ደስ ይላል መስከረም
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በግርሻ'ጣይ ሰርዶ ነቅሎ በሚያዚያንሽ ተርበጥብጦ ...
በግንቦት ሐሩር ተቀቅሎ ... በፀሐይ አብስሎ በዝናብ አብቅሎ
ከወዳጅ ከዘመድ ተቀላቅሎ ...
ባዝራን ከአህያ አዳቅሎ ...
በባለበርሸት ሽልም በቅሎ ...
ተፈናጦ አብሮ ገስግሶ ...
ጅራፍ ግርፊያ ሆያ ሆዬ ...ቡሄ በሉ ተጫውቶ ...
ኪዳነ ምሕረትን አንግሶ ... ደግሞ በወሩ ለአስተሮዬው..
ግሼን ማሪያም እማአርያም ... ደጀሰላም ደርሶ ለመሳለም..
" እዮሃ አበባዬ መስከረም ጠባዬ ..
ዐደይ ለምለም ለኔ እንዳንቺ የለም..."
እያሉ ንጥቂያ ...
ከጀንበር መፍለቂያ እሥከ ጀንበር መጥለቂያ
አለላ ነቅሎ ባሕር እንጉዳይ ...
ጀግና ሰውገዳይ...
አካል እንጉዳይ...
እያሉ ሲያንጎራጉሩ
ደስ ይላል መስከረም !
.
ቡቃያው ጣል ከንበል ሲስ ...
ሽሩባዋ ወርዶ እንዲያ ሲዘናፈል ...
ልቤ እንደበቆሎ ያድራል ሲፈለፈል...
በቀጭን ተሰርታ ሥትል ዘንከት ዘንከት ...
ጃሎ ሲል ሊያነጋ አገር በመለከት ...
ለመስቀል ጠንስሶ ... በማድጋ ገንቦ ለእንግዳ ቀንሶ ...
በሞቴ አፈር ስሆን እያለ ሲያጋፍር ...
ጥርስ እንጎቻ አስፍቶ አሞጭ በመሰለው እርጎ ፍርፍር ...
እንኳን ሳቅ ጨዋታው ድብድቡ ልፊያው ...
ድገሙኝ ያሰኛል ሰፈፍ የለሽ ሞገድ መደዶ ዘር ዜማ ሲቆረቆር ክትፊያው..
ደስ ይላል መስከረም !
.
የሽንብራ ሸት እየጠረጠሩ ...
የልጅነት ሚዜ 'ኧረ አይዋ ክንዴ' እያሉ እየጠሩ ..
አብሮ ወፍ ጥበቃ ማማ ላይ ተሰቅሎ ...
ካፊያውን በገሳ በአንድ ተጠልሎ...
እሳት አቀጣጥሎ በቆሎ ጠባብሶ ...
አየሁ አላየሁም...ሰማሁ አልሰማሁም ...
በላልቶ አፍ አብሶ ...
ለስለሶ አስፈትሎ የ'ናት ኩታ ለብሶ ...
ላዋቂ ተልኮ ለልጅ ተጎናብሶ ...
ደስ ይላል መስከረም !
.
እንደቢራ ቢሮ አበባ ለአበባ ዐደይ እንቡር እንቡር ...
በፍቅር ለመክረም ... !
ደስ ይላል መስከረም !
ወፉ ከነ ጎጆው እሥከ መናጆው ...
ንቡ ከነ ቀፎው መረባ ከነ እርፎው ...
በዐደይ ለምለም ክብር ለመስከረም ክብር ...
ቅዱስ ! ቅዱስ ! ቅዱስ !
የዓመት አሥራት ሊያፈስ ...
ሊያስገባለት ግብር ...
በዝማሬ ሲያብር ...
አንጄት ሲበረብር ... !
ደስ ይላል መስከረም !
ተዋዶ ወዶ ተወሕዶ ... ያንጀት ተፈቃቅዶ ...
ባንድ አብሮ ለመክረም ...
ደስ ይላል መስከረም !
ለቅኔ ዘረፋው ጠፈፍ ሲል ፈፋው ...
የቆሎ ተማሪ ያ ተመራማሪ ...
የወላዲት አምላክ የድንግል አዝማሪ ...
ያ ደበሎ ለባሽ .... !
በእግዚትነ ማሪያም ...እባካቹህ እባሽ እባካቹህ ቁራሽ..
እያለ ሲለምን ...
ከጥንቅሹ ቅንጥሽ ማሩቴ ባይሰጠው ...
አይቀር መደንገጡ አራሽ አባ ወራሽ ማብላት ያሰለጠው..!
የማይለወጠው..!
በዐይኑ እየመዘነ በልቡ እማይመርጠው ...
ገሩ ባላገሩ...!
ያ ባለሞፈሩ ያ ባለዘገሩ ...,!
በሞቴ ነው ቋንቋው ስሞት ነው ነገሩ...!
ደስ ይላል መስከረም !
.
ወዶ ተወሕዶ ያንጀት ተፈቃቅዶ ...!
አንድ ልብ አቅዶ...!
አንድ ላይ ለመክረም...!
ደስ ይላል መስከረም !
...
ጥቅምትና ኅዳር ቢያዋውል ምንጭ ዳር ...
ታኅሳስና ጥር ዐውድማ አስለቅልቆ ጥሪት እሚያስቋጥር..
የካቲት መጋቢት መኸር አስከትቶ ቢያበስል እንደ ዐቃቢት..
ሚያዚያና ግንቦቱ ተርቲበኛው ቀርቦ ወርዶ ራከቦቱ...
የላም ልጅ በዋንጫ ቢቀርብ ሥልባቦቱ...
ሰኔ ሐምሌ ነሐሴ እንደ ቄስ ምናሴ...
እያረበረበ ደግሞ እየወረበ...
ሰማይ በበረቀ ታርሶርሶ ሲስረቀረቅ...
ከራሱ እስኪታረቅ...!
ሁሉም እንደ ግብሩ..
ሁሉም እንደ ሙያው...!
አሥራ ሁለቱም ወር ...
እዮሃ አበባዬ መስከረም ሲጠባ..
ያኔ ነው ገቢያ..
ያኔ ነው መታያው ...
ያኔ ነው ማባያው ...
ደስ ይላል መስከረም ! ! !
.
( ሙሉ ጌታ ተስፋዬ )💚🌼💛🌼❤️🌼
… እንቁጣጣሽ ነበር መስከረም ሲጠባ
አውቆ የበቀለ ወፍ ዘራሽ አበባ፡፡
ለምለም አረንጓዴ…
ያልተጠበቀ መስክ ከብት የሚግጥበት
የደመና ግላጭ የሚጫወትበት፡፡
ሌላም ብዙ ነበር
ሌላም… ደግሞ ሌላ
አለብኝ ትዝታ!
ዘመዶቼ ሳሙኝ
ጓደኞቼም ጋብዙኝ
ሊስትሮ ጨብጠኝ
ባለጋሪ ንዳ መንገዴን አሳየኝ
ያገሬ ልጅ ቆንጆ ‹‹ቤት ለእንግዳ›› በይኝ
አለብኝ ትዝታ…
ገ/ክርስቶስ ደስታ
(እንደገና)🌼🌼🌼
…በይ ብር በይ ቢራ ቢሮ፣ ክረምት ላንቺ
ብቻ አለፈ
ሌላው በጎርፍ ጎረፈ
ሞተ፣ በተኛበት ረጋ…
ፀደይ ላንቺ ብቻ ነጋ
ሽር ብለሽ መንቆጥቆጥ ነው፤ ከዚያም፤
ከዚያም፤ ከዚያም ሰምሮ
አወቅሁብሽ፤ ነቃሁብሽ፤ አንቺ ሕይወት
ቢራ ቢሮ…
ቀናሁ መሰል አንች ወላዋይ?
