ግጥም ብቻ 📘
64.2K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
(ዘ፡ፓሳህ ፡!፡ )
<~~~~~~~~~~~>
ረስቼሻለሁ ፡፡፡
*
ድንገት ሳስታውስሽ ብትናፍቂኝም ፣
ፍቅሬ አለሜ ስልሽ ፍቅርን ባትሰጭኝም ፣
አንቺነትሽ ናፍቆኝ
ፍቅሬ ፍቅሬ ብልም ፣
ማፍቀር ከመለየት ባይስተካከልም ፣
እውነት እውነት ፍቅሬ ረስቼሻለሁ
ብትታወሽኝም ።
#::::::::::::::::::::::::::::::::::::#

ግን አፈቅርሻለሁ !!!

መርሳት ማለት ዳሩ ምን ይሆን ግን
ፍቅሬ ¿?
በልብ ውስጥ ያደገች ያበበችን ፍሬ ;
ከፍቅር ብራና ፣
ከላባ ጫፍና ፣
ከቀይ ቀለምና ፣
የደመቀን ፊደል የሚሰርዝ አርማ ፣
ማፍቀር የሚልን ቃል የሚሰርዝ ቃል ነው መርሳት ማለትማ !፤!

ብትናፍቂኝም
ረስቼሻለሁ ፥
ግን አፈቅርሻለሁ ፡፡...

#getamiwochu
@getem
@getem
@getem
👍1
#የኔ_ሌላ_ምስል
:
እንቅፋት አግኝቶኝ ፥ ስጓዝ በዱር በመንገድ
ከወገቤ ቢያጥፈኝ ፥ ሰላምታ እንደ መስገድ፣
ዘመዴ እጄን ሲይዝ ፥ 'እኔን!' ሲለኝ ፈጥኖ
'ይድፋህ!' ሲል ጠላቴ ፥ ሲረግመኝ ጨክኖ፣
ጓዴ ግን ሳቀብኝ ፥ አንጀቱ እስኪቆስል
እርሱ ነው ወዳጄ ፥ የኔው ሌላ ምስል።
--------------------//--------------------------
( በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@getem
📗📒📕 ኢ - ስብራት

-- ልዑል ሀይሌ

ለተሰበረ እግር ድጋፍ ቢፈጠርም
ምርኩዝን ተማምኖ እግር አይሰበርም

@getem
@getem
ታገል ሰይፉ ለ ዶክተር አብይ 16k
ግጥም ብቻ
ታገል ሰይፍ

፨ ፍቅር ያሸንፋል 😊

ግጥሞን ይላኩ ▼▼▼▼▼
@Getemsource
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈

@getem
@getem
የጁምኣው አርበኛ! !!!


እንዴት ነህ አህመዲን፤
ገሞራው ከታቢ ። የጁምኣው አርበኛ ፤
አውቀዋለሁ እኔ ፤
አልሃምዱ ሚለውን ፤ ያንተን አማርኛ ፤
ዱኣማ ይዘናል፤ አላረፍንም እኛ ።
እንዴት ነህ ፊርአውን፤ የአህመዲን አሳሪ ፤
እንጃልህ ዘንድሮ ፤
እንደቆላ ሽፍታ ፤ አጥተሃል መካሪ ።


ተራራው ቢከመር ፤
ገደሉ ቢከመር ፤ ያው ላንድ ሰሞን ነው ፤
አትጠራጠሩኝ ፤
ባህሩን ሰንጥቆ ፤
በመሃል የሚያልፈው ፤
የጀሊሉ ባሪያ ፤ አህመዲናችን ነው! !!!!
ይኸው ነው!!!!!
ወላሂ ይኸው ነው! !!!!!

