ግጥም ብቻ 📘
64.2K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
"""የጦቢያ ባለሃብት"" !!!!!!


እርሻዬን ቀምቶ፣
ማጀቴን ደፋፍቶ ፣
ከቤቴ አስወጥቶ፣
ማረሻየን ሰብሮ፣ ሞፈሬን ቆስቁሶ፣
ጎተራዬን ንዶ፣ ጎጆዬን አፍርሶ፣
ቂጣዬን አንኩሮ፣ ኑሮዬን ከርችሞ፣
እንቁጭልህ ይላል፣
የማየውን እንጅ፣
የማያጎርሰኝን፣ ዳቦ ተሸክሞ።

((( ጃ ኖ )))


((( ሸጋ ጁምኣ ))


@balmbaras
@getem
@getem
የመድረሳ ፍቅር

(ለሐሊማ)



አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .

ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ

ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ. . .

የኡስታዝን ቁጣ ትንሽ ነፍሴ ፈርታ

ለማሃፈዝ ስጣጣር ሳፋቅድ ስፈታ…

ደግሞ ባንቺ ፍቅር ቀልቤ ሩኋን ስታ

ሰርቄ እያየሁሽ በኩርኩም ስመታ

ያደግኩብሽ ውዴ ናፍቆቴ ሐሊማ

የልጅነት ገዴ ነይ ድምጽሽን ልስማ…

አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .

ኹሩፍ ስንለያይ ተቀምጠን መድረሳ

ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…

ቁርአኑን ወጣሁት ጨረስኩት ሃፍዤ

አንቺን ለማስደሰት በፍቅርሽ ተይዤ

ታዲያ አሁን ዛሬ ትልቅ ሰው ተብዬ

በትልቆች መሃል በክብር ቁጭ ብዬ

ቁርአኑን ልቀራው በገለጽኩት ቁጥር

ጀነትን ያሳየኝ ቀናው የልጅ ፍቅር

ድቅን እያለብኝ ተቸገርኩ ሐሊማ

ለበይክ አለሁ በይኝ በይ ድምጽሽን ልስማ…

አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .

ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ

ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…

ትዝ ይልሽ እንደሆን ያኔ ልጆች ሳለን

ሐራም ሐላል ሳንል በቅን አብረን ዘለን

አንቺም እጄን ይዘሽ እኔም አንቺን ይዤ

ቁርአኑን ስትወጭው እኔም ባንዴ ሃፍዤ

ቦርቀን ነበረ ለዱንያም ላኼራ

ዛሬ ድምጽሽ ጠፋ በይ ስሚኝ ስጣራ

የኒካው ቀለበት ተቀምጧል በአደራ …

አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .

ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ

ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…

© አብዲ ሰ.

ማስታወሻ:

ከአረብኛ የተወሰዱና ምናልባት መድረሳ ላልተማረ ሰው ግር ይሉ እንደሁ
ብዬ ያሰብኳቸውን ቃላት ትርጓሚያቸው:-

መድረሳ: የቁርአን ትምህርት ቤት፡፡

አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሳ፣ . . . የአረብኛ ፊደል ቆጠራ፡፡

ኡስታዝ… የቁርአን ወይም የሃይማኖታዊ ትምህርት አስተማሪ፡፡

ማሃፈዝ… በቃል ሸምድዶ መያዝ… ወይም በቃል ብቻ መውጣት፡፡

ኹሩፍ… የአረብኛ ፊደል ወይም ፊደል ቆጠራ፡፡

ለበይክ … አቤት.. አለሁ እንደማለት፡፡

ሐራም… የተከለለ… በሃይማኖት አስተምህሮት የማይፈቀድ፡፡

ሐላል… የተፈቀደ… ሊደረግ የሚቻል


((( ሸጋ ሸጊቱ ጁምኣ ))

