ግጥም ብቻ 📘
64.2K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
የከፍታ ቅኔ!!!!!!!


እንደዋልያ እግሮች፤ ፀንቶልኝ ጉልበቴ፤
ይኸው ደግሞ ዛሬ፤
ቆንጥሩን ጉድባውን ዳገቱን ወጥቼ፤
በተራራው ጫፍ ላይ፤
ከፍ ብዬ ስሄድ፤
ቁልቁል ተሸቀንጥሮ፤ወደቀ ጠላቴ!!!"""
Ameeeeeennnn

((ጃኖ ))

@balmbaras
@getem
@getem
"ለፍቅር ብተኛት ለጠብ አረገዘች"
ሆነና ነገሩ
በነጭ እርግብ ፋንታ ቦምቡን ወረወሩ
የእፉኝት ልጅ ሁሉ ተስፋ ቢስ ደረመን
ገደልናቸዉ ቢልም አንጠፋም ደህና ነን
ከመኖርም በላይ ነገን የሚያሳየን
ባንድ የተገመደ ትልቅ ፍቅር አለን።

(ሰለሞን ሰሃለ)

@getem
@getem
‘’ ኢትዩጵያዬ ‘’
እንኳን ሰው ፣ ተደስቶ ተሽሞንሙኖ ሳር ቅጠሉ
ተከትቦ ተጠርዞ ፣ መሪ ቃሉ
ከመደመር መብዛት ፣ ከመብዛት አንድነት
ካንድነት መዋደድ ፣ ከመዋደድ እድገት
ያለን ህዝብ ለመግታት
ምን ሚሉት ቂልነት ፣ ወገን ላይ ማፈንዳት?
እናት እህት መጉዳት?

ይህን የሚደግፍ ፣ ካለ በየቤቱ
ህሊና የሌለው ፣ የሆነ ነው ከንቱ
ይልቅ ሳይረፍድበት ፣ ይደመር ከጀማው
የፍቅር ስንኝ ነው ከኛ የሚሰማው
የማያልቅ ይቅርታ ከ አብይ ሚፈልቀው
መደመር ብቻ ነው
ኢትዩጵያዊነት ብቻ
ስሜት የሚሰጠው
ፍቅርን የሚያበዛው።

#አሸናፊ ገብሬ ከጅማ ዩኒቨርስቲ

@getem
@getem
#መደመር_ቅኔ_ነዉ !! ((1)) "
-
( ምንተስኖት ዋቆ)
-
ይነጋል ታያለሽ ፣
ብዬ የገጠምኩልሽ ፣
የሶስት ሺ አመት : ታላቋ ወይዘሮ ፣
ብርሀን ወጣልሽ : ፅልመት ተዘርሮ ።
ዛሬ ላይ ቢነጋም : ከመቼዉም ማልዶ ፣
# ለማ አንድነትሽ : # አብይሽን ወልዶ ።
-
-
( # 2010_ዴቻ )

ETHIOPIAN

@getem
@getem
፧፧፧ እስቲ በመሰንቆ ቅኔ እንዝረፍ፦
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፦ ያዝ እንግዲህ ፦፦፦፦
የቅጠሉ ሽታ ፥ እጅግ አፍኖኛል
ይሄንን ሺፈራው ፥ ብነቅል ይሻለኛል
ተወዲህ ሲዳማ ፥ ተወዲያ ጋምጎፋ
በሞሪንጋ ሽታ ፥ ቤታችን ከረፋ ።



አይ አባ ሀይለ ማርያም ፥ ጭቁኑ የግዜር ሰው
መንበሩ ለብልቦት ፥ ሆዴን አላወሰው
ይሻል ነበር ወንጌል ፥ እንደልማዳችን
ውርስ አስቀጥል ብለው ፥ወጡ ተልባችን ።



ለቆረሱት ስጋ ፥ ላፈሰሱት ጠጅ
ከፋዩ አንተ ነህ ፥ በርትተህ ስራ'ጅ
ትነዳለህ አሉ ፥ ተቀምጠህ ጋቢና
ስንቱ ወጣት ቆሞ ፥ ቀርቶ በጎዳና ።



ለማ ለማ ሲሉኝ ፥ አረሙ መስሎኛል
ለካስ ጤናዳም ነው ፥ተሩቁ ታይቶኛል
ስንቱን ጂኒ ሁላ ፥ ያስላቅቃል አሉ
አባይ እረገፈ ፥ እንደሳር ቅጠሉ ።