ነይ ብር በይ እንወያይ
አንቺ የዕፅዋት አዋዋይ
ከፀደይ ጋር ፀደይ መሳይ
ከአበባም አበባ መሳይ…
ምን አለበት ላንዲት ሰሞን
ቢራ ቢሮ እኔ አንቺን ብሆን?
ፀጋዬ ገ/መድህን
(ሕይወት ቢራቢሮ)🌼🌼🌼
… ወፎች ሲዘምሩ ሰማይ ደማስ መስሎ፣
ሐሴት ገባ ልቤ በውበት ተኩሎ፡፡
ዮሐንስ አድማሱ
(ወፎች በተጥለግለግ - 1955 ዓ.ም)
* * *
…ነበረች አበባ፣
በሾህ ተቀንብባ፣
መዓዛዋ ዘምቶ፣
ተወርዋሪን ኮከብ አቀረበው ጠርቶ፡፡
በውበት ብትልቅ ይህች የዋህ አበባ፣
ረብ የሰው ዘየ በሾህ ተቀንብባ፣
እሾህ አያስደርስ፣ ቆንጥሩ አያስጠጋ፣ የዘመን
ጋሬጣ አድርጓት ሰለባ፣
በእጦት መቃጠል ነው መዓዛዋ ሲያውድ
ከልብ እየገባ፡፡
ዮሐንስ አድማሱ
(ተወርዋሪ ኮከብ)🌼🌼🌼
የተስፋዬ ዛፉ
ሊከረከም ቅርንጫፉ፣
ሥሩ ሲነቃቀል
ሲበጠስ ሲፈነገል፤
ጭላንጭል ስትዳፈን
ብርሀን ዐይኑ ሲከደን፣
አንጥፌ ደርቤ ማቄን
ዘንግቻት እንቁጣጣሽን
ፀደይ አበባ ዐደዬን፣
በድቅድቅ ተቀመጥሁኝ
ላለማሰብ እያሰብሁኝ፣
የልቤን ልበ ባሻነት ገሰጽኩኝ
ተስፋ መቁረጥን ተስፋ አረኩኝ፡፡
ደበበ ሰይፉ
(የተስፋዬ ዛፉ)🌼🌼🌼
@getem
@getem
@balmbaras
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በግርሻ'ጣይ ሰርዶ ነቅሎ በሚያዚያንሽ ተርበጥብጦ ...
በግንቦት ሐሩር ተቀቅሎ ... በፀሐይ አብስሎ በዝናብ አብቅሎ
ከወዳጅ ከዘመድ ተቀላቅሎ ...
ባዝራን ከአህያ አዳቅሎ ...
በባለበርሸት ሽልም በቅሎ ...
ተፈናጦ አብሮ ገስግሶ ...
ጅራፍ ግርፊያ ሆያ ሆዬ ...ቡሄ በሉ ተጫውቶ ...
ኪዳነ ምሕረትን አንግሶ ... ደግሞ በወሩ ለአስተሮዬው..
ግሼን ማሪያም እማአርያም ... ደጀሰላም ደርሶ ለመሳለም..
" እዮሃ አበባዬ መስከረም ጠባዬ ..
ዐደይ ለምለም ለኔ እንዳንቺ የለም..."
እያሉ ንጥቂያ ...
ከጀንበር መፍለቂያ እሥከ ጀንበር መጥለቂያ
አለላ ነቅሎ ባሕር እንጉዳይ ...
ጀግና ሰውገዳይ...
አካል እንጉዳይ...
እያሉ ሲያንጎራጉሩ
ደስ ይላል መስከረም !
.
ቡቃያው ጣል ከንበል ሲስ ...
ሽሩባዋ ወርዶ እንዲያ ሲዘናፈል ...
ልቤ እንደበቆሎ ያድራል ሲፈለፈል...
በቀጭን ተሰርታ ሥትል ዘንከት ዘንከት ...
ጃሎ ሲል ሊያነጋ አገር በመለከት ...
ለመስቀል ጠንስሶ ... በማድጋ ገንቦ ለእንግዳ ቀንሶ ...
በሞቴ አፈር ስሆን እያለ ሲያጋፍር ...
ጥርስ እንጎቻ አስፍቶ አሞጭ በመሰለው እርጎ ፍርፍር ...
እንኳን ሳቅ ጨዋታው ድብድቡ ልፊያው ...
ድገሙኝ ያሰኛል ሰፈፍ የለሽ ሞገድ መደዶ ዘር ዜማ ሲቆረቆር ክትፊያው..
ደስ ይላል መስከረም !
.
የሽንብራ ሸት እየጠረጠሩ ...
የልጅነት ሚዜ 'ኧረ አይዋ ክንዴ' እያሉ እየጠሩ ..
አብሮ ወፍ ጥበቃ ማማ ላይ ተሰቅሎ ...
ካፊያውን በገሳ በአንድ ተጠልሎ...
እሳት አቀጣጥሎ በቆሎ ጠባብሶ ...
አየሁ አላየሁም...ሰማሁ አልሰማሁም ...
በላልቶ አፍ አብሶ ...
ለስለሶ አስፈትሎ የ'ናት ኩታ ለብሶ ...
ላዋቂ ተልኮ ለልጅ ተጎናብሶ ...
ደስ ይላል መስከረም !
.
እንደቢራ ቢሮ አበባ ለአበባ ዐደይ እንቡር እንቡር ...
በፍቅር ለመክረም ... !
ደስ ይላል መስከረም !
ወፉ ከነ ጎጆው እሥከ መናጆው ...
ንቡ ከነ ቀፎው መረባ ከነ እርፎው ...
በዐደይ ለምለም ክብር ለመስከረም ክብር ...
ቅዱስ ! ቅዱስ ! ቅዱስ !
የዓመት አሥራት ሊያፈስ ...
ሊያስገባለት ግብር ...
በዝማሬ ሲያብር ...
አንጄት ሲበረብር ... !
ደስ ይላል መስከረም !
ተዋዶ ወዶ ተወሕዶ ... ያንጀት ተፈቃቅዶ ...
ባንድ አብሮ ለመክረም ...
ደስ ይላል መስከረም !
ለቅኔ ዘረፋው ጠፈፍ ሲል ፈፋው ...
የቆሎ ተማሪ ያ ተመራማሪ ...
የወላዲት አምላክ የድንግል አዝማሪ ...
ያ ደበሎ ለባሽ .... !
በእግዚትነ ማሪያም ...እባካቹህ እባሽ እባካቹህ ቁራሽ..
እያለ ሲለምን ...
ከጥንቅሹ ቅንጥሽ ማሩቴ ባይሰጠው ...
አይቀር መደንገጡ አራሽ አባ ወራሽ ማብላት ያሰለጠው..!
የማይለወጠው..!
በዐይኑ እየመዘነ በልቡ እማይመርጠው ...
ገሩ ባላገሩ...!
ያ ባለሞፈሩ ያ ባለዘገሩ ...,!
በሞቴ ነው ቋንቋው ስሞት ነው ነገሩ...!
ደስ ይላል መስከረም !
.
ወዶ ተወሕዶ ያንጀት ተፈቃቅዶ ...!
