ጥፋቱን በሙሉ
በድንቁርና ልጅ
ማሳበብ ነው ሚያምረው


እንዳውም እንዳውም
ማንም ተነሳስቶ
ስሙን እንዳያጎድፈው
የሰይጣንን ትርጉም
እዚ ታች ልፃፈው


በድንቁርናህ ልክ
የ -ተ-ፈ-ለ-ፈ-ለ-ው
አሳሳችህ ሳይሆን
ሰይጣን ቅጣትህ ነው
በካሽ የምትከፍለው


አምደማሪያም ጠይብ(ፊዳው)

@getem
@getem
@saveme24
👍1
ሰይጣን ቅጣትህ ነው



"ሀጥያቴ" ነው አትበል
ኮሽ ባለ ቁጥር
" በደሌ" ነው አትበይ
ኮሽ ባለ ቁጥር


ሀጥያቴ በደሌ
'ምትሉት ሽንገላ
ከጀርባው ያዘለው

ሰይጣን አሳሳተን
የሚል አንድምታ አለው

እንዲህ ነው እንግዲህ
ሰው ድንቁርናውን
ማመን ሲቸግረው
ጥፋቱን በሙሉ
በድንቁርና ልጅ
ማሳበብ ነው ሚያምረው


እንዳውም እንዳውም
ማንም ተነሳስቶ
ስሙን እንዳያጎድፈው
የሰይጣንን ትርጉም
እዚ ታች ልፃፈው


በድንቁርናህ ልክ
የ -ተ-ፈ-ለ-ፈ-ለ-ው
አሳሳችህ ሳይሆን
ሰይጣን ቅጣትህ ነው
በካሽ የምትከፍለው

@getem
@getem
@getem
#አምደማሪያም ጠይብ(ፊዳው)
1
የታወሩ ነፍሶች
©ሲራክ
አንባቢው ጀግና ሰውዬ
ባለ ስል አእምሮ ያለው
ከቅኔ አሸት መፅሀፎች
ያሻውን ቀጥፎ የበላው
አውሮፓን በቀኙ ረግጦ
ሀገሩን በግራ አሳልጦ
እራሱን ማንበብ ያልቻለው
ምን ልቦናን ቢያጣ ነው????
======//=======
@siraaq
#
@getem
@getem
@getem
     #ቀናሽ አሉ
በቆምሽበት ሌላ ሳቆም
ማዶ ሆነሽ አየሽ አሉ
ስሜን ጠራሽ ጮሽም አሉ
አውለበለበሽ በጅሽ ሁሉ
በእንባ ጠፋ የአይንሽ ኩሉ

ግን ስህተቱ አንቺ ጋ ነው
አጉል ቅናት መለየት ነው
ሺ ቢመጣ ሚወደድ ሰው
ንግስቴ አንቺ
 ፍቅሬ እኮ ላንቺ ነው

                 ተፃፈ በብላቴናው ብዕር
--------------//----------
@getem
@getem
@getem
:::::::::::ሐሌታ ስርዞች:::::::::::

በኖርክበት ምድር ባለህበት መሬት
ለማኖርህ እንጂ ለመሮር አትሙት
ስለየቱ ገላህ ካፈር ለተሰራው
ሰገነትም ሆነክ ራስህን አድነው
ከወረተኛ ሰው የታነፅኩኝ ልባም
ህመሜን ለመፃፍ ወረቀት ምቃርም
ካሌታዎች ተርታ ከልለችው አለም
ወይ ኖሬ አላለኩኝ ወይ ሞቼ አላወኩም

@getem
@getem
@getem
#ሳምሶን_ጌቱ
Event - Goshu Meda Camping Trip ⛺️

Date :- February 1 - 2, 2020 🎈

Departure Spot - Piassa Tayitu Hotel 🎪

Departure Time - 2:00Am Local time 🚩

Price - 1199.99 🙈💰

🎉🎊Package 🎋🎊

🔵🚍 - Tourist level Bus
🔴⛺️- Tent, campfire &tea
⚫️🍝 - Traditional Roasted meat ( 🐏), Lunch and snaks🍟🍤
⚪️ 2 liter Bottled water
🔵 Park entrance with Guide
🔴photograph 📷