ታደሰልኝ ሀይሌ ፥ ካሱም እንደ ካሳ
መርገም ቤቴ ቀርቶ ፥ በረከት ተረሳ
ጳጳስ ቄስ አልጠፋ ፥በሀገር በቤቱ
ስብሃት እያሉ ፥ምነው የማይፈቱ ።



አቢይ አቢይ ቢሉ ፥ ያው ጦሙን ነው ብዬ
ሰውም አቢይ አለው ፥ኸረ እናንተ ሆዬ
በመንበር ቢሆኑ ፥ በመድረክ ቢቆሙ
ቁርጥ የመሰለኝ ፥ ድስትና ግጣሙ
ሲናዳነ ኖሮ ፥ ስንቱ እንከፍ ጋሬጣ
ይገዛኛል ያልኩት ፥ አባት ሆኖኝ መጣ
ልክ እንደብሉያት ፥ እንደመፃህፍት
ክፋ መጣ ብዬ ፥ ስጀምር ትንቢት
ጣድቅ ንጉስ ታየኝ ተወደ ናዝሬት ።



እኔ እጣን አለበኝ ፥ ለፂዮን ታቦት
ልቦና ይስጥህ ብዬ ፥ የተሳልኩበት
ወይ እንደ ገሞራ ፥ ያሙቅህ በሳት ።



እንዴት አድሯል አባይ ፥ያፈለገ ጣና
ገዴን ያመጣልኝ ፥ አርጎ ባለዝና
በኣባይ አናት ላይ ፥ ባህር ዳር ደመቀ
ዛሬ ያኮራኝ ገባ ፥ እንዳልተሳቀቀ ።



ወየሁ መጣ ፍቅሬ ፥ የብዕሩ ጌታ
ፍቅር የድሬ ሰው ፥ የቶሎሳ ሽታ
ቲያስተሳስር ያድራል ፥ ሀበሻን ባንዳፍታ
ፍቅር ጠፋ ብዬ ፥ ባገር በመንደሩ
ቀለም ይዞ መጣ ፥ ፍቅሬ ተነክብሩ
ይቀባኝ ጀመረ ፥ ያረሰርሰኝ
ሀገሬን ሀገሬን ፥ ሀገር አሰኘኝ
በመስተፋቅሩ ፥ አስለፈለፈኝ ።



በሉ ፍቷትማ ፦
እነባለ እውቀት ፥ እነ በሳሰሉ
እንዳሻው ይሆናል ፥ ብላችሗል አሉ
ሰው ታልዘለለበት ፥ እንዳሻው ባገሩ
ሀገሬ ማለቱ ፥ ምንድነው ሚስጥሩ ።


አልያም ተርጉሟት ፦
እነ ወሬ አደር ፥ እነ ነውር ጌጡ
እንዳሻው ይጥፉል ፥ ብላቹ አቃልጡ
እኔ እንደው ብያለሁ ፥ ዐለሙ ይፍረደኝ
እንኳን በናት ምድሬ ፥ የትም እንዳሻው ነኝ ።





14-10-10
( እንዳሻው አለማየሁ ፦ ፦ ።)

@getem
@getem
#ወረት_ብቻ_እንዳይሆን

ወደ ገነት ስትሮጥ ፥ ቅን ነብሴን ለማፅደቅ
ቀኜን ቀን ቢጥላት ፥ ተቆርጣ ብትወድቅ፣
ወረት ብቻ እንዳይሆን ፥ ነገረ ሥራዬ
እግሬን ተሸከምኳት ፥ እኔም በተራዬ።
-----------><----------
( በርናባስ ከበደ )

@getem_sourcebot
@getem
@getem
ቢኒ የቅዱስ ሚካኤል ልጅ

ዶ= ዶግ አመድ አድርጎት የጅቦቹን ሴራ
ክ= ክብር አጎናፅፎ የእማማን አደራ
ተ= ተገኘቷል ሙሴያችን ፍቅር ለሀገራችን
ር= ርስት ሆኖ ሊቆየን ውሎ ከልባችን
አ= አብሮነት አዋቂ በፍቅር ማራኪ
ብ= ብርሃን ፈንጣቂ አንድነት ሰባኪ
ይ= ይሁን ብሎ አማኝ
አ= አይሰስት ቸር አዳኝ
ህ= ህያው አስተሳሰብ ብሄራዊ አርማ
መ= መድሃኒቷ የሆነ ከልብ የሀገር ካስማ
ድ= ድንቅ ሰው ተገኝቷል ዛሬ ደስ ይበልሽ ኩሪልን እማማ


