#ዝክረ ሙሉ ጌታ ተስፋዬ
ለሰዓት እላፊ !
❤️❤️❤️
በመጨረሻም ሁለት ግጥም በድምፅም በፅሁፍም ጀባ ብለን እንሰናበት🙏
ሙሌ አባ መንገዴ
አስያ አስያ፣
ንኡድ ቃል አምሳያ፣
እንኪ ስላንትያ፣
እሸትሽ ቅኔ ነዉ፣ ገላሽ ቦለቅያ፣
አቦ በየጁ ሞት፣ አቦ በወልዲያ፣
አቀብይኝ ዛሬ፣
ቅኔ እምኩልበት ፤ ቅኔ መሞሸሪያ፤
ትመጫለሽ አሉ፣
በ “ሙልየ..” ሲሉሽ ፣
የጁ ኪቢ ቃሉ፤ ማክሰኞ ገበያ፡፡
አስያ ጨብራሪት፣
የሃራ ወበሎ ፤ የታች ቆላይቱ፣
ጨብረር ጨብረር በይ፣
ተንጎማለይበት ፤ ነይማ ሸጊቱ፣
ወፈፍ ወፈፍ በይ፣
በጎጆየ ታዛ፣ አልፈሽ በምርጊቱ፡፡
ሀድራዉ ከሞቀበት፣
ቱፍታው ከሞላበት ፤ ከእነ ኩሌ ማጀት፣
ሀቂቃ አይደለም ወይ?
ካ'ስያ ጋር ኑሮ ፤ ካ'ስያ ጋር ማርጀት።
አውገረድ አስያ ፤
በበልጅግሽ ባሩድ፣ ባልቤንሽ ማንገቻ፣
እንደ ንጉስ አሽከር ፤
አሻቅቦ ያያል ፤ ቀልቤ አንችኑ ብቻ፤
ምን ያድርግ ብለሽ ነው፤
ወትሮም ከላይ ቤት ነዉ፣ ቅኔና ኮርቻ፡፡
ተገማሸሪበት ፤
ቀብረር ቀብረር በይ፣ አስያ በሞቴ፣
አህሪቡ ስትይኝ ፤
ጅስሜ ይበረታል ፤ ይጠናል ጉልበቴ ።
ከሙሉጌታ ጋር፣
ከሙሉ ሸጋ ጋር፣
ጉባርጃ ማርያም ላይ ፤ ያሰርሽዉ ቃል ኪዳን፣
እኔንም ዘንድሮ ፤
ጠራኝ ግጠም አለኝ፣ አወደኝ እንደእጣን፡፡
እኔም እንደ ሙሌ፣ እንደሙሉጌታ፣
ቀየዉ እንዳስከፋዉ፣ እንደቆላ ሽፍታ፣
ግጠም ግጠም አለኝ፣ የያዘኝ በሽታ፡፡
እገጥማለሁ እንጅ፣
በየበራበሩ ቅኔ ዛር አለብኝ፣
ላዩን በውድመን ፤
ታቹን በሶደማ ፤
አስያ ጨብራሪት፣ ወስዳ ሸሽጋብኝ፡፡
ልለማመን እስቲ፣
በእነነየ ጉፍታ ፤ በየጁ ቀለበት፣
ልመጀነዉ እስቲ፣
በአውገረድ ሹምባሽ ቤት ፤የላስቴን አቀበት፣
እንደግሽር ገላ፣ እንደወዳጅ እብለት፣
ምርኩዝ የሚሆነዉ፣ ለታፈረ ጉልበት፣
ጠብቆ ሲሰፋ ነው ፤ ቅኔና ዘለበት፡፡
ሀየ በል ገለሌ፣ እምቢ በል ጃዉሳ፣
ልቤ “..ቸ..” በል አለኝ “..ቸ..” በል ደንገላሳ፣
ብረር ብረር አለኝ፣ ቅኔ ቀለም አንሳ፣
ወትሮም ወደ ላይ ነዉ፣ ቅኔና ግሪሳ፣
ግጠም ግጠም አለኝ ፣ በልጅግህን አንሳ፣
አውቃለሁ አምናለሁ፤
የሞት ባልንጀር ነዉ፣ ቅኔና ወሳንሳ፡፡
አስያ ከገባች፣ ከማጀቷ ወጥታ፣
ጎዝጉዙልኝ ካለች፣ ወዳጃ ተጠርታ፣
ጀማዉ ከደመቀ፣ ቅጥሩ ከተፈታ፣
ግጠም ግጠም አለኝ፣ እንደሙሉጌታ፡፡
አያ ሙሌ ሆዴ፣
ቅኔ እሳት አመዴ፣
ከርታታዉ ዘመዴ፣
እኔ አለሁህ ልበል? አንተ አለሀኝ እንዴ?
ሰገነት ባትወጣ፣ ግብርህ ባይታወቅ፣
በሺህ ጋዜጠኛ፣ ስምህ ባይዳመቅ፣
በቲፎዞ ባሩድ፣ ባይሞቅ ያንተ ሽታ፣
በጭብጨባ ባይድን፣ ያንተ ሆድ በሽታ፣
ቃል አልተሸነፈም፣ ቅኔህ አልተረታ፣
“ታላቁ ሰዉ መጣ”፣
“ባለቅኔዉ መጣ”፣
“ያ ደራሲዉ መጣ”፣
ብለዉ ባይሰግዱልህ፣
ብለዉ ባይጮሁልህ፣ ምን ግድህ ምን ግዴ፣
አትንሰፈሰፍም ፣ለሹመት ለጓንዴ
ስሙልኝ አያምርህ፣ እንደቆላ ገዴ፣
አቦ ሆድ ይመርቅ፣ ሙሌ አባ መንገዴ፡፡
((( ጃ ኖ )))💚💛❤️
(( ማስታወሻነቱ ለባለቅኔው
ሙሉጌታ ተስፋዬ ❤️❤️❤️) )
@balmbaras
@getem
@getem
ለሰዓት እላፊ !
❤️❤️❤️
በመጨረሻም ሁለት ግጥም በድምፅም በፅሁፍም ጀባ ብለን እንሰናበት🙏
ሙሌ አባ መንገዴ
አስያ አስያ፣
ንኡድ ቃል አምሳያ፣
እንኪ ስላንትያ፣
እሸትሽ ቅኔ ነዉ፣ ገላሽ ቦለቅያ፣
አቦ በየጁ ሞት፣ አቦ በወልዲያ፣
አቀብይኝ ዛሬ፣
ቅኔ እምኩልበት ፤ ቅኔ መሞሸሪያ፤
ትመጫለሽ አሉ፣
በ “ሙልየ..” ሲሉሽ ፣
የጁ ኪቢ ቃሉ፤ ማክሰኞ ገበያ፡፡
አስያ ጨብራሪት፣
የሃራ ወበሎ ፤ የታች ቆላይቱ፣
ጨብረር ጨብረር በይ፣
ተንጎማለይበት ፤ ነይማ ሸጊቱ፣
ወፈፍ ወፈፍ በይ፣
በጎጆየ ታዛ፣ አልፈሽ በምርጊቱ፡፡
ሀድራዉ ከሞቀበት፣
ቱፍታው ከሞላበት ፤ ከእነ ኩሌ ማጀት፣
ሀቂቃ አይደለም ወይ?
