# ሠላሜ_ሠላሜ
፡
ልዩ አመል ያመጣን
ከመስመር የወጣን
መሪ አንገት አዙሮ ፥ በዱላው ሚመታው
ሰለሜ ~ ሰለሜው ፥ አብቅቷል ጨዋታው።
:
ያውና ... ያውልሽ ...
እዪ ወዲያ ማዶ
ተመልከች አሻግረሽ፣
:
እንደ ጥማድ በሬ ፥ ሸክም ወስደው ድርሻ
ህዝብ እና ሹመኛው ፥ ገጥመዋል ትከሻ።
-------------------------//------------------------
( በርናባስ ከበደ )
፡
[ # የጠቅላይ_ሚኒስትር_ዶክተር_አብይ_አህመድን_ማስተ
ዋል_የተሞላበት_አላማና_መንገድ_እደግፋለሁ ።]
@Getem_sourcebot
@getem
@getem
፡
ልዩ አመል ያመጣን
ከመስመር የወጣን
መሪ አንገት አዙሮ ፥ በዱላው ሚመታው
ሰለሜ ~ ሰለሜው ፥ አብቅቷል ጨዋታው።
:
ያውና ... ያውልሽ ...
እዪ ወዲያ ማዶ
ተመልከች አሻግረሽ፣
:
እንደ ጥማድ በሬ ፥ ሸክም ወስደው ድርሻ
ህዝብ እና ሹመኛው ፥ ገጥመዋል ትከሻ።
-------------------------//------------------------
( በርናባስ ከበደ )
፡
[ # የጠቅላይ_ሚኒስትር_ዶክተር_አብይ_አህመድን_ማስተ
ዋል_የተሞላበት_አላማና_መንገድ_እደግፋለሁ ።]
@Getem_sourcebot
@getem
@getem
የከፍታ ቅኔ!!!!!!!
እንደዋልያ እግሮች፤ ፀንቶልኝ ጉልበቴ፤
ይኸው ደግሞ ዛሬ፤
ቆንጥሩን ጉድባውን ዳገቱን ወጥቼ፤
በተራራው ጫፍ ላይ፤
ከፍ ብዬ ስሄድ፤
ቁልቁል ተሸቀንጥሮ፤ወደቀ ጠላቴ!!!"""
Ameeeeeennnn
((ጃኖ ))
@balmbaras
@getem
@getem
እንደዋልያ እግሮች፤ ፀንቶልኝ ጉልበቴ፤
ይኸው ደግሞ ዛሬ፤
ቆንጥሩን ጉድባውን ዳገቱን ወጥቼ፤
በተራራው ጫፍ ላይ፤
ከፍ ብዬ ስሄድ፤
ቁልቁል ተሸቀንጥሮ፤ወደቀ ጠላቴ!!!"""
Ameeeeeennnn
((ጃኖ ))
@balmbaras
@getem
@getem
‘’ ኢትዩጵያዬ ‘’
እንኳን ሰው ፣ ተደስቶ ተሽሞንሙኖ ሳር ቅጠሉ
ተከትቦ ተጠርዞ ፣ መሪ ቃሉ
ከመደመር መብዛት ፣ ከመብዛት አንድነት
ካንድነት መዋደድ ፣ ከመዋደድ እድገት
ያለን ህዝብ ለመግታት
ምን ሚሉት ቂልነት ፣ ወገን ላይ ማፈንዳት?
እናት እህት መጉዳት?
፥
ይህን የሚደግፍ ፣ ካለ በየቤቱ
ህሊና የሌለው ፣ የሆነ ነው ከንቱ
ይልቅ ሳይረፍድበት ፣ ይደመር ከጀማው
የፍቅር ስንኝ ነው ከኛ የሚሰማው
የማያልቅ ይቅርታ ከ አብይ ሚፈልቀው
መደመር ብቻ ነው
ኢትዩጵያዊነት ብቻ
ስሜት የሚሰጠው
ፍቅርን የሚያበዛው።
#አሸናፊ ገብሬ ከጅማ ዩኒቨርስቲ
@getem
@getem
እንኳን ሰው ፣ ተደስቶ ተሽሞንሙኖ ሳር ቅጠሉ
ተከትቦ ተጠርዞ ፣ መሪ ቃሉ
ከመደመር መብዛት ፣ ከመብዛት አንድነት
ካንድነት መዋደድ ፣ ከመዋደድ እድገት
ያለን ህዝብ ለመግታት
ምን ሚሉት ቂልነት ፣ ወገን ላይ ማፈንዳት?