እናመሰግናለን ታላቁ መሪያችን
ታሪካዊ ቀን 16/10/2009
ለዚች ታሪካዊ ቀን በመብቃታችን እድለኞች ነን ለሞቱት ወገኖቻችን ነፍስ ይማርልን🙏🙏🙏
ለተጎዱትም ምህረቱን ስጥልን 🙏🙏🙏

@getem
@getem
@getem
👍3
ነቢል መሐመድ (ዘ፡ፓሳህ ፡!፡)

ከምድረ ሐበሻ ሀገር ፍቅርን ሊሰብኩ
ቢሹ ፣
በቦምብ አድርገው ፈጇቸው አገርን ከህብረት ሊያሸሹ ፣
ቢሸሽ ወዴት ሰው ከራሱ ፣
ኀላም ፊቱም ያለው ከ'ርሱ ፣
የማንነት ጥንቱም ፊቱ ፣
እኔነት ነው እርሱነቱ ፡፡

መታሰቢያነቱ ፦ ክቡር ጠ/ሚኒስቴር
ዶ/ር አብይ አህመድን ለምንደግፍ ሁሉ እርሱ ውስጥ እኛነታችን አለ ላልን ሁላ ፡፡

@getem
@getem
ምስክሬ ናቸው

በንፋስ ሽውታ የመጣው ናፍቆትሽ፣
በልቤ ከትቤ ያነገስኩት ፍቅርሽ፣
በመልህቅ ሸብቦ ኣስሮ የያዘኝ ልብሽ፣
በፍላፃ የወጉኝ ክዋክብት አይኖችሽ፣
ምስክር ተደርገው ከሸንጎ ይቅረቡ፣
ሀቄን ያስረዱልኝ ሳይንተባተቡ፣
በውስጤ ያለውን እውነት ስለሚያውቁ፣
አልሻም ሌላ ኣካል እነርሱ ይጠየቁ።

29–09–2010 አብርሽ(ሀዩ)

@getem
@getem
የኔ መንገድ!!!!!


ከባርነት ጫጉላ፤
ከግርድና ማጀት፤
ና ውጣ ተብየ፤
የተጠራሁበት፤
የተቀባሁበት፤
የተመረጥኩበት፤
የልቤን ከነአን፤
በነፍሴ ሰሌዳ፤ በደም ቀለም ፅፌ፤
እንደ ኢያሱ ካሌብ፤
ከነአንን ወረስኳት፤
የሞት ውሽንፍሩን፤ ባህሩን አልፌ።


ፈርኦን ሞኝ ነው፤
ተከትሎኝ ነበር፤
በግዞት ማድጋ ፤
መልሶ ሊግተኝ፤ የምሬት ሰፍነጉን፤
ተመለስ እያለ፤
እያግተለተለ፤
የፉከራ ሰልፉን፤ የትእቢት ፈረሱን።


እናም እንደዚህ ነው፤
በሰው መንገድ ቀንተው፤
በሄድኩበት ዱካ፤
እንሂድ እናስቀረው፤ ብለው የፎከሩ፤
ባህሩ ተከፍሎ፤
መልካውን ስሻገር፤
መንገዱ በላቸው፤ ውሃ ሆነው ቀሩ።


ይኸው በኔ ቀዬ፤
የሰው መንገድ ጥጉ፤
ለነሱም የሚሆን እየመሰላቸው፤
በሰው መንገድ ቀንተው፤
ከመንገድ ሊያስቀሩኝ፤
መንገድ የጀመሩ፤
እንደ ፈርኦን ጦር፤ ቀይ ባህር ዋጣቸው።

((( ጃ ኖ )))

@Balmbaras
@getem
@getem
#ከመለስ የተላከ ደብዳቤ


እንደው ዶክተር አብይ
ህዝቡን ምን አረከው ~ ምንድን አስነካኸው

ራዕዬን ትቶ
ከኔ በላይ ላንተ ~ እንዲህ የሰገደው??

ከሁሉ ከሁሉ
እኔን የገረመኝ
የሲኦሉ ጌታ ~ ሰይጣን እንኳ ባቅሙ

በመደመር ወንጌል
የፍቅር ደብዳቤ
ማመልከቻ ፅፎ
ለእግዜር በመላኩ
መልአክታት ሁሉ ~ ባንተ ተገረሙ፡፡

ምን ሰይጣኑ ብቻ
ሲኦልም ቃጠሎው ~ በፍቅር ቀዝቅዞ

ሰላም የበዛበት
መዝናኛ ይመስላል ~ ባንተ ድርጊት ፈዞ፡፡

እንደው ግን በሞቴ
ሀምሳ ሎሚ ላንዱ ~ መጫኛ ሸክም ነው

የሚለውን ተረት
የሀገሬን እውነት ~ እንዴት እረሳኸው??

የሚል ፅሁፍ ፅፌ
በመንፈሴ ብልክ ~ እንድተነትነው

አንተ ግን ብልጥ ነህ
ክፍልፍሉን ሁላ
ደምረህ ደምረህ ~ ወደ አንድ አመጣኸው፡

እና ይገርምሀል
እኔ በሰራሁት ግፍና መከራ ~ ይደሰታል ያልኩት

ሰይጣንም እንደ ሰው
ሙድ እዬያዘብኝ
አያጅቦ እንዴት ነህ ~ ይለኛል ቀን ከሌት፡፡
፡<
እናም እባክህን
እዚህ እንኳ ልረፍ ~ ፍቅርህን ላክልኝ

እዚያም ላሉ ጅቦች
መደመር ይበጃል ~ ብለህ ንገርልኝ፡፡

# መለስ ነኝ ከሲኦል
ሚኪያስ

@getem
@getem
ትንሽ ቁረጭና!!!!!!!


አንች እናት!!!!!
ውብ እናት!!!!!!
ልስጥህ አትበይኝ፣
ውሰድ አትበይኝ፣ ርስትሽ ይቅርብኝ፣
ሰርክ ከሚያበራው፣
ከብርሃን ፈገግታሽ፣
ከሩህሩህ አንጀትሽ፣ መቼም አይበልጥብኝ።
ከብቱን ላሙን ተይው፣
አልፈልግም እኔ፣
ያንችን ጠገራ ብር፣ ወርቅ ማርትሬዛ፣
እምዬ ልንገርሽ፣
ክስካሽ ፈረንካ፣
እንጀራ ነው እንጅ፣ደግነት አይገዛ።


እናም አንች ሸጋ፣
እናም አንች እናቴ፣
የሆዴን ልንገርሽ፣
ቤትሽን የሞላው፣ ጠገራው ርስቱ፣
ጋሻ የገመሰው፣ ከብትና መሬቱ፣
ውሰድ አትበይኝ
ከቶ ምን ሊሆነኝ፣ ኮተታ ኮተቱ፣
እረ ምን ሊረባኝ፣ ምን ሊሆነኝና፣
ብሩንም እርስቱን፣
እኔ አልፈልገውም፣ ይቅርብኝ ተይና፣
ካንጀትሽ አካፍሊኝ፣ትንሽ ቁረጭና።

((( ጃ ኖ )))

ሸጋ ቀን !!!


@balmbaras
@getem
@getem
👍1
:
"ተያይዞ ቢቆም ፥ ሁሉም ለአመሉ
አጥር አይምሰልሽ ፥ የከበበሽ ሁሉ!"
。。。
በረከት በላይነህ©

@getem
@getem
@getem
ሞሪንጋ!!!!


የፈረንጅ ሞሪንጋ ፤
ስንት አይነት በሽታ ፤ ሰርክ እየፈወሰ ፤
የኛ አገር ሽፈራው ፤
በጠራራ ጸሃይ እልፍ ሰው ጨረሰ ።
ብለን ተቀኝተን ፤
ነግረን ሳናበቃ ፤ በጉባኤ ፊት ፤
ያገሬ ገበሮች ፤
ይህንን ሺፈራው ፤
በዶማ ቆፍረው፤ መንግለው ጣሉት ።

(( ጃ ኖ ))

@Balmbaras
@getem
@getem
አቤቱ . . .
(አሌክስ አብርሃም)