ካ'ስያ ጋር ኑሮ ፤ ካ'ስያ ጋር ማርጀት።
አውገረድ አስያ ፤
በበልጅግሽ ባሩድ፣ ባልቤንሽ ማንገቻ፣
እንደ ንጉስ አሽከር ፤
አሻቅቦ ያያል ፤ ቀልቤ አንችኑ ብቻ፤
ምን ያድርግ ብለሽ ነው፤
ወትሮም ከላይ ቤት ነዉ፣ ቅኔና ኮርቻ፡፡
ተገማሸሪበት ፤
ቀብረር ቀብረር በይ፣ አስያ በሞቴ፣
አህሪቡ ስትይኝ ፤
ጅስሜ ይበረታል ፤ ይጠናል ጉልበቴ ።
ከሙሉጌታ ጋር፣
ከሙሉ ሸጋ ጋር፣
ጉባርጃ ማርያም ላይ ፤ ያሰርሽዉ ቃል ኪዳን፣
እኔንም ዘንድሮ ፤
ጠራኝ ግጠም አለኝ፣ አወደኝ እንደእጣን፡፡
እኔም እንደ ሙሌ፣ እንደሙሉጌታ፣
ቀየዉ እንዳስከፋዉ፣ እንደቆላ ሽፍታ፣
ግጠም ግጠም አለኝ፣ የያዘኝ በሽታ፡፡
እገጥማለሁ እንጅ፣
በየበራበሩ ቅኔ ዛር አለብኝ፣
ላዩን በውድመን ፤
ታቹን በሶደማ ፤
አስያ ጨብራሪት፣ ወስዳ ሸሽጋብኝ፡፡
ልለማመን እስቲ፣
በእነነየ ጉፍታ ፤ በየጁ ቀለበት፣
ልመጀነዉ እስቲ፣
በአውገረድ ሹምባሽ ቤት ፤የላስቴን አቀበት፣
እንደግሽር ገላ፣ እንደወዳጅ እብለት፣
ምርኩዝ የሚሆነዉ፣ ለታፈረ ጉልበት፣
ጠብቆ ሲሰፋ ነው ፤ ቅኔና ዘለበት፡፡
ሀየ በል ገለሌ፣ እምቢ በል ጃዉሳ፣
ልቤ “..ቸ..” በል አለኝ “..ቸ..” በል ደንገላሳ፣
ብረር ብረር አለኝ፣ ቅኔ ቀለም አንሳ፣
ወትሮም ወደ ላይ ነዉ፣ ቅኔና ግሪሳ፣
ግጠም ግጠም አለኝ ፣ በልጅግህን አንሳ፣
አውቃለሁ አምናለሁ፤
የሞት ባልንጀር ነዉ፣ ቅኔና ወሳንሳ፡፡
አስያ ከገባች፣ ከማጀቷ ወጥታ፣
ጎዝጉዙልኝ ካለች፣ ወዳጃ ተጠርታ፣
ጀማዉ ከደመቀ፣ ቅጥሩ ከተፈታ፣
ግጠም ግጠም አለኝ፣ እንደሙሉጌታ፡፡
አያ ሙሌ ሆዴ፣
ቅኔ እሳት አመዴ፣
ከርታታዉ ዘመዴ፣
እኔ አለሁህ ልበል? አንተ አለሀኝ እንዴ?
ሰገነት ባትወጣ፣ ግብርህ ባይታወቅ፣
በሺህ ጋዜጠኛ፣ ስምህ ባይዳመቅ፣
በቲፎዞ ባሩድ፣ ባይሞቅ ያንተ ሽታ፣
በጭብጨባ ባይድን፣ ያንተ ሆድ በሽታ፣
ቃል አልተሸነፈም፣ ቅኔህ አልተረታ፣
“ታላቁ ሰዉ መጣ”፣
“ባለቅኔዉ መጣ”፣
“ያ ደራሲዉ መጣ”፣
ብለዉ ባይሰግዱልህ፣
ብለዉ ባይጮሁልህ፣ ምን ግድህ ምን ግዴ፣
አትንሰፈሰፍም ፣ለሹመት ለጓንዴ
ስሙልኝ አያምርህ፣ እንደቆላ ገዴ፣
አቦ ሆድ ይመርቅ፣ ሙሌ አባ መንገዴ፡፡
((( ጃ ኖ )))💚💛❤️
(( ማስታወሻነቱ ለባለቅኔው
ሙሉጌታ ተስፋዬ ❤️❤️❤️) )
@balmbaras
@getem
@getem
❤1👍1
#ዝክረ ሙሉጌታ ተስፋዬ ( አያ ሙሌ )❤️
ሙሉ-- ጌታ!!!!!!!
ቅኔን ያህል ክህነት፤
አረሆን ያህል ሹመት፤
ካማልክቶቹ ዘንድ፤ ተሰጥቶት በደቦ፤
የብእሩ ልሳን፤
ሰው በሚባል ቅኔ፤
ሰው በሚባል ታምር፤ ዙሪያውን ተከቦ፤
በሰው ሳቅ ረብቶ፤ በሰው እንባ ባክኖ፤
ያም ለኔ ያም ለኔ፤
ለኔ ሁን እያለ፤
ግብር ቢደረደር፤ በጎጥ ልቡ ባዝኖ፤
እሱማ አጃኢብ ነው፤
ሰም ቅኔውን ፈታው፤ ለሁሉም ዘብ ሆኖ።
ዘብ እንጅ ዘብ አደር፤
ቋሚ እንጅ፤ ወጥቶ አደር፤
ያዳም ጎጆ ሲፈርስ፤
ሰብቅታኒ ብሎ፤ በእምባው የሚገደር፤
ዘማች የቀናው ቀን፤
ዳቦውን አግምጦ፤
ስለ ስሟ ማርያም፤
ቀን የሚሸኝበት፤ ቆሎ የሚበደር።
ሰውን ያህል ሰማይ፤ ሰብን ያህል ፀጋ፤
ኑሮን ያህል እንቅልፍ፤ ሞትን ያህል አልጋ፤
ተሸክሞ ሚዞር፤ በነጋ በጠባ፤
በጥውልግ ነፍስያ፤ በንጣት ሲላጋ፤
መዳኒት በራቀው፤ በማይቆም ፍለጋ፤
ህመሙ ሚሽረው፤
ወይ በቅንጣት ቅኔ፤ ወይ በድፍርስ እንባ።
ሰማያት ተቀደው፤ እንባ ካላዋሱ፤
አእዋፍ በማለዳ፤
አፍ መሻሪያ ቅኔ፤
እጅ መንሻ አምሃ፤ ዜማ ካልደረሱ፤
ይኸ ባለቅኔ፤
ቅኔ ማር ካልነካው፤ ካልደረሰ ምሱ፤
ዝናብ ቢጥል እንኳ፤
መልካው አይወረዛ፤ ወንዞችም አይፈሱ።
ምን ጎተራ ቢጎድል፤ አውድማው ቢሳሳ፤
ምን መሬት ብትከዳ፤ ሰማይ ጠል ቢነሳ፤
አፍ ሳይሽር ማለዳ፤
ከማእዱ በፊት፤
የህጣናት እምባ፤ ሲቃ እየቀደመ፤
አባት በልጁ ፊት፤
አባትነት ጎድሎት፤ከፈን እያለመ፤
ይህን ባዬ ጊዜ፤
ምስኪን ባለቅኔ፤
ጎደለ ወይ ብሎ ፤
ፈረሰ ወይ ብሎ፤ ልቡ ይጨነቃል፤
ስማኝ ኧረ ስማኝ፤
እያለ አዶናይን፤ ሰርክ ይጨቀጭቃል፤
ከጭቅጨቃው ወርዶ፤
ከመንበረህ የለህ፤
የለህም እያለ፤
ዘመን ሚያሻግር፤ ውብ ቅኔ ያፈልቃል።
ስለ ፍቅር መፃፍ፤
ስለ እንባ መቀኘት፤
ስለ ርሃብ መደስኮር፤ ምን ያቅታል ወጉ፤
ምን ያቅታል ደግሞ፤
ስለ እርሻው መንደቅደቅ፤
ስለ በሬው ማውራት፤ ከተማ መሃል ላይ እያረገረጉ።
ውነቴን ውነቴን፤
ሽርፍራፊ ቃላት፤
ማዳወር አይከብድም፤
የቃል ጮማ መቁረጥ፤ በየጥጋጥጉ፤
አዳ ምን ዋጋ አለው፤
ስለ ውጋት መፃፍ፤
ውጋት አያክምም፤ አብረው ካልተወጉ።
ግን ፤
ደግሞ ግን፤
ፍቅር መሆን እንጅ፤
እንባ መሆን እንጅ፤
ሩህሩህ እንስፍስፍ፤በብእርም በእውንም፤
በብእር ደግ ሆኖ፤
በሩን የሚዘጋ፤
እሱም አይፈልገን፤ እኛም አንከጅልም።
ብእር ቀለም ቢያጥረው፤ በላቡ እየፃፈ፤
ላቡ ሲደርቅበት፤ ደም እየቀፈፈ፤
ህላዌና ተስፋ፤
ቅኔና ሰውነት፤ እየተጠራሩ፤
ከደም የተቀዳ፤
ከመቅኖ ያደረ፤ ህያው ቅኔ ሰሩ፤
በቃ፤
ይኸው ነው ማጀቱ፤ ይኸው ነው ትዳሩ።
ርስቱን፤
ጠፍ ድስቱን፤
ልጅ ሚስቱን፤
በፊደል ተክቶ፤
ያባትነት እጁን፤
በቅኔ እያሰላ፤ ምስኪን ልቡን ሰጥቶ፤
የዘረ ሰብ ቀልቡን፤ ዳር ከዳር ዘርግቶ፤
በነፍስያ ሀቂቅ፤
የቀልብያን ስስት፤ በቸር ቅኔ ዘግቶ፤
በክፋት ምንዳ ላይ፤
የተንኮልን ጫካ፤ በሳቅ ጦር ረቶ፤
ከጉድለት ባርነት፤
በምህላ በአርምሞ፤ ራሱን አንፅቶ፤
ሙሉ-ጌታ ሆነ፤
በእንባና በቅኔ፤ ጎዶሎውን ሞልቶ።
(((( ጃ ኖ )))💚💛❤️
(((ለባለቅኔው ሙሉጌታ ተስፋዬ))
@balmbaras
@getem
@getem
አያ ሙሌ በሀይል ነፍፍፍፍፍ ብዙዙዙዙ እልፍ አእላፍ ወድሀለው❤️❤️❤️ ነፍስህን በገነት ያኑራት ! !!!!!!