አንድ ልብ አቅዶ...!
አንድ ላይ ለመክረም...!
ደስ ይላል መስከረም !
...
ጥቅምትና ኅዳር ቢያዋውል ምንጭ ዳር ...
ታኅሳስና ጥር ዐውድማ አስለቅልቆ ጥሪት እሚያስቋጥር..
የካቲት መጋቢት መኸር አስከትቶ ቢያበስል እንደ ዐቃቢት..
ሚያዚያና ግንቦቱ ተርቲበኛው ቀርቦ ወርዶ ራከቦቱ...
የላም ልጅ በዋንጫ ቢቀርብ ሥልባቦቱ...
ሰኔ ሐምሌ ነሐሴ እንደ ቄስ ምናሴ...
እያረበረበ ደግሞ እየወረበ...
ሰማይ በበረቀ ታርሶርሶ ሲስረቀረቅ...
ከራሱ እስኪታረቅ...!
ሁሉም እንደ ግብሩ..
ሁሉም እንደ ሙያው...!
አሥራ ሁለቱም ወር ...
እዮሃ አበባዬ መስከረም ሲጠባ..
ያኔ ነው ገቢያ..
ያኔ ነው መታያው ...
ያኔ ነው ማባያው ...
ደስ ይላል መስከረም ! ! !
.
( ሙሉ ጌታ ተስፋዬ )💚🌼💛🌼❤️🌼
… እንቁጣጣሽ ነበር መስከረም ሲጠባ
አውቆ የበቀለ ወፍ ዘራሽ አበባ፡፡
ለምለም አረንጓዴ…
ያልተጠበቀ መስክ ከብት የሚግጥበት
የደመና ግላጭ የሚጫወትበት፡፡
ሌላም ብዙ ነበር
ሌላም… ደግሞ ሌላ
አለብኝ ትዝታ!
ዘመዶቼ ሳሙኝ
ጓደኞቼም ጋብዙኝ
ሊስትሮ ጨብጠኝ
ባለጋሪ ንዳ መንገዴን አሳየኝ
ያገሬ ልጅ ቆንጆ ‹‹ቤት ለእንግዳ›› በይኝ
አለብኝ ትዝታ…
ገ/ክርስቶስ ደስታ
(እንደገና)🌼🌼🌼
…በይ ብር በይ ቢራ ቢሮ፣ ክረምት ላንቺ
ብቻ አለፈ
ሌላው በጎርፍ ጎረፈ
ሞተ፣ በተኛበት ረጋ…
ፀደይ ላንቺ ብቻ ነጋ
ሽር ብለሽ መንቆጥቆጥ ነው፤ ከዚያም፤
ከዚያም፤ ከዚያም ሰምሮ
አወቅሁብሽ፤ ነቃሁብሽ፤ አንቺ ሕይወት
ቢራ ቢሮ…
ቀናሁ መሰል አንች ወላዋይ?
ነይ ብር በይ እንወያይ
አንቺ የዕፅዋት አዋዋይ
ከፀደይ ጋር ፀደይ መሳይ
ከአበባም አበባ መሳይ…
ምን አለበት ላንዲት ሰሞን
ቢራ ቢሮ እኔ አንቺን ብሆን?
ፀጋዬ ገ/መድህን
(ሕይወት ቢራቢሮ)🌼🌼🌼
… ወፎች ሲዘምሩ ሰማይ ደማስ መስሎ፣
ሐሴት ገባ ልቤ በውበት ተኩሎ፡፡
ዮሐንስ አድማሱ
(ወፎች በተጥለግለግ - 1955 ዓ.ም)
* * *
…ነበረች አበባ፣
በሾህ ተቀንብባ፣
መዓዛዋ ዘምቶ፣
ተወርዋሪን ኮከብ አቀረበው ጠርቶ፡፡
በውበት ብትልቅ ይህች የዋህ አበባ፣
ረብ የሰው ዘየ በሾህ ተቀንብባ፣
እሾህ አያስደርስ፣ ቆንጥሩ አያስጠጋ፣ የዘመን
ጋሬጣ አድርጓት ሰለባ፣
በእጦት መቃጠል ነው መዓዛዋ ሲያውድ
ከልብ እየገባ፡፡
ዮሐንስ አድማሱ
(ተወርዋሪ ኮከብ)🌼🌼🌼
የተስፋዬ ዛፉ
ሊከረከም ቅርንጫፉ፣
ሥሩ ሲነቃቀል
ሲበጠስ ሲፈነገል፤
ጭላንጭል ስትዳፈን
ብርሀን ዐይኑ ሲከደን፣
አንጥፌ ደርቤ ማቄን
ዘንግቻት እንቁጣጣሽን
ፀደይ አበባ ዐደዬን፣
በድቅድቅ ተቀመጥሁኝ
ላለማሰብ እያሰብሁኝ፣
የልቤን ልበ ባሻነት ገሰጽኩኝ
ተስፋ መቁረጥን ተስፋ አረኩኝ፡፡
ደበበ ሰይፉ
(የተስፋዬ ዛፉ)🌼🌼🌼
@getem
@getem
@balmbaras
❤1👍1
ወቅታዊ አበባየሁሽ
(በላይ በቀለ ወያ)ፈገግ ብላችሁ ዋሉ
.
.
ዋ ብለን መጣን ዋ ብለን
እስከመቼ "እህ " ሆ እንላን
ዋ ብለን መጣን ዋ ብለን
አበባየሁሽ
/ለምለም/
ገንቡ በተራ
/ለምለም/
እንጨት ሰባብረን
/ለምለም/
ቤት እስክንሰራ
/ለምለም/
እንኳን ቤትና
/ለምለም/
የለንም አጥር
/ለምለም/
ደጅ እናድራለን
/ለምለም/
ዘር ስንቆጥር
/ለምለም/
ዘርማንዘር ቆጥረን
/ለምለም/
ሥንሰራ ቤት
/ለምለም/
ለውጡን ሚመራው
/ለምለም/
ደጉ መንግስት
/ለምለም/
ያፈርስብናል
/ለምለም/
መዝናኛ ቦታ ለመገንባት ፡፡
........................... ......
አደይ
ያገር ጉዳይ
ውይ ስቃይ፡፡
አደይ
የጋራ ታሪክ ፣ የለንም ባይ
የጋራ ድንጋይ አይደለም ወይ
።።።
እቴ አበሳ አቴ አበሳዬ
"አዬ እቴ አበሳዬ"
አቴ አበሳ ስትለኝ ከርማ
"አዬ እቴ አበሳዬ"
ባንክ ዘርፋ ነፃ አውጪዬማ
ጥላኝ ጠፋሽ ፣ ድምጿን ሳልሰማ
"አዬ እቴ አበሳዬ"
መብራት ሀይል ሁሌ ጨለማ
"አዬ እቴ አበሳዬ"
ውሃ ልማት ውሃ ሚያስጠማ
"አዬ እቴ አበሳዬ"
መንገድ ሞልቶ መጎዝ ነው አድማ
"አዬ አቴ አበሳዬ"
ይሁን ኑሮ ከተባለማ
"አዬ አቴ አበሳዬ"
አዬ
"እቴ አበሳዬ"
አዬ
"እቴ አበሳዬ"
...................
እዬዬ
እህ ሁሌ እዬዬ
ገዦች አሉ ብዬ
በገዛ ሀገሬ ላይ በዛብኝ ስቃዬ፡፡
........... ......................
ይሸታል ሽንኩርት ሽንኩርት
የአባብዬ ምኩት
አይሸትም ዶሮ ዶሮ
የእማምዬ ጓሮ
ዶሮ አልሰሩም መሠል ፣ ሽንኩርት ዋጋው ንሮ
።።
ከብረው ይቆዩን ከብረው
ተረኝነትን ጥለው ፣ዘረኝነትን ቀብረው
ሺህ አክቲቪስቶች አስረው
ቅድሚያ ለሰው ልጅ ሰጥተው
ህዝቦችን አቀራርበው
ሜንጫና ዱላ ጥለው
አንዲት ኢትዮጵያን ይዘው
ከብረው ይቆዩን ከብረው።
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ለመላው የአንዲት ኢትዮጵያ እምነት ተከታዮች መልካም አዲስ አመት
@getem
@getem
@GEBRIEL_19
(በላይ በቀለ ወያ)ፈገግ ብላችሁ ዋሉ
.
.
ዋ ብለን መጣን ዋ ብለን
እስከመቼ "እህ " ሆ እንላን
ዋ ብለን መጣን ዋ ብለን
አበባየሁሽ
/ለምለም/
ገንቡ በተራ
/ለምለም/
እንጨት ሰባብረን
/ለምለም/
ቤት እስክንሰራ
/ለምለም/
እንኳን ቤትና
/ለምለም/
የለንም አጥር
/ለምለም/
ደጅ እናድራለን
/ለምለም/
ዘር ስንቆጥር
/ለምለም/
ዘርማንዘር ቆጥረን
/ለምለም/
ሥንሰራ ቤት
/ለምለም/
ለውጡን ሚመራው
/ለምለም/
ደጉ መንግስት
/ለምለም/
ያፈርስብናል
/ለምለም/
መዝናኛ ቦታ ለመገንባት ፡፡
........................... ......
አደይ
ያገር ጉዳይ
ውይ ስቃይ፡፡
አደይ
የጋራ ታሪክ ፣ የለንም ባይ
የጋራ ድንጋይ አይደለም ወይ
።።።
እቴ አበሳ አቴ አበሳዬ
"አዬ እቴ አበሳዬ"
አቴ አበሳ ስትለኝ ከርማ
"አዬ እቴ አበሳዬ"
ባንክ ዘርፋ ነፃ አውጪዬማ
ጥላኝ ጠፋሽ ፣ ድምጿን ሳልሰማ
"አዬ እቴ አበሳዬ"
መብራት ሀይል ሁሌ ጨለማ
"አዬ እቴ አበሳዬ"
ውሃ ልማት ውሃ ሚያስጠማ
"አዬ እቴ አበሳዬ"
መንገድ ሞልቶ መጎዝ ነው አድማ
"አዬ አቴ አበሳዬ"
ይሁን ኑሮ ከተባለማ
"አዬ አቴ አበሳዬ"
አዬ
"እቴ አበሳዬ"
አዬ
"እቴ አበሳዬ"
...................
እዬዬ
እህ ሁሌ እዬዬ
ገዦች አሉ ብዬ
በገዛ ሀገሬ ላይ በዛብኝ ስቃዬ፡፡
........... ......................
ይሸታል ሽንኩርት ሽንኩርት
የአባብዬ ምኩት
አይሸትም ዶሮ ዶሮ
የእማምዬ ጓሮ
ዶሮ አልሰሩም መሠል ፣ ሽንኩርት ዋጋው ንሮ
።።
ከብረው ይቆዩን ከብረው
ተረኝነትን ጥለው ፣ዘረኝነትን ቀብረው
ሺህ አክቲቪስቶች አስረው
ቅድሚያ ለሰው ልጅ ሰጥተው
ህዝቦችን አቀራርበው
ሜንጫና ዱላ ጥለው
አንዲት ኢትዮጵያን ይዘው
ከብረው ይቆዩን ከብረው።
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ለመላው የአንዲት ኢትዮጵያ እምነት ተከታዮች መልካም አዲስ አመት
@getem
@getem
@GEBRIEL_19
👍1
እነሆ መስከረም መጣ
ኑ!
አዲስ እቅድ እናውጣ።
ቃል-ኪዳናችንን..
ራስ-ለራስ የገባነውን...
ከኻቻምና ያሳደርነውን...
አምናም አስበን ያልፈፀምነውን ...
ኑ!
አሮጌው ውጥናችንን እንኳል
ዘንድሮስ አይቀርም ይሳካል...!!!
(በርናባስ ከበደ)
@getem
@getem
@gebriel_19
ኑ!
አዲስ እቅድ እናውጣ።
ቃል-ኪዳናችንን..
ራስ-ለራስ የገባነውን...
ከኻቻምና ያሳደርነውን...
አምናም አስበን ያልፈፀምነውን ...
ኑ!
አሮጌው ውጥናችንን እንኳል
ዘንድሮስ አይቀርም ይሳካል...!!!
(በርናባስ ከበደ)
@getem
@getem
@gebriel_19
እይታ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼
እዮሀ አበባዬ
መስከረም ጠባዬ
መስከረም ሲጠባ
ወደ ሀገሬ ልግባ
ሐሜት ባይሆንብኝ ስር የሌለው ወሬ
መኖርን እሻለው እኔስ በሀገሬ
እኔን የገረመኝ
በዚህች ሀገር ውስጥ ሰርክ የሚለፈለፍ
መስከረም በጠባ በወራቱ ግዜ ሁሌ የሚለፈፍ
ይህ መዝሙር መልክቱ በሌላ ስናየው
ብዙ ያልተመለሰ ግዙፍ ጥያቄ አለው
ለምሳሌ
አንድ ሀገር ላይ
ሆኖ ወደ ሀገሬ ልግባ ምን አይነት ፈሊጥ ነው
አንድ ሀገር ውስጥ
ሆኖ ወደ ሀገሬ ልሂድ ማለትስ ምንድነው
አንዳች ነገር ባይኖር ድብቅ ሴራ ነገር
ባለ ሀገሩ ህዝቤ እንዲህ አይልም ነበር
በዛኛው ጫፍ ሆነን ነገሩን ስናየው
ግጥሙ ሲገጠም
ስንኝ ሲደረደር ክልል እና ብሄር አለ እንደማለት ነው
አለበለዚያ ግን
ገጣሚው ሰውዬ
ወይ ይጠነቁላል ወይ ነብይ ነበር ብሎ መመስከር ነው
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መልካም አዲስ ዓመት
✍✍ ናብሊስ
@nablis12
@getem
@getem
@getem
🌼🌼🌼🌼🌼🌼
እዮሀ አበባዬ
መስከረም ጠባዬ
መስከረም ሲጠባ
ወደ ሀገሬ ልግባ
ሐሜት ባይሆንብኝ ስር የሌለው ወሬ
መኖርን እሻለው እኔስ በሀገሬ
እኔን የገረመኝ
በዚህች ሀገር ውስጥ ሰርክ የሚለፈለፍ
መስከረም በጠባ በወራቱ ግዜ ሁሌ የሚለፈፍ
ይህ መዝሙር መልክቱ በሌላ ስናየው
ብዙ ያልተመለሰ ግዙፍ ጥያቄ አለው
ለምሳሌ
አንድ ሀገር ላይ
ሆኖ ወደ ሀገሬ ልግባ ምን አይነት ፈሊጥ ነው
አንድ ሀገር ውስጥ
ሆኖ ወደ ሀገሬ ልሂድ ማለትስ ምንድነው
አንዳች ነገር ባይኖር ድብቅ ሴራ ነገር
ባለ ሀገሩ ህዝቤ እንዲህ አይልም ነበር
በዛኛው ጫፍ ሆነን ነገሩን ስናየው
ግጥሙ ሲገጠም
ስንኝ ሲደረደር ክልል እና ብሄር አለ እንደማለት ነው
አለበለዚያ ግን
ገጣሚው ሰውዬ
ወይ ይጠነቁላል ወይ ነብይ ነበር ብሎ መመስከር ነው
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መልካም አዲስ ዓመት
✍✍ ናብሊስ
@nablis12
@getem
@getem
@getem
እንዲህ ነኝ!(ልዑል ሀይሌ)
“እንዴት ነህ?” ከምትሉ
እስቲ እንደዚህ ሁኑ!