ካገር ማድጋችን ውስጥ
የጥላቻ እርሾ …የቂም ቡኮ ይፍሰስ
ኑሮ የደቆሰው ደሳሳ ጎጇችን በባርኮት ይታደስ
እንደ አደይ ድምቀት ፈገግታችን ይፍካ
የተራቆተ ኪስ ይሙላ በፍራንካ
የታመሙ ነፍሳት … በገፍ ይፈወሱ
የጤና አንፋሳት በምድራችን ፊት ላይ ዘላለም ይንፈሱ
የኑሮ እርካታ ይወረድ እንደመና
የተጨቆነ ነብስ ይፈታ ይዝናና
ከኑሮ ማሳችን የፍራት አዝመራ
በነፃነት ማጭድ ከስሩ የጋጠጥ ፍራት እኛን ይፍራ !
የህፃናቶች ሳቅ በደጃችን ይድመቅ
ያዋቂወች እረፍት በሰላም ይመረቅ
ከእስረኞች አንጓ ካቴናቸው ይውለቅ
የመለያየት ግንብ በፍቅር መብረቅህ ተንኮታኩቶ ይውደቅ !!
ጎዳናዎቻችን ሞት ሞት አይሽተቱ
ወጣቶች አሻግረው ነገን ይመልከቱ
ቤታችን ይጎዝጎዝ ተስፋ እንደቄጤማ
ለተራብን እህል ውሃ ለተጠማ
በሰ. . .ፊው ይከፈት የመሪዎች ጆሮ
ህዝብ ድምፁ ይሰማ ያመፃን መቃብር
የአፈናን ትቢያ በፅናት ቆፍሮ !
ብሶት ሰለቸና
ምሬቱ መረረና
በማያልቅ ውቂያኖስ የማያልቅ ዋና
መዳከር ይብቃና
የፈጣሪ እጆች በባርኮት ይዘርጉ
እንደኖህ መርከብ ደጅ...
የክፋት ቀዳዶች በጣቱ ይዘጉ!!
ጥግንግን እድገቶች ውሽልሽል ፍስሃ
ተጠራርጎ ይሂድ እንደክረምት ውሃ
እንዳዲስ ውለደን አዲስ ጀምበር ይውጣ
ጥላቻ ያልፀነሰ አዲስ ትውልድ ይምጣ
ለሁሉም የሚታይ ብልፅግና ይዝነብ
አንዱ ሃሴት ሲያደርግ በተከፉ ዓይኖቹ ሌላው አይታዘብ
እንደጥጋብ ማእድ ምድራችን አትግፋን
ስደት ያቀጨጨን ዘፀአት ያፋፋን
ከፋን
ከምር ከፋን !!
እስከመቸ ድረስ
በልተን …ራብተኞች
ከፍለን ባለ እዳ
በራሳችን ምድር
መኖር እንደባዳ
ተዋልደን መካኖች
ተባዝተን ብቸኞች
ተከናንበን …..እርቃን ?
በቃን
ከምር በቃን !!\

@getem
@getem
@getem
#የጥምቀት_ጨዋታ_በሰኔ_16

ቦንብ ብወረውር ደረቱን ልመታው
በፍቅር ሸፍኖት አጣሁት ከቦታው
እንኪያስ...
የመሪው ልብ እና የተመሪ ቀንዶች
በአንድ ተደምሮ
የወረወርኩት ቦንብ እራሴን ከተፈኝ
አቅጣጫ ቀይሮ ፡፡

Anteneh_Tesfaye


@getem
@getem
@getem
የሁለት ዓለም ሰዎቹ 16k
ግጥም ብቻ
ክፍት ግጥም

፨ የሁለት ዓለም ሰዎች

▼▼▼▼▼
@Getemsource
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈

@getem
@getem
ወዮ ተዋህዶ!

አበው ከበቁበት እግዚኦታ እንደ ጥንቱ
ማህረነ ክርስቶስ ኪራላይሶ ማለቱ
ከነዛ ገዳማት አለ ወይ ጠሎቱ
የካህናቱ ወረብ ሽብሻቦ ውበቱ
ምነው ቅጡን ጎላብኝ ቅለቱ?
ገድል ድርሳናቱ ተዓምር ድህነታቸው፤
ማመስገኛው ወረብ ማህሌት
ዜማቸው
ከወዴት ዘመመ ከወዴት ጠፋቸው?
እስኪ ተጠየቁኝ ፈላጊስ አላቸው?
በፀሎት በምልጃ ደጁን ሚጠብቁ፤
ቀን ከሌት በመቅረዝ ባሉበት ሚደምቁ፤
መቃዳቸው የታል የትስ ተደበቁ?

÷÷÷÷÷

ታቦት ለንግስ ወቶ ገበያ ሚያደራ
ካህንሽ ምን ሆናል ለይቶ ሚጠራ?
ምዕመንሽ በረከት ለዛ ቅጡን ያጣ
ለምን ይሆን እንደው እማይፈራ ቁጣ
የተክልዬ አቋቋም ሰዓታት ማህሎቱን
አስተምረሽ መክረሽ ሆነሽ ፀሐይቱ
ልጅሽ ጥርስ አወጣ ሊነክስሽ በብርቱ
ቅዳሴሽ በዛ አለ ይቀነስ ሰዓቱ
የሰማዕታት ዝክር ሁሉ ታምራቱ
ሲል ሰማው ያ ልጅሽ ደርሶ ወረቱ፡፡
ወዮ ተዋህዶ ....
ዋኔ ለሄደ ክዶ

ናርዶስ ካሳሁን ና ውድነህ ተሾመ

@getem
@getem
@getem
👍1