ሙሉ-- ጌታ!!!!!!!
ቅኔን ያህል ክህነት፤
አረሆን ያህል ሹመት፤
ካማልክቶቹ ዘንድ፤ ተሰጥቶት በደቦ፤
የብእሩ ልሳን፤
ሰው በሚባል ቅኔ፤
ሰው በሚባል ታምር፤ ዙሪያውን ተከቦ፤
በሰው ሳቅ ረብቶ፤ በሰው እንባ ባክኖ፤
ያም ለኔ ያም ለኔ፤
ለኔ ሁን እያለ፤
ግብር ቢደረደር፤ በጎጥ ልቡ ባዝኖ፤
እሱማ አጃኢብ ነው፤
ሰም ቅኔውን ፈታው፤ ለሁሉም ዘብ ሆኖ።
ዘብ እንጅ ዘብ አደር፤
ቋሚ እንጅ፤ ወጥቶ አደር፤
ያዳም ጎጆ ሲፈርስ፤
ሰብቅታኒ ብሎ፤ በእምባው የሚገደር፤
ዘማች የቀናው ቀን፤
ዳቦውን አግምጦ፤
ስለ ስሟ ማርያም፤
ቀን የሚሸኝበት፤ ቆሎ የሚበደር።
ሰውን ያህል ሰማይ፤ ሰብን ያህል ፀጋ፤
ኑሮን ያህል እንቅልፍ፤ ሞትን ያህል አልጋ፤
ተሸክሞ ሚዞር፤ በነጋ በጠባ፤
በጥውልግ ነፍስያ፤ በንጣት ሲላጋ፤
መዳኒት በራቀው፤ በማይቆም ፍለጋ፤
ህመሙ ሚሽረው፤
ወይ በቅንጣት ቅኔ፤ ወይ በድፍርስ እንባ።
ሰማያት ተቀደው፤ እንባ ካላዋሱ፤
አእዋፍ በማለዳ፤
አፍ መሻሪያ ቅኔ፤
እጅ መንሻ አምሃ፤ ዜማ ካልደረሱ፤
ይኸ ባለቅኔ፤
ቅኔ ማር ካልነካው፤ ካልደረሰ ምሱ፤
ዝናብ ቢጥል እንኳ፤
መልካው አይወረዛ፤ ወንዞችም አይፈሱ።
ምን ጎተራ ቢጎድል፤ አውድማው ቢሳሳ፤
ምን መሬት ብትከዳ፤ ሰማይ ጠል ቢነሳ፤
አፍ ሳይሽር ማለዳ፤
ከማእዱ በፊት፤
የህጣናት እምባ፤ ሲቃ እየቀደመ፤
አባት በልጁ ፊት፤
አባትነት ጎድሎት፤ከፈን እያለመ፤
ይህን ባዬ ጊዜ፤
ምስኪን ባለቅኔ፤
ጎደለ ወይ ብሎ ፤
ፈረሰ ወይ ብሎ፤ ልቡ ይጨነቃል፤
ስማኝ ኧረ ስማኝ፤
እያለ አዶናይን፤ ሰርክ ይጨቀጭቃል፤
ከጭቅጨቃው ወርዶ፤
ከመንበረህ የለህ፤
የለህም እያለ፤
ዘመን ሚያሻግር፤ ውብ ቅኔ ያፈልቃል።
ስለ ፍቅር መፃፍ፤
ስለ እንባ መቀኘት፤
ስለ ርሃብ መደስኮር፤ ምን ያቅታል ወጉ፤
ምን ያቅታል ደግሞ፤
ስለ እርሻው መንደቅደቅ፤
ስለ በሬው ማውራት፤ ከተማ መሃል ላይ እያረገረጉ።
ውነቴን ውነቴን፤
ሽርፍራፊ ቃላት፤
ማዳወር አይከብድም፤
የቃል ጮማ መቁረጥ፤ በየጥጋጥጉ፤
አዳ ምን ዋጋ አለው፤
ስለ ውጋት መፃፍ፤
ውጋት አያክምም፤ አብረው ካልተወጉ።
ግን ፤
ደግሞ ግን፤
ፍቅር መሆን እንጅ፤
እንባ መሆን እንጅ፤
ሩህሩህ እንስፍስፍ፤በብእርም በእውንም፤
በብእር ደግ ሆኖ፤
በሩን የሚዘጋ፤
እሱም አይፈልገን፤ እኛም አንከጅልም።
ብእር ቀለም ቢያጥረው፤ በላቡ እየፃፈ፤
ላቡ ሲደርቅበት፤ ደም እየቀፈፈ፤
ህላዌና ተስፋ፤
ቅኔና ሰውነት፤ እየተጠራሩ፤
ከደም የተቀዳ፤
ከመቅኖ ያደረ፤ ህያው ቅኔ ሰሩ፤
በቃ፤
ይኸው ነው ማጀቱ፤ ይኸው ነው ትዳሩ።
ርስቱን፤
ጠፍ ድስቱን፤
ልጅ ሚስቱን፤
በፊደል ተክቶ፤
ያባትነት እጁን፤
በቅኔ እያሰላ፤ ምስኪን ልቡን ሰጥቶ፤
የዘረ ሰብ ቀልቡን፤ ዳር ከዳር ዘርግቶ፤
በነፍስያ ሀቂቅ፤
የቀልብያን ስስት፤ በቸር ቅኔ ዘግቶ፤
በክፋት ምንዳ ላይ፤
የተንኮልን ጫካ፤ በሳቅ ጦር ረቶ፤
ከጉድለት ባርነት፤
በምህላ በአርምሞ፤ ራሱን አንፅቶ፤
ሙሉ-ጌታ ሆነ፤
በእንባና በቅኔ፤ ጎዶሎውን ሞልቶ።
(((( ጃ ኖ )))💚💛❤️
(((ለባለቅኔው ሙሉጌታ ተስፋዬ))
@balmbaras
@getem
@getem
አያ ሙሌ በሀይል ነፍፍፍፍፍ ብዙዙዙዙ እልፍ አእላፍ ወድሀለው❤️❤️❤️ ነፍስህን በገነት ያኑራት ! !!!!!!