.
የቁስሌን መጠን ቁሰሉና ለኩ ፤
የሚያሳክከኝን ውሰዱና እከኩ፤
የሚያመኝን ሕመም ታመሙና ኑሩት፤
የልቤን ፍላሎት
አይገልፀውምና እንዲሁ ሲናገሩት።
.
“እንዴት ነህ?” ከምትሉ
እስቲ እንደዚህ ሁኑ!
.
’ሚነፍሰውን ንፋስ
በጎኔ ሚዘልቀው በጎናችሁ አዝልቁት፤
’ሚዘንበውን ዝናብ
’ሚያበሰብሰኝን በጉንጫችሁ አውርዱት፤
..
የሚያንገበግበኝ
የወዳጄን ክህደት በወዳጅ ተካዱ፤
እሾህ ላይ ስራመድ በእሾህ ላይ ሂዱ።
..
ያኔ ነው ምታውቁት
የኔን የሕይወት ፈር፤
“ደህና ነው” በሚል ቃል ይህ ሁሉ ሲሰፈር።
፲፪.፩.፲፩ ዓ.ም.
@getem
@getem
@gebriel_19
“እንዴት ነህ?” ከምትሉ
እስቲ እንደዚህ ሁኑ!
.
የቁስሌን መጠን ቁሰሉና ለኩ ፤
የሚያሳክከኝን ውሰዱና እከኩ፤
የሚያመኝን ሕመም ታመሙና ኑሩት፤
የልቤን ፍላሎት
አይገልፀውምና እንዲሁ ሲናገሩት።
.
“እንዴት ነህ?” ከምትሉ
እስቲ እንደዚህ ሁኑ!
.
’ሚነፍሰውን ንፋስ
በጎኔ ሚዘልቀው በጎናችሁ አዝልቁት፤
’ሚዘንበውን ዝናብ
’ሚያበሰብሰኝን በጉንጫችሁ አውርዱት፤
..
የሚያንገበግበኝ
የወዳጄን ክህደት በወዳጅ ተካዱ፤
እሾህ ላይ ስራመድ በእሾህ ላይ ሂዱ።
..
ያኔ ነው ምታውቁት
የኔን የሕይወት ፈር፤
“ደህና ነው” በሚል ቃል ይህ ሁሉ ሲሰፈር።
፲፪.፩.፲፩ ዓ.ም.
@getem
@getem
@gebriel_19
👍1
ለ 10ኛ ክፍል የማትሪክ ተፈታኞች በሙሉ ውጤት ዛሬ 10:00
ስላሚወጣ በቀላሉ ውጤቶን ለማየት @neaea_neaea_bot ተጠቀሙ ፣ ቀላል ፣ ቀልጣፋ እና ታአማኒ ያለምንም የሰው ጣልቃ ገበነት 24/7 የሚሰራ ።
@neaea_neaea_bot
የእርሶን እና የጓደኞዎቾ ለማየት ይህን bot ይጠቀሙ
12 ኛ ምድብ ምት ጠብ ቁም እዚሁ bot ላይ ታገኙታላችሁ
@getem
@getem
ስላሚወጣ በቀላሉ ውጤቶን ለማየት @neaea_neaea_bot ተጠቀሙ ፣ ቀላል ፣ ቀልጣፋ እና ታአማኒ ያለምንም የሰው ጣልቃ ገበነት 24/7 የሚሰራ ።
@neaea_neaea_bot
የእርሶን እና የጓደኞዎቾ ለማየት ይህን bot ይጠቀሙ
12 ኛ ምድብ ምት ጠብ ቁም እዚሁ bot ላይ ታገኙታላችሁ
@getem
@getem
#እንቁ_ለጌጥሽ
🌼🌼🌼🌼🌼
እንዴት ያለ እድል ፥ አወይ ጥቁር ምላስ
ባከላትሽ ታዞ
በትንታግ ዘመንሽ አዲስ እጣሽ ሲላስ
ምርቃት ይሁን እርግማን
ዋርሳ ይሁን ስጦታ .....ሳይገባሽ
እንቁ-ለጣጣሽ ብትባይ
ስለምን ለቤ'ክ አልሽ?
እልፍ አዲስ አመት ፥ አያሌ መባቻ
ጌጡ የት ሄዶብሽ ?
ችጋር የተረፈሽ ፥ ባያትሽ ስልቻ
አንድ ቀን እልልታ ፥ ሶስት መቶ ቀን ለቅሶ
ዘረኛ ቋቁቻ
እንደ ሸማ ጥለት ፥ ሰውነትሽን ወርሶ
አንጀቱ የቀናው ፥ መብሉን አስመልሶ
የሚበላው ያጣም
ጥሬውን ቆርጥሞ ፥ በምራቅ ለውሶ
እኩል ...እየ-ዬ ነው !!!
ባሳለፍነው ዘመን ፥ ከእልልታው ለጥቆ
ለነብስ እየሰጉ ፥ ለስጋ ተሳቆ
አይሻገር የለ ፥ ሶስት መቶ ቀን አልቆ
አዲስ ዘመን መጣ
ካለንበት ቡኮ ፥:ከማጡ ሳንወጣ።
አዲስ አመት በሚል ፥ ደስታ ልትቃርሚ
ጭቃ መደላድል ፥ ምን አምነሽ ትቆሚ?
ጣትሽ ሳይጠነከር እድፍሽ ሳይጠራ
ሽንሽን ብትለብሺ ከሀር የተሰራ
ያዳለጠሽ ግዜ
መሬት ባለጌ ነው ስጋሽን አይፈራ
ለቀን አያውልሽ የጥበብሽ ጮራ።
እና ከተረዳሽ ከገባሽ መልእክቴ
እርግማንሽን አንሺ !!!
ላይተር ሳያጠፉ ፥ መመፃደቅ ይቅር ፥ መዘወሩ ቦቴ
የተመረቀ ቀን
እንኳንስ በእንቁ ፥ ይከብራል በአርቴ
እንቁ ለጣጣሽ ይታጠፍ
እንቁ ለጌጥሽ #እናቴ !! ።
✍ #አብርሀም_ተክሉ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
#መልካም_አዲስ_አመት_ጣጣችን_ይፈንገል_በሰላም_በፍቅር_በደስታ_በብልፅግና_ማጌጫ_2012_ይሁንልን
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@getem
@getem
@getem
🌼🌼🌼🌼🌼
እንዴት ያለ እድል ፥ አወይ ጥቁር ምላስ
ባከላትሽ ታዞ
በትንታግ ዘመንሽ አዲስ እጣሽ ሲላስ
ምርቃት ይሁን እርግማን
ዋርሳ ይሁን ስጦታ .....ሳይገባሽ
እንቁ-ለጣጣሽ ብትባይ
ስለምን ለቤ'ክ አልሽ?