@balmbaras
@getem
@getem
❤️ቴዲ አፍሮ❤️

አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ነው አርማዬ
ልጄ ብለሽ ጥሪኝ አለሁ ኢትዮጵያዬ
ስቀሉት አርማዬን እንደማርያም ልጅ
ስቀሉት አርማዬን አውጡና እንጨት ላይ
ፍቅር ከሰው ሁሉ ከፍ በሎ እንዲታይ #Ethiopia

@getem
@getem
እኔ ብቻ ቀረሁ
( #ካፒቴን ናትናኤል ጌቱ )

ስንት ሐመሩ "ሐ" ዎች
በሐመር መኪና ፥ ተንደላቀው ሲያልፉ
ስንት ፎሌው "ሀ" ዎች
በወርቃማ ዋንጫ ፥ ውስኪ ሲጨልፉ
ስንት ንጉስ "ኃ" ዎች
ከመሬት ተነስተው ፥ ዙፋኑን ሲወርሱ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
በድሮ ልብና
በድሮ ሽክና ፥ ተከብቤ እንደቆምኩ
ጠላ ትዝታሽን
በፎሌ ተግቼ ፥ እየተንገዳገድኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! እኔ ብቻ ተከዝኩ!!
ያውና! … ያውና !
አለምነሽ ካሳነሽ
እንደተሳፈሩት ፥ የድሮ መኪና
ጭሱ ቦለል ይላል ፥ የቤቴ ኩሽና
አንቺኮ የለሽም ፥ ቤቴ ምን ነክቶታል ?
ብቸኛው ርስቴን ፥ በቃ አቃጥለውታል !!
እኔ ብቻ ቀረሁ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ሰባራ ፍቅርሽን ፥ እንደተመረኮዝኩ
ስንት ንጉስ "ሰ" ዎች
ንጉሱ "ኃ" ዎችን ፥ ሊጥሉ ሲነሱ
ስንት እሳቱ "ሰ"ዎች
አመፅ ለማስነሳት ፥ እሳት ሲለኩሱ
ስንት አለሙ "ዓ" ዎች
በደስታ ሲሰክሩ ፥ ቡጊ ሲደንሱ
አንገቴን ደፍቼ ፥ ከልቤ እያነባሁ
እኔ ብቻ ከፋኝ ፥ እኔ ብቻ ባባሁ!
ካንዲት ተራ ወንበር ፥ ቂጤ ተዘፍዝፎ
ጨቡዴና አማረ ፥ ካስተረፉት ገንፎ
እጄን እየሰደድኩ
በጎዳናው መሀል
ሺዎች ሲቀየሩ እየተመለከትኩ
እንጃ ማን እንደሆን ሽቶ የረጫቸው
ስንት ሐመሯ "ሐ" ዎች ሸክላ ከንፈራቸው
ሊፒስቲክ ተቀብቶ
ጫላ ጩቤ ጥሎ ፥ ዲሞፍተር አንስቶ
አድጎ ተመንድጎ ፥ ማሙሽ ምግብ በልቶ
እኔ ብቻ ከፋኝ
ትውስታሽ ተጠጋኝ ፥ ትዝታሽ ደረሰ
እሽሩሩ ፍቅር
እንባዬ እንደ ካሮት ፥ ቁልቁል ገሰገሰ
እኔ ብቻ ቀረሁ
የቡሄ በአልን ፥ ድፎ ሳላስደፋ
ራሴው ተደፍቼ
ሙስሊም ወንድሞቼ
ተምሩ በቅቷቸው ፥ ታምር ሲመገቡ
መካን ሊያዩ ወተው ፥ ዱባይ ሲያንጃብቡ
የረመዳን ጦሜን ፥ በውሀ እያፈጠርኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ያውና ያውና
ፊደል በሚመስል ፥ የህይወት ጎዳና
እነ ጸሎቱ "ጸ" ፥ ለስግደት ተደፍተው
ስለታቸው ሰምሮ ፥ ጭፈራ ቤት ከፍተው
ስንት አይናማው "ዐ" ዎች ፥ ባንድ አይናቸው ጠቅሰው
ከቆንጆ ተጣብሰው ፥ ቆንጆ ልጅ ወለዱ
እኔ ብቻ ጎደልኩ ፥ ከደስታ መንገዱ
እኔ ብቻ ዋተትኩ
እኔ ብቻ አዘንኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ
ፊደል ከሚመስለው ፥ የህይወት ገበታ
ነይ ታገኚኛለሽ
የዛሬ ሺ አመታት ፥ ካስቀመጥሺኝ ቦታ
እኔ ብቻ ቀረሁ…


@getemsource
@getem
@getem
ዜብራን ረገጥነው!!!!!