ያያሙሌ ስንብት
“ኸረ ይሄ ሰው ነብይ ሳይሆን አይቀርም፡፡እንዲችው ሌሊቱን ሙሉ ለጆሮ የሚከብዱ
ነገሮችን ሲናገር ነው ያነጋው”
አያ ሙሌ ድንገት አምርሮ የሚያለቅስባቸው ጊዜያትም ነበሩ፡፡ በግንቦት ወር 1996 አሁን
ማረፍ ነው የምፈልግው ብሎ ቤት ተከራየ፡፡ ወይዘሮ ከበቡሽን ሲሰናበትም…” ነገርኩሽ
አልሰማሽም፣ ልሄድ ነው አልረሳሽም” ብሏቸው ነበር፡፡
የፒያሳን አቀበት እየወጣ ቴድሮስ አደባባይ ሲደርስ ድንገት ሐሳቡን ቀይሮ ወደ ጎላ ሚካኤል
ዞሮ አማትቦ ዘለግ ላለ ሰዓት ፀለየ፡፡ ሦስት ቁጥር አውቶብስ ይዞ ዓለምገና ሄደ፡፡ አንድ
ሆቴል ዉስጥ 13 ቁጥር መኝታ ይዞ አደረ፡፡ ጓደኞቹ ግማሽ በድን ኾኖ ከሆቴሌ ሲያወጡት
የሆቴሉ ዘበኛ እንዲህ ተናገሩ፡፡
“ኸረ ይሄ ሰው ነብይ ሳይሆን አይቀርም፡፡እንዲችው ሌሊቱን ሙሉ ለጆሮ የሚከብዱ
ነገሮችን ሲናገር ነው ያነጋው”
በነገታው ነሐሴ 28፣ ቀን 1996 ዓ.ም አረፈ፡፡
ሰላም እደሩልኝ!💚
@balmbaras
@getem
“ኸረ ይሄ ሰው ነብይ ሳይሆን አይቀርም፡፡እንዲችው ሌሊቱን ሙሉ ለጆሮ የሚከብዱ
ነገሮችን ሲናገር ነው ያነጋው”
አያ ሙሌ ድንገት አምርሮ የሚያለቅስባቸው ጊዜያትም ነበሩ፡፡ በግንቦት ወር 1996 አሁን
ማረፍ ነው የምፈልግው ብሎ ቤት ተከራየ፡፡ ወይዘሮ ከበቡሽን ሲሰናበትም…” ነገርኩሽ
አልሰማሽም፣ ልሄድ ነው አልረሳሽም” ብሏቸው ነበር፡፡
የፒያሳን አቀበት እየወጣ ቴድሮስ አደባባይ ሲደርስ ድንገት ሐሳቡን ቀይሮ ወደ ጎላ ሚካኤል
ዞሮ አማትቦ ዘለግ ላለ ሰዓት ፀለየ፡፡ ሦስት ቁጥር አውቶብስ ይዞ ዓለምገና ሄደ፡፡ አንድ
ሆቴል ዉስጥ 13 ቁጥር መኝታ ይዞ አደረ፡፡ ጓደኞቹ ግማሽ በድን ኾኖ ከሆቴሌ ሲያወጡት
የሆቴሉ ዘበኛ እንዲህ ተናገሩ፡፡
“ኸረ ይሄ ሰው ነብይ ሳይሆን አይቀርም፡፡እንዲችው ሌሊቱን ሙሉ ለጆሮ የሚከብዱ
ነገሮችን ሲናገር ነው ያነጋው”
በነገታው ነሐሴ 28፣ ቀን 1996 ዓ.ም አረፈ፡፡
ሰላም እደሩልኝ!💚
@balmbaras
@getem
ቆንጆ ነኝ
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ስላንቺ ቁንጅና
ስላንቺ ቁመና
ከንፈር እና ዳሌ
ጥርስና ተረከዝ ፣ ፀጉር ገለመሌ
ለጡት ለወገብሽ ፣ ለፀባይሽ ጭምር
በግጥም በዝርው ፣ ባድናቆት ስዘምር
እስከዛሬ ድረስ...
ውበትሽን አግንኜ ፣ ሰርክ መለፈፌ
እኔ ስለራሴ ...
አንዳች ቀን እንኳን ፣ ግጥም አለመፃፌ
ሲትጠዪኝ ቆጨኝ
ቢሆንም ቆንጆ ነኝ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እርግጥ ነው ብዙዎች...
ስለኔ ሳወራ ፣ ድንገት ያኮርፉኛል
ያንተን ሌሎች ያውሩ ፣ ብለው ይነግሩኛል
እኔን ከኔ በላይ...
እርግጠኛ ሆኖ ፣ ሌላ እንዴት ያውቀኛል?!
።።።።፣፣
እናም እኔ ማለት...
ቁመቴ ከአክሱም ፣ በእጥፍ ይረዝማል
ጣፋጭ አንደበቴ...
መስማት ለተሳነው ፣ ለስልሶ ይሰማል
ውብ አረማመዴ...
እንኳን መንገደኛን ፣ መንገድን ያቆማል፡፡
፡፡፡፡፡፡
የከንፈሬ ወዙ ፣ ጥፍጥናው አያልቅም
ጥርሴ ሺ ገዳይ ነው!
ሺ ሟች ላለማየት ፣ ኗሪ ፊት አልስቅም፡፡
ከአይኔ ብሌን ውስጥ ፣ ብርሐን ይፈልቃል
አይኔን ያየ ሁሉ
ልቡን አሳውሮ ፣ በፍቅር ይወድቃል፡፡
፡፡፡፡፡
የገላዬ ጠረን ፣ ከሽቱ እጥፍ ነው
መልካም ጠረን ሁሉ...
አለ ባሉት ስፍራ ፣ እኔ አለሁ ማለት ነው፡፡
ፀባየ ትሁት ነኝ ፣ ምጡቅ ነው እውቀቴ
ግርማ ሞገሳም ነው ፣ ተክለ ሰውነቴ
ያየኝ ይወደኛል
የወደየኝ ሁሉ ፣ መቼም አይጠላኝም
ከዚ በላይ እንኳን...
ብዙም ስለራሴ ፣ የማውቀው የለኝም፡፡
እንደውም እንደውም...
አልጎርርም እንጂ ፣
ያፈር ሰውነቴን ፣ በቁንጅና አብየው
ቆንጆ ማየት ሲያምረኝ ፣ራሴን ነው ማየው፡፡
ብቻ ግን ቆንጆ ነኝ!!!
@getem
@getem
@gebriel_19
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ስላንቺ ቁንጅና
ስላንቺ ቁመና
ከንፈር እና ዳሌ
ጥርስና ተረከዝ ፣ ፀጉር ገለመሌ
ለጡት ለወገብሽ ፣ ለፀባይሽ ጭምር
በግጥም በዝርው ፣ ባድናቆት ስዘምር
እስከዛሬ ድረስ...
ውበትሽን አግንኜ ፣ ሰርክ መለፈፌ
እኔ ስለራሴ ...
አንዳች ቀን እንኳን ፣ ግጥም አለመፃፌ
ሲትጠዪኝ ቆጨኝ
ቢሆንም ቆንጆ ነኝ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እርግጥ ነው ብዙዎች...
ስለኔ ሳወራ ፣ ድንገት ያኮርፉኛል
ያንተን ሌሎች ያውሩ ፣ ብለው ይነግሩኛል
እኔን ከኔ በላይ...
እርግጠኛ ሆኖ ፣ ሌላ እንዴት ያውቀኛል?!
።።።።፣፣
እናም እኔ ማለት...
ቁመቴ ከአክሱም ፣ በእጥፍ ይረዝማል
ጣፋጭ አንደበቴ...
መስማት ለተሳነው ፣ ለስልሶ ይሰማል
ውብ አረማመዴ...
እንኳን መንገደኛን ፣ መንገድን ያቆማል፡፡
፡፡፡፡፡፡
የከንፈሬ ወዙ ፣ ጥፍጥናው አያልቅም
ጥርሴ ሺ ገዳይ ነው!
