እናት እሙ ገላ !
ደግሞ አንድ ቀን ላንቺ ከቶ ምን ሊረባ?
ዓመት ሙሉ ማሰብ
ዓመት ሙሉ ማክበር
ዓመት ሙሉ መውደድ
ዓመት ሙሉ ማፍቀር
በዘመን ቢመተር ከአንጀት ላይገባ !
ሰማሽ እሙ ገላ …
ተወርቶ ተነግሮ
በጽሁፍ ተሞንጭሮ
በፎቶ ተሰቅሎ
በቃል ተሸልሎ
ብዙ ተፎክሮ ያልቅ እንደሆን እንጃ
የተራመድኩበት የፍቅር ስጋጃ..
እማምዬ ውዴ …
አንቺ የኔ ምንጣፍ መረማመጃዬ
የኑሮ ግብግብ መለማመጃዬ
መውጣቴ መውረዴ
መውደቅ መነሳቴ
ደስታዬ ኩራቴ
ሃዘኔ ክሳቴ
ጉስቁልና ጥጌ
ጌጤና ማረጌ…
ደግሞ አንድ ቀን ላንቺ ከቶ ምን ሊረባ?
ዓመት ሙሉ ማሰብ
ዓመት ሙሉ ማክበር
ዓመት ሙሉ መውደድ
ዓመት ሙሉ ማፍቀር
በዘመን ቢመተር ከአንጀት ላይገባ!
_ // አብዲ ሰዒድ // _
@balmbaras
@getem
@getem
ደግሞ አንድ ቀን ላንቺ ከቶ ምን ሊረባ?
ዓመት ሙሉ ማሰብ
ዓመት ሙሉ ማክበር
ዓመት ሙሉ መውደድ
ዓመት ሙሉ ማፍቀር
በዘመን ቢመተር ከአንጀት ላይገባ !
ሰማሽ እሙ ገላ …
ተወርቶ ተነግሮ
በጽሁፍ ተሞንጭሮ
በፎቶ ተሰቅሎ
በቃል ተሸልሎ
ብዙ ተፎክሮ ያልቅ እንደሆን እንጃ
የተራመድኩበት የፍቅር ስጋጃ..
እማምዬ ውዴ …
አንቺ የኔ ምንጣፍ መረማመጃዬ
የኑሮ ግብግብ መለማመጃዬ
መውጣቴ መውረዴ
መውደቅ መነሳቴ
ደስታዬ ኩራቴ
ሃዘኔ ክሳቴ
ጉስቁልና ጥጌ
ጌጤና ማረጌ…
ደግሞ አንድ ቀን ላንቺ ከቶ ምን ሊረባ?
ዓመት ሙሉ ማሰብ
ዓመት ሙሉ ማክበር
ዓመት ሙሉ መውደድ
ዓመት ሙሉ ማፍቀር
በዘመን ቢመተር ከአንጀት ላይገባ!
_ // አብዲ ሰዒድ // _
@balmbaras
@getem
@getem
. . . የኔታና ሚስ . . .
ሀ – ሁ . . . አ – ቡ – ጊ – ዳ
ሀ – ሁ . . . አ – ቡ – ጊ – ዳ
ገና ከማለዳ ልጅነቴን ለምዳ
ከስትንፋስ ከደሜ ከነፍሴ ተዋህዳ . . .
ሀ – ግእዝ . . . ሁ – ካእብ
ሂ – ሳልስ . . . ሃ – ራብእ
ሄ – ኻምስ . . . ህ – ሳድስ
ሆ – ሳብእ . . . ስክልስ . . .
በዜማ ስለቅም፣ በህብር ሳወድስ
መልእክተ ዮሐንስ፣ መልክተ ዮሐንስ
ስከልስ ስከልስ፣ ለነፍሴ ሳሰልስ . . .
በአገራዊ ቃና
ሕይወቴ እንዲቃና
የኔነት፣ እኔነት፣ በደሜ እንዲዘራ
የኔታ በኩርኩም፣ አባም በከዘራ
የለፉልኝ እኔ፣ ያደድኩት ልጃቸው
ዛሬ ወጉ ደርሶኝ አባት ሆኜላቸው . . .
ልጄን ከቀለም ቤት በኩራት ሰድጄ
አቡጊዳም እዳ፣
እኔነትም ባዳ፥
ሆኖበት ሲቸገር አይቼ ነድጄ! . . .
እ – ን – ደ – ተ – ብ – ከ – ነ – ከ – ን – ኩ
እ – ን – ደ – ተ – ብ – ሰ – ለ – ሰ – ል – ኩ
“ኤ ፎር አፕል” ብሎ ልጄ አፉን ፈታ
“ኤን ብቻ!” የምትሰብክ ከፊደል ገበታ
ግእዝ የማታዜም፣ ቅኔ የማትፈታ
ማንነት ‘ማይገዳት፣ ለ’ሱ የሌላት ቦታ
ሚስ ናት የሱ የኔታ
ሚስ ናት የሱ ጌታ::
_ // _
_ // © አብዲ ሰዒድ // _
@Balmbaras
@Getem
@getem
ሀ – ሁ . . . አ – ቡ – ጊ – ዳ
ሀ – ሁ . . . አ – ቡ – ጊ – ዳ
ገና ከማለዳ ልጅነቴን ለምዳ
ከስትንፋስ ከደሜ ከነፍሴ ተዋህዳ . . .
ሀ – ግእዝ . . . ሁ – ካእብ
ሂ – ሳልስ . . . ሃ – ራብእ
ሄ – ኻምስ . . . ህ – ሳድስ
ሆ – ሳብእ . . . ስክልስ . . .
በዜማ ስለቅም፣ በህብር ሳወድስ
መልእክተ ዮሐንስ፣ መልክተ ዮሐንስ
ስከልስ ስከልስ፣ ለነፍሴ ሳሰልስ . . .
በአገራዊ ቃና
ሕይወቴ እንዲቃና
የኔነት፣ እኔነት፣ በደሜ እንዲዘራ
የኔታ በኩርኩም፣ አባም በከዘራ
የለፉልኝ እኔ፣ ያደድኩት ልጃቸው
ዛሬ ወጉ ደርሶኝ አባት ሆኜላቸው . . .
ልጄን ከቀለም ቤት በኩራት ሰድጄ
አቡጊዳም እዳ፣
እኔነትም ባዳ፥
ሆኖበት ሲቸገር አይቼ ነድጄ! . . .
እ – ን – ደ – ተ – ብ – ከ – ነ – ከ – ን – ኩ
እ – ን – ደ – ተ – ብ – ሰ – ለ – ሰ – ል – ኩ
“ኤ ፎር አፕል” ብሎ ልጄ አፉን ፈታ
“ኤን ብቻ!” የምትሰብክ ከፊደል ገበታ
ግእዝ የማታዜም፣ ቅኔ የማትፈታ
ማንነት ‘ማይገዳት፣ ለ’ሱ የሌላት ቦታ
ሚስ ናት የሱ የኔታ
ሚስ ናት የሱ ጌታ::
_ // _
_ // © አብዲ ሰዒድ // _
@Balmbaras
@Getem
@getem
❤1
# ሞት_ቀደመኝ
፡
ሳታንኳኳ፣ ባጥር ዘላ
ከግቢዬ ዘው ብላ
ስለት ብጤ አንጠልጥላ፣
ግራ ቀኟን ስታማትር ...
ስትንሿከክ ብደርስባት
እላዯ ላይ ሰፈርኩባት።
፡
ገዳዬ ጋር ተቆላልፈን
ገጥመን ሳለ ፍልሚያ ትግል፣
(አፍታም ሳትቆይ ...)
ድፍት አለች -- መሬት ክንብል።
፡
(ወድቃ ሳያት ....)
መስሎኝ ነበር ለአንድ አፍታ
ትንፋሽ አጥሯት ራሷን ስታ።
(ፈራች መሰል ...)
ሳትመለስ በዛው ቀረች
ባልገድላትም በጄ ሞተች።
፡
ወየው! ወየው!
ወየው! ወየው!
ጉድ አረገኝ መልኣከ ሞት
(አዘናግቶ... አደናግሮ )
በማር ማንኪያ ጋተኝ ሃሞት።
፡
ራሱን ሳይገልጥ
ፍንጭ ሳይሰጥ፣
መጣሁ ሳይል ሰዓት ጠቅሶ
አጉል ሰራኝ ድንገት ደርሶ።
፡
ድንገት ውርድ
ነብሷን ውስድ።
ቋጠሮዬን መሬት ብትን
ሳልጠይቃት የላካትን።
-----------//------------
( በርናባስ ከበደ )
@getem
@getem
@getem
፡
ሳታንኳኳ፣ ባጥር ዘላ
ከግቢዬ ዘው ብላ
ስለት ብጤ አንጠልጥላ፣
ግራ ቀኟን ስታማትር ...
ስትንሿከክ ብደርስባት
እላዯ ላይ ሰፈርኩባት።
፡
ገዳዬ ጋር ተቆላልፈን
ገጥመን ሳለ ፍልሚያ ትግል፣
(አፍታም ሳትቆይ ...)
ድፍት አለች -- መሬት ክንብል።
፡
(ወድቃ ሳያት ....)
መስሎኝ ነበር ለአንድ አፍታ
ትንፋሽ አጥሯት ራሷን ስታ።
(ፈራች መሰል ...)
ሳትመለስ በዛው ቀረች
ባልገድላትም በጄ ሞተች።
፡
ወየው! ወየው!
ወየው! ወየው!
ጉድ አረገኝ መልኣከ ሞት
(አዘናግቶ... አደናግሮ )
በማር ማንኪያ ጋተኝ ሃሞት።
፡
ራሱን ሳይገልጥ
ፍንጭ ሳይሰጥ፣
መጣሁ ሳይል ሰዓት ጠቅሶ
አጉል ሰራኝ ድንገት ደርሶ።
፡
ድንገት ውርድ
ነብሷን ውስድ።
ቋጠሮዬን መሬት ብትን
ሳልጠይቃት የላካትን።
-----------//------------
( በርናባስ ከበደ )
@getem
@getem
@getem
ㅤ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇷🇪🇷🇪🇷
✍ ቴዲ አፍሮ (ዳህላክ)
በይ እንዲህ ነው ህልሜ ሲፈታ
ለህፃን ነፍስ ይራራል ጌታ
አትሙት ብሎት ያለ ሀጢያቱ
መዳን ሆነ ለመርከቢቱ
ቂም ማወቁ ልቡን አይረዳም
እስከሚደርስ ፍሬያችን ለአዳም
ካስተማርሺው ፍቅርን በጊዜ
አይሻለሁ ወይ በሱ ጊዜ
እንዳልከዳሽ ቃል አለብኝ እንዳልከዳሽ
እንዳልከዳሽ ቃል አለብኝ እንዳልከዳሽ
ግጥሞን ይላኩ ▼▼▼▼▼
@Getemsource
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈
@getem
@getem
✍ ቴዲ አፍሮ (ዳህላክ)
በይ እንዲህ ነው ህልሜ ሲፈታ
ለህፃን ነፍስ ይራራል ጌታ
አትሙት ብሎት ያለ ሀጢያቱ
መዳን ሆነ ለመርከቢቱ
ቂም ማወቁ ልቡን አይረዳም
እስከሚደርስ ፍሬያችን ለአዳም
ካስተማርሺው ፍቅርን በጊዜ
አይሻለሁ ወይ በሱ ጊዜ
እንዳልከዳሽ ቃል አለብኝ እንዳልከዳሽ
እንዳልከዳሽ ቃል አለብኝ እንዳልከዳሽ
ግጥሞን ይላኩ ▼▼▼▼▼
@Getemsource
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈
@getem
@getem
📖 በ — ቃ— ኝ (ብዬ ነበር)
እኔማ,
ሀዘንን ጉዳትን ህመም ስብራትን
ፍቅር ምናምንቴ ጂኒ ጃንካ ወሬ የላዉኩት እኔ
ባለመኖሬ ዉስጥ ደስታን ያተረፍኩኝ
ሀሴትን ያቀፍኩኝ
ሰላም ዉስጥ ነበርኩኝ
ግና,
አንድ ዘላለም ላይ
እድል ጀርባ ሰጥታኝ ለመኖር ብታጨኝ
ሳልፈልግ ፈልገህ 'ረፍቴን ሰረ'ከኝ
መኖርህን በግድ ኑረህ እየዉ አልከኝ
ዛሬ ግን ተለመን ይብቃህ በለኝ በቃኝ
እስትንፋስህ ስራ ኑሮህ ደግሞ ቀንበር
ሆኖብኛል እና
መኖርህን ወሰድ ኑሮዬን ግን ስጠኝ
ካለመኖሬ ዉስጥ ጎትተህ አዉጥተህ
ከፈቃዴ ዉጭ ኑር ብለህ እንዳልከኝ
አሁን አልኑርና ኑሮህን አንሳልኝ
መኖርህን እንካ መኖሬን ግን ስጠኝ::
©ናትናኤል ሰለሞን (ናት ሰን) (24/05/2010
@getem
@getem
@getem
እኔማ,
ሀዘንን ጉዳትን ህመም ስብራትን
ፍቅር ምናምንቴ ጂኒ ጃንካ ወሬ የላዉኩት እኔ
ባለመኖሬ ዉስጥ ደስታን ያተረፍኩኝ
ሀሴትን ያቀፍኩኝ
ሰላም ዉስጥ ነበርኩኝ
ግና,
አንድ ዘላለም ላይ
እድል ጀርባ ሰጥታኝ ለመኖር ብታጨኝ
ሳልፈልግ ፈልገህ 'ረፍቴን ሰረ'ከኝ
መኖርህን በግድ ኑረህ እየዉ አልከኝ
ዛሬ ግን ተለመን ይብቃህ በለኝ በቃኝ
እስትንፋስህ ስራ ኑሮህ ደግሞ ቀንበር
ሆኖብኛል እና
መኖርህን ወሰድ ኑሮዬን ግን ስጠኝ
ካለመኖሬ ዉስጥ ጎትተህ አዉጥተህ
ከፈቃዴ ዉጭ ኑር ብለህ እንዳልከኝ
አሁን አልኑርና ኑሮህን አንሳልኝ
መኖርህን እንካ መኖሬን ግን ስጠኝ::
©ናትናኤል ሰለሞን (ናት ሰን) (24/05/2010
@getem
@getem
@getem
ተራማጅ ህልም
(ናትናኤል ጌቱ)
በለምለም መስክ ላይ
አበባ 'ሚበትን ፥ ክንፋም ሰረገላ
እንደ ጠዋት ጸሀይ
ፈገግታ እያደለ ፥ ነፍስን የሚሞላ
አትመስይም?..ትመስያለሽ?...አላውቅም ...እኔንጃ!