እናት እህት መጉዳት?
፥
ይህን የሚደግፍ ፣ ካለ በየቤቱ
ህሊና የሌለው ፣ የሆነ ነው ከንቱ
ይልቅ ሳይረፍድበት ፣ ይደመር ከጀማው
የፍቅር ስንኝ ነው ከኛ የሚሰማው
የማያልቅ ይቅርታ ከ አብይ ሚፈልቀው
መደመር ብቻ ነው
ኢትዩጵያዊነት ብቻ
ስሜት የሚሰጠው
ፍቅርን የሚያበዛው።
#አሸናፊ ገብሬ ከጅማ ዩኒቨርስቲ
@getem
@getem
፧፧፧ እስቲ በመሰንቆ ቅኔ እንዝረፍ፦
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፦ ያዝ እንግዲህ ፦፦፦፦
የቅጠሉ ሽታ ፥ እጅግ አፍኖኛል
ይሄንን ሺፈራው ፥ ብነቅል ይሻለኛል
ተወዲህ ሲዳማ ፥ ተወዲያ ጋምጎፋ
በሞሪንጋ ሽታ ፥ ቤታችን ከረፋ ።
፨
፨
፨
አይ አባ ሀይለ ማርያም ፥ ጭቁኑ የግዜር ሰው
መንበሩ ለብልቦት ፥ ሆዴን አላወሰው
ይሻል ነበር ወንጌል ፥ እንደልማዳችን
ውርስ አስቀጥል ብለው ፥ወጡ ተልባችን ።
፨
፨
፨
ለቆረሱት ስጋ ፥ ላፈሰሱት ጠጅ
ከፋዩ አንተ ነህ ፥ በርትተህ ስራ'ጅ
ትነዳለህ አሉ ፥ ተቀምጠህ ጋቢና
ስንቱ ወጣት ቆሞ ፥ ቀርቶ በጎዳና ።
፨
፨
፨
ለማ ለማ ሲሉኝ ፥ አረሙ መስሎኛል
ለካስ ጤናዳም ነው ፥ተሩቁ ታይቶኛል
ስንቱን ጂኒ ሁላ ፥ ያስላቅቃል አሉ
አባይ እረገፈ ፥ እንደሳር ቅጠሉ ።
፨
፨
፨
ታደሰልኝ ሀይሌ ፥ ካሱም እንደ ካሳ
መርገም ቤቴ ቀርቶ ፥ በረከት ተረሳ
ጳጳስ ቄስ አልጠፋ ፥በሀገር በቤቱ
ስብሃት እያሉ ፥ምነው የማይፈቱ ።
፨
፨
፨
አቢይ አቢይ ቢሉ ፥ ያው ጦሙን ነው ብዬ
ሰውም አቢይ አለው ፥ኸረ እናንተ ሆዬ
በመንበር ቢሆኑ ፥ በመድረክ ቢቆሙ
ቁርጥ የመሰለኝ ፥ ድስትና ግጣሙ
ሲናዳነ ኖሮ ፥ ስንቱ እንከፍ ጋሬጣ
ይገዛኛል ያልኩት ፥ አባት ሆኖኝ መጣ
ልክ እንደብሉያት ፥ እንደመፃህፍት
ክፋ መጣ ብዬ ፥ ስጀምር ትንቢት
ጣድቅ ንጉስ ታየኝ ተወደ ናዝሬት ።
፨
፨
፨
እኔ እጣን አለበኝ ፥ ለፂዮን ታቦት
ልቦና ይስጥህ ብዬ ፥ የተሳልኩበት
ወይ እንደ ገሞራ ፥ ያሙቅህ በሳት ።
፨
፨
፨
እንዴት አድሯል አባይ ፥ያፈለገ ጣና
ገዴን ያመጣልኝ ፥ አርጎ ባለዝና
በኣባይ አናት ላይ ፥ ባህር ዳር ደመቀ
ዛሬ ያኮራኝ ገባ ፥ እንዳልተሳቀቀ ።
፨
፨
፨
ወየሁ መጣ ፍቅሬ ፥ የብዕሩ ጌታ
ፍቅር የድሬ ሰው ፥ የቶሎሳ ሽታ
ቲያስተሳስር ያድራል ፥ ሀበሻን ባንዳፍታ
ፍቅር ጠፋ ብዬ ፥ ባገር በመንደሩ
ቀለም ይዞ መጣ ