የአስተርዮ ማርያም!!!!!
የማሽላው ሃገር፤
የጁ ዶሮ ግብር፤ ኣላ ገዶ ነው፤
ጥንቅሹን ወልዲያ፤ ምን አበቀለው???
ጥንቅሹ ወልዲያ የበቀለውማ፤
ሸጋ ልጅ ዘርታው ነው፤
መቻሬ ሜዳ ላይ፤
በእነነየ ቱፍታ፤ በየጁ ከራማ።
በወይብላ ማርያም፤
በጉባርጃ ማርያም፤ በወለላይቱ፤
መቻሬ ውድመን፤
ዋልካውን ቢጭሩት፤
አፈሩን ቢያዋዩት፤ ጥንቅሽ ነው መሬቱ።
ላዩን በውድመን፤
ታቹን በሸህ ዳና፤
በአውጋሩ በአድባሩ እኔው ተመርቄ፤
ይኸው ዛሬ ድረስ፤
እርሻየ ጥንቅሽ ነው ከጉራ እስከ ወርቄ።
የጁን ያህል ሃገር፤
መርጦን ያህል ደብር፤
ያበቀለው ጥንቅሽ፤
በልቼ ነው እንጅ፤
ማር ከንፈር አድርጎ፤ አጣፍጦ ሚያኖረኝ፤
የማር ዘነብ ሚዜ፤
የነ ጥንቅሽ ወንድም፤
ለወዳጅ ነው እንጅ፤
ለሷሂብ ነው እንጅ፤ እኔን የሚገደኝ፤
ላሽከር ለሹምባሹ፤ አይሞቀኝ አይበርደኝ፤
ዘበናይ ወሎየ፤
ሰው ለክቶ ሚያድር፤ሰው ነው ያሳደገኝ።
መልኬ ጥቁር ውሃን፤
አላውሃን ጅረቱን፤ እየቆነጠረ ፤
ቱባው ማንነቴ፤
በሰውኛ ጠረን፤
በሰው መሆን ሚዛን እየተሰፈረ፤
በአዳምነት ወረት ፤
ጓዳና ማጀቴ እየተሞሸረ፤
መገን የኔ ነገር፤
ከድፍረስ ባህር ላይ፤
ጅረት እለያለሁ፤
ያውም እኔን እኔን፤ እኔን የመሰለ፤
በፍቅር ረመጥ፤
በሙሃባው እሳት የተንቀለቀለ፤
በሰውነት ቀለም፤
በሰው መሆን አጀብ፤
ነፍሱ የሸገነ፤ አይኑ የተኳለ፤
አላውሃ መሌው ዳር፤
ይጠብቃል ጓዴ፤
ርጥብ ማሽላውን ውልቢኝ እንዳዘለ፤
በናፍቆት አይኖቹ ፤
በራ በሩን ያያል፤
ደግሞ ለጥምቀቱ፤ ለአስተርዮ ማርያም ይመጣል እያለ።
እንዲህ ያለም የለ!!!!!!
((( ጃ ኖ))💚💛❤️
@getem
@getem
@Nagayta
የማሽላው ሃገር፤
የጁ ዶሮ ግብር፤ ኣላ ገዶ ነው፤
ጥንቅሹን ወልዲያ፤ ምን አበቀለው???
ጥንቅሹ ወልዲያ የበቀለውማ፤
ሸጋ ልጅ ዘርታው ነው፤
መቻሬ ሜዳ ላይ፤
በእነነየ ቱፍታ፤ በየጁ ከራማ።
በወይብላ ማርያም፤
በጉባርጃ ማርያም፤ በወለላይቱ፤
መቻሬ ውድመን፤
ዋልካውን ቢጭሩት፤
አፈሩን ቢያዋዩት፤ ጥንቅሽ ነው መሬቱ።
ላዩን በውድመን፤
ታቹን በሸህ ዳና፤
በአውጋሩ በአድባሩ እኔው ተመርቄ፤
ይኸው ዛሬ ድረስ፤
እርሻየ ጥንቅሽ ነው ከጉራ እስከ ወርቄ።
የጁን ያህል ሃገር፤
መርጦን ያህል ደብር፤
ያበቀለው ጥንቅሽ፤
በልቼ ነው እንጅ፤
ማር ከንፈር አድርጎ፤ አጣፍጦ ሚያኖረኝ፤
የማር ዘነብ ሚዜ፤
የነ ጥንቅሽ ወንድም፤
ለወዳጅ ነው እንጅ፤
ለሷሂብ ነው እንጅ፤ እኔን የሚገደኝ፤
ላሽከር ለሹምባሹ፤ አይሞቀኝ አይበርደኝ፤
ዘበናይ ወሎየ፤
ሰው ለክቶ ሚያድር፤ሰው ነው ያሳደገኝ።
መልኬ ጥቁር ውሃን፤
አላውሃን ጅረቱን፤ እየቆነጠረ ፤
ቱባው ማንነቴ፤
በሰውኛ ጠረን፤
በሰው መሆን ሚዛን እየተሰፈረ፤
በአዳምነት ወረት ፤
ጓዳና ማጀቴ እየተሞሸረ፤
መገን የኔ ነገር፤
ከድፍረስ ባህር ላይ፤
ጅረት እለያለሁ፤
ያውም እኔን እኔን፤ እኔን የመሰለ፤
በፍቅር ረመጥ፤
በሙሃባው እሳት የተንቀለቀለ፤
በሰውነት ቀለም፤
በሰው መሆን አጀብ፤
ነፍሱ የሸገነ፤ አይኑ የተኳለ፤
አላውሃ መሌው ዳር፤
ይጠብቃል ጓዴ፤
ርጥብ ማሽላውን ውልቢኝ እንዳዘለ፤
በናፍቆት አይኖቹ ፤
በራ በሩን ያያል፤
ደግሞ ለጥምቀቱ፤ ለአስተርዮ ማርያም ይመጣል እያለ።
እንዲህ ያለም የለ!!!!!!