ሺ ሟች ላለማየት ፣ ኗሪ ፊት አልስቅም፡፡
ከአይኔ ብሌን ውስጥ ፣ ብርሐን ይፈልቃል
አይኔን ያየ ሁሉ
ልቡን አሳውሮ ፣ በፍቅር ይወድቃል፡፡
፡፡፡፡፡
የገላዬ ጠረን ፣ ከሽቱ እጥፍ ነው
መልካም ጠረን ሁሉ...
አለ ባሉት ስፍራ ፣ እኔ አለሁ ማለት ነው፡፡
ፀባየ ትሁት ነኝ ፣ ምጡቅ ነው እውቀቴ
ግርማ ሞገሳም ነው ፣ ተክለ ሰውነቴ
ያየኝ ይወደኛል
የወደየኝ ሁሉ ፣ መቼም አይጠላኝም
ከዚ በላይ እንኳን...
ብዙም ስለራሴ ፣ የማውቀው የለኝም፡፡
እንደውም እንደውም...
አልጎርርም እንጂ ፣
ያፈር ሰውነቴን ፣ በቁንጅና አብየው
ቆንጆ ማየት ሲያምረኝ ፣ራሴን ነው ማየው፡፡
ብቻ ግን ቆንጆ ነኝ!!!
@getem
@getem
@gebriel_19
የተከበራችሁ የ ግጥም ብቻ ቤተሰቦች
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
ሥዕል ብቻ ሚለው ቻናላችን ላይ የ ሥዕል ውድድር እየተካሄደ ይገኛል ገብታችሁ ይመጥናል ለምትሉት ሥዕል ድምዕ እንድትሰጡልን በ አክብሮት እንጠይቃለን 🙏
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
@seiloch
@seiloch
@seiloch
➖➖➖➖➖
ግጥም ብቻ
ሥዕል ብቻ
@gebriel_19
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
ሥዕል ብቻ ሚለው ቻናላችን ላይ የ ሥዕል ውድድር እየተካሄደ ይገኛል ገብታችሁ ይመጥናል ለምትሉት ሥዕል ድምዕ እንድትሰጡልን በ አክብሮት እንጠይቃለን 🙏
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
@seiloch
@seiloch
@seiloch
➖➖➖➖➖
ግጥም ብቻ
ሥዕል ብቻ
@gebriel_19
///// "አልሰጥም!" ትያለሽ?/////
ይህን ሁሉ ግዜ
ይህን ሁሉ ወራት
መልሶ መላልሶ
ዘውትር ቢለምንሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ?
እንዲህ ተመችቶሽ
እንዲህ ተወልውለሽ
ሊፈርጥ የደረሰ
ዳሌ ተሸክመሽ
ትርንጎ ጉንጭሽን
በዲምፕል አስጊጠሽ
ውብ ከናፍርሽን
እንዲህ አሞጥሙጠሽ
በአሎሎ አይኖችሽ
ተድላን እያስነበብሽ
ይህ ምስኪን "እባክሽ?"
ብሎ ሲማፀንሽ
ድምፅሽን ከፍ አርገሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ?
በችግርሽ ዘመን
ነበረ ከጎንሽ
ሰው በሚያሻሽ ግዜም
ከቶም አልተለየሽ
የስኬትን እርካብ-
"ሀ" ብለሽ ስትርግጪ
ነበር ድጋፍሽ
የዝና ፈረስሽን ስትፈናጠጪ።
እኮ አሁን ያ አልፎ
ታሪክ ተቀይሮ
ሃሴት አስፈንድቆሽ
እሮሮሽ ተቀብሮ
ካንቺ ተመኝቶ
ካንቺ እግር ተደፍቶ
በ'ንባ ሲማፀንሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ?
ዛሬ ቀን ሞልቶልሽ
ተመልካች አግኝተሽ
በአንድናቂ ተከበሽ
በዝና ተውጠሽ
ረጅም ሽንጥሽን
ያለልክ መዘሽ
በወርቅ አልማዝ ዕንቁ
እንዲህ ተንቆጥቁጥሽ
በሃብት በልፅገሽ
ሁሉ ተርፎ ሞልቶሽ
ቁንጅና አረስርሶሽ
ውበት ተደፍቶብሽ
አንዳችም ሳታጪ
አንዳች ሳይጎልሽ
በረከት የሚያፈስ
ያን ገነት አንደበት
ያን ውብ አፍሽን
በ እምቢታ ሞልተሽ
"እባክሽን እቱ አንድ ሺህ ብር
ብድር"
ስጪኝ ብሎ ቢልሽ
እንዲህ ሲማፀንሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ???
እቱ ሙች! ክፉ ነሽ!!!
Hahahaha....
I Gotch you guys!
(መንግስቱ መ)
@getem
@getem
@getem
ይህን ሁሉ ግዜ
ይህን ሁሉ ወራት
መልሶ መላልሶ
ዘውትር ቢለምንሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ?
እንዲህ ተመችቶሽ
እንዲህ ተወልውለሽ
ሊፈርጥ የደረሰ
ዳሌ ተሸክመሽ
ትርንጎ ጉንጭሽን
በዲምፕል አስጊጠሽ
ውብ ከናፍርሽን
እንዲህ አሞጥሙጠሽ
በአሎሎ አይኖችሽ
ተድላን እያስነበብሽ
ይህ ምስኪን "እባክሽ?"
ብሎ ሲማፀንሽ
ድምፅሽን ከፍ አርገሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ?
በችግርሽ ዘመን
ነበረ ከጎንሽ
ሰው በሚያሻሽ ግዜም
ከቶም አልተለየሽ
የስኬትን እርካብ-
"ሀ" ብለሽ ስትርግጪ
ነበር ድጋፍሽ
የዝና ፈረስሽን ስትፈናጠጪ።
እኮ አሁን ያ አልፎ
ታሪክ ተቀይሮ
ሃሴት አስፈንድቆሽ
እሮሮሽ ተቀብሮ
ካንቺ ተመኝቶ
ካንቺ እግር ተደፍቶ
በ'ንባ ሲማፀንሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ?
ዛሬ ቀን ሞልቶልሽ
ተመልካች አግኝተሽ
በአንድናቂ ተከበሽ
በዝና ተውጠሽ
ረጅም ሽንጥሽን
ያለልክ መዘሽ
በወርቅ አልማዝ ዕንቁ
እንዲህ ተንቆጥቁጥሽ
በሃብት በልፅገሽ
ሁሉ ተርፎ ሞልቶሽ
ቁንጅና አረስርሶሽ
ውበት ተደፍቶብሽ
አንዳችም ሳታጪ
አንዳች ሳይጎልሽ
በረከት የሚያፈስ
ያን ገነት አንደበት
ያን ውብ አፍሽን
በ እምቢታ ሞልተሽ
"እባክሽን እቱ አንድ ሺህ ብር
ብድር"
ስጪኝ ብሎ ቢልሽ
እንዲህ ሲማፀንሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ???
እቱ ሙች! ክፉ ነሽ!!!
Hahahaha....
I Gotch you guys!
(መንግስቱ መ)
@getem
@getem
@getem
#ልቀቀን!
-
አንት ራስ-አምላኪ ፥ ለራስ ምስል ሰጋጅ
ያዙኝ ልቀቁኝ ባይ -
ቃልህ እንደ ንጉሥ ፥ ንግግርህ አዋጅ፣
ጉልበትህ የድመት ፥ ግሳትህ ያንበሳ
ዕንባህ ቅርር የሚል -
መሽቶ ማይነጋልህ ፥ ሥምህ ካልተነሳ፣...
ዋ! ብቻ ሙዚቃህ ፥ ሰርክ ማስፈራራት
ትን ይለን ይመስል -
አንተ ሳትባርከው ፥ የበላነው እራት፣...
.
ባክህ ተለመነን
ዛሬን እሺ በለን፣ ...
በፈጠረህ አምላክ ፥ ባበጀህ ከጭቃ
ባልቀጠርንህ ችሎት ፥ አትቁም ጠበቃ!!