ብቻ ገበያው ላይ
በሸማቾች መንገድ ፥ በሻጭ መነገጃ
ብርቱካን አነሳሽ...
ትርንጎም አነሳሽ
ብዙ ቀሚስ ለካሽ
ብዙ እቃዎች ነካሽ !
ይህን ሁሉ እያረግሽ
የሻጭ አይኖች በርተው ፥ አፍጠው ሲያዩሽም
ይደነቃሉ እንጂ ፥ አያስከፍሉሽም
.
ለምን ያስከፍሉሽ?
የጀነትን ታምር ማየት ፥ ምድርም ሁኖ ሰው ይጠማል
እውን መሀል የሚራመድ ፥ ህልም ማየት ያስገርማል
@getem
@getem
@lula_al_greeko
(ናትናኤል ጌቱ)
በለምለም መስክ ላይ
አበባ 'ሚበትን ፥ ክንፋም ሰረገላ
እንደ ጠዋት ጸሀይ
ፈገግታ እያደለ ፥ ነፍስን የሚሞላ
አትመስይም?..ትመስያለሽ?...አላውቅም ...እኔንጃ!
ብቻ ገበያው ላይ
በሸማቾች መንገድ ፥ በሻጭ መነገጃ
ብርቱካን አነሳሽ...
ትርንጎም አነሳሽ
ብዙ ቀሚስ ለካሽ
ብዙ እቃዎች ነካሽ !
ይህን ሁሉ እያረግሽ
የሻጭ አይኖች በርተው ፥ አፍጠው ሲያዩሽም
ይደነቃሉ እንጂ ፥ አያስከፍሉሽም
.
ለምን ያስከፍሉሽ?
የጀነትን ታምር ማየት ፥ ምድርም ሁኖ ሰው ይጠማል
እውን መሀል የሚራመድ ፥ ህልም ማየት ያስገርማል
@getem
@getem
@lula_al_greeko
#ወድሽ_ነበር_አለሁ !
፡
አሁን ደረስኩ ሲል ፥ ጓዙን አንጠልጥሎ
ቅድም ተብሎ ሊሸኝ ፥ ሊሄድ ተገንጥሎ፣
አሁን ከአሁን በፊት ፥ ከአፌ ላይ ቢበርም
በሚመጣው አሁን ፥ ሳልወድሽ አልቀርም።
------------------------//------------------------
( በርናባስ ከበደ )
@getem
@Getem
@getem
፡
አሁን ደረስኩ ሲል ፥ ጓዙን አንጠልጥሎ
ቅድም ተብሎ ሊሸኝ ፥ ሊሄድ ተገንጥሎ፣
አሁን ከአሁን በፊት ፥ ከአፌ ላይ ቢበርም
በሚመጣው አሁን ፥ ሳልወድሽ አልቀርም።
------------------------//------------------------
( በርናባስ ከበደ )
@getem
@Getem
@getem
አቤቱታ ለፈጣሪ
(ልዑል ሀይሌ)
.
ምን አቅም አለኝና
ከማሳህ ዘር ልምረጥ
ምን ጉልበትስ ኖሮኝ
ከተከልከው ችግኝ
ለኔ ሚሆን ልቁረጥ?
.
ይሄ ዘርህ ያምራል
ያንን ዘር ልንቀለው
እያልኩ ብፎክርም
እኔም ቅንጣት ዘር ነኝ
አንተ የተከልከውን ልቀጥፍም አልችልም
.
እስቲ ልጠይቅህ
ያ'ለሙ ገበሬ
የምድሩ ዘር ሁሉ ባንተ እጅ ነውና
የዘር አረም በቅሏል
ጎተራህ ሳይወድም ጣለው ንቀልና
.
አንተን ላዝህ ቀርቶ
ቀና ብዬ ላይህ ድፍረትም ባይኖረኝ
የዘራኸን ሁሉ እየተቋጠርን
የምናልቅ መስሎኝ
ያንተ ልፋት መና ከንቱ ሆኖ ታየኝ
.
እባክህ ፈጣሪ!
እባክህ ኤልሻዳይ
ዘር ሚባለውን
ከዓይምሯችን ጣለው
እኛ ፍጥረቶችህ ተዋደን እንድታይ!
.
እባክህ!
እባክህ!
.
እባክህ ፈጣሪ
በፈጠርካት ምድር ድንበር አበጅተን
የኔ ነው የኔ ነው ተባብለን አድረናል
ሁሉ ያንተ መሆኑን
ዘንግተን ከኖርን ብዙ ዓመት ሆኖናል
.
ትዕዛዝ አይሁንና
ከበረት ወጥተናል
ምናለ ብትመጣ ላፍታ ብትመልሰን
በምድርህ አይደል ወይ
ዘር እያማረጥን ምንጋጨው አርሰን
በተጋጨን ቁጥር
ምናመሸው ቀኑን
ምናነጋው ሌቱን አልቅሰን አልቅሰን
.
እባክህ!
እባክህ!
.
.
እባክህ አምላኬ
.
በባቢሎን ምክንያት
ሐጢያታችን በዝቶ
ቋንቋ ልሳናችን ለይተህ ቃኝተሃል
ግድ የለም አሁን ግን
ቋንቋችንን ቀማን
እንዳንደርስብህ ግንቡ ይሻልሃል
.
እባክህ!
እባክህ!
.
.
.
እባክህ ጌታ ሆይ
.
መጮሁ ደክሞናል
መጮህ አቅቶናል
መጣራት አቃተን
ተዋደዱ እንዳልከን
ተፋቀሩ እንዳልከን
መስማማቱን አጥተን
በአምሳልህ ተፈጥረን
አምሳልህን ሸጠን
ለዘር ቀለም ሰጥተን
.
እባክህ!
እባክህ!
.
.
.