Brought to you by Sunset Hiking Group
for more join the
🔸channel @sunsethiking
🔹the group @sunsethike
🔻📷 @sunsetphotography

🎫 tickets available at
@Paappii
@thomaskagnew
@useryise
@Chere_daregot
_________________________

በተስፋ ቃል ልብ ውስጥ ሺህ ንጋት ቢኖርም፣
ዛሬ ካልተኖረ "ነገ"ነት አይሰምርም፡፡

እናም፤

በትላንት ዛሬ በቅብብል አለም፣
ከዛሬ በስተቀር ነገ ያንተ አይደለም፡፡

@abiye12

@getem
@getem
@getem
ለባለ ልደቷ!
🎂❤️❤️🎂

............ቅኔ ነው፣
.......መንፈስ ነው፣
....ረቂቅ ዜማ ነው፣
ይናገራል አይንሽ፡ይሰማል ድምፅ አለው፣
መለኮት ነው ቋንቋው፡ ወትሮም የፍቅር ሰው፣
አ•••••ፈ•••••ቅ•••••ር•••••ሻ•••••ለ•••••ሁ!!❤️❤️❤️


ሰው የመሆን ዜማ!!
•፨፨፨•፨፨•፨፨፨•፨፨•
ምክረ ቃልሽን ተቋድሶ፡ ልቤ በቅን ተቃና፣
ተግሳጽ ቃልሽን አድምጦ፡ መንፈሴ በተስፋው ፀና፣
...............................ልሳኔ አንቺን ዘመረ፡
ይሄው ሀሳቤ ረጋ፡ ውጥን እቅዴ ተሳካ፡ ቁስል ህመሜ ተሻረ፣
.
በፍቅር በክብር፡ ከስጋ ከፍ ሲል፡ ወደ ነፍስ ሲጠጋ፣
ለካስ ሴትነት ነው፡
..............ሰው የመሆን ግምት፡ ሰው የመሆን ዋጋ፣
.
ልቤ ከምነት ላቀ፡ በሐቅሽ ታሰረ፣
ድሮም ከሴት ልጅ ነው፡ እስትንፋስ ያገኘ፡ ህይወት የጀመረ፣
.
ሔድ ይለኛል እግሬ፡ ና! ይለኛል መንገድ፣
በጥዑም መዓዛሽ፡ ይጠራኛል መውደድ፣
ይታየኛል ታቦት፡ ይሰማኛል ዜማ፡ ያውደኛል እጣን፣
ሰው የመሆን ቅኝት፡ ህይወት ባዘለ ቃል፡ ልሳንሽ አዚሟን፣
.
..............ከንፈርሽ ንዳዱ፣
..............የፅድቅ መንገዱ፣
ነበልባል ነው እሳት፡
ከምነት ይለካካል፡ ከፀበል ይልቃል፣
.............አቃጥሎ ለብልቦ፡ ህመም ይፈውሳል፣
.
ፈገግታሽ ዜማ ነው፡
...................ሳቅሽ እምቅ ቅኔ፡ ወደ ልብ ይሰርፃል፣
ቅዳሴ ነው አዛን፡ እርግማንን ፍቆ፡ ባርኮ ይቀድሳል፣
.
..............እቅፍሽ ግለቱ፣
..............የምድር ጀነቱ፣
በማዓዛው ጣእም፡ በሙቀቱ ብርታት፡ በገላሽ ያነግሳል፣
በፍቅር ሞሽሮ፡ በመውደድ አስጊጦ፡ ህይወት ያጣፍጣል፣
.
ቅኔ ነሽ አንቺዬ፡
የቅን ልብ ርስቱ፡ የፍቅር ሙክራቡ፡ የውበት እትብቱ፣
የመላው ተፈጥሮ፡ ያፅናፈ አለሙ፡ ስሪቱ ግኝቱ፣
አንቺ ነሽ ልሳኑ፡ አንቺ ነሽ ቅኝቱ፡
.
ወጌሻ ነው ቃልሽ፡
በምክርሽ አንቅቶ፡ ስብራት ጠግኖ፡ መንፈስ ያበረታል፣
ፍቅር ነው ዙፋንሽ፡
በማዓዛው ጣእም፡ በሙቀቱ ብርታት፡ በገላሽ ያነግሳል፣
.
በፍቅር በክብር፡ ከስጋ ከፍ ሲል፡ ወደ ነፍስ ሲጠጋ፣
ድሮም ሴትነት ነው፡
..............ሰው የመሆን ግምት፡ ሰው የመሆን ዋጋ፣