((( ጃ ኖ))💚💛❤️
@getem
@getem
@Nagayta
ጥምቀትና ውበት
"""""""""""""""""""""
አንድ ሎሚ ይዤ
ከውቢት ደረት ላይ ወርውሬ ላስቀምጥ
በታቦት ማረፊያ
ከእላይ እታች ስል ቆንጆዎች ሳማርጥ
ዓይኔ ዛብሮ ቀረ
እግሬም ተንከራውቶ
ሀሞቴ ፈሰሰ ልቤም ዋትቶ ዋትቶ
ማንን ከማን ይምረጥ
ቆንጆ ባገር ሞልቶ።
መገን አዲስ አበባ
ስንቱ ጉብል ታየ ከታች እስከላይ
የሴት ልጅ ውበቷ
ያገር ባህል ልብሷ ሽንሽኗ ነው ወይ?
ያገር ልብሷን ለብሳ
ታቦት ስታወጣ ታቦቱን ስትሸኝ
ሁሏ ሴት ማማሯ
ምድር አረገደች ለወዳጇ ይብላኝ።
(የኔማ😔)
ሎሚውም ደረቀ
አይናዋጅ ሆነበት ልቤም ተንሰላውጆ
ሸገር አሸብርቃ
ነክሽ ነካ ስትል በከተሜ ጉብል በአዲስ አበባ ቆንጆ።
ብላም አስመኘችኝ
የውበቷ ንግስት መለሎ ወጣት
ምን አለ በሆነ
ሁል ጊዜ ከተራ ሁል ግዜ ጥምቀት።
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@getem
@getem
@getem
"""""""""""""""""""""
አንድ ሎሚ ይዤ
ከውቢት ደረት ላይ ወርውሬ ላስቀምጥ
በታቦት ማረፊያ
ከእላይ እታች ስል ቆንጆዎች ሳማርጥ
ዓይኔ ዛብሮ ቀረ
እግሬም ተንከራውቶ
ሀሞቴ ፈሰሰ ልቤም ዋትቶ ዋትቶ
ማንን ከማን ይምረጥ
ቆንጆ ባገር ሞልቶ።
መገን አዲስ አበባ
ስንቱ ጉብል ታየ ከታች እስከላይ
የሴት ልጅ ውበቷ
ያገር ባህል ልብሷ ሽንሽኗ ነው ወይ?
ያገር ልብሷን ለብሳ
ታቦት ስታወጣ ታቦቱን ስትሸኝ
ሁሏ ሴት ማማሯ
ምድር አረገደች ለወዳጇ ይብላኝ።
(የኔማ😔)
ሎሚውም ደረቀ
አይናዋጅ ሆነበት ልቤም ተንሰላውጆ
ሸገር አሸብርቃ
ነክሽ ነካ ስትል በከተሜ ጉብል በአዲስ አበባ ቆንጆ።
ብላም አስመኘችኝ
የውበቷ ንግስት መለሎ ወጣት
ምን አለ በሆነ
ሁል ጊዜ ከተራ ሁል ግዜ ጥምቀት።
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@getem
@getem
@getem
ሎሚ ወሳጅ ጠፋ?????!!!!!!!!!
በሃምሌ ተለክፎ ፤
በነሃሴ አፍቅሮ፤ ህዳር የጠናበት ፤
በጥምቀት ይድናል ፤
የመምሬ ጠበል ፤ ውሃ ሲፈስበት ።
ይብላኝ እንጅ ላንች ፤ እኔስ ግዴለኝም ፥
ጥምቀት ከደረሰ ፤
እታጠበዋለሁ ፍቅርሽ አይገለኝም ።
አምና ጉባላፍቶ ፤ ሎሚ እንኪ ብልሽ ፤
ግንባርሽ ተቆጣኝ ፤ አባጨኝ ፊትሽ፤
ዘንድሮ ሸጎቹ ፤ መጡ ሊነጥቁሽ ።
ሎሚ አልከጅል ብለሽ፤ ስትይ ገባ ወጣ ፤
ከእጅ የሚመነጥቅ፤ ሎሚ መጣጭ መጣ ።
እንካ ሲሉት ሎሚ፤ የተግደረደረ ፤
ዘንድሮም እንዳምናው፤ሎሚ ናፍቆ ቀረ ።
ይብላኝልሽ ላንች ፤ ሎሚየን ለናቅሽው ፤
ወዶ መለመንን ፤ ከእንግዲህ ቅመሽው ።
ተሽሎኛል ዛሬ፤ ከአምናው በጥቂቱ ፤
በጠበል ለቆኛል ፤ የመውደድ ግዝቱ ።
ሎሚ ስጠኝ ያልሽው፤ አለቀብኝ እኔ ፤
የስንት ሰው ሎሚ ፤
መጥምጠሽ አኝከሽ ፤
መሮሽ ስትጥይው ፤ እያየሁሽ ባይኔ ።
እቴ በታቦቱ ፤
እቴ በጥምቀቱ ፤ በአድባሩ በአውጋሩ፤
ያንች ሰፈር ልጆች ፤
ሎሚ አንወስድም ብለው ፤ ሎሚ ናፍቀው ቀሩ ።
አንች ባለ ዱኣ ፤
ቀየው የመረቀሽ ፤ በተራ በተራ ፤
እየው በዚያ ሰፈር ፤
ተከምሮልሻል ፤
ሊወረወርብሽ ፤ የሎሚ ተራራ ።
እመጣለሁ ቆንጂት ማለዳ ቀድሜ ፤
ጠበሉን ሲረጩኝ ፤
ከተፋዘዝኩበት፤ ይገለጣል አይኔ ።
አምና በትፍትፍሽ ዛሬ በአንባርሽ ፤
ሎሚ ስወረውር የገረገረሽ ፤
የወደደ ገላ በቀልብ ያሰረሽ፤
ማለዳ ነይና ፤
ሎሚው እንዲቀናሽ ፤ ጠበሉ ይፍታሽ! !!!