እባክህ ፈጣሪ!
አንተን ልናከብር
የፈጠርክልን አንደበት ተዘጋ
አንተን ዘንግተናል
ውዳሴያችን ሁሉ
ዘሬ ዘሬ ሆኗል በነጋ በጠባ!
.
እባክህ!
እባክህ!
.
እባክህ ፈጣሪ
በፈጠርካት ምድር ድንበር አበጅተን
የኔ ነው የኔ ነው ተባብለን አድረናል
ሁሉ ያንተ መሆኑን
ዘንግተን ከኖርን ብዙ ዓመት ሆኖናል
.
እባክህ!
እባክህ!
.
አንተን ላዝህ ቀርቶ
ቀና ብዬ ላይህ ድፍረትም ባይኖረኝ
የዘራኸን ሁሉ እየተቋጠርን
የምናልቅ መስሎኝ
ያንተ ልፋት መና ከንቱ ሆኖ ታየኝ
.
እባክህ ፈጣሪ!
እባክህ ኤልሻዳይ
ዘር ሚባለውን
ከዓይምሯችን ጣለው
እኛ ፍጥረቶችህ ተዋደን እንድታይ!
20-10-10
(ልዑል ሀይሌ)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
(ልዑል ሀይሌ)
.
ምን አቅም አለኝና
ከማሳህ ዘር ልምረጥ
ምን ጉልበትስ ኖሮኝ
ከተከልከው ችግኝ
ለኔ ሚሆን ልቁረጥ?
.
ይሄ ዘርህ ያምራል
ያንን ዘር ልንቀለው
እያልኩ ብፎክርም
እኔም ቅንጣት ዘር ነኝ
አንተ የተከልከውን ልቀጥፍም አልችልም
.
እስቲ ልጠይቅህ
ያ'ለሙ ገበሬ
የምድሩ ዘር ሁሉ ባንተ እጅ ነውና
የዘር አረም በቅሏል
ጎተራህ ሳይወድም ጣለው ንቀልና
.
አንተን ላዝህ ቀርቶ
ቀና ብዬ ላይህ ድፍረትም ባይኖረኝ
የዘራኸን ሁሉ እየተቋጠርን
የምናልቅ መስሎኝ
ያንተ ልፋት መና ከንቱ ሆኖ ታየኝ
.
እባክህ ፈጣሪ!
እባክህ ኤልሻዳይ
ዘር ሚባለውን
ከዓይምሯችን ጣለው
እኛ ፍጥረቶችህ ተዋደን እንድታይ!
.
እባክህ!
እባክህ!
.
እባክህ ፈጣሪ
በፈጠርካት ምድር ድንበር አበጅተን
የኔ ነው የኔ ነው ተባብለን አድረናል
ሁሉ ያንተ መሆኑን
ዘንግተን ከኖርን ብዙ ዓመት ሆኖናል
.
ትዕዛዝ አይሁንና
ከበረት ወጥተናል
ምናለ ብትመጣ ላፍታ ብትመልሰን
በምድርህ አይደል ወይ
ዘር እያማረጥን ምንጋጨው አርሰን
በተጋጨን ቁጥር
ምናመሸው ቀኑን
ምናነጋው ሌቱን አልቅሰን አልቅሰን
.
እባክህ!
እባክህ!
.
.
እባክህ አምላኬ
.
በባቢሎን ምክንያት
ሐጢያታችን በዝቶ
ቋንቋ ልሳናችን ለይተህ ቃኝተሃል
ግድ የለም አሁን ግን
ቋንቋችንን ቀማን
እንዳንደርስብህ ግንቡ ይሻልሃል
.
እባክህ!
እባክህ!
.
.
.
እባክህ ጌታ ሆይ
.
መጮሁ ደክሞናል
መጮህ አቅቶናል
መጣራት አቃተን
ተዋደዱ እንዳልከን
ተፋቀሩ እንዳልከን
መስማማቱን አጥተን
በአምሳልህ ተፈጥረን
አምሳልህን ሸጠን
ለዘር ቀለም ሰጥተን
.
እባክህ!
እባክህ!
.
.
.
እባክህ ፈጣሪ!
አንተን ልናከብር
የፈጠርክልን አንደበት ተዘጋ
አንተን ዘንግተናል
ውዳሴያችን ሁሉ
ዘሬ ዘሬ ሆኗል በነጋ በጠባ!
.
እባክህ!
እባክህ!
.
እባክህ ፈጣሪ
በፈጠርካት ምድር ድንበር አበጅተን
የኔ ነው የኔ ነው ተባብለን አድረናል
ሁሉ ያንተ መሆኑን
ዘንግተን ከኖርን ብዙ ዓመት ሆኖናል
.
እባክህ!
እባክህ!
.
አንተን ላዝህ ቀርቶ
ቀና ብዬ ላይህ ድፍረትም ባይኖረኝ
የዘራኸን ሁሉ እየተቋጠርን
የምናልቅ መስሎኝ
ያንተ ልፋት መና ከንቱ ሆኖ ታየኝ
.
እባክህ ፈጣሪ!
እባክህ ኤልሻዳይ
ዘር ሚባለውን
ከዓይምሯችን ጣለው
እኛ ፍጥረቶችህ ተዋደን እንድታይ!
20-10-10
(ልዑል ሀይሌ)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ጥ – ሬ. . . !
“ዶሮ ብታልም ያው ጥሬዋን”
_ ብለህ ያልከኝ ጓዴ
በል እንካ ጥሬ ቃል
_ ከጥሬ ልቦና፣ ለጥሬው ዘመዴ . . .
*
ዶሮስ ጥሬ አለመች፣ ጥሬ ነው አለሟ ፣
ጥሬ ነው ህይወቷ፣ ጥሬ ነው ሰላሟ . . .
‘ምትከርመው በጥሬ
‘ምትኖረው ለጥሬ
አኗኗሯ ጥሬ
አሟሟቷም ጥሬ
ጥሬ… ጥሬ… ጥሬ…
እሷን መች ጠርጥሬ?! …
*
ይብላኝ እንጂ ለኔ፣ ይብላኝ እንጂ ላንተ !
በጥሬ ህልም ዓለም፣ ቀንህና ቀኔ ለተንከራተተ . . .
ተቃውሟችን ጥሬ
ድጋፋችን ጥሬ
ሽብራችን ጥሬ
ህዳሴያችን ጥሬ
ሃዘናችን ጥሬ
ደስታችንም ጥሬ
ጥሬ… ጥሬ… ጥሬ…
ብዙ ቀባጥሬ
“ልማት አሸብሬ” . . .
ሐይሌን አስደንብሬ . . .
እኔና አገሬን አጉል ከማጠፋ
ጥሬ እየጠረጠርኩ እስቲ ላንቀላፋ
አንተም ከጥሬህ ጋር ጥሬ ቀንህን ግፋ . . .