ለህይወቴ ፋኖስ አ ፈ ቅ ር ሻ ለ ሁ ኝ❤️❤️❤️❤️❤️❤️


እንኳን ተወለድሽልኝ❤️❤️❤️እማፈቅርሽዋ🎂❤️🎂😘🎂❤️

@getem
@getem
@Nagayta
👍2
ደህና ነኝ!
[ሰለሞን ሣህለ]

"ደህና ነህ?" እያሉ
ለጠየቁኝ ሁሉ
"ደህና ነኝ" ልበል ወይ?
ደህና ነዉ እንዲሉ
ብየ ብጠይቀዉ
"ደህና መሆንህን
ከልባቸዉ ሽተዉ ለጠየቁህ ቀርቶ
ደህና መሆንህም ለሚያሳምማቸዉ
ይበልጥ እንዲያማቸዉ ደህና ነኝ በላቸው።

@getem
@getem
@getem
👍1
አዎ እኔ ደህና ነኝ
============
አዎ እኔ ደህና ነኝ፣
ብቻ ዝም ብሎ እራሴን ያመኛል
የወገኔ ስቃይ፣
አንቅልፍ እየነሳ ይቀሰቅሰኛል!
አዎ እኔ ደህና ነኝ፣
ሽብር አናውዞታል የልቤን ከተማ
ሰው በሞተ ቁጠር፣
ደረት እየደቃሁ አበራለሁ ሻማ!
አዎ እኔ ደህናነኝ፣
እብደት ተጠግቶኝ ዝም ብዬ ስቃለሁ
ሀገሬ ቁጭ ብዬ፣
ልክ እንደ ባይተዋር ሀገር ናፍቃለሁ!
አዎ እኔ ደህና ነኝ፣
ወገኔ ባልኩት ሰው ዘመኔን ምጉላላ
ሆዴን እየራበው፣
በቀን ሀያ ግዜ መከራ ምበላ!
እናም፣
ሀዘን አሰቃይቶኝ ልቤ እየበገነ
አሁን ያልኩት ነገር ደህንነት ከሆነ
አዎ እኔ ደህና ነኝ!

©እዮብ ዘ ማርያም
@getem
@getem
#jeko
#አልገጥምም


ጦረኛ ተዋጊ
የጎሳ ነፃ አውጪ ፥ #በቀፈቀፈ አገር
ከብዕር በዘለል
ባፈሙዝ ቃታ ነው ፥ ብዙ የሚነገር
በኔ.....አገር
ሲወድ ፣ ሲጠላ
ለሀዘን ለደስታው ፥ ባሩድ እየማገ
ሲፎክር ፣ ሲሸልል ፥ በጥይት ላደገ
ካደባየው በላይ
ከመግደሉ በላይ ፥ አፈር ከከተተው
የጣለው ሲነሳ
ተኩሶ ሲስት ነው ፥ ፀፀት የሚያኝከው ።
ይህንን ስታውቂ...
አጠገቤ ቆሞ ፥ የቀኑ ጃዊሳ
አረ ጎራው ሲለኝ ......ሊሸልል ሲነሳ
ስለ #ሀገር ግጠም
ለምን ትይኛለሽ ? ሸጉበሽ ከክንዴ
ቃልሽን የሰማ...
እንጋጠም ቢለኝ
ማስታወሻ ደብተር ፥ ጋሻ ይሆናል እንዴ?

#አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)

@Abr_sh


@getem
@getem
@getem
አራራይ
°°°°°°°
የኔ እዉነት መሸነፌ
የኔ ጠላት መሸነፌ
የኔ አቅም መሸነፌ
አትናፍቀኝ ትለኛለች -
በሷ መኖር ተለክፌ፣

ያ'ለም ነገር አያጓጓኝ
ያለኝ አድጎም አያስመካኝ።
ይሰለቻል ሁሉ ኑሮ…
ድግግሞሽ ቀጣይ -ድሮ፣
ይታክታል አፈር ላ'ፈርሥ
ሆኖ ላያልፍ መንፈራፈር…
ናፍቃኝ እንጂ ምስራቅ ያየሁ፣
በፍቅሯ እንጂ ቀን የለየሁ፣
ምን ያጓጓል ሰባት ዓለም
መኖሯ እንጂ ኸይር ለምለም…
እሷ ለኔ መዳን መምጫ
እሷ ለኔ ፀሐይ መዉጫ
ከታካች ቀን ከጨለማዉ፣
ማርያም መንገድ የማምለጫ…

እኔ ለሷ ጎርፍ ደራሽ
እኔ ለሷ ግንቧን አፍራሽ፣
ወገብ አስራ ከካበችዉ
ጥርሷን ነክሳ ካፀናችዉ፣
ዓለም መሳይ አላቃቂ
በግራ መንገድ < ቀኝ አጥማቂ፣

የኔ እዉነት መሸነፌ
የኔ ጠላት መሸነፌ
የኔ አቅም መሸነፌ
አትናፍቀኝ ትለኛለች -
በሷ መኖር ተለክፌ፣

እንዴት ልቻል እሷን መተዉ
እንዴት ቻለች እኔን መተዉ፣
ምን ብከፍ በመዉደዴ
ምን ብፀና በንዳዴ፣
ችዬ ነበር እንደ ቃሏ
ናፍቆት እንጂ የማይከላ…

አዉ አቃለሁ እንዳቅሜ
እንደ መቻል እንደ ቆሜ፣
ያኖረኝም የኖረኝም
ይሁን ብዬ በኔ ስፈርድ፣
ችዬበት ነዉ ናፍቆ መንደድ…

እና ለምን ይከፋታል…?
እና ለምን ይነዳታል…?
ያዉ ንገሯት ቁርጧን ትወቅ…
መናፈቄ ዓለሜ ነዉ
መተከሌ- መቆም መፅደቅ…!
ቢቻ ትዉሰድ ይቅርታዬን…
የሞኝ ፍቅር ዉትወታዬን…



"ናካይታ"