ዜብራ ቡራቡሬ፣ መልኩን አሳምሮ፣
በሽንቅጥ ወገቡ፣ አምሮ ተገሽሮ፣
ቁልቁል እያባጨን፣
በሞንዳላ ጭኑ፣ ከላይ ተከምሮ፣
ሁሌም ይለን ነበር፣
"መረጋገጥ ነበር፣ ይህን ሁሉ ዶሮ።"
ግና፣
መንገድ አያመጣው፣ አይስበው አያጣ፣
እኛ ያገር ዶሮች፣
ዛሬ ተሳክቶልን፣ ሽርሽር ስንወጣ፣
ዜብራ አባ ፎካሪው፣
ድንገት መንገድ ገብቶ፣
ያን ሁሉ ሽለላ፣ ቀረርቶ ዘንግቶ፣
ዶሮ ረጋገጠው፣ መንገድ ላይ ተኝቶ።
ጉድ እኮ ነው!!!!!
በቀረርቶ ጩኸት፣
በረጋጭ ፉከራ፣ እረግጣለሁ ያለ፣
አይ ቅሌት!!!!!!
ርጋጩ ረግጦት ፣ ሲረጋገጥ ዋለ!!!!!!!!!!

((( ጃ ኖ )))

ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!!!!

@balmbaras
@getem
@getem
👱እኔ ሳነብልሽ👱‍♀

👦👧👨👱‍♀👱👩👴👵

ፀሐይ ማቃጠልዎን ትታ፡
ታዳምጠኛለች ሁሉንም እረስታ፡
እኔ ሳነብልሽ እሚሄዱት ይቆማሉ፡
የጠወለጉ አበባዎች መልሰው ይፈካሉ፡
ያጐነበሱ ዘፎች ቀና ቀና ይላሉ፡
ወፎች ሊሰሙኝ ተሰብስበው ይመጣሉ።

እኔ ሳነብልሽ

በልጅነት አፌ በሚንኮላተፈው፡
ሁሉም ነው የሚሰማኝ ማንም ሳይሰለቸው፡
ውዴ እኔ ለ አንቺ ሳነብ፡
ሊያዳምጡኝ ዝሆኖች ቁጭ ይላሉ፡
ኤሊዎች ሊሰሙኝ ፈጥነው ይመጣሉ፡
ወንዝ፣ፋፎቴዎች ቃላያት በሙሉ፡
እኔ ሳነብልሽ ለአፍታ ፀጥ ይላሉ።

📝📝📝📝📝📝📝📝
ፊሊሞን የማርያም ልጅ
22/10/2010

@getem
@getem
@itsmefilimon
👍1
...እመኚኝ !!
:
ነይ ግቢ በሞቴ
እቤት ማንም የለም የለችም እናቴ
እመኚኝ ግዴለም ምንም አናደርግም
ወደ ውስጥ ገብተሽ በሩን ብዘጋውም
አንድ ላይ ተቀምጠን አብረን ብናወጋም
ከንፈርሽን ልስም ወዳንቺ ብጠጋም
ብስምሽም እንኳን ስጋት እንዳገባሽ
ምንም አናደርግም
.
..
በፀጉሮችሽ መሃል ጣቴን ባንሸራሽር
ጠረንሽን ቢሸተኝ ገብቼ አንገትሽ ስር
እጄ ይይዘው አጥቶ ጡትሽን ቢነካካ
እየጨባበጠ መጠኑን ቢለካ
እንዳትጠረጥሪኝ
ለሌላ እንዳይመስልሽ ውዴ ሙች እመኚኝ
.
..
በዚህ ሁሉ መሃል በስሜት ገንፍዬ
ልብስሽን ባወልቅም ልብሴን ወዲያ ጥዬ
እርቃንሽን ሆነሽ እርቃኔንም ሆኜ
አልጋው ላይ ብጥልሽ በክንዴ ዘግኜ
በሚገርም ሁኔታ ፍቅር ብንሰራም
እመኚኝ አለሜ እኔ ልሙትልሽ ምንም
አናደርግም
------------//-----------
(ምንጭ
ግጥምና ገጣሚያን ማህደር)
.
:
@getem
@getem
@getem
1
////-----//////