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
ሸጋ የጥምቀት በዓል!!💚💛❤️
@getem
@getem
@Nagayta
በሃምሌ ተለክፎ ፤
በነሃሴ አፍቅሮ፤ ህዳር የጠናበት ፤
በጥምቀት ይድናል ፤
የመምሬ ጠበል ፤ ውሃ ሲፈስበት ።
ይብላኝ እንጅ ላንች ፤ እኔስ ግዴለኝም ፥
ጥምቀት ከደረሰ ፤
እታጠበዋለሁ ፍቅርሽ አይገለኝም ።
አምና ጉባላፍቶ ፤ ሎሚ እንኪ ብልሽ ፤
ግንባርሽ ተቆጣኝ ፤ አባጨኝ ፊትሽ፤
ዘንድሮ ሸጎቹ ፤ መጡ ሊነጥቁሽ ።
ሎሚ አልከጅል ብለሽ፤ ስትይ ገባ ወጣ ፤
ከእጅ የሚመነጥቅ፤ ሎሚ መጣጭ መጣ ።
እንካ ሲሉት ሎሚ፤ የተግደረደረ ፤
ዘንድሮም እንዳምናው፤ሎሚ ናፍቆ ቀረ ።
ይብላኝልሽ ላንች ፤ ሎሚየን ለናቅሽው ፤
ወዶ መለመንን ፤ ከእንግዲህ ቅመሽው ።
ተሽሎኛል ዛሬ፤ ከአምናው በጥቂቱ ፤
በጠበል ለቆኛል ፤ የመውደድ ግዝቱ ።
ሎሚ ስጠኝ ያልሽው፤ አለቀብኝ እኔ ፤
የስንት ሰው ሎሚ ፤
መጥምጠሽ አኝከሽ ፤
መሮሽ ስትጥይው ፤ እያየሁሽ ባይኔ ።
እቴ በታቦቱ ፤
እቴ በጥምቀቱ ፤ በአድባሩ በአውጋሩ፤
ያንች ሰፈር ልጆች ፤
ሎሚ አንወስድም ብለው ፤ ሎሚ ናፍቀው ቀሩ ።
አንች ባለ ዱኣ ፤
ቀየው የመረቀሽ ፤ በተራ በተራ ፤
እየው በዚያ ሰፈር ፤
ተከምሮልሻል ፤
ሊወረወርብሽ ፤ የሎሚ ተራራ ።
እመጣለሁ ቆንጂት ማለዳ ቀድሜ ፤
ጠበሉን ሲረጩኝ ፤
ከተፋዘዝኩበት፤ ይገለጣል አይኔ ።
አምና በትፍትፍሽ ዛሬ በአንባርሽ ፤
ሎሚ ስወረውር የገረገረሽ ፤
የወደደ ገላ በቀልብ ያሰረሽ፤
ማለዳ ነይና ፤
ሎሚው እንዲቀናሽ ፤ ጠበሉ ይፍታሽ! !!!
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
ሸጋ የጥምቀት በዓል!!💚💛❤️
@getem
@getem
@Nagayta
(በላይ በቀለ ወያ)
በተራበው ጎኔ፣ በተጎዳው ኪሴ
እኔም ሰው ነኝና፣
የከንፈር ወዳጄን ተጠምታብኝ ነበሴ
የጥምቀት ለት ሎሚ፣
ኪሴን በሚጎዳ በሚነርት ዋጋ
ይሁን ብየ ገዛሁ፣
ደረቷን ልመታ የዛችን ውብ ሸጋ።
ሎሚውን በእጄ ያዝኩ
ኮረዳዋን ፈለግኩ
ባ'ይኖቼ አማተርኩ
ከኋላዋ አየኋት...
ፀጉሯ ሹሩባ ነው፣ ፊቷ አይታይም
ኋላዋ ካማረ...
ፊቷ ምንም ይሁን እኔን አይጨንቀኝም
ዳሌዋ... ቢዮንሴን ያስንቃል
በንቅልፍ የቧዘዘን አጣድፎ ያነቃል
ስንት የወጣባትን፣
የኛን ሳተላይት ከቻይና ያመጥቃል (አንጥሮ😂)
ወገቧ... አካበድክ ባትሉኝ
ከቀጭኗ እግሬ ሚወፍር አይመስለኝ
ወይኔ ሹሩባዋ
ለመግለፅም እንኳን አንደበትን ያስራል
በቆሙበት መሬት አፍዞ ያስቀራል።
ወደራሴ መጣሁ...
ልወርውር አልወርውር?
ልወርውር አልወርውር?
ወረወርኩ...
ድምም... እዛው ዳሌዋ ላይ
አሟት ዩን ደስ ብሏት ዞር ብላ ብታይ
የኔ ልብ ደንግጣ ልትበር ወደ ሰማይ
እየሮጠች መጣች፣
እያነፈነፈች ትንፋሿ እስከሚያጥራት
ክፉ አስባ ይሆን ልሩጥ ልጠብቃት?
ደረሰች...
ፊቴ ከመድረሷ፣
አንድ ጊዜ በጥፊ አወላመመችኝ
ወደላይ ወደታች፣
መላ ሰውነቴን በደምብ ቃኘችኝ
ወደግራ ጆሮየ በጣም ተጠጋችኝ
ጊዜው የድንጋይ ነው ሎሚ አታባክን
ኪስህን አሟጠህ፣
በገዛኸው ሎሚ ፈፅሞ አትጨክን
አሁን ሳናቅማማ ቶሎ እንሽጠው
ይሄ ውድ ሎሚ፣
ላ'ዲሱ ጎጇችን ትልቅ መሰረት ነው
ብላ አቀፈችኝ
እሰየው ዘንድሮ ለኔም ተሳካልኝ።
@getem
@getem
#jeko
በተራበው ጎኔ፣ በተጎዳው ኪሴ
እኔም ሰው ነኝና፣
የከንፈር ወዳጄን ተጠምታብኝ ነበሴ
የጥምቀት ለት ሎሚ፣
ኪሴን በሚጎዳ በሚነርት ዋጋ
ይሁን ብየ ገዛሁ፣
ደረቷን ልመታ የዛችን ውብ ሸጋ።
ሎሚውን በእጄ ያዝኩ
ኮረዳዋን ፈለግኩ
ባ'ይኖቼ አማተርኩ
ከኋላዋ አየኋት...
ፀጉሯ ሹሩባ ነው፣ ፊቷ አይታይም
ኋላዋ ካማረ...
ፊቷ ምንም ይሁን እኔን አይጨንቀኝም
ዳሌዋ... ቢዮንሴን ያስንቃል
በንቅልፍ የቧዘዘን አጣድፎ ያነቃል
ስንት የወጣባትን፣
የኛን ሳተላይት ከቻይና ያመጥቃል (አንጥሮ😂)
ወገቧ... አካበድክ ባትሉኝ
ከቀጭኗ እግሬ ሚወፍር አይመስለኝ
ወይኔ ሹሩባዋ
ለመግለፅም እንኳን አንደበትን ያስራል
በቆሙበት መሬት አፍዞ ያስቀራል።
ወደራሴ መጣሁ...
ልወርውር አልወርውር?