እልፍ አዲስ አመት ፥ አያሌ መባቻ
ጌጡ የት ሄዶብሽ ?
ችጋር የተረፈሽ ፥ ባያትሽ ስልቻ
አንድ ቀን እልልታ ፥ ሶስት መቶ ቀን ለቅሶ
ዘረኛ ቋቁቻ
እንደ ሸማ ጥለት ፥ ሰውነትሽን ወርሶ
አንጀቱ የቀናው ፥ መብሉን አስመልሶ
የሚበላው ያጣም
ጥሬውን ቆርጥሞ ፥ በምራቅ ለውሶ
እኩል ...እየ-ዬ ነው !!!
ባሳለፍነው ዘመን ፥ ከእልልታው ለጥቆ
ለነብስ እየሰጉ ፥ ለስጋ ተሳቆ
አይሻገር የለ ፥ ሶስት መቶ ቀን አልቆ
አዲስ ዘመን መጣ
ካለንበት ቡኮ ፥:ከማጡ ሳንወጣ።
አዲስ አመት በሚል ፥ ደስታ ልትቃርሚ
ጭቃ መደላድል ፥ ምን አምነሽ ትቆሚ?
ጣትሽ ሳይጠነከር እድፍሽ ሳይጠራ
ሽንሽን ብትለብሺ ከሀር የተሰራ
ያዳለጠሽ ግዜ
መሬት ባለጌ ነው ስጋሽን አይፈራ
ለቀን አያውልሽ የጥበብሽ ጮራ።
እና ከተረዳሽ ከገባሽ መልእክቴ
እርግማንሽን አንሺ !!!
ላይተር ሳያጠፉ ፥ መመፃደቅ ይቅር ፥ መዘወሩ ቦቴ
የተመረቀ ቀን
እንኳንስ በእንቁ ፥ ይከብራል በአርቴ
እንቁ ለጣጣሽ ይታጠፍ
እንቁ ለጌጥሽ #እናቴ !! ።
✍ #አብርሀም_ተክሉ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
#መልካም_አዲስ_አመት_ጣጣችን_ይፈንገል_በሰላም_በፍቅር_በደስታ_በብልፅግና_ማጌጫ_2012_ይሁንልን
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@getem
@getem
@getem
"ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን"
(ይኸው ነው!)
"የዘመን ዕውነት ነን በደግነት ሰማይ በጥበብ የኖርን
ትግስትም ልክ አለው ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን
ማተብ አስሮን እንጂ ተጣልተን እንዳንቀር በክፍፍል ገደል
ካገር ፍቅር በልጦ ሞት ብርቃችን አይደል
ንገሩት_ለዛ_ሰው
ከአለም ጫፍ እስከ ጫፍ
ሀይል እንደተራራ ገዝፎ ቢከመርም
ክንዱን አፈርጥሞ
እልፍ የሰገደለት ጀግና ቢሰደርም
ዓለም የሞተበት
የጠላት ማርከሻ ጦር ቢደረድርም
በአንድ አይናችን ሰላም
በኢትዮጵያችን ክብር አንደራደርም "
ገጣሚ ህሊና ደሳለኝ
@getem
@getem
@getem
(ይኸው ነው!)
"የዘመን ዕውነት ነን በደግነት ሰማይ በጥበብ የኖርን
ትግስትም ልክ አለው ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን
ማተብ አስሮን እንጂ ተጣልተን እንዳንቀር በክፍፍል ገደል
ካገር ፍቅር በልጦ ሞት ብርቃችን አይደል
ንገሩት_ለዛ_ሰው
ከአለም ጫፍ እስከ ጫፍ
ሀይል እንደተራራ ገዝፎ ቢከመርም
ክንዱን አፈርጥሞ
እልፍ የሰገደለት ጀግና ቢሰደርም
ዓለም የሞተበት
የጠላት ማርከሻ ጦር ቢደረድርም
በአንድ አይናችን ሰላም
በኢትዮጵያችን ክብር አንደራደርም "
ገጣሚ ህሊና ደሳለኝ
@getem
@getem
@getem
ግጥም ሲፃፍበት!!!
ሲሄድ እያየነው ፤
እንደ ደራሽ ውሃ በስሜት ገንፍሎ፤
ጉልፍልፍ እያለ፤
ትልቁን ትንሹን በጉያው አጅሎ፤
ሃገሬው እያየው፤
ይሉኝታ ጠፍቶበት በአጀብ በሆሆታ ሲሄዴ ተግተልትሎ፤
ወንድሙን እንደ በግ፤
ሆ ብሎ በደቦ ዛፍ ላይ አንጠልጥሎ፤
በመንጋ ጉባኤ፤ ንፁሃንን ሰቅሎ፤
የገዛ ወገኑን በድንጋይ ውርጅብኝ በአደባባይ ወግሮ፤
በሜንጫ በዱላ ምስኪኖቹን ቀብሮ፤
መኪና እያስቆመ ፤
የገዛ ወገኑን ንብረት እየቀማ በሽፍትነት አድሮ፤
ዘሎ እየዘረፈ የሰው ድንኳን ሰብሮ፤
ወንድሙን ሲያደማ ሙቅ ውሃ እየደፋ ጀበና ወርውሮ፤
እንዴት መንጋ ይክፋው ፤
ግጥም ሲፃፍበት መንጋ ነህ ተብሎ???
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
ሲሄድ እያየነው ፤
እንደ ደራሽ ውሃ በስሜት ገንፍሎ፤
ጉልፍልፍ እያለ፤
ትልቁን ትንሹን በጉያው አጅሎ፤
ሃገሬው እያየው፤
ይሉኝታ ጠፍቶበት በአጀብ በሆሆታ ሲሄዴ ተግተልትሎ፤
ወንድሙን እንደ በግ፤
ሆ ብሎ በደቦ ዛፍ ላይ አንጠልጥሎ፤
በመንጋ ጉባኤ፤ ንፁሃንን ሰቅሎ፤
የገዛ ወገኑን በድንጋይ ውርጅብኝ በአደባባይ ወግሮ፤
በሜንጫ በዱላ ምስኪኖቹን ቀብሮ፤
መኪና እያስቆመ ፤
የገዛ ወገኑን ንብረት እየቀማ በሽፍትነት አድሮ፤
ዘሎ እየዘረፈ የሰው ድንኳን ሰብሮ፤
ወንድሙን ሲያደማ ሙቅ ውሃ እየደፋ ጀበና ወርውሮ፤
እንዴት መንጋ ይክፋው ፤
ግጥም ሲፃፍበት መንጋ ነህ ተብሎ???