(© አብዲ ሰዒድ፣ ነሐሴ 2004)
@Balmbaras
@getem
@getem
“ዶሮ ብታልም ያው ጥሬዋን”
_ ብለህ ያልከኝ ጓዴ
በል እንካ ጥሬ ቃል
_ ከጥሬ ልቦና፣ ለጥሬው ዘመዴ . . .
*
ዶሮስ ጥሬ አለመች፣ ጥሬ ነው አለሟ ፣
ጥሬ ነው ህይወቷ፣ ጥሬ ነው ሰላሟ . . .
‘ምትከርመው በጥሬ
‘ምትኖረው ለጥሬ
አኗኗሯ ጥሬ
አሟሟቷም ጥሬ
ጥሬ… ጥሬ… ጥሬ…
እሷን መች ጠርጥሬ?! …
*
ይብላኝ እንጂ ለኔ፣ ይብላኝ እንጂ ላንተ !
በጥሬ ህልም ዓለም፣ ቀንህና ቀኔ ለተንከራተተ . . .
ተቃውሟችን ጥሬ
ድጋፋችን ጥሬ
ሽብራችን ጥሬ
ህዳሴያችን ጥሬ
ሃዘናችን ጥሬ
ደስታችንም ጥሬ
ጥሬ… ጥሬ… ጥሬ…
ብዙ ቀባጥሬ
“ልማት አሸብሬ” . . .
ሐይሌን አስደንብሬ . . .
እኔና አገሬን አጉል ከማጠፋ
ጥሬ እየጠረጠርኩ እስቲ ላንቀላፋ
አንተም ከጥሬህ ጋር ጥሬ ቀንህን ግፋ . . .
(© አብዲ ሰዒድ፣ ነሐሴ 2004)
@Balmbaras
@getem
@getem
"""የጦቢያ ባለሃብት"" !!!!!!
እርሻዬን ቀምቶ፣
ማጀቴን ደፋፍቶ ፣
ከቤቴ አስወጥቶ፣
ማረሻየን ሰብሮ፣ ሞፈሬን ቆስቁሶ፣
ጎተራዬን ንዶ፣ ጎጆዬን አፍርሶ፣
ቂጣዬን አንኩሮ፣ ኑሮዬን ከርችሞ፣
እንቁጭልህ ይላል፣
የማየውን እንጅ፣
የማያጎርሰኝን፣ ዳቦ ተሸክሞ።
((( ጃ ኖ )))
((( ሸጋ ጁምኣ ))
@balmbaras
@getem
@getem
እርሻዬን ቀምቶ፣
ማጀቴን ደፋፍቶ ፣
ከቤቴ አስወጥቶ፣
ማረሻየን ሰብሮ፣ ሞፈሬን ቆስቁሶ፣
ጎተራዬን ንዶ፣ ጎጆዬን አፍርሶ፣
ቂጣዬን አንኩሮ፣ ኑሮዬን ከርችሞ፣
እንቁጭልህ ይላል፣
የማየውን እንጅ፣
የማያጎርሰኝን፣ ዳቦ ተሸክሞ።
((( ጃ ኖ )))
((( ሸጋ ጁምኣ ))
@balmbaras
@getem
@getem
የመድረሳ ፍቅር
(ለሐሊማ)
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ. . .
የኡስታዝን ቁጣ ትንሽ ነፍሴ ፈርታ
ለማሃፈዝ ስጣጣር ሳፋቅድ ስፈታ…
ደግሞ ባንቺ ፍቅር ቀልቤ ሩኋን ስታ
ሰርቄ እያየሁሽ በኩርኩም ስመታ
ያደግኩብሽ ውዴ ናፍቆቴ ሐሊማ
የልጅነት ገዴ ነይ ድምጽሽን ልስማ…
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ኹሩፍ ስንለያይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…
ቁርአኑን ወጣሁት ጨረስኩት ሃፍዤ
አንቺን ለማስደሰት በፍቅርሽ ተይዤ
ታዲያ አሁን ዛሬ ትልቅ ሰው ተብዬ
በትልቆች መሃል በክብር ቁጭ ብዬ
ቁርአኑን ልቀራው በገለጽኩት ቁጥር
ጀነትን ያሳየኝ ቀናው የልጅ ፍቅር
ድቅን እያለብኝ ተቸገርኩ ሐሊማ
ለበይክ አለሁ በይኝ በይ ድምጽሽን ልስማ…
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…
ትዝ ይልሽ እንደሆን ያኔ ልጆች ሳለን
ሐራም ሐላል ሳንል በቅን አብረን ዘለን
አንቺም እጄን ይዘሽ እኔም አንቺን ይዤ
ቁርአኑን ስትወጭው እኔም ባንዴ ሃፍዤ
ቦርቀን ነበረ ለዱንያም ላኼራ
ዛሬ ድምጽሽ ጠፋ በይ ስሚኝ ስጣራ
የኒካው ቀለበት ተቀምጧል በአደራ …
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…
© አብዲ ሰ.
ማስታወሻ:
ከአረብኛ የተወሰዱና ምናልባት መድረሳ ላልተማረ ሰው ግር ይሉ እንደሁ
ብዬ ያሰብኳቸውን ቃላት ትርጓሚያቸው:-
መድረሳ: የቁርአን ትምህርት ቤት፡፡
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሳ፣ . . . የአረብኛ ፊደል ቆጠራ፡፡
ኡስታዝ… የቁርአን ወይም የሃይማኖታዊ ትምህርት አስተማሪ፡፡
ማሃፈዝ… በቃል ሸምድዶ መያዝ… ወይም በቃል ብቻ መውጣት፡፡
ኹሩፍ… የአረብኛ ፊደል ወይም ፊደል ቆጠራ፡፡
ለበይክ … አቤት.. አለሁ እንደማለት፡፡
ሐራም… የተከለለ… በሃይማኖት አስተምህሮት የማይፈቀድ፡፡
ሐላል… የተፈቀደ… ሊደረግ የሚቻል
((( ሸጋ ሸጊቱ ጁምኣ ))
@balmbaras
@getem
@getem
(ለሐሊማ)
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ. . .
የኡስታዝን ቁጣ ትንሽ ነፍሴ ፈርታ
ለማሃፈዝ ስጣጣር ሳፋቅድ ስፈታ…
ደግሞ ባንቺ ፍቅር ቀልቤ ሩኋን ስታ
ሰርቄ እያየሁሽ በኩርኩም ስመታ
ያደግኩብሽ ውዴ ናፍቆቴ ሐሊማ
የልጅነት ገዴ ነይ ድምጽሽን ልስማ…
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ኹሩፍ ስንለያይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…
ቁርአኑን ወጣሁት ጨረስኩት ሃፍዤ
አንቺን ለማስደሰት በፍቅርሽ ተይዤ
ታዲያ አሁን ዛሬ ትልቅ ሰው ተብዬ
በትልቆች መሃል በክብር ቁጭ ብዬ
ቁርአኑን ልቀራው በገለጽኩት ቁጥር
ጀነትን ያሳየኝ ቀናው የልጅ ፍቅር
ድቅን እያለብኝ ተቸገርኩ ሐሊማ
ለበይክ አለሁ በይኝ በይ ድምጽሽን ልስማ…
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…
ትዝ ይልሽ እንደሆን ያኔ ልጆች ሳለን
ሐራም ሐላል ሳንል በቅን አብረን ዘለን
አንቺም እጄን ይዘሽ እኔም አንቺን ይዤ
ቁርአኑን ስትወጭው እኔም ባንዴ ሃፍዤ
ቦርቀን ነበረ ለዱንያም ላኼራ
ዛሬ ድምጽሽ ጠፋ በይ ስሚኝ ስጣራ
የኒካው ቀለበት ተቀምጧል በአደራ …
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሣ . . .
ፊደላት ስንለይ ተቀምጠን መድረሳ
ልሳንና ቀለም ስንመጥን በአበሳ…
© አብዲ ሰ.
ማስታወሻ:
ከአረብኛ የተወሰዱና ምናልባት መድረሳ ላልተማረ ሰው ግር ይሉ እንደሁ
ብዬ ያሰብኳቸውን ቃላት ትርጓሚያቸው:-
መድረሳ: የቁርአን ትምህርት ቤት፡፡
አሊፍ፣ ባ፣ ታ፣ ሳ፣ . . . የአረብኛ ፊደል ቆጠራ፡፡
ኡስታዝ… የቁርአን ወይም የሃይማኖታዊ ትምህርት አስተማሪ፡፡
ማሃፈዝ… በቃል ሸምድዶ መያዝ… ወይም በቃል ብቻ መውጣት፡፡
ኹሩፍ… የአረብኛ ፊደል ወይም ፊደል ቆጠራ፡፡
ለበይክ … አቤት.. አለሁ እንደማለት፡፡
ሐራም… የተከለለ… በሃይማኖት አስተምህሮት የማይፈቀድ፡፡
ሐላል… የተፈቀደ… ሊደረግ የሚቻል
((( ሸጋ ሸጊቱ ጁምኣ ))
@balmbaras
@getem
@getem
እኔ ብቻ ቀረሁ
( #ካፒቴን ናትናኤል ጌቱ )
…
ስንት ሐመሩ "ሐ" ዎች
በሐመር መኪና ፥ ተንደላቀው ሲያልፉ
ስንት ፎሌው "ሀ" ዎች
በወርቃማ ዋንጫ ፥ ውስኪ ሲጨልፉ
ስንት ንጉስ "ኃ" ዎች
ከመሬት ተነስተው ፥ ዙፋኑን ሲወርሱ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
በድሮ ልብና
በድሮ ሽክና ፥ ተከብቤ እንደቆምኩ
ጠላ ትዝታሽን
በፎሌ ተግቼ ፥ እየተንገዳገድኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! እኔ ብቻ ተከዝኩ!!
ያውና! … ያውና !
አለምነሽ ካሳነሽ
እንደተሳፈሩት ፥ የድሮ መኪና
ጭሱ ቦለል ይላል ፥ የቤቴ ኩሽና
አንቺኮ የለሽም ፥ ቤቴ ምን ነክቶታል ?
ብቸኛው ርስቴን ፥ በቃ አቃጥለውታል !!
እኔ ብቻ ቀረሁ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ሰባራ ፍቅርሽን ፥ እንደተመረኮዝኩ
ስንት ንጉስ "ሰ" ዎች
ንጉሱ "ኃ" ዎችን ፥ ሊጥሉ ሲነሱ
ስንት እሳቱ "ሰ"ዎች
አመፅ ለማስነሳት ፥ እሳት ሲለኩሱ
ስንት አለሙ "ዓ" ዎች
በደስታ ሲሰክሩ ፥ ቡጊ ሲደንሱ
አንገቴን ደፍቼ ፥ ከልቤ እያነባሁ
እኔ ብቻ ከፋኝ ፥ እኔ ብቻ ባባሁ!
ካንዲት ተራ ወንበር ፥ ቂጤ ተዘፍዝፎ
ጨቡዴና አማረ ፥ ካስተረፉት ገንፎ
እጄን እየሰደድኩ
በጎዳናው መሀል
ሺዎች ሲቀየሩ እየተመለከትኩ
እንጃ ማን እንደሆን ሽቶ የረጫቸው
ስንት ሐመሯ "ሐ" ዎች ሸክላ ከንፈራቸው
ሊፒስቲክ ተቀብቶ
ጫላ ጩቤ ጥሎ ፥ ዲሞፍተር አንስቶ
አድጎ ተመንድጎ ፥ ማሙሽ ምግብ በልቶ
እኔ ብቻ ከፋኝ
ትውስታሽ ተጠጋኝ ፥ ትዝታሽ ደረሰ
እሽሩሩ ፍቅር
እንባዬ እንደ ካሮት ፥ ቁልቁል ገሰገሰ
እኔ ብቻ ቀረሁ
የቡሄ በአልን ፥ ድፎ ሳላስደፋ
ራሴው ተደፍቼ
ሙስሊም ወንድሞቼ
ተምሩ በቅቷቸው ፥ ታምር ሲመገቡ
መካን ሊያዩ ወተው ፥ ዱባይ ሲያንጃብቡ
የረመዳን ጦሜን ፥ በውሀ እያፈጠርኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ያውና ያውና
ፊደል በሚመስል ፥ የህይወት ጎዳና
እነ ጸሎቱ "ጸ" ፥ ለስግደት ተደፍተው
ስለታቸው ሰምሮ ፥ ጭፈራ ቤት ከፍተው
ስንት አይናማው "ዐ" ዎች ፥ ባንድ አይናቸው ጠቅሰው
ከቆንጆ ተጣብሰው ፥ ቆንጆ ልጅ ወለዱ
እኔ ብቻ ጎደልኩ ፥ ከደስታ መንገዱ
እኔ ብቻ ዋተትኩ
እኔ ብቻ አዘንኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ
ፊደል ከሚመስለው ፥ የህይወት ገበታ
ነይ ታገኚኛለሽ
የዛሬ ሺ አመታት ፥ ካስቀመጥሺኝ ቦታ
እኔ ብቻ ቀረሁ…
@getemsource
@getem
@getem
( #ካፒቴን ናትናኤል ጌቱ )
…
ስንት ሐመሩ "ሐ" ዎች
በሐመር መኪና ፥ ተንደላቀው ሲያልፉ
ስንት ፎሌው "ሀ" ዎች
በወርቃማ ዋንጫ ፥ ውስኪ ሲጨልፉ
ስንት ንጉስ "ኃ" ዎች
ከመሬት ተነስተው ፥ ዙፋኑን ሲወርሱ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
በድሮ ልብና
በድሮ ሽክና ፥ ተከብቤ እንደቆምኩ
ጠላ ትዝታሽን
በፎሌ ተግቼ ፥ እየተንገዳገድኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ! እኔ ብቻ ተከዝኩ!!