ልወርውር አልወርውር?
ወረወርኩ...
ድምም... እዛው ዳሌዋ ላይ
አሟት ዩን ደስ ብሏት ዞር ብላ ብታይ
የኔ ልብ ደንግጣ ልትበር ወደ ሰማይ
እየሮጠች መጣች፣
እያነፈነፈች ትንፋሿ እስከሚያጥራት
ክፉ አስባ ይሆን ልሩጥ ልጠብቃት?
ደረሰች...
ፊቴ ከመድረሷ፣
አንድ ጊዜ በጥፊ አወላመመችኝ
ወደላይ ወደታች፣
መላ ሰውነቴን በደምብ ቃኘችኝ
ወደግራ ጆሮየ በጣም ተጠጋችኝ
ጊዜው የድንጋይ ነው ሎሚ አታባክን
ኪስህን አሟጠህ፣
በገዛኸው ሎሚ ፈፅሞ አትጨክን
አሁን ሳናቅማማ ቶሎ እንሽጠው
ይሄ ውድ ሎሚ፣
ላ'ዲሱ ጎጇችን ትልቅ መሰረት ነው
ብላ አቀፈችኝ
እሰየው ዘንድሮ ለኔም ተሳካልኝ።
@getem
@getem
#jeko
" #ባውቶማቲክ_ግዜ ፥ #መሸከሙ_ጓንዴ ...
#አይከብድም_ወይ_ጓዴ"
ይብላኙን ለነሱ…
በጠዋት ገስግሰው ፥ አንድ ኪሎ ሎሚ ፥ ገዝተው ለደረሱ
ያውም በዚ ግዜ
ሎሚ ጥሪው ከብሮ ፥ ከጅ ላይ በጠፋ ፥.... በተወደደበት
ሜክ አፕ የለቀመው ፥ ሴቱም እንከን የለሽ ፥ ውበት በደፋበት
ወንዱም አቅሉን ስቶ
ሎሚ በተረሳው ፥ የመኪና ቁልፉን ፥ እያነጣጠረ
አይፎኑን ደረት ላይ ፥ ሰዶ እያነጠረ
"አይፎን ብወረውር .....እስፖንጇን መታሁት
አወይ ተሳክቶልኝ......ጡቷን ባገኘሁት"
በሚል ሀርሞኒካ .....ትዳር የሚናፍቅ
አልሞ ተኳሿ .....ከሷ ብዙም ሳይርቅ
እያረጋገፈች ከመሬት አንስታ
የላክልኝ አይፎን .....የሰደድከው ቁልፉ
ከደረቴ ነጥሮ....መሬት መዘርገፉ
አንተም ጎበዝ አጥቂ.....
ጎበዝ ተከላካይ ፥ መርጦ ገራም ልብህ የመሸናነፉ
ማመላከቻ ነው ፥ ቅኔው ሲተረተር ፥ እንዲያው በግርድፉ
ለዚህ ....ለዚህ እንጂ ፥ ዱላ ለመመከት
ውበት ጎሎት አይደል
በል ነዳጁን ስጠው ፥ ቦታ እንያዝ እና ፥ ማማሩን ተመልከት
ብለው ተያይዘው ፥ ከስርፋው ታበሱ
ያንን ሁሉ ሎሚ ፥ የሸመተው ጉብል ፥ ለማን ይስጠው እርሱ
በዚህ የሀሳብ ዚቅ....... እንደተዘፈቀ
ታቦቱን ያጀበ ፥ የሞንሟኖች መንጋ ፥ ሳይገላመጠው ከተራው አለቀ
ይህን እያየሁኝ....
ከሎሚም ፣ ከቁልፉ ፥ የቀረሁኝ እኔ
ጉብታው ላይ ቆሜ ፥ ሲወጣና ሲወርድ ፥ አየዋለው ባይኔ
ድንገት ፥ ተስፋ ራሱ ፥ ተስፋ ቆርጦ ሳለ
ለመሄድ ሲነሳ ፥ የኪሎ ዘንቢሉን ፥ እንደጠቀለለ
አምሮት የምታጭር...ጥበቃ እምትገታ
ካለችነት ቦታ ፥ በፍጥነት ተነስታ
ወደርሱ ቸኮለች ፥ ተሳልሞ ለመሄድ ፥መነሳቱን አይታ
ለጥቂት ሰአታት ፥ አንድ ላይ አወሩ
ፈገግ አለች እሷ......ተፈታ ግንባሩ
ነጠላ ሸፍና ፥ እጁን ጨበጠችው
ያንን ሁሉ ሎሚ ፥ አንድ ራሷ መጥታ ፥ እሷው ወሰደችው።
ይህኔ...
የማላውቀው ጓዴ
በለስ ቀንቶት ባየው ፥ በባከነው አይኔ
እሰይ..........አልኩኝ እኔ....
እንደአቅሙ ጣጥሯል ...
አልተሰበሰበም ...በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ፥ አዝኖ ልክ እንደኔ
ከቆመ የዳኸ ፥ አስር እጅ እንዲሻል ፥ መክሮኛል ዘመኔ ።
#ኋላ_ግን_ስሰማ .... #ልጅቷ_ጭማቂ_ቤት_አላት...(😁😁😁)
✍ #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
✍ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
#አይከብድም_ወይ_ጓዴ"
ይብላኙን ለነሱ…
በጠዋት ገስግሰው ፥ አንድ ኪሎ ሎሚ ፥ ገዝተው ለደረሱ
ያውም በዚ ግዜ
ሎሚ ጥሪው ከብሮ ፥ ከጅ ላይ በጠፋ ፥.... በተወደደበት
ሜክ አፕ የለቀመው ፥ ሴቱም እንከን የለሽ ፥ ውበት በደፋበት
ወንዱም አቅሉን ስቶ
ሎሚ በተረሳው ፥ የመኪና ቁልፉን ፥ እያነጣጠረ
አይፎኑን ደረት ላይ ፥ ሰዶ እያነጠረ
"አይፎን ብወረውር .....እስፖንጇን መታሁት
አወይ ተሳክቶልኝ......ጡቷን ባገኘሁት"
በሚል ሀርሞኒካ .....ትዳር የሚናፍቅ
አልሞ ተኳሿ .....ከሷ ብዙም ሳይርቅ
እያረጋገፈች ከመሬት አንስታ
የላክልኝ አይፎን .....የሰደድከው ቁልፉ
ከደረቴ ነጥሮ....መሬት መዘርገፉ
አንተም ጎበዝ አጥቂ.....