((( ጃ ኖ )))

@balmbaras
@getem
@getem
አሰታራቂ የለም
(በእውቀቱ ስዩም)

ጠብ ምድርን ባይሞላት
አቤል ባይፈጠር
አቤል ያቤል ጠላት
አቤል የራሱ ጠር
አንድ ሰው ለሁለት ተከፍሎ ሲፋለም
ሸምጋይ ወይ ገላጋይ
አስታራቂ የለም

@getem
@getem
@lula_al_greeko
---------------------------------------------------
በፀጉሩ ጫፍ ስቦ ፥ አለት ሲያንቀሳቅስ
አይተን ተደምመን ፥ ተገርመን ሳንጨርስ፣
አጃኢብ! ... አጃኢብ! ...
ማን እንደሱ ታላቅ?
ማን እንደሱ ጠቢብ?
እግሩን ሽቅብ ልኮ ፥ የዝቅዝቅ ወረደ
በጭንቅላት መጥቶ ፥ በምላሱ ሄደ።
---------------------------------------------
( በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@getem
...ጆርጅቡሽ . አናውጤው...
>[ ትዳር በጠመንጃ ]<
///////////////////////
አንጀት ልቧን ከፍታ
ውስጧ ሳታኖረው
ባህሪውን ሳታውቅ ምላሱን ሳትስለው
ፍቅሬ ሆዴ ብላ ሳታቆላምጠው
ይቺ የባላገሩዋን ልጂ
ትዳር ጠመንጃ አዝሎት
እጁዋ ተጠርፎ ከኋላ እያጀባት
ዋይ ዋይ ብላ ብትጮህ
ምንም ሰሚ የላት
ግፋ ቢል የሰማት አንድ ሂዎት ነበራት
ያ ሂዎት ሂዎቷ ትንሽ ቢያዳምጣት
ዝም ነው ዝምታ
ማንም መልስ አይሰጣት
በዝምታው መሃል ተከቦ ሹክሹክታ
በሃሳብ ማእበል እራሱን ሲማታ
እጣው ለሷ እንዳይደርስ ዝም ስትል ፈርታ
የሷ እውነት ነው የማታ የማታ

ይቀጥላል
@getem
@getem
@getem
#በአቋራጭ

በነገሮች አትሳቅ በጥርስህ ይደርሳል
ስትሉኝ አድጌ
ስንት ነገር አለፍኩ ለመሳቅ ፈልጌ
ፈሊጡ ሲገባኝ ዛሬ ደሞ ይኸው
ሀብታም ባየው ቁጥር እገለፍጣለው ፡፡

Anteneh_Tesfaye

@getem
@getem
@getem
ሪጎሬ!!!!!!


እሱም ቀኑ ደርሶት፤
በሙዚቃው ሜዳ፤
ከባድ ሪጎሬ፤ ጠርዞ ሲያስገባ፤
ሎጬ የገባበት፤
ጎሉን እንዳነቀ፤ ምነው ሆዱ ባባ።


ከጦቢያ ቅጠል ላይ፤
በጦቢያ ተሳልቀው፤
ባንዲራዋን ንቀው፤
አፋቸውን ለቀው፤
ምች የመታቸውን፤
የሚፈውስበት፤
ደማ ከሴ ዜማ፤
ከበገናው ጋራ፤ ሆ ብሎ ሲያነሳ፤
ምች የመታው ሁሉ፤
እንደ እንቆቆ ጠጪ፤ ተንዘፈዘፈሳ።
በአንዲት ሪጎሬ እየተበሳጩ፤
በደርቅ እግራቸው እየተወራጩ ፤
ኳሱም እየካደ፤ ሲያመልጥ ከእግራቸው፤
ይኸ ብላቴና፤
ዛሬም በሪጎሬ በሎጬ ሸኛቸው።


((( ጃ ኖ )))


((( መልካም ልደት ጀግናዬ )))🎂🎂🎂🎂

@balmbaras
@getem
@getem
👍2
ሁለት የካሳ ልጅ!!!!!!