ፈጣሪ ነው እንጂ ፣ ሰው አይፈርድም በሰው
ብሎ ሲያንጎራጉር...
ሰዎች ፈርደውበት የተበደለ ሰው
እኔ ግን እላለሁ!
የሰው ልጅ ነው እንጂ ፣ አምላክ ፍርድ አያውቅም
በበደሎች ሁሉ...
የማይሸነፍ ነው ፣ የቸርነቱ አቅም፡፡
፡፡፡፡
ከሐጢያቶች ሁሉ ፣ ምህረቱ ያይላል
እኛ "ፍረድ" ስንል ፣ እርሱ "ይቅር" ይላል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
አናም እኔ ለኔ...
የማንጎራጉረው ፣ አንድ ዘፈን አለኝ
ፍርዱ ቢለያይም...
ይቅር ብሎ ማለፍ ፣ ፍርድ ነው መሠለኝ!"

ምንጭ፦የቴሌግራም ግጥም ምሽት
አቤ

@getem
@getem
@lula_al_greeko
ሰው መስለሺኝ ነበር
...............
እስኪ ስሚኝ ውዴ
ልጠይቅሽ አንዴ
ላንቺ የሰው ልጅ ማለት ትርጉሙ ምንድነው?
ፍቅርና ክብር ተስፋስ ምን ማለት ነው?
ስላንቺ ሳወራ ስላንቺ ስናገር
ለካስ አላውቅሽም ሰው መስለሺኝ ነበር
ለኔ እንኳን ግድ የለም ኃላ እንዳትጎጂ
መናቁን ተይና ሰው ማክበር ልመጂ
ለኔ ሲሆን ጊዜ ስጠራሽ ብውልም
እየቻልሽ አትችዪም እያለሽ የለሽም
ከቻልሽ አገናዝቢ ካልገባሽ ጠይቂ
ትንሽ የሚባል ሰው እንደሌለ እወቂ
ህሊና ላለው ሰው ትርግሙ ለገባው
እሺ ብሎ መቅረት እምቢ እንደማለት ነው
እኔ እኮ የሚገርመኝ ታሪክ እንደሰራ
አላፊ በሆነው በመልኳ ስትኮራ
ትመጪያለሽ እያልኩ በተስፋ ብኖርም
ባትመጪም ቅጠሪኝ ማለት ግን አልችልም
እናም አንዴ ስሚኝ ይጠቅምሻልና
ማስመሰሉን ትተሽ ሰው ሁኚ እንደገና

(ጉልላት አበበ)

@getem
@getem
@lula_al_greeko
👍2
💗ታ ስ ፈ ል ጊ ኛ ለ ሽ

በተለይ በክረምት ሙቀት ሲያስፈልገኝ

በተለይ በምሽት ለብቻየ ስገኝ

ብርድና ባዶነት ተባብረው ሲመጡ

ባንች ተገፍትረው ፈጥነው እንዲወጡ

ከላዬ ቁጭ በይ ግርማዬ ሞገሴ

እቅፍፍፍ ስታደርጊኝ ትረካለች ነፍሴ

ጌጤ ነሽ ለአካሌ ክብርና ውበቴ

በይ ነይ ልደርብሽ ከታናሿ ቤቴ
.
.