ጎበዝ ተከላካይ ፥ መርጦ ገራም ልብህ የመሸናነፉ
ማመላከቻ ነው ፥ ቅኔው ሲተረተር ፥ እንዲያው በግርድፉ
ለዚህ ....ለዚህ እንጂ ፥ ዱላ ለመመከት
ውበት ጎሎት አይደል
በል ነዳጁን ስጠው ፥ ቦታ እንያዝ እና ፥ ማማሩን ተመልከት
ብለው ተያይዘው ፥ ከስርፋው ታበሱ
ያንን ሁሉ ሎሚ ፥ የሸመተው ጉብል ፥ ለማን ይስጠው እርሱ
በዚህ የሀሳብ ዚቅ....... እንደተዘፈቀ
ታቦቱን ያጀበ ፥ የሞንሟኖች መንጋ ፥ ሳይገላመጠው ከተራው አለቀ
ይህን እያየሁኝ....
ከሎሚም ፣ ከቁልፉ ፥ የቀረሁኝ እኔ
ጉብታው ላይ ቆሜ ፥ ሲወጣና ሲወርድ ፥ አየዋለው ባይኔ
ድንገት ፥ ተስፋ ራሱ ፥ ተስፋ ቆርጦ ሳለ
ለመሄድ ሲነሳ ፥ የኪሎ ዘንቢሉን ፥ እንደጠቀለለ
አምሮት የምታጭር...ጥበቃ እምትገታ
ካለችነት ቦታ ፥ በፍጥነት ተነስታ
ወደርሱ ቸኮለች ፥ ተሳልሞ ለመሄድ ፥መነሳቱን አይታ
ለጥቂት ሰአታት ፥ አንድ ላይ አወሩ
ፈገግ አለች እሷ......ተፈታ ግንባሩ
ነጠላ ሸፍና ፥ እጁን ጨበጠችው
ያንን ሁሉ ሎሚ ፥ አንድ ራሷ መጥታ ፥ እሷው ወሰደችው።
ይህኔ...
የማላውቀው ጓዴ
በለስ ቀንቶት ባየው ፥ በባከነው አይኔ
እሰይ..........አልኩኝ እኔ....
እንደአቅሙ ጣጥሯል ...
አልተሰበሰበም ...በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ፥ አዝኖ ልክ እንደኔ
ከቆመ የዳኸ ፥ አስር እጅ እንዲሻል ፥ መክሮኛል ዘመኔ ።
#ኋላ_ግን_ስሰማ .... #ልጅቷ_ጭማቂ_ቤት_አላት...(😁😁😁)
✍ #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
✍ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
"ይድረስ ለኔይቱ እንስት"
(መልአኩ ስብሐት ባይህ)
************
እቴዋ መቀነቴ
ድምቅ ዓለሜ
በግብርሽ ክሳሜ
እምዘልቅ ቆሜ
ወና ነው ሌማቴ ከንቱነው ባዶነት
እኔ እምትወክል ሰርጻ እማትገባበት
በአፍላ ጅማሮ የአፍታ እድሜዬን
ፈትለሽ ላትቋጪው አልቦ ክዳን ሕልሜን
እቴዋ መቀነቴ
አንቺ የሕዋሴ ባህር ኃዳፍ
የሥጋ ነፍሴ መዳፍ
በሸክላ ሰሪው የአፈር ክምር
ባንቺነትሽ ግብዓት እኔነቴ ሲጣመር
ምነው ግና?
ምነው ግና? ስንፍ ሆነብኝ
ሳልጀምረው ያ ውዳዴሽ አበቃብኝ።
ምነው ግና?
ምነው ግና?
በፍቅራችን ቀነ ውልደት ሕልፈታቱ የታወጀ
በቅምጥናው አሉታነት ለዘመናት የደረጀ
ምነው? ምነው? ቅ.....ር.....ባ.....ታ.....ች.....ን ባጀ ።
@getem
@getem
@poem_with_mela
(መልአኩ ስብሐት ባይህ)
************
እቴዋ መቀነቴ
ድምቅ ዓለሜ
በግብርሽ ክሳሜ
እምዘልቅ ቆሜ
ወና ነው ሌማቴ ከንቱነው ባዶነት
እኔ እምትወክል ሰርጻ እማትገባበት
በአፍላ ጅማሮ የአፍታ እድሜዬን
ፈትለሽ ላትቋጪው አልቦ ክዳን ሕልሜን
እቴዋ መቀነቴ
አንቺ የሕዋሴ ባህር ኃዳፍ
የሥጋ ነፍሴ መዳፍ
በሸክላ ሰሪው የአፈር ክምር
ባንቺነትሽ ግብዓት እኔነቴ ሲጣመር
ምነው ግና?
ምነው ግና? ስንፍ ሆነብኝ
ሳልጀምረው ያ ውዳዴሽ አበቃብኝ።
ምነው ግና?
ምነው ግና?