አ ፈ ቅ ር ሻ ለ ሁ ኝ❤️


@getem
@getem
@Nagayta
👍2
እናፍቅሻለሁ ! !
(በ ሰለሞን ሳህለ)
.
ልንገርሽ አይደለ
ከፍ ካለው ቦታ ከፍ ብዬ ቁሜያለሁ
ሰው ያለ አይመሥለኝም ባንቺ ቆርቤያለሁ
አሁንም አሁንም እናፍቅሻለሁ...
ሥላንቺ ከሆነ፣ ብርቱ ነኝ ኃያል ነኝ!
የሸረኞች ደባ፣ የተፈጥሮ እንቅፋት ችሎ እማያቆመኝ
ሐብሌ አይደለሽም አንገቴ ላይ የዋልሽ
ቀለበቴም ሳትሆኝ ጣቴ ላይ ያኖርኩሽ
ዕድሜ የማይፍቀው ንቅሳቴ አንቺ ነሽ!...
ያንተው ነኝ ብለሽኝ
የራስሽ ነኝ ብዬ...
እንዴት አልናፍቅሽ ናፍቆት አበባዬ?
መናፈቅስ በእርሱ - በእርሱ ያምርበታል፣
ተብሎ እሥከሚወራ
ተብሎ እሥከሚነገር
እናፍቅሻለሁ አንቺ የኔ ፍቅር!...
...
እንኳን ከኔ ጠፍተሽ...እንኳን ከኔ እርቀሽ
አጠገቤም ሆነሽ ትናፍቂኛለሽ...
የመዋደድ ኬላ መድረሻ ደንበሩ
መናፈቅ እኮ ነው የፍቅር ደም ሥሩ
አለሽ ጨረቃ ላይ
አለሽ ፀሐይዋ ላይ
አለሽ ሰማዩ ላይ
የትም አይሻለሁ የኔ ሙሉ ክፋይ
ተራራው አንቺ ነሽ
ባሕር ወንዙ አንቺ ነሽ
አገር ምድሩ አንቺ ነሽ
የትም ቦታ ሆኜ የትም ቦታ ሆነሽ
እናፍቅሻለሁ ትናፍቂኛለሽ...
...
ርዕሰ አንቀጽ ሠበር ዜና አንቺ ነሽ
ትረካዬ አንቺ ነሽ
ገሃድ ሕልሜ አንቺ ነሽ
ልብ ወለዴ አንቺ ነሽ
ቲያትሬ አንቺ ነሽ
ሰኞና ማክሰኞ ሮብ ሐሙሴ ነሽ
ዓርብ ቅዳሜ ነሽ
እለተ ሰንበቴ ሁሌ ምሳለምሽ
ማረፍያዬ እሁድ ነሽ
የትም ቦታ ሆኜ የትም ቦታ ሆነሽ
እናፍቅሻለሁ ትናፍቂኛለሽ ! ! !
@getem
@getem
#jeko
❗️Only 2 more days left!(ሁለት ቀናት ብቻ ይቀራሉ!)
⛺️ ⛺️ ⛺️ የካንፒንግ ጉዞ ወደ ጎሹ ሜዳ ⛺️ ⛺️ ⛺️

የመነሻ ቀን: - ጥር 26/2012🎈
የመመለሻ ቀን: - ጥር 27/2012🎈
የመነሻ ቦታ - ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል 🎪
የመነሻ ሰዓት - 2: 00 🚩

ዋጋ - 1199.99 🙈💰🙈💰

🎉🎊 “ጥቅል” 🎋🎊
🔵🚍 -የትራንስፖርት አገልግሎት(በቱሪስት ደረጃ አውቶቡስ)
🔴⛺️-ቴንት(ድንኳን)፣ ሻይ ቡና፣ ካንፕፋየር
⚫️🍝 - የተጠበሰ የበግ ሥጋ (🐏)፣ ምሳ እና እስናክ(ሃይል ሰጪ ምግቦች)🍟🍤
⚪️ 2 ሊትር የታሸገ ውሃ
🔵 የጋይዳንስ ክፍያ ከፓርክ መግቢያ ጋር
🔴ፎቶግራፍ ፎቶግራፍ 📷

በሰንሴት ሃይኪንግ የተዘጋጀ
የበለጠ መረጃ ፓናሎቻችንን ይቀላቀሉ
🔸channel @sunsethiking
🔹the group @sunsethike
🔻📷 @sunsetphotographyy

🎫ቲኬቶች
@Paappii
@thomaskagnew
@useryise
@Chere_daregot
ጋር ይገኛሉ
እኔ ተውኩሽ እንጂ፣ ማን አባቱ ቀማኝ
ከኔ ለባሰበት፣ ሰጠውሽ ለለማኝ።

(ገጣሚ:--ልዑል ሀይሌ)


@getem
@getem
የጃገማ ፀሃይ!!!!!!!


ጠየቀችው ልጅት፣
ይህንን ሳተና፣ይህንን ጅግሳ፣
ሲራመድ የኖረ፣
ሲጨፍር የኖረ፣
በባንዳ መቃብር፣በሰላቶ ሬሳ።


ደግማ ጠየቀችው፣
ጃገማ ግን ማነው????
የኬሎ ልጅ ማነው????
እንደ አደይ አበባ፣
እንደ መስቀሏ ወፍ፣ የተሽሞነሞነው፣
በአበሻ ጦር ሜዳ፣
በዲሞፍተር ቃንቄ፤ ሜዳይ ያሸገነው?