መቼስ ዘመን አይደል፣
ዶሴ እየገለጠ፣
ነቃሽ እየጠራ፣ ፍርድ የሚያስተነትን፣
መቼስ ትውልድ አይደል፣
በእናት ሃገር ምሎ፣
ትንሳኤ እየራበው፣
ባንዲራውን አምኖ፣ በሞት የሚኳትን።
ከዶሴው ፅህፈት ላይ፣
ደመቅመቅ ብሎ፣
በደም የተፃፈ የብራና ገላ፣
ባይኑ ሲዞርበት፣
የጥቁር ሰው ማተብ፣ የፍኖው ጀበርና፣
በጆሮው ሲያሽቃርር፣
የበልጅጉ ጬኸት፣ የፈረሱ ዳና፤
እያንገበገበው፣
የጫካው ጦም ማደር፣ የአንበሳው እርጅና፣
ለካስ ከሞት መሃል፣
ቴዲም ይወለዳል፣ ዳግም እንደገና።
አንዱ መዩ ካሳ ፣ የቋራው ሞስለኔ፣
ህልመ ምትሃተኛ፣
እንደ ቆላ መደድ፣ እንደ ዲማ ቅኔ፣
አገር ሰርቶ ሲሰጥ ፣
ጋፋት ጉብታው ላይ፣ አይቻለሁ ባይኔ።
ይህኛው ትንሹ፣ የኔ ዘመን ፋኖ፣
ጃ!!!!! ተነስ ይለኛል፣
ካባቶቹ ድካ፣ ጉብታው ላይ ሆኖ።
በላይ በመቅደላ፣ከመይሳው ጋራ፣
ጎፈር አጋሚዶ፣
አፍሮ የማበጥር፣ሹርቤ ' ምሰራ፣
የምመነሽረው፣
አንዱን በቀረርቶ፣ አንዱን በውጅግራ፣
የምወዘውዘው፣
አንዱን በጎራዴ፣ አንዱን በዳንኪራ፣
እኔም የካሳ ነኝ፣
በባንዲራው ቀለም፣
ድካየን የማበጅ፣ ህልሜን የምሰራ።


በጨለማ መሃል፣
ላይን በጋረደው፣ ድንግዝግዝ ጎዳና፣
አላይም እያለ፣
ውሃ ውሃ ሲሸት፣
የእናቴን ባዶ አንጀት፣ የእንቅቧን ገመና፣
በጨለማው መሃል፣ጨለማ እያሰሰ፣
ወጋገን ፍለጋ፣
ሰርጣ ሰርጡን በእጁ፣ በእግሩ እየዳበሰ፣
በጨለማው መሃል፣
ድብታን ተጋብቶ፣
ሃገር እያዛጋ፣ በሞት አዚም ታንቆ፣
የብርሃን ሽንቁር፣
አይቻለሁ ያለ፣
በንስር አይኖቹ፣ አደባባይ ዘልቆ፣
እነ ጆፌ አሞራ፣
ና እንምከር እያሉ፣
ና ውረድ እያሉ፣ መቼ ያቆዩታል፣
ሰማይ የዋለውን፣
በዱልዱም ክንፋቸው፣ መሬት ያወርዱታል፣
ከሄደበት ሳይደርስ፣
ወራጅ ነው እያሉ፣ ስም ያወጡለታል።
ጆፌ አሞራ ነክሶት፣
ቁራ ቁሬ ለክፎት፣
የብርሃን ክንፎቹን፣
የጠሊቅ አይኖቹን፣
በጆፌዎች ምንቃር ፣
እየተጎተተ ፣
ምናብና ህልሙን፣ ንስር ከተቀማ፣
ከተፈረደበት፣
በነፈዞች ጉባይ፣ በጅሎች ከተማ፣
አይኖርም ባለራይ፣ አይቆይም አይናማ።


ግና መዩ ካሳ፣
እኒያ ጥላቶችህ፤
ካልተረዱት ራእይ፣
ካልጀመሩት መንገድ፣
ሌላ ወሽመጥ ከፍተው፣ መስቀልያ አበጁ፣
ሂደው ሳይጨርሱ፣
በጎዳና ቆመው፣ በጎዳና አረጁ።


ይኸው ደግሞ መጣ፣
የማለዳው ኮከብ፣
የመድረኩ ልኡል፣ ሸገናው ሸገኑ፣
ጃ !!!! ብሎ ሲፎክር፣
ይኸ ያገሬ ሰው፣
ይሽራል በሽታው፣ ይከፈታል አይኑ።


እኔም በመይሳው፣
በገብርዬ ጓንዴ፣ በአካልዬ ጥላ፣
ያስተሰርእይ የምል፣
በጥቁር ሰው ቅኔ፣ በቴዲ ሽለላ፣
እኔም መይሳው ነኝ፣
የሚጋረፍ ቃንቄ፣ የጠላት አሽከላ፣
በጀግና ስም ምየ፣
ህልሜን የምቀጥል፣ ህልሜን የማሰላ።

((( ጃ ኖ )))