በፍቅራችን ቀነ ውልደት ሕልፈታቱ የታወጀ
በቅምጥናው አሉታነት ለዘመናት የደረጀ
ምነው? ምነው? ቅ.....ር.....ባ.....ታ.....ች.....ን ባጀ ።
@getem
@getem
@poem_with_mela
#ተነድፈሽ_ክበሪ
:
:
እኔ አልነደፍም የሚለው ፉከራ
በገዛ አንደበትሽ በኩራት ሲወራ
ካንዴም አስር ጊዜ ደርሶ ሰምቻለው
ትክክል ነው ብሎም የሚያጎበጉብ ሰው በቅርብ አይቻለው።
:
:
እውነት ነው ወይ ብዬም በዙሪያሽ ያሉትን ዞሬ ሳጤናቸው
መላከፍ ነው እንጂ መንደፍ የማይችሉ ተራ ዝንቦች ናቸው።
:
:
አፍኜው ነው እንጂ ድሮም ያንቺ ነገር ያንገበግበኛል
ከንቱ ፉጨት ከቦሽ መኩራትሽ ገርሞኛል።
:
:
ከ ዐጀቦችሽ አንፃር መደምደምሽን ሳይ አናገረኝ እንጂ የሆዴ መከፋት
ባንቺ አልተጀመረም አደባባይ ቆሞ በጀሌ ተከቦ አጉል ጉራ መንፋት።
:
:
እውነት እውነት ስልሽ ያለመነደፍሽን ሚስጥሩን ላወቀው
ልክ እንደኔ ሁሉ ሆድ ቢብሰው እንጂ ቅንጣትም አይደንቀው።
:
:
ይልቁን አንቺ ሴት አንዣባቢሽ በዝቶ እንዳትዘናጊ
የማሩን እንጀራም ያንቺ እንድታደርጊ
ተነድፎ ለመክበር በይ ከንብ ተጠጊ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henokbirhanu
@getem
@getem
@getem
:
:
እኔ አልነደፍም የሚለው ፉከራ
በገዛ አንደበትሽ በኩራት ሲወራ
ካንዴም አስር ጊዜ ደርሶ ሰምቻለው
ትክክል ነው ብሎም የሚያጎበጉብ ሰው በቅርብ አይቻለው።
:
:
እውነት ነው ወይ ብዬም በዙሪያሽ ያሉትን ዞሬ ሳጤናቸው
መላከፍ ነው እንጂ መንደፍ የማይችሉ ተራ ዝንቦች ናቸው።
:
:
አፍኜው ነው እንጂ ድሮም ያንቺ ነገር ያንገበግበኛል
ከንቱ ፉጨት ከቦሽ መኩራትሽ ገርሞኛል።
:
:
ከ ዐጀቦችሽ አንፃር መደምደምሽን ሳይ አናገረኝ እንጂ የሆዴ መከፋት
ባንቺ አልተጀመረም አደባባይ ቆሞ በጀሌ ተከቦ አጉል ጉራ መንፋት።
:
:
እውነት እውነት ስልሽ ያለመነደፍሽን ሚስጥሩን ላወቀው
ልክ እንደኔ ሁሉ ሆድ ቢብሰው እንጂ ቅንጣትም አይደንቀው።
:
:
ይልቁን አንቺ ሴት አንዣባቢሽ በዝቶ እንዳትዘናጊ
የማሩን እንጀራም ያንቺ እንድታደርጊ
ተነድፎ ለመክበር በይ ከንብ ተጠጊ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henokbirhanu
@getem
@getem
@getem
#ጌታ የተጠመቀብሽ
በጥምቀት በዓለት ቀሚስ ይበጣጠስ
ለኔ ጥምቀት ጊዜ ፍቅርን መበጣጠስ
ለጌታ ጥምቀት ለት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሴጣን ይባረራል
ለኔና አንቺ ፍቅር ግን ለጥምቀት በዓል ለት
መለያየት የሚል ክፉ መንፈስ ወርዷል
ባብሮነት ጎዳና ካንቺ ልሆን ብዬ
በስምሽ በጥምቀቱ አንቺዬ
ምን ጉድ አሰማሽው ለዚ ለጆሮዬ
ጌታ የተጠመቀብሽ ወቧ የኔ ባህር
አልኩልሽ ስብርብር
ጭንቀት አደረገኝ ውርር
ሚያለያየን ነገር ሚያራርቀን ነገር በዛ ብለሺኛል
መሆንን ከፈራሽ እኔ ብላቴናው ምንስ ይሻለኛል
ጌታ የተጠመቀብሽ
ከልብሽ ከሆነ በቀኑ ሚካኤል እስቲ አንዴ ማዩልኝ
ምለሽ ከተገዘትሽ እቺን ቅኔ ፍቺ እንደው በማልሺልኝ
ፍቅርን ማግኘት ስሻ
መፅሀፍ ቅዱስ ብሻ
ከቅዱስ መፅሀፍ ገፅ ያዝኩኝ ፍተሻ
ጌታ የተጠመቀባት ይለኛል አንዱ ገፅ
ተነስቷል ያለችው ትንሳኤን አብሳሪ ይለኛል ሌላው ገፅ
የእዳ ደብዳቤ ባንቺ በባህሯ ዛሬ እኮ ተፋቀ
መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሴጣንም በሸቀ
በትንሳኤው ጊዜ
መንፈስ ቅዱስ አረገ
ዲያቢሎስ ታሰረ ክርስቶስ በደሙ ሰውን ከሲኦል ታደገ
✍ተፃፈ በብላቴናው ብዕር
@getem
@getem
በጥምቀት በዓለት ቀሚስ ይበጣጠስ
ለኔ ጥምቀት ጊዜ ፍቅርን መበጣጠስ
ለጌታ ጥምቀት ለት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሴጣን ይባረራል
ለኔና አንቺ ፍቅር ግን ለጥምቀት በዓል ለት
መለያየት የሚል ክፉ መንፈስ ወርዷል
ባብሮነት ጎዳና ካንቺ ልሆን ብዬ
በስምሽ በጥምቀቱ አንቺዬ
ምን ጉድ አሰማሽው ለዚ ለጆሮዬ
ጌታ የተጠመቀብሽ ወቧ የኔ ባህር
አልኩልሽ ስብርብር
ጭንቀት አደረገኝ ውርር
ሚያለያየን ነገር ሚያራርቀን ነገር በዛ ብለሺኛል
መሆንን ከፈራሽ እኔ ብላቴናው ምንስ ይሻለኛል