.
ጣቶችህን ሰብስብ ፥ ደጃችን አትድረስ፣
እርግፍ አርገህ ተወን ፥ እንሙት ... እንጨረስ!
ግዴለም እንፈንዳ ፥ እንፍረጥ እንደ እንቧይ
ብቻ አንተ ልቀቀን ፥ ከቅዠትህ ሰማይ ፨፨
------------------------//------------------------
(በርናባስ ከበደ )
@getem
@getem
@getem
-
አንት ራስ-አምላኪ ፥ ለራስ ምስል ሰጋጅ
ያዙኝ ልቀቁኝ ባይ -
ቃልህ እንደ ንጉሥ ፥ ንግግርህ አዋጅ፣
ጉልበትህ የድመት ፥ ግሳትህ ያንበሳ
ዕንባህ ቅርር የሚል -
መሽቶ ማይነጋልህ ፥ ሥምህ ካልተነሳ፣...
ዋ! ብቻ ሙዚቃህ ፥ ሰርክ ማስፈራራት
ትን ይለን ይመስል -
አንተ ሳትባርከው ፥ የበላነው እራት፣...
.
ባክህ ተለመነን
ዛሬን እሺ በለን፣ ...
በፈጠረህ አምላክ ፥ ባበጀህ ከጭቃ
ባልቀጠርንህ ችሎት ፥ አትቁም ጠበቃ!!
.
ጣቶችህን ሰብስብ ፥ ደጃችን አትድረስ፣
እርግፍ አርገህ ተወን ፥ እንሙት ... እንጨረስ!
ግዴለም እንፈንዳ ፥ እንፍረጥ እንደ እንቧይ
ብቻ አንተ ልቀቀን ፥ ከቅዠትህ ሰማይ ፨፨
------------------------//------------------------
(በርናባስ ከበደ )
@getem
@getem
@getem
ይህን ያህል ዘመን ፤
በኦና ጎጆው ውስጥ ፤
ምነው በባዶ ቤት ፤
ቆልፎ መቀመጥ ዘግቶ ብቻ ማውራት ፤
አይጨንቀውም ዛሬም በሩን ገርበብ አርጎ አይወጣም አንዳንዴ ፤
ትይኛለሽ አሉ የማለዳዋ ልጅ የከንፈር ወዳጄ፤
የልቤን አዳራሽ፤
በላምባዲና ቁልፍ፤
ቆልፈሽ የሄድሽው አንችው መሆንሽን ዘነጋሽው እንዴ???
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
በኦና ጎጆው ውስጥ ፤
ምነው በባዶ ቤት ፤
ቆልፎ መቀመጥ ዘግቶ ብቻ ማውራት ፤
አይጨንቀውም ዛሬም በሩን ገርበብ አርጎ አይወጣም አንዳንዴ ፤
ትይኛለሽ አሉ የማለዳዋ ልጅ የከንፈር ወዳጄ፤
የልቤን አዳራሽ፤
በላምባዲና ቁልፍ፤
ቆልፈሽ የሄድሽው አንችው መሆንሽን ዘነጋሽው እንዴ???
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
የ 2011 # የአመቱ_የመጨረሻው_ዝክረ_ኸሚስ
☞ ዝክረ ኸሚስ ( 43 )
..
ሰው በመሆን መንገድ
።።።።።።።።።።።።።።።።
ሸጋ ነፍስ ገልጦ ፣
ሰው በማለት ዜማ ፣
ከዱንያ እራስጌ ላይ የሀቁን ውብ ሀድራ እያንጎራጎረው ፣
" ስማኝማ " እያለ እርቀት ላይገረግር መድረስ ላያክረው።
የነፍሴን ባልጃ ፣
የጂስሜን ቢሊኮ ፣
ያፈር ገላ ልብሴን ቁረንጮየን ገፎ ድቤነት አውጥቶኝ ፣
ሲደባኝ ሰማሁት በውደታው መዳፍ እንደ ሀድራው ሽቶኝ ።
.
<< ብቻነት ጥፍጥናው ፣
ከነፍስህ አንጀት ላይ ደስ የሚል ህመሙ ፣
ሰው የሆንክ ለት ነው ጣሙ የሚገባህ የመሄጃ መሙ ።
ሰው ለመሆን ደግሞ ...
መነጠል አለብህ ከሚሸነግልህ ቁስልህን አግሞ ።
ለመነጠል ደግሞ ...
ካብሮነት ሊያጋልል በዳይ ያስፈልጋል ገፍታሪ ደጋግሞ ! >>
.
ይለኛል !
በገምሻራው ሌሊት ፣
ሀድራው ገደምዳሜ ፣
ጋሜው ክምብል ደፋ በኸሚሱ ሞገድ ፣
ዋናው ከኒያው ነው ቼቼ ለመኮልኮል ዝምቻው ላይታገድ ፣
በነፍስያ እንቅፋትገርፍጦ በሚያደርስ ሰው በማለት መንገድ ።
..
እውነቱን ነው !
ሰው የመሆን ጣሙ ...
የነፍስያን ቡጡ የእኔነትን ትግል ፣
ተጋጥመው ረተው እንደመገላገል ፣
የኔነትን አመል ከራስ እንደማግለል ፣
የሚጣፍጥ የለም መቻያ ላደለው ሀቁን ለጠቆመ ፣
ከመገፋት መንገድ በብቻነት ምርኩዝ ሰው ሆኖ ለቆመ ።
..
ሰው ነው የሰው ወንፊት ...
ግርዱ ተለይቶ ሰው የመሆን ፍሬ ለዘር እንዲታደም ፣
አዙሮ ‘ ሚመታ ካለም ግፋት በፊት ሰው ነው የሚቀደም ።
ያኔ ነው ከፍታ ፣
የከጀሉት መኖር ፣
ወና ሌሊት ገፍተው ፣
ብቻ ሲማልዱ ከቀን ወፍ ተቀድቶ ፈጅሩ ሲዘምር ፣
ያኔ ነው ሰው መሆን የወጋገኑ ቀን ንጋቱ ‘ ሚጀምር ።
.
ሰው መሆን አፍታ ነው ...
ማርፈጃ አያስደካም አይገፋም እስኪጠር እስኪመሽ ይርቃል
ደግሞ አፍታ ለመሆን በአቅል ለማስተንተን ብቻነት ይበቃል ።
ያኔ ...
ሰው በመሆን ንጋት ፣
ሰው በመሆምን ቀትር ፣
ሰው በመሆን ጀንበር ፣
በህብሩ ሰንጠረዥ በቀን ስሌት ግብር ፣
ሸጋ ህልም ፈትሎ ሌሊቱን ሲያደግስ ምሽቱ ሲነጠፍ ፣
በሰውነት ንጋት ሸጋ አድማስ ለመኳል ማምሻው ሲዘነጠፍ ፣
( ያኔ ነው ሰው መሆን )
በሚያቆስል ቀን ውስጥ በሚያገረሽ ሌሊት ፣
ባለፈው ሲያክሙት የህመሙን መግል የፊቱን በኋሊት ።
..
ሀየይይይ ... !
..
..
ሸጋ ነፍስ ገልጦ ፣
ሰው በማለት ዜማ ፣
ከዱንያ እራስጌ ላይ የሀቁን ውብ ሀድራ እያንጎራጎረው ፣
ስማኝማ እያለ እርቀት ላይገረግር መድረስ ላያክረው።
የነፍሴን ባልጃ ፣
የጂስሜን ቢሊኮ ፣
ያፈር ገላ ልብሴን ቁረንጮየን ገፎ ድቤነት አውጥቶኝ ፣
ሲደባኝ ሰማሁት በመወዳድ መዳፍ እንደ ሀድራው ሽቶኝ ።
..