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
ሚሌ ወዲህ ሃራ መጋሌ ስመራ፤
ኩርሚንጋፎ ቆቦ ዳዩ መንደፈራ፤
አቧራው ጨሰ አሉ፤
ከመሆኒ ጨርጨር ፤ ከዋጃ እስከ ጉራ ፤
መቼም ራያ ላይ፤
ወትሮም በሽበሽ ነው ልብና ተራራ።
ያች የራያ ልጅ ባለ ጥርቅ ጫማ ባለመልጎሚቱ ፤
ባለ ኩሌ ከንፈር ባለወተቲቱ ፤
የአባቶቿ ድንበር፤
ከዳዩ እስከ ራማ፤
ከኢቦ እስከ አላውሃ ፤ ታይቷት ምልክቱ፤
ራያ ነኝ ብላ ስመራ ስመራ ስመራ ልጅቱ ፤
ቦፌዋን ታቅፋ ፤
ጎንቢሶዋን ይዛ ለቀየው ተረፈች እንኳን ለማጀቱ።
ይኸ የራያ ሰው ፤
ይኸ የጨርጨር ሰው፤ ሁለትና ሶስቱ ፤
ድብ ይደረምሳል ፤
ሺ ቡከን ቢሰለፍ አይታጠፍ ፊቱ፤
ራቁት ያስኬዳል ደርሰው ከመጡበት በርስቱ በሚስቱ።
እንካ ልበስማ ፤
ማይ ማዩን ደርበው ጎንቢሶውን ታጠቅ፤
ለእነዚያ ሆዳሞች፤
ብለህ ንገርልኝ ፤
እዳው ለልጅ ልጅ ነው ራያን መዳፈር ማንነቱን መስረቅ።
ይህን ሸጋ ቦፌ፤
ይህንን ጎንቢሶ ታጠቅ በወገብህ፤ ዱላም ጨምርበት፤
ይኸው ነው ሰንደቁ፤
ይኸው ነው ባንዲራው የራያ ነፃነት የሚታወጅበት!!
አላ ዝናብ ባይጥል፤ ጎሊና ጅረቱ ቢሞላ ባይሞላ፤
አትጠራጠረኝ፤
ራያ ወሎ እንጅ፤ ራያ ራያ እንጅ አይደለም የሌላ።
ሃበከው !!!!ሃበከው!!!! ሃበከው !!!!!
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
እምወድሽዋ እንኳን መጣሽልኝ ❤️ ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!!❤️
በነገራችን ላይ ዛሬ ከ 7:00 ጀምሮ ሸገር ሬድዮ ብትሰሙ ጋዜጠኛ መኣዛ ብሩ ከጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያደረገችው ቃለመጠይቅ ትሰማላቹ ...ሁሌም ቅዳሜ ከሰዓታችን ገምሸርሸር የሚያደርግልን #ሸገር ሬድዮ ነው !! ይኸው ነው!!
@getem
@getem
@balmbaras
ኩርሚንጋፎ ቆቦ ዳዩ መንደፈራ፤
አቧራው ጨሰ አሉ፤
ከመሆኒ ጨርጨር ፤ ከዋጃ እስከ ጉራ ፤
መቼም ራያ ላይ፤
ወትሮም በሽበሽ ነው ልብና ተራራ።
ያች የራያ ልጅ ባለ ጥርቅ ጫማ ባለመልጎሚቱ ፤
ባለ ኩሌ ከንፈር ባለወተቲቱ ፤
የአባቶቿ ድንበር፤
ከዳዩ እስከ ራማ፤
ከኢቦ እስከ አላውሃ ፤ ታይቷት ምልክቱ፤
ራያ ነኝ ብላ ስመራ ስመራ ስመራ ልጅቱ ፤
ቦፌዋን ታቅፋ ፤
ጎንቢሶዋን ይዛ ለቀየው ተረፈች እንኳን ለማጀቱ።
ይኸ የራያ ሰው ፤
ይኸ የጨርጨር ሰው፤ ሁለትና ሶስቱ ፤
ድብ ይደረምሳል ፤
ሺ ቡከን ቢሰለፍ አይታጠፍ ፊቱ፤
ራቁት ያስኬዳል ደርሰው ከመጡበት በርስቱ በሚስቱ።
እንካ ልበስማ ፤
ማይ ማዩን ደርበው ጎንቢሶውን ታጠቅ፤
ለእነዚያ ሆዳሞች፤
ብለህ ንገርልኝ ፤
እዳው ለልጅ ልጅ ነው ራያን መዳፈር ማንነቱን መስረቅ።
ይህን ሸጋ ቦፌ፤
ይህንን ጎንቢሶ ታጠቅ በወገብህ፤ ዱላም ጨምርበት፤
ይኸው ነው ሰንደቁ፤
ይኸው ነው ባንዲራው የራያ ነፃነት የሚታወጅበት!!
አላ ዝናብ ባይጥል፤ ጎሊና ጅረቱ ቢሞላ ባይሞላ፤
አትጠራጠረኝ፤
ራያ ወሎ እንጅ፤ ራያ ራያ እንጅ አይደለም የሌላ።
ሃበከው !!!!ሃበከው!!!! ሃበከው !!!!!
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
እምወድሽዋ እንኳን መጣሽልኝ ❤️ ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!!❤️
በነገራችን ላይ ዛሬ ከ 7:00 ጀምሮ ሸገር ሬድዮ ብትሰሙ ጋዜጠኛ መኣዛ ብሩ ከጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያደረገችው ቃለመጠይቅ ትሰማላቹ ...ሁሌም ቅዳሜ ከሰዓታችን ገምሸርሸር የሚያደርግልን #ሸገር ሬድዮ ነው !! ይኸው ነው!!
@getem
@getem
@balmbaras
ሲነጋ ልንገርሽ
።።።።።።።።።።።
(ከድር መሀመድ)
ገለጥ ሲልልኝ
ድርብርቡ አፈና፤ጨለማው ተገፎ፤
ሽኩቻ ለትግል
እንቅልፍ ሲነሳ፤በሀገሩ ለፍፎ፤
ምንም አትበይ
ዛሬ ቃላት አጥተሽ፤አፍሽ ቢቀየድም፤
አትስጊ ግዴለም
ዶሮ ጮኸ አልጮኸ፤መንጋቱ አይቀርም፤
እንደነቃሁ ገና
ሲነጋ ልነግርሽ ፤ከንፈሬን ላልሼ ቃላት ፈልግና፤
ሳስብ እፈራለው
ሚስጥር እንዳይሾልከኝ፤ቃል እንዳላዛባ ሳላስብሆነና፤
ምን አልባት
በነገርሽ መሃል ሌላን፤ብተነፍስ ከመሀል ቆይቼ፤
ቃል ግቢልኝ!
አዝልቀሽ ላትሰጪኝ ላሳደኳቸው ነፍስ ወስደሽ ለጅቦቼ፤
በነገርሽ መሀል?
አትስጊ ግዴለም!
ዶሮ ጮኸ አልጮኸም መንጋቱ አይቀርም፤
ይሄው ነው
በጅ ያሳደጉት ጅብ አጉራሽ እጁን ቢነክስ መልሶ፤
ዘመኑ ይሆናል!
ወላጁን ሰዉቶ ተሹሞ የሚኖር መንጎችን ገርስሶ፤
ይሁና ከሆነ?
በመገርሰስ መሀል ራስ ሆኖ ከኖረ፤
መስማቱን ዘንግቶ
ወራጅ አለ እያሉት ዘግቶ ከበረረ፤
ለምን እንዳትይ?
አትስጊ ግዴለም
ዶሮ ጮኸ አልጮኸም መንጋቱ አይቀርም።
@getem
@getem
@kedir
።።።።።።።።።።።
(ከድር መሀመድ)
ገለጥ ሲልልኝ
ድርብርቡ አፈና፤ጨለማው ተገፎ፤
ሽኩቻ ለትግል
እንቅልፍ ሲነሳ፤በሀገሩ ለፍፎ፤
ምንም አትበይ
ዛሬ ቃላት አጥተሽ፤አፍሽ ቢቀየድም፤
አትስጊ ግዴለም
ዶሮ ጮኸ አልጮኸ፤መንጋቱ አይቀርም፤
እንደነቃሁ ገና
ሲነጋ ልነግርሽ ፤ከንፈሬን ላልሼ ቃላት ፈልግና፤
ሳስብ እፈራለው
ሚስጥር እንዳይሾልከኝ፤ቃል እንዳላዛባ ሳላስብሆነና፤
ምን አልባት
በነገርሽ መሃል ሌላን፤ብተነፍስ ከመሀል ቆይቼ፤
ቃል ግቢልኝ!
አዝልቀሽ ላትሰጪኝ ላሳደኳቸው ነፍስ ወስደሽ ለጅቦቼ፤
በነገርሽ መሀል?
አትስጊ ግዴለም!
ዶሮ ጮኸ አልጮኸም መንጋቱ አይቀርም፤
ይሄው ነው
በጅ ያሳደጉት ጅብ አጉራሽ እጁን ቢነክስ መልሶ፤
ዘመኑ ይሆናል!
ወላጁን ሰዉቶ ተሹሞ የሚኖር መንጎችን ገርስሶ፤
ይሁና ከሆነ?
በመገርሰስ መሀል ራስ ሆኖ ከኖረ፤
መስማቱን ዘንግቶ
ወራጅ አለ እያሉት ዘግቶ ከበረረ፤
ለምን እንዳትይ?
አትስጊ ግዴለም
ዶሮ ጮኸ አልጮኸም መንጋቱ አይቀርም።
@getem
@getem
@kedir
#ጥማት
በኮርማ ፣ በርችት ፣ ከምንቀበለው የዘመን መባቻ
ባርቲ ቡርቲ ወሬ ፥ በወገን ጥላቻ
እንደ ሀገር ኖሮ ፥ መሞት ለየብቻ
ምን አውቅልሽ በዝቶ.....
ውሎ ማደር ፈርተን ፥ በማጀት ጉልቻ
ቀናችንን ሳናምን
ጠጥተን ሳንረካ ፥ ጎርሰን ሳንጠግብ
ዛሬ ሳያከትም ፥ ለነገ ስናስብ
የሰቀቀን ጉርሻ ፥ ደጋግሞ እያነቀን
የኑሮ ውድነት ፥ በጠኔ እየናጠን
ዝም ባለ ሰፈር ፥ በፍርሀት ተጣብቀን
በጠራራ ፀሀይ ፥ ጨለማ አውሮን ፥ ምርኩዝ ተስፋ እያጣን
በልተን እንዳልበላ ፥ ስጋት እያከሳን
ካዲስ አመት በላይ ፥ ሰላም ነው የጠማን።
እንጂ!!
አሻፈረን ብንል ፥ ዘመን መች ይቆማል
ሲሻው የሳት እራት ፥ አልያ ዶሴ ገድል
የምንከትብበት
ባለ ሶስት መቶ ገፅ ፥ ብራና ያበጃል።
#ሰላማችን_ይብዛ
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
በኮርማ ፣ በርችት ፣ ከምንቀበለው የዘመን መባቻ
ባርቲ ቡርቲ ወሬ ፥ በወገን ጥላቻ
እንደ ሀገር ኖሮ ፥ መሞት ለየብቻ
ምን አውቅልሽ በዝቶ.....
ውሎ ማደር ፈርተን ፥ በማጀት ጉልቻ
ቀናችንን ሳናምን
ጠጥተን ሳንረካ ፥ ጎርሰን ሳንጠግብ
ዛሬ ሳያከትም ፥ ለነገ ስናስብ
የሰቀቀን ጉርሻ ፥ ደጋግሞ እያነቀን
የኑሮ ውድነት ፥ በጠኔ እየናጠን
ዝም ባለ ሰፈር ፥ በፍርሀት ተጣብቀን
በጠራራ ፀሀይ ፥ ጨለማ አውሮን ፥ ምርኩዝ ተስፋ እያጣን
በልተን እንዳልበላ ፥ ስጋት እያከሳን
ካዲስ አመት በላይ ፥ ሰላም ነው የጠማን።
እንጂ!!
አሻፈረን ብንል ፥ ዘመን መች ይቆማል
ሲሻው የሳት እራት ፥ አልያ ዶሴ ገድል
የምንከትብበት
ባለ ሶስት መቶ ገፅ ፥ ብራና ያበጃል።
#ሰላማችን_ይብዛ
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
#ሳቅና_እንባ😁😭
አትላወስ ፡ ሆዴ
እባክህ ፡ ሁን ፡ ደስተኛ
ዘንድሮ ፡ አልተገኘም
አርፎ ፡ የሚተኛ
አትጭስ ፡ አትብገን
አትላወስ ፡ ሆዴ
ኑሮና ፡ ተራራ
ይገፋል ፡ በዘዴ
ኸረ ፡ ፍቅር ፡ ፍቅር
ፍቅር ፡ ጠፋ ፡ ይላሉ
አፍቃሪ ፡ አይደለም
ጓደኛ ፡ የሆነ ፡ ሁሉ
የዚህ ፡ አለም ፡ ነገር
በጣም ፡ ይገርመኛል
ልሙትልህ ፡ እንዳላለ
ሊገልህ ፡ ይመጣል
በክፉ ፡ ቀን ፡ ጊዜ
ፍቅር ፡ የት ፡ ይገኛል ።
አንድ ፡ ሁለት
እያለ ፡ እያለሳለሰ
ፍቅርም ፡ ጠፋ
ትንቢቱ ፡ ደረሰ
መከራና ፡ ደስታ
ማግኘትና ፡ ማጣት
ሰማይና ፡ ምድር
ጨለማና ፡ ንጋት
ፅድቅና ፡ ኩነኔ
አዝመራና ፡ አበባ
ወትሮም ፡ የነበረ ፡ ነው
ድሮም ፡ ሳቅና ፡ እንባ ።
ግጥም ፡- ኢሳ ፡ ሙሀመድ ፡ (ዳና)
@getem
@getem
@getem
አትላወስ ፡ ሆዴ
እባክህ ፡ ሁን ፡ ደስተኛ
ዘንድሮ ፡ አልተገኘም
አርፎ ፡ የሚተኛ
አትጭስ ፡ አትብገን
አትላወስ ፡ ሆዴ
ኑሮና ፡ ተራራ
ይገፋል ፡ በዘዴ
ኸረ ፡ ፍቅር ፡ ፍቅር
ፍቅር ፡ ጠፋ ፡ ይላሉ
አፍቃሪ ፡ አይደለም
ጓደኛ ፡ የሆነ ፡ ሁሉ
የዚህ ፡ አለም ፡ ነገር
በጣም ፡ ይገርመኛል
ልሙትልህ ፡ እንዳላለ
ሊገልህ ፡ ይመጣል
በክፉ ፡ ቀን ፡ ጊዜ
ፍቅር ፡ የት ፡ ይገኛል ።
አንድ ፡ ሁለት
እያለ ፡ እያለሳለሰ
ፍቅርም ፡ ጠፋ
ትንቢቱ ፡ ደረሰ
መከራና ፡ ደስታ
ማግኘትና ፡ ማጣት
ሰማይና ፡ ምድር
ጨለማና ፡ ንጋት
ፅድቅና ፡ ኩነኔ
አዝመራና ፡ አበባ
ወትሮም ፡ የነበረ ፡ ነው
ድሮም ፡ ሳቅና ፡ እንባ ።
ግጥም ፡- ኢሳ ፡ ሙሀመድ ፡ (ዳና)
@getem
@getem
@getem
👍1