ጌታ የተጠመቀብሽ
ከልብሽ ከሆነ በቀኑ ሚካኤል እስቲ አንዴ ማዩልኝ
ምለሽ ከተገዘትሽ እቺን ቅኔ ፍቺ እንደው በማልሺልኝ
ፍቅርን ማግኘት ስሻ
መፅሀፍ ቅዱስ ብሻ
ከቅዱስ መፅሀፍ ገፅ ያዝኩኝ ፍተሻ
ጌታ የተጠመቀባት ይለኛል አንዱ ገፅ
ተነስቷል ያለችው ትንሳኤን አብሳሪ ይለኛል ሌላው ገፅ
የእዳ ደብዳቤ ባንቺ በባህሯ ዛሬ እኮ ተፋቀ
መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሴጣንም በሸቀ
በትንሳኤው ጊዜ
መንፈስ ቅዱስ አረገ
ዲያቢሎስ ታሰረ ክርስቶስ በደሙ ሰውን ከሲኦል ታደገ
✍ተፃፈ በብላቴናው ብዕር
@getem
@getem
👍1
"የመረጨት ስምረት"
(መልአኩ ስብሐት ባይህ)
************
በባሕረ ቡራኬው
በጥባሌ ጥማቄው
ሕዝበ አዳም ፍጥረቱ
በንጋት ጉዞ ፍሰቱ
ምራቄውን ሰንቆ
እርኩስናውን አርቆ
በእግዚኦታው ተማጽኖ
ዕምንተ ክሩን ጎንጉኖ
ሲተም በትማሜ ዥረት
ለይቅርታ ለበረከት
ለጉዳሌው ጉድል ሙሌት
ውዳሴውን ሊደርስበት
በዓለ ክብሩን ሊነግስብት
የእመቤቴን ቸርነቷን
የምልጃዋን ተአምራቷን
ሊነፍስበት ደግነቷን
ሊጸናበት መሠረቷን
አደግድጎ በነጠላ
በጧፍ ከርቤ በዣንጥላ
ስዕለቱን ለምህላ
መባ ሲሰጥ ፍጡር ሁላ ።
ሻማ ዘቢብ ውብ ካባውን
የምስጋና በረካውን
ዕጹብ ሊያደርግ መከራውን።
በቀኑ ስምር ቀኑን ሰርቶ
ከእጦት ይልቅ አግኚ ሞልቶ
በአንድነት ግምድ ግፍፊ ዓለም
አንዱ ባንዱ ሲተራረም
ሕብር ሸማ ፍቅርን ሲቀልም
ድምጻችን ላይነጥፍ ተሰማ
ከሰማየ ሰማያት ከዘለዓለሙ ከራማ
አዬ ጥምቀት የነፍስ አርማ ።
ተጻፈ:-11/05/2012 ዓ.ም
@getem
@getem
@poem_with_mela
(መልአኩ ስብሐት ባይህ)
************
በባሕረ ቡራኬው
በጥባሌ ጥማቄው
ሕዝበ አዳም ፍጥረቱ
በንጋት ጉዞ ፍሰቱ
ምራቄውን ሰንቆ
እርኩስናውን አርቆ
በእግዚኦታው ተማጽኖ
ዕምንተ ክሩን ጎንጉኖ
ሲተም በትማሜ ዥረት
ለይቅርታ ለበረከት
ለጉዳሌው ጉድል ሙሌት
ውዳሴውን ሊደርስበት
በዓለ ክብሩን ሊነግስብት
የእመቤቴን ቸርነቷን
የምልጃዋን ተአምራቷን
ሊነፍስበት ደግነቷን
ሊጸናበት መሠረቷን
አደግድጎ በነጠላ
በጧፍ ከርቤ በዣንጥላ
ስዕለቱን ለምህላ
መባ ሲሰጥ ፍጡር ሁላ ።
ሻማ ዘቢብ ውብ ካባውን
የምስጋና በረካውን
ዕጹብ ሊያደርግ መከራውን።
በቀኑ ስምር ቀኑን ሰርቶ
ከእጦት ይልቅ አግኚ ሞልቶ
በአንድነት ግምድ ግፍፊ ዓለም
አንዱ ባንዱ ሲተራረም
ሕብር ሸማ ፍቅርን ሲቀልም
ድምጻችን ላይነጥፍ ተሰማ
ከሰማየ ሰማያት ከዘለዓለሙ ከራማ
አዬ ጥምቀት የነፍስ አርማ ።
ተጻፈ:-11/05/2012 ዓ.ም
@getem
@getem
@poem_with_mela
።።።።።።የምርቃና ግፉ።።።።።።
በረከት በላይነህ
የሙዚቃ ሊቁ፣
ሙዚቃ ቀማሚው ዜማ እየቀመረ
ጠባቧ "ስቲዲዮ " ጫት ሞልቷት ነበረ።
ሳተናው ነጋዴ ትርፉን እያሰላ
ሊቅም ቁርሱን በላ።
ሹማምንቶቻችን ፣
ገንቢ አፍራሾቻችን ፣
ዕቅዱን ሲጽፉ ፣
በትዕዛዝ ያደገ አወደይ ቀጠፉ።
ጎረምሳው አፍቃሪሽ ጫት በዱቤ ቅሞ፣
ደብዳቤ ጻፈልሽ ከገረባ መሃል
ምርቅን ቃላት ለቅሞ።
እናስ!
መሪ ከተከታይ፣
ፍትህ ከተበዳይ፣
ጥበብ ከአድናቂው፣
መላሽ ከጠያቂው
የነቃ ከእውኑ
የተኛ ከሕመሙ
ውበት ከቀለሙ
እኮ በምን ስሌት? እንደምን ይስማማ?
ሰጪና ተቀባይ እኩል አልቃሙማ።
@getem
@getem
@getem
በረከት በላይነህ
የሙዚቃ ሊቁ፣
ሙዚቃ ቀማሚው ዜማ እየቀመረ
ጠባቧ "ስቲዲዮ " ጫት ሞልቷት ነበረ።
ሳተናው ነጋዴ ትርፉን እያሰላ
ሊቅም ቁርሱን በላ።
ሹማምንቶቻችን ፣
ገንቢ አፍራሾቻችን ፣
ዕቅዱን ሲጽፉ ፣
በትዕዛዝ ያደገ አወደይ ቀጠፉ።
ጎረምሳው አፍቃሪሽ ጫት በዱቤ ቅሞ፣
ደብዳቤ ጻፈልሽ ከገረባ መሃል
ምርቅን ቃላት ለቅሞ።
እናስ!
መሪ ከተከታይ፣
ፍትህ ከተበዳይ፣
ጥበብ ከአድናቂው፣
መላሽ ከጠያቂው
የነቃ ከእውኑ
የተኛ ከሕመሙ
ውበት ከቀለሙ
እኮ በምን ስሌት? እንደምን ይስማማ?
ሰጪና ተቀባይ እኩል አልቃሙማ።
@getem
@getem
@getem
ተሻገር ስትባል
:
ፍቃዱ ጌታቸው
፡
<<ነገን አታያትም!>>
ብሎ ያለኝ ዶክተር
በቅጡ ቻው ሳይለኝ ፣ አጠገቤ ሞተ
ሳይንሳዊ እውቀቱ
የለገሰው ትንቢት ፣ ዓይኔ ስር ሻገተ
መቆም ለመሻገር ፣ ዋስ ላይሆን ታወቀኝ
ልቤም በቅፅበቷ
በሞት ላይ ተበተ!