ያውና! … ያውና !
አለምነሽ ካሳነሽ
እንደተሳፈሩት ፥ የድሮ መኪና
ጭሱ ቦለል ይላል ፥ የቤቴ ኩሽና
አንቺኮ የለሽም ፥ ቤቴ ምን ነክቶታል ?
ብቸኛው ርስቴን ፥ በቃ አቃጥለውታል !!
እኔ ብቻ ቀረሁ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ሰባራ ፍቅርሽን ፥ እንደተመረኮዝኩ
ስንት ንጉስ "ሰ" ዎች
ንጉሱ "ኃ" ዎችን ፥ ሊጥሉ ሲነሱ
ስንት እሳቱ "ሰ"ዎች
አመፅ ለማስነሳት ፥ እሳት ሲለኩሱ
ስንት አለሙ "ዓ" ዎች
በደስታ ሲሰክሩ ፥ ቡጊ ሲደንሱ
አንገቴን ደፍቼ ፥ ከልቤ እያነባሁ
እኔ ብቻ ከፋኝ ፥ እኔ ብቻ ባባሁ!
ካንዲት ተራ ወንበር ፥ ቂጤ ተዘፍዝፎ
ጨቡዴና አማረ ፥ ካስተረፉት ገንፎ
እጄን እየሰደድኩ
በጎዳናው መሀል
ሺዎች ሲቀየሩ እየተመለከትኩ
እንጃ ማን እንደሆን ሽቶ የረጫቸው
ስንት ሐመሯ "ሐ" ዎች ሸክላ ከንፈራቸው
ሊፒስቲክ ተቀብቶ
ጫላ ጩቤ ጥሎ ፥ ዲሞፍተር አንስቶ
አድጎ ተመንድጎ ፥ ማሙሽ ምግብ በልቶ
እኔ ብቻ ከፋኝ
ትውስታሽ ተጠጋኝ ፥ ትዝታሽ ደረሰ
እሽሩሩ ፍቅር
እንባዬ እንደ ካሮት ፥ ቁልቁል ገሰገሰ
እኔ ብቻ ቀረሁ
የቡሄ በአልን ፥ ድፎ ሳላስደፋ
ራሴው ተደፍቼ
ሙስሊም ወንድሞቼ
ተምሩ በቅቷቸው ፥ ታምር ሲመገቡ
መካን ሊያዩ ወተው ፥ ዱባይ ሲያንጃብቡ
የረመዳን ጦሜን ፥ በውሀ እያፈጠርኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ ፥ እኔ ብቻ ተከዝኩ
ያውና ያውና
ፊደል በሚመስል ፥ የህይወት ጎዳና
እነ ጸሎቱ "ጸ" ፥ ለስግደት ተደፍተው
ስለታቸው ሰምሮ ፥ ጭፈራ ቤት ከፍተው
ስንት አይናማው "ዐ" ዎች ፥ ባንድ አይናቸው ጠቅሰው
ከቆንጆ ተጣብሰው ፥ ቆንጆ ልጅ ወለዱ
እኔ ብቻ ጎደልኩ ፥ ከደስታ መንገዱ
እኔ ብቻ ዋተትኩ
እኔ ብቻ አዘንኩ
እኔ ብቻ ቀረሁ
ፊደል ከሚመስለው ፥ የህይወት ገበታ
ነይ ታገኚኛለሽ
የዛሬ ሺ አመታት ፥ ካስቀመጥሺኝ ቦታ
እኔ ብቻ ቀረሁ…
@getemsource
@getem
@getem
ዜብራን ረገጥነው!!!!!
ዜብራ ቡራቡሬ፣ መልኩን አሳምሮ፣
በሽንቅጥ ወገቡ፣ አምሮ ተገሽሮ፣
ቁልቁል እያባጨን፣
በሞንዳላ ጭኑ፣ ከላይ ተከምሮ፣
ሁሌም ይለን ነበር፣
"መረጋገጥ ነበር፣ ይህን ሁሉ ዶሮ።"
ግና፣
መንገድ አያመጣው፣ አይስበው አያጣ፣
እኛ ያገር ዶሮች፣
ዛሬ ተሳክቶልን፣ ሽርሽር ስንወጣ፣
ዜብራ አባ ፎካሪው፣
ድንገት መንገድ ገብቶ፣
ያን ሁሉ ሽለላ፣ ቀረርቶ ዘንግቶ፣
ዶሮ ረጋገጠው፣ መንገድ ላይ ተኝቶ።
ጉድ እኮ ነው!!!!!
በቀረርቶ ጩኸት፣
በረጋጭ ፉከራ፣ እረግጣለሁ ያለ፣
አይ ቅሌት!!!!!!
ርጋጩ ረግጦት ፣ ሲረጋገጥ ዋለ!!!!!!!!!!
((( ጃ ኖ )))
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!!!!
@balmbaras
@getem
@getem
ዜብራ ቡራቡሬ፣ መልኩን አሳምሮ፣
በሽንቅጥ ወገቡ፣ አምሮ ተገሽሮ፣
ቁልቁል እያባጨን፣
በሞንዳላ ጭኑ፣ ከላይ ተከምሮ፣
ሁሌም ይለን ነበር፣
"መረጋገጥ ነበር፣ ይህን ሁሉ ዶሮ።"
ግና፣
መንገድ አያመጣው፣ አይስበው አያጣ፣
እኛ ያገር ዶሮች፣
ዛሬ ተሳክቶልን፣ ሽርሽር ስንወጣ፣
ዜብራ አባ ፎካሪው፣
ድንገት መንገድ ገብቶ፣
ያን ሁሉ ሽለላ፣ ቀረርቶ ዘንግቶ፣
ዶሮ ረጋገጠው፣ መንገድ ላይ ተኝቶ።
ጉድ እኮ ነው!!!!!
በቀረርቶ ጩኸት፣
በረጋጭ ፉከራ፣ እረግጣለሁ ያለ፣
አይ ቅሌት!!!!!!
ርጋጩ ረግጦት ፣ ሲረጋገጥ ዋለ!!!!!!!!!!
((( ጃ ኖ )))
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!!!!