ኧረ ይህ ሰው ማነው?????
እየገራረማት፣
እየደናነቃት፣
ዘመን በማይሽረው፣
በአባቷ ወላፈን፣ በቃንቄው ተገርማ፣
ጠየቀች አባቷን፣
በጨዋ ልጅ ወገብ፣ ጎንበስ ቀለስ ብላ፣
ጃገማ አባ ዳማ፣
የበረሃው ግለት፣ የናዳው ስባሪ፣
የጠላትን ምሽግ፣
የሰላቶን ክምር ደርምሶ ፎካሪ።


ጀግና ልብ እንጅ የለውም ምላስ፤
እንኳንስ ስሙ ጥላው የሚዋስ።
ብሎ ጃገማ፤
አልጋውን ንቆ ድንገት ቀጥ አለ፤
በሃሳብ ጥሻ፤
በትዝታ ጦር እየሸለለ።


""" ዘራፍ!!!!!!!
ዘራፍ!!!!!!
ዘራፍ ፣አካኪ ዘራፍ!!!!!!!!
ጃገማ ኬሎ፣
የጦቢያ ዶቃ፣ የዳማ ፈረስ፣
ጎራው ላይ ሲዘልቅ፣ ምሽግ እሚያፈርስ።
ሃይ ዘራፍ ብሎ፣ ዘሎ ሲገባ፣
ይዝረጠረጣል ባንዳና ሌባ።
ዘራፍ ጃገማ ባለውጅግራ፣
ጎጆ መስርቷል፣
ቃል ኪዳን አስሯል፣ ከጦቢያ ጋራ።
ስማ ንገረው፣ ያን የባንዳ ዘር፣
እንጫጫዋለሁ፣ እንደ ጎመንዘር!!!!
የበጋው መብረቅ፣ የእሳቱ ጉማጅ፣
እንደ እርጥብ ቃሪያ፣
የሚለበልብ፣ ስሙ የሚፋጅ፣
የአባ ዳማ ልጅ፣
ከዘር ማንዘሩ፣ ጠላት አዋራጅ።""

"""
ብሎ ሲፎክር
እንደ ፈላ መጅ፣ እንደጀበና፣
ፊቱ ለበሰ ፣
ኢትዮጲያ የሚል፤ ቀስተ ደመና።


ይች ልጅ ጠየቀች፣
አባቷን ደጋግማ፣ ደጋግማ ጠየቀች፣
በአበሻ ልጅ ማእረግ፣
የዚህን ጃውሳ፣ አይን አይኑን እያዬች።
ጅግሳው ጃገማ፣
በሸገነው ቃሉ፣ ባጭሩ ነገራት፣
መቼስ የጀግና ልጅ፣የአባት ወግ አይጠፋት።
ትክዝክዝ እንዳለ፣
እንባ እንዳቀረረ፣
ይኸው ይኸ ጀግና፣ እንዲህ ተናገረ፣


አየሽ የትምወርቄ፤
አርበኛ በደሙ፤
ጀግና በድምድሙ፤
በአጥንቱ መግሮ ፤በተሰራች ሃገር፤
ከሞት ይቆጠራል፤
ለሠላቶ ውላጅ፤
የሚቆራርሱት ጣቢታ መጋገር።


ባንዳ ቀኑ ገጥሞት፤
ወንበር የሰጡት ቀን፤ ሃገር ይወገሻል፤
አርበኛም ዱር ወዶ፤
ካገር ሞት የኔ ሞት፤
ይቅደምና ልሙት፤
እያለ ከቤቱ ከደጁ ይሸሻል።


ግን እንዲህም ሆኖ፤
በአርበኞቹ ጥላ፤
በደም የተዋጀ፤
በአጥንት የታጠረ፤
የነፃነት ቅኔ፤
በትውልዱ ቀለም፤
እየተማገረ ቅኔው እስኪፈታ፤
አይፈርስም ሰንደቁ፤
በአልብላቢት ከንፈር፤ በምላስ ሩምታ፤
ያኔ ይፈወሳል፤
ምን አገባኝ ይሉት፤ የዘመን በሽታ።