:
ዶክተሩን ያመኑት
ለፍትሐቴ ቄስ ለእርቃኔ ከፈን ፣ ተግተው ሲያሰናዱ
የፀኑት ሊያተርፉኝ
ተዓምር እንዲሆን ፣ ደጀ ሰላም ሔዱ።
፡
ተዓምር ገዘፈ
ነገ ዛሬ ሆነች ፣ ተገኘሁ በእቅፏ
ተነጥቄ ወጣሁ ፣ ከሟቾች ወረፋ!
:
የእድሩን ጥሩንባ ፣ የፀሐይ ሳቅ ውጦት
የወዳጅን እንባ ፣ መፍነክነክ ተክቶት
የሐሴት ፅንሰቱ ፣ ካልጋዬ ሲወለድ
አየኋት ረፍቴን
ካረዳኝ ተናንቃ ፣ አስከትላው ስትሔድ።
፡
ሌላ ቀን
ሌላ እድል
ሌላ መኖር አቅፎኝ ፣ አዲስ ፀሐይ ፈካ
ከትንቢት ይልቃል
ከእውቀት ይመጥቃል
በሕይወት ሲፈልግህ ፣ የእጣህ በረካ።
@getem
@getem
@getem
:
ፍቃዱ ጌታቸው
፡
<<ነገን አታያትም!>>
ብሎ ያለኝ ዶክተር
በቅጡ ቻው ሳይለኝ ፣ አጠገቤ ሞተ
ሳይንሳዊ እውቀቱ
የለገሰው ትንቢት ፣ ዓይኔ ስር ሻገተ
መቆም ለመሻገር ፣ ዋስ ላይሆን ታወቀኝ
ልቤም በቅፅበቷ
በሞት ላይ ተበተ!
:
ዶክተሩን ያመኑት
ለፍትሐቴ ቄስ ለእርቃኔ ከፈን ፣ ተግተው ሲያሰናዱ
የፀኑት ሊያተርፉኝ
ተዓምር እንዲሆን ፣ ደጀ ሰላም ሔዱ።
፡
ተዓምር ገዘፈ
ነገ ዛሬ ሆነች ፣ ተገኘሁ በእቅፏ
ተነጥቄ ወጣሁ ፣ ከሟቾች ወረፋ!
:
የእድሩን ጥሩንባ ፣ የፀሐይ ሳቅ ውጦት
የወዳጅን እንባ ፣ መፍነክነክ ተክቶት
የሐሴት ፅንሰቱ ፣ ካልጋዬ ሲወለድ
አየኋት ረፍቴን
ካረዳኝ ተናንቃ ፣ አስከትላው ስትሔድ።
፡
ሌላ ቀን
ሌላ እድል
ሌላ መኖር አቅፎኝ ፣ አዲስ ፀሐይ ፈካ
ከትንቢት ይልቃል
ከእውቀት ይመጥቃል
በሕይወት ሲፈልግህ ፣ የእጣህ በረካ።
@getem
@getem
@getem
ነግሬሽ ነበረ !
(በላይ በቀለ ወያ)
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን ያስደምማል
ከንፈርሽ አየር ነው ፣ በሁሉም ይሳማል
ነግሬሽ ነበረ፡፡
ሰማይ ሚያህል ጭንሽ ፣ ከጭንቅላት ያንሳል
ምን ተራራ ቢያህል...
ጡትሽ አቅመ ቢስ ነው ፣ ሲነኩት ይፈርሳል፡፡
ነግሬሽ ነበረ
ክብረ ቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ ፣ እናቶች አይደሉም፡፡
ነግሬሽ ነበረ
የናትነት ስሟ ፣
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ፡፡
ነግሬሽ ነበረ
አትስደበኝ እያልሽ ፣ የነገርኩሽ ሁሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ውሸት ፊት ፣ ስድብ ይመስላሉ፡፡
@getem
@getem
#jeko
(በላይ በቀለ ወያ)
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን ያስደምማል
ከንፈርሽ አየር ነው ፣ በሁሉም ይሳማል
ነግሬሽ ነበረ፡፡
ሰማይ ሚያህል ጭንሽ ፣ ከጭንቅላት ያንሳል
ምን ተራራ ቢያህል...
ጡትሽ አቅመ ቢስ ነው ፣ ሲነኩት ይፈርሳል፡፡
ነግሬሽ ነበረ
ክብረ ቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ ፣ እናቶች አይደሉም፡፡
ነግሬሽ ነበረ
የናትነት ስሟ ፣
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ፡፡
ነግሬሽ ነበረ
አትስደበኝ እያልሽ ፣ የነገርኩሽ ሁሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ውሸት ፊት ፣ ስድብ ይመስላሉ፡፡
@getem
@getem
#jeko
❤1
Forwarded from Sunset Hiking
Event - Goshu Meda Camping Trip ⛺️
Date :- February 1 - 2, 2020 🎈
Departure Spot - Piassa Tayitu Hotel 🎪
Departure Time - 2:00Am Local time 🚩
Price - 1199.99 🙈💰
🎉🎊Package 🎋🎊
🔵🚍 - Tourist level Bus
🔴⛺️- Tent, campfire &tea
⚫️🍝 - Traditional Roasted meat ( 🐏), Lunch and snaks🍟🍤
⚪️ 2 liter Bottled water
🔵 Park entrance with Guide
🔴photograph 📷
Brought to you by Sunset Hiking Group
for more join the
🔸channel @sunsethiking
🔹the group @sunsethike
🔻📷 @sunsetphotography
🎫 tickets available at
@Paappii
@thomaskagnew
@useryise
@Chere_daregot
Date :- February 1 - 2, 2020 🎈
Departure Spot - Piassa Tayitu Hotel 🎪
Departure Time - 2:00Am Local time 🚩
Price - 1199.99 🙈💰
🎉🎊Package 🎋🎊
🔵🚍 - Tourist level Bus
🔴⛺️- Tent, campfire &tea
⚫️🍝 - Traditional Roasted meat ( 🐏), Lunch and snaks🍟🍤
⚪️ 2 liter Bottled water
🔵 Park entrance with Guide
🔴photograph 📷
Brought to you by Sunset Hiking Group
for more join the
🔸channel @sunsethiking
🔹the group @sunsethike
🔻📷 @sunsetphotography
🎫 tickets available at
@Paappii
@thomaskagnew
@useryise
@Chere_daregot