.
.
.
.
.
.
.
.
.
ታስፈልጊኛለሽ ወፍራሟ ጃኬቴ፡፡


ዘላለም
❤️😂
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ምታተኛነትህን
@getem
@getem
መፍትሄ
(በረከት በላይነህ)

በር መስኮት ዘግተህ ፣
ቀዳዳውን ደፍነህ
የለኮስከው ሻማ "በራ"! ፣"ጠፋ"! ካለ፤

ጠርጥር!
ቤት ያፈራወ ንፋስ ከጎጆው እነዳለ።

@getem
@getem
@getemsource
እረፍት_የለሽ_ስሜት

የንጉርጉሮ ~ ንዝረት፣
እምቅ የሃሳብ ንፍዘት፣

ህይወት በቅሬታ ምጥ ሲሞላ፣
ነገር ውስጥ ውስጡን ሲብላላ፣
አንጎል ተወጥሮ በጭንቅ ሲጉላላ፣

በመፍትሄ አልባ አልቦነት፣
አዕምሮ ተጠቦ በጭንቀት፣
የተስፋ ሻማ እልም ያለ 'ለት፣

ሆኖ ይቀራል ያልለየለት፣
የተዳፈነ እሳት
ወኔ የለሽ ~ ዕብደት!!!

እረፍት



ስሜት!!!

# ሀብታሙ_ወዳጅ


#ETHIOPIAN
@getem
@getem
@getem
ከሳቁ አይቀር፣ እንደ ጃገማ!!!!
ልብ እስኪሰማ!!!!!!
ካዮ አይቀር፣ እንደጃኖ!!!
በጥልቅ ሆኖ!!!

@balmbaras
@getem
@getem
(ዘ፡ፓሳህ ፡!፡ )
<~~~~~~~~~~~>
ረስቼሻለሁ ፡፡፡
*
ድንገት ሳስታውስሽ ብትናፍቂኝም ፣
ፍቅሬ አለሜ ስልሽ ፍቅርን ባትሰጭኝም ፣
አንቺነትሽ ናፍቆኝ
ፍቅሬ ፍቅሬ ብልም ፣
ማፍቀር ከመለየት ባይስተካከልም ፣
እውነት እውነት ፍቅሬ ረስቼሻለሁ
ብትታወሽኝም ።
#::::::::::::::::::::::::::::::::::::#

ግን አፈቅርሻለሁ !!!

መርሳት ማለት ዳሩ ምን ይሆን ግን
ፍቅሬ ¿?
በልብ ውስጥ ያደገች ያበበችን ፍሬ ;
ከፍቅር ብራና ፣
ከላባ ጫፍና ፣
ከቀይ ቀለምና ፣
የደመቀን ፊደል የሚሰርዝ አርማ ፣
ማፍቀር የሚልን ቃል የሚሰርዝ ቃል ነው መርሳት ማለትማ !፤!

ብትናፍቂኝም
ረስቼሻለሁ ፥
ግን አፈቅርሻለሁ ፡፡...

#getamiwochu
@getem
@getem
@getem
👍1
#የኔ_ሌላ_ምስል
:
እንቅፋት አግኝቶኝ ፥ ስጓዝ በዱር በመንገድ
ከወገቤ ቢያጥፈኝ ፥ ሰላምታ እንደ መስገድ፣
ዘመዴ እጄን ሲይዝ ፥ 'እኔን!' ሲለኝ ፈጥኖ
'ይድፋህ!' ሲል ጠላቴ ፥ ሲረግመኝ ጨክኖ፣
ጓዴ ግን ሳቀብኝ ፥ አንጀቱ እስኪቆስል
እርሱ ነው ወዳጄ ፥ የኔው ሌላ ምስል።
--------------------//--------------------------
( በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@getem
📗📒📕 ኢ - ስብራት

-- ልዑል ሀይሌ

ለተሰበረ እግር ድጋፍ ቢፈጠርም
ምርኩዝን ተማምኖ እግር አይሰበርም

@getem
@getem