መልካም ልደት ጀግናዬ!!!🎂🎂🎂🎂🎂


@balmbaras
@Getem
@getem
🎉1
«አለቅሽም»
እድሜ ቢገረጅጅ
ኑሮዬ ቢል እጅጅ
ብወረር በሽበት
አካሌ ቢሻግት
መንገዱ ቢያደክመኝ
አድራሻሽ ቢርቀኝ
ሌላ ስጠብቂ
ሌላ ስትናፍቂ
ስቃየን ባታውቂ
ስከተልሽ እኔ
በህይወት ዘመኔ
ሌላ አይታይ ለኔ
እኔ አልታይ ላንቺ
ባትረጅም አንቺ
ባይገባሽ ማፍቀሬ
አይሻለሁ ማሬ
አይኖችን ወርውሬ

አሰናብቶኝ ብሄድ
ጊዜም በኔ ቢፈርድ
አንቺም ብለሽ እምቢ
ሌላ ~ስታልሚ ስታስቢ
አይንሽ እኔን ጠልቶ
ልብሽ እኔን ከድቶ
ሆኘብሽ ቡትቶ
ተሽቀንጥሬ ብወድቅ
ልቤ አንቺን ሲናፍቅ
ለምን ሆንኩኝ ብርቱ
ማፍቀር ማለት እቱ
ይህ ነውና እውነቱ
ተጠልቶ መውደድን
ተሸሽቶ መቅረብን
ተረስቶ ማሰብን
እንዳንቺ እና እንደኔ
እንድህ ነው ሔዋኔ

አሰናብታይ ምድር
ብገባም መቃብር
ይመጣል እምባዬ
ይፈልቃል እምባዬ
ልክ በምንጭ መልክ
ከደጅሽ ጉብን ስር
ይመጣል አጥንቴ
ባይችልም ጉልበቴ
ይመጣል ብሶቴ
ይመጣል ናፍቆቴ

በህይወት እንዳለሁ ወደኔ ባትመጭም
እመጣለሁ እኔ መጓዝ አልሰለችም
አፈር ቢጫነኝም መቸም አለቅሽም!
.....................
ተፃፈ፡ በአወቀ ካሳው
ሰኔ 29/2010 ዓ.ም

@getem @getem
@getem @getem
በርዬ እሽሩሩ!!!!


ሰውን ያህል ንጉስ፣
ሰውን ያህል ቅዱስ፤
አምኜው የነበር፤
እስከልቤ ድረስ፤ እስከ አለም ፍፃሜ፤
እምነት እየበላ፤
ቃል እያፈረሰ፤
ይኸው ዛሬ ድረስ፤ አልሻረም ህመሜ።


አዎ አልተሻለኝም፤
ማመን ያነቆረው፤ አልጠገገም ቁስሉ፤
ይሻለኝ እንደሆን፤
ደበስበስ አድርገኝ፤ በርዬ እሽሩሩ፤
አንተ ስትዳብሰኝ፤
የጭካኔ ሰንኮፍ፤ ይነቀላል ስሩ፤
የተዘጋው ተስፋ፤
ባንተ ፍቅር ትንፋሽ፤ ይከፈታል በሩ።

(( ጃ ኖ ))

ሸጋ ሸጊቱ ጁምኣ!!!!!

@balmbaras
@getem
@getem
✦✦ እጣ ፈንታ ✦✦

ከመንገድ ተመርጠህ
በሞቴ ተብለህ
ዳቦ የምትጎርሰው።

ገና ስትዘራ
በዚያች ስዴ ግንባር
ስምህ ተፅፎ ነው።

አንዷለም አባተ

ግጥሞን ይላኩ ▼▼▼▼▼
@Getem_sourcebot
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈

@getem
@getem
✦✦ ጎልማሳው ✦✦

እድሜው ተቆጠረ
ልደቱም ደረሰ

አርባ ዓመቱ ሞልቶ
ድግስ አስደገሠ

የሻማ ዋጋ ግን
ስላልተቀመሠ

ሁለት °ፓኮ° ክብሪት
ለክብሩ ለኮሠ።

አንድነት ሰርፀ

ግጥሞን ይላኩ ▼▼▼▼▼
@Getem_sourcebot
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈

@getem
@getem