እንግዲህ ምን እችል ፣
በምን አቅሜ ልዘልቅ የወዳጄን መዝሙር ፣
በገዛ እኔው ድቤ ሰው በመሆን አግቦ የናልኝን አሽሙር ።
አልጅልም ባልንጀር ፣
አልሶብርም ለይሉን ፣
በኸሚሱ ግላጭ የጠናውን ሃጃ ዘንበን ለማረስረስ ፣
የሙሃባን ፈረስ በሀድራ ለጉሜ በነፍሴ ለመድረስ ።
..
( ወዲህም እዝነት ነው .. )
ቢንድው ተማያልቅ ፣
ከፍቅሩ ቁልል ነገን መሻገሪያ ሊያድል ሲገመድል ፣
የሻለት ብቻ ነው ሰው እንሁን የሚል ወዳጅ የሚታደል ።
..
በልማ ባልንጀር ፣
መጣሁኝ እንግዲህ ፣
ካለመድረስ ወዲህ
ኸሚስ ሽቅርቅሩ ቀሃ ጀባው ደርሷል አወሉን ገምጨ ፣
የመሻገሪያውን የቀለሙን ቀንድል ቀንበጤን ሸምጥጨ ፣
አፍታም አላረፍድ ፣
ሰው በመሆን መንገድ ፣
በተገማሸረው በወዳጃው ጥርጊያ ደግ ልንገናኝ ፣
በኮከብ ምልክት በጠፍ ጨረቃ ሌት እደወጣ መናኝ ፣
በወለላው ሀድራ እንደ ከፋው ሽፍታ እያንጎራጎርኩኝ ።
እዘልቅልሃለሁ ... !!
___
ሙሀመድ ሙፍቲ ( ጀዋድ ) 💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
☞ ዝክረ ኸሚስ ( 43 )
..
ሰው በመሆን መንገድ
።።።።።።።።።።።።።።።።
ሸጋ ነፍስ ገልጦ ፣
ሰው በማለት ዜማ ፣
ከዱንያ እራስጌ ላይ የሀቁን ውብ ሀድራ እያንጎራጎረው ፣
" ስማኝማ " እያለ እርቀት ላይገረግር መድረስ ላያክረው።
የነፍሴን ባልጃ ፣
የጂስሜን ቢሊኮ ፣
ያፈር ገላ ልብሴን ቁረንጮየን ገፎ ድቤነት አውጥቶኝ ፣
ሲደባኝ ሰማሁት በውደታው መዳፍ እንደ ሀድራው ሽቶኝ ።
.
<< ብቻነት ጥፍጥናው ፣
ከነፍስህ አንጀት ላይ ደስ የሚል ህመሙ ፣
ሰው የሆንክ ለት ነው ጣሙ የሚገባህ የመሄጃ መሙ ።
ሰው ለመሆን ደግሞ ...
መነጠል አለብህ ከሚሸነግልህ ቁስልህን አግሞ ።
ለመነጠል ደግሞ ...
ካብሮነት ሊያጋልል በዳይ ያስፈልጋል ገፍታሪ ደጋግሞ ! >>
.
ይለኛል !
በገምሻራው ሌሊት ፣
ሀድራው ገደምዳሜ ፣
ጋሜው ክምብል ደፋ በኸሚሱ ሞገድ ፣
ዋናው ከኒያው ነው ቼቼ ለመኮልኮል ዝምቻው ላይታገድ ፣
በነፍስያ እንቅፋትገርፍጦ በሚያደርስ ሰው በማለት መንገድ ።
..
እውነቱን ነው !
ሰው የመሆን ጣሙ ...
የነፍስያን ቡጡ የእኔነትን ትግል ፣
ተጋጥመው ረተው እንደመገላገል ፣
የኔነትን አመል ከራስ እንደማግለል ፣
የሚጣፍጥ የለም መቻያ ላደለው ሀቁን ለጠቆመ ፣
ከመገፋት መንገድ በብቻነት ምርኩዝ ሰው ሆኖ ለቆመ ።
..
ሰው ነው የሰው ወንፊት ...
ግርዱ ተለይቶ ሰው የመሆን ፍሬ ለዘር እንዲታደም ፣
አዙሮ ‘ ሚመታ ካለም ግፋት በፊት ሰው ነው የሚቀደም ።
ያኔ ነው ከፍታ ፣
የከጀሉት መኖር ፣
ወና ሌሊት ገፍተው ፣
ብቻ ሲማልዱ ከቀን ወፍ ተቀድቶ ፈጅሩ ሲዘምር ፣
ያኔ ነው ሰው መሆን የወጋገኑ ቀን ንጋቱ ‘ ሚጀምር ።
.
ሰው መሆን አፍታ ነው ...
ማርፈጃ አያስደካም አይገፋም እስኪጠር እስኪመሽ ይርቃል
ደግሞ አፍታ ለመሆን በአቅል ለማስተንተን ብቻነት ይበቃል ።
ያኔ ...
ሰው በመሆን ንጋት ፣
ሰው በመሆምን ቀትር ፣
ሰው በመሆን ጀንበር ፣
በህብሩ ሰንጠረዥ በቀን ስሌት ግብር ፣
ሸጋ ህልም ፈትሎ ሌሊቱን ሲያደግስ ምሽቱ ሲነጠፍ ፣
በሰውነት ንጋት ሸጋ አድማስ ለመኳል ማምሻው ሲዘነጠፍ ፣
( ያኔ ነው ሰው መሆን )
በሚያቆስል ቀን ውስጥ በሚያገረሽ ሌሊት ፣
ባለፈው ሲያክሙት የህመሙን መግል የፊቱን በኋሊት ።
..
ሀየይይይ ... !
..
..
ሸጋ ነፍስ ገልጦ ፣
ሰው በማለት ዜማ ፣
ከዱንያ እራስጌ ላይ የሀቁን ውብ ሀድራ እያንጎራጎረው ፣
ስማኝማ እያለ እርቀት ላይገረግር መድረስ ላያክረው።
የነፍሴን ባልጃ ፣
የጂስሜን ቢሊኮ ፣
ያፈር ገላ ልብሴን ቁረንጮየን ገፎ ድቤነት አውጥቶኝ ፣
ሲደባኝ ሰማሁት በመወዳድ መዳፍ እንደ ሀድራው ሽቶኝ ።
..
እንግዲህ ምን እችል ፣
በምን አቅሜ ልዘልቅ የወዳጄን መዝሙር ፣
በገዛ እኔው ድቤ ሰው በመሆን አግቦ የናልኝን አሽሙር ።
አልጅልም ባልንጀር ፣
አልሶብርም ለይሉን ፣
በኸሚሱ ግላጭ የጠናውን ሃጃ ዘንበን ለማረስረስ ፣
የሙሃባን ፈረስ በሀድራ ለጉሜ በነፍሴ ለመድረስ ።
..
( ወዲህም እዝነት ነው .. )
ቢንድው ተማያልቅ ፣
ከፍቅሩ ቁልል ነገን መሻገሪያ ሊያድል ሲገመድል ፣
የሻለት ብቻ ነው ሰው እንሁን የሚል ወዳጅ የሚታደል ።
..
በልማ ባልንጀር ፣
መጣሁኝ እንግዲህ ፣
ካለመድረስ ወዲህ
ኸሚስ ሽቅርቅሩ ቀሃ ጀባው ደርሷል አወሉን ገምጨ ፣
የመሻገሪያውን የቀለሙን ቀንድል ቀንበጤን ሸምጥጨ ፣
አፍታም አላረፍድ ፣
ሰው በመሆን መንገድ ፣
በተገማሸረው በወዳጃው ጥርጊያ ደግ ልንገናኝ ፣
በኮከብ ምልክት በጠፍ ጨረቃ ሌት እደወጣ መናኝ ፣
በወለላው ሀድራ እንደ ከፋው ሽፍታ እያንጎራጎርኩኝ ።
እዘልቅልሃለሁ ... !!
___
ሙሀመድ ሙፍቲ ( ጀዋድ ) 💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
ሀገር ማለትማ...
(ሚካኤል አስጨናቂ )
.
ሀገር ማለት ሰው ነው ብለሽ ያልሽኝ ዕለት
ሀገር ሰው አይደለም እያልኩሽ ስሟገት
ምክንያት ነበረኝ!