እየውልሽ ልጄ፤
የጃገማን ድንበር፤
የጃገማን ሰንደቅ፤
ቀስተ ደመናውን፤
ብጣሽ ጨርቅ እያሉ፤
በርኩሰት አፋቸው፤ ንቀው ያዋረዱ፤
በየመሸታው ቤት፤
ቂጡን ገልቦ ሚሄድ፤
ችው ችው የሚባል፤ ቡችላ ወለዱ።


እናምልሽ ልጄ፤
ሞተን የሰራናት፤
ወድቀን ያነሳናት፤
ኢትዮጲያ እምትባል፣
ገራሚ አገር አለች፣
እድሜዋን ፈጀችው፣
አርበኛን አዋርዳ፣ ባንዳ እየሰቀለች።
ዘመን ቡቱቶዋን፤
እከክዋን አራግፋ፤
ባንዳ ቤቱ ሲፈርስ፣
ሰላቶ ሲረክስ፣ ፊቱ ሲገረጣ፣
ያኔ ነው የኔ ልጅ፣
የጃገማ ፀሃይ፣
በአበሾቹ ሰማይ፣ ቀድማ የምትወጣ።
ኧረ ትውጣ!!!!!!!!!"
"""

( ብወደው፣ብወደው ለማልጠግበው፣ ለጄኔራል ጃገማ
ኬሎና ለልጁ የትም ወርቅ ጃገማ)

መልካም ልደት!!!💚💛❤️

(( ጃ ኖ ))💚💛❤️

@Nagayta
@getem
@getem
#እ-ህ-ቴ
አዎን ይሰማኛል
እረቀሽ ብጠፊ
መልክሽ ይታየኛል
የሰው ያለህ የሚል የሲቃማው ድምፅሽ አዎን ይሰማኛል
ተማፅኖ ልመናሽ ከሩቅ ይጠራኛል
ከመአድ ስቀርብ ተርቦ የሚጮኸው ሆድሽ እኔን ያስርበኛል
ትኩስ የአይን እንባሽ አይኔን እያቃጠለ
የደም እንባ እኔን ያስነባኛል
እህቴ
አረ ወዴት አለሽ
ውቧ እህት አለሜቱ
እርዛቱ እንዴት ያዘሽ እቴዋይቱ
ጀግናዋ ተማሪ ቁሩስ እንዴት ያዘሽ ብላቴናይቱ
የአፋኝሽ ዛቻ አረ እንዴት አረገሽ እህቴ ባለተስፋይቱ
ቱ ቱ ቱ ቱ ቱ ቱ
አረ ለኔ ያርገው
ወዴት ከተተብኝ
ምን ጅብስ በላብኝ
ምኑ የሰው ጅብ ነው አንቺን የበላብኝ
አልጮህ ያለ አፋኝ  -እህቴን- ከየት ከተተብኝ
ከየትኛው ዋሻ አንቺን ደበቀብኝ
የቱ መግነዣ ነው አንቺን የሳበብኝ
አልጮህ ያለ አፋኝ
የሰው በላ አፋኝ
እህቴን ከየት አረገብኝ
ወዴት ከተተብኝ
ከየት ደበቀብኝ
እምዬ ኢትዮጵያ
ዋሻሽ ሚስጥር እኮ ያዘብኝ
ሸለቆሽ የእህቴን መገኛ አልነግርህም አለኝ
ደንሽ አረንጓዴው እንዳልሰማ ሆኖ ዝምታ አበዛብኝ
እምዬ ልጅሽ ጠፍታ እርቃ እንዴት ይዝለቅልኝ
መላ በዪኝና ጫካሽን ጠይቀሽ
ዋሻ ሸለቆውን ሚስጥር አስፈትተሽ
እህቴን ከቤት መልሺልኝ



                         ተፃፈ በብላቴናው ብዕር
@getem
@getem
@getem
👍3
====================

"አጣ መነመነ"
"የለውም" ተብሎ ሰው እንዴት ይናቃል፣
ሰው ሆነው ለማለፍ ሰው መሆን ይበቃል፡፡

@abiye12

@getem
@getem
@getem
1