@balmbaras
@getem
@getem
👱እኔ ሳነብልሽ👱♀
👦👧👨👱♀👱👩👴👵
ፀሐይ ማቃጠልዎን ትታ፡
ታዳምጠኛለች ሁሉንም እረስታ፡
እኔ ሳነብልሽ እሚሄዱት ይቆማሉ፡
የጠወለጉ አበባዎች መልሰው ይፈካሉ፡
ያጐነበሱ ዘፎች ቀና ቀና ይላሉ፡
ወፎች ሊሰሙኝ ተሰብስበው ይመጣሉ።
እኔ ሳነብልሽ
በልጅነት አፌ በሚንኮላተፈው፡
ሁሉም ነው የሚሰማኝ ማንም ሳይሰለቸው፡
ውዴ እኔ ለ አንቺ ሳነብ፡
ሊያዳምጡኝ ዝሆኖች ቁጭ ይላሉ፡
ኤሊዎች ሊሰሙኝ ፈጥነው ይመጣሉ፡
ወንዝ፣ፋፎቴዎች ቃላያት በሙሉ፡
እኔ ሳነብልሽ ለአፍታ ፀጥ ይላሉ።
📝📝📝📝📝📝📝📝
ፊሊሞን የማርያም ልጅ
22/10/2010
@getem
@getem
@itsmefilimon
👦👧👨👱♀👱👩👴👵
ፀሐይ ማቃጠልዎን ትታ፡
ታዳምጠኛለች ሁሉንም እረስታ፡
እኔ ሳነብልሽ እሚሄዱት ይቆማሉ፡
የጠወለጉ አበባዎች መልሰው ይፈካሉ፡
ያጐነበሱ ዘፎች ቀና ቀና ይላሉ፡
ወፎች ሊሰሙኝ ተሰብስበው ይመጣሉ።
እኔ ሳነብልሽ
በልጅነት አፌ በሚንኮላተፈው፡
ሁሉም ነው የሚሰማኝ ማንም ሳይሰለቸው፡
ውዴ እኔ ለ አንቺ ሳነብ፡
ሊያዳምጡኝ ዝሆኖች ቁጭ ይላሉ፡
ኤሊዎች ሊሰሙኝ ፈጥነው ይመጣሉ፡
ወንዝ፣ፋፎቴዎች ቃላያት በሙሉ፡
እኔ ሳነብልሽ ለአፍታ ፀጥ ይላሉ።
📝📝📝📝📝📝📝📝
ፊሊሞን የማርያም ልጅ
22/10/2010
@getem
@getem
@itsmefilimon
👍1
✍...እመኚኝ !!
:
ነይ ግቢ በሞቴ
እቤት ማንም የለም የለችም እናቴ
እመኚኝ ግዴለም ምንም አናደርግም
ወደ ውስጥ ገብተሽ በሩን ብዘጋውም
አንድ ላይ ተቀምጠን አብረን ብናወጋም
ከንፈርሽን ልስም ወዳንቺ ብጠጋም
ብስምሽም እንኳን ስጋት እንዳገባሽ
ምንም አናደርግም
.
..
በፀጉሮችሽ መሃል ጣቴን ባንሸራሽር
ጠረንሽን ቢሸተኝ ገብቼ አንገትሽ ስር
እጄ ይይዘው አጥቶ ጡትሽን ቢነካካ
እየጨባበጠ መጠኑን ቢለካ
እንዳትጠረጥሪኝ
ለሌላ እንዳይመስልሽ ውዴ ሙች እመኚኝ
.
..
በዚህ ሁሉ መሃል በስሜት ገንፍዬ
ልብስሽን ባወልቅም ልብሴን ወዲያ ጥዬ
እርቃንሽን ሆነሽ እርቃኔንም ሆኜ
አልጋው ላይ ብጥልሽ በክንዴ ዘግኜ
በሚገርም ሁኔታ ፍቅር ብንሰራም
እመኚኝ አለሜ እኔ ልሙትልሽ ምንም
አናደርግም
------------//-----------
(ምንጭ
ግጥምና ገጣሚያን ማህደር)
.
:
@getem
@getem
@getem
:
ነይ ግቢ በሞቴ
እቤት ማንም የለም የለችም እናቴ
እመኚኝ ግዴለም ምንም አናደርግም
ወደ ውስጥ ገብተሽ በሩን ብዘጋውም
አንድ ላይ ተቀምጠን አብረን ብናወጋም
ከንፈርሽን ልስም ወዳንቺ ብጠጋም
ብስምሽም እንኳን ስጋት እንዳገባሽ
ምንም አናደርግም
.
..
በፀጉሮችሽ መሃል ጣቴን ባንሸራሽር
ጠረንሽን ቢሸተኝ ገብቼ አንገትሽ ስር
እጄ ይይዘው አጥቶ ጡትሽን ቢነካካ
እየጨባበጠ መጠኑን ቢለካ
እንዳትጠረጥሪኝ
ለሌላ እንዳይመስልሽ ውዴ ሙች እመኚኝ
.
..
በዚህ ሁሉ መሃል በስሜት ገንፍዬ
ልብስሽን ባወልቅም ልብሴን ወዲያ ጥዬ
እርቃንሽን ሆነሽ እርቃኔንም ሆኜ
አልጋው ላይ ብጥልሽ በክንዴ ዘግኜ
በሚገርም ሁኔታ ፍቅር ብንሰራም
እመኚኝ አለሜ እኔ ልሙትልሽ ምንም
አናደርግም
------------//-----------
(ምንጭ
ግጥምና ገጣሚያን ማህደር)
.
:
@getem
@getem
@getem
❤1
////-----//////
ፈጣሪ ነው እንጂ ፣ ሰው አይፈርድም በሰው
ብሎ ሲያንጎራጉር...
ሰዎች ፈርደውበት የተበደለ ሰው
እኔ ግን እላለሁ!
የሰው ልጅ ነው እንጂ ፣ አምላክ ፍርድ አያውቅም
በበደሎች ሁሉ...
የማይሸነፍ ነው ፣ የቸርነቱ አቅም፡፡
፡፡፡፡
ከሐጢያቶች ሁሉ ፣ ምህረቱ ያይላል
እኛ "ፍረድ" ስንል ፣ እርሱ "ይቅር" ይላል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
አናም እኔ ለኔ...
የማንጎራጉረው ፣ አንድ ዘፈን አለኝ
ፍርዱ ቢለያይም...
ይቅር ብሎ ማለፍ ፣ ፍርድ ነው መሠለኝ!"
ምንጭ፦የቴሌግራም ግጥም ምሽት
አቤ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ፈጣሪ ነው እንጂ ፣ ሰው አይፈርድም በሰው
ብሎ ሲያንጎራጉር...
ሰዎች ፈርደውበት የተበደለ ሰው
እኔ ግን እላለሁ!
የሰው ልጅ ነው እንጂ ፣ አምላክ ፍርድ አያውቅም
በበደሎች ሁሉ...
የማይሸነፍ ነው ፣ የቸርነቱ አቅም፡፡
፡፡፡፡
ከሐጢያቶች ሁሉ ፣ ምህረቱ ያይላል
እኛ "ፍረድ" ስንል ፣ እርሱ "ይቅር" ይላል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
አናም እኔ ለኔ...
የማንጎራጉረው ፣ አንድ ዘፈን አለኝ
ፍርዱ ቢለያይም...
ይቅር ብሎ ማለፍ ፣ ፍርድ ነው መሠለኝ!"
ምንጭ፦የቴሌግራም ግጥም ምሽት
አቤ
@getem
@getem
@lula_al_greeko