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ትዝ ይልሽ እንደሆን እንዲህ እልሽ ነበር ከመስኩ ዳር ሆነን
ተራራውን ወንዙን ሜዳውን እያየን..
.
ዓለሜ!
ሀገር ማለት እኮ ተራራ ማለት ነው
ከምድር ከፍ አርጎ ፈጣሪ ያነፀው
.
ከተራራው አናት ከላይ ተቀምጠሽ
ቁልቁል እንደምታይ መስኩን ዝቅ ብለሽ
ሀገርም ያለሽ ቀን ከፍታው ያንቺ ነው
ከማማው አናት ላይ በኩራት እንደቆምሽ
ዝቅ ብለሽ ማየት ነው!
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ!
ሀገር ማለትማ....
አዎን ተራራ ነው
ማንም እየካበ ማንም የሚያፈርሰው።
.
በቆመ ተራራ አናት የወጡ ለት
ከበላይ እንዳሉ የበታችን ማየት
አውቃለሁ ያኮራል..
እመኚኝ የኔ ውድ!
ሀገርም ያለሽ ቀን እንደዚህ ያደርጋል።
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
የተናደስ ዕለት?...
የተናደስ ዕለት ተራራው ሲፈርስ?!
ከፍታሽ ያልፍና ይጀመራል ማነስ
ወርዶ መገኘት ነው ቁመት መለካካት
ትከሻን አስታኮ አቀብ መንጠራራት
.
አየሽው ዓለሜ?
አየሽው ዓለሜ? .... ሀገር ተራራ ነው
ማንም እየካበ ማንም የሚያፈርሰው
.
ሀገር ማለትማ ሲክቡት የሚካብ በኩራት የሚያደምቅ
ሲንዱት የሚናድ ተስፋሽን የሚያደቅ
ተራራ ማለት ነው!
እና ታዲያ ፍቅሬ...
ዕውን አንቺ እንዳልሽው ሀገር ማለት ሰው ነው?
.
አይደለም የኔ ውድ!
ሀገር ሰው አይደለም!
ሀገር ማለትማ ሜዳና መስኩ ነው
ፈጣሪ አንጣሎ ዘርግቶ የጣለው።
አዎን!
.
አዎን!
.
አዎን ሀገር ማለት ሳር ያቆጠቆጠ ለጥ ያለ ሜዳ ነው
የቤት ብቻ ሳይሆን የጫካም እንስሳ መቶ የሚግጠው።.
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ
ሀገር ማለትማ ሜዳና መስክ ነው
ከጫካ ውስጥ ወቶ በቤት እንስሳ ላይ አለቃ መሆን ነው።
.
እና ታዲያ ዓለሜ
ሀገር ማለት ሰው ነው?
እኔ ብቻ ልጋጥ የሚሉት አባባል
የሰው ባህሪይ ነው?
.
አይደለም የኔ ውድ
አይደለም ዓለሜ
እንደውም ልንገርሽ.. .
ሀገር ማለትማ
ሀገር ማለትማ ፏፏቴው ወንዙ ነው
አፈር ተሸክሞ የመጓዝን ዕጣ ፈጣሪ የቸረው
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ!
ሀገር ማለትማ..ጉቶ እየነደሉ ግንድ ይዞ መዞር ነው
ማደሪያ ዳስ አጥቶ ህልምን መናፈቅ ነው
.
ሀገር መቆለል ነው
ሀገር መደርመስ ነው
ሀገር በመስክ ላይ
ቦርቆ መዝለል ነው
ግንድና አፈር ይዞ
ሲጓዙ እየዋሉ ሲጓዙ ማደር ነው።
እና አንቺ እንዳልሽ ሀገር ሰው አይደለም
ቀን እየተጓዙ ማታ በማሸለብ ሀገርነት የለም
.
እልሽ ነበር ያኔ ከመስኩ ዳር ሆነን
ተራራውን ወንዙን ሜዳውን እያየን።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ )
.
ሀገር ማለት ሰው ነው ብለሽ ያልሽኝ ዕለት
ሀገር ሰው አይደለም እያልኩሽ ስሟገት
ምክንያት ነበረኝ!
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ትዝ ይልሽ እንደሆን እንዲህ እልሽ ነበር ከመስኩ ዳር ሆነን
ተራራውን ወንዙን ሜዳውን እያየን..
.
ዓለሜ!
ሀገር ማለት እኮ ተራራ ማለት ነው
ከምድር ከፍ አርጎ ፈጣሪ ያነፀው
.
ከተራራው አናት ከላይ ተቀምጠሽ
ቁልቁል እንደምታይ መስኩን ዝቅ ብለሽ
ሀገርም ያለሽ ቀን ከፍታው ያንቺ ነው
ከማማው አናት ላይ በኩራት እንደቆምሽ
ዝቅ ብለሽ ማየት ነው!
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ!
ሀገር ማለትማ....
አዎን ተራራ ነው
ማንም እየካበ ማንም የሚያፈርሰው።
.
በቆመ ተራራ አናት የወጡ ለት
ከበላይ እንዳሉ የበታችን ማየት
አውቃለሁ ያኮራል..
እመኚኝ የኔ ውድ!
ሀገርም ያለሽ ቀን እንደዚህ ያደርጋል።
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
የተናደስ ዕለት?...
የተናደስ ዕለት ተራራው ሲፈርስ?!
ከፍታሽ ያልፍና ይጀመራል ማነስ
ወርዶ መገኘት ነው ቁመት መለካካት
ትከሻን አስታኮ አቀብ መንጠራራት
.
አየሽው ዓለሜ?
አየሽው ዓለሜ? .... ሀገር ተራራ ነው
ማንም እየካበ ማንም የሚያፈርሰው
.
ሀገር ማለትማ ሲክቡት የሚካብ በኩራት የሚያደምቅ
ሲንዱት የሚናድ ተስፋሽን የሚያደቅ
ተራራ ማለት ነው!
እና ታዲያ ፍቅሬ...
ዕውን አንቺ እንዳልሽው ሀገር ማለት ሰው ነው?
.
አይደለም የኔ ውድ!
ሀገር ሰው አይደለም!
ሀገር ማለትማ ሜዳና መስኩ ነው
ፈጣሪ አንጣሎ ዘርግቶ የጣለው።
አዎን!
.
አዎን!
.
አዎን ሀገር ማለት ሳር ያቆጠቆጠ ለጥ ያለ ሜዳ ነው
የቤት ብቻ ሳይሆን የጫካም እንስሳ መቶ የሚግጠው።.
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ
ሀገር ማለትማ ሜዳና መስክ ነው
ከጫካ ውስጥ ወቶ በቤት እንስሳ ላይ አለቃ መሆን ነው።
.
እና ታዲያ ዓለሜ
ሀገር ማለት ሰው ነው?
እኔ ብቻ ልጋጥ የሚሉት አባባል
የሰው ባህሪይ ነው?
.
አይደለም የኔ ውድ
አይደለም ዓለሜ
እንደውም ልንገርሽ.. .
ሀገር ማለትማ
ሀገር ማለትማ ፏፏቴው ወንዙ ነው
አፈር ተሸክሞ የመጓዝን ዕጣ ፈጣሪ የቸረው
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ሀገር ማለትማ!
ሀገር ማለትማ..ጉቶ እየነደሉ ግንድ ይዞ መዞር ነው
ማደሪያ ዳስ አጥቶ ህልምን መናፈቅ ነው
.
ሀገር መቆለል ነው
ሀገር መደርመስ ነው
ሀገር በመስክ ላይ
ቦርቆ መዝለል ነው
ግንድና አፈር ይዞ
ሲጓዙ እየዋሉ ሲጓዙ ማደር ነው።
እና አንቺ እንዳልሽ ሀገር ሰው አይደለም
ቀን እየተጓዙ ማታ በማሸለብ ሀገርነት የለም
.
እልሽ ነበር ያኔ ከመስኩ ዳር ሆነን
ተራራውን ወንዙን ሜዳውን እያየን።
@getem
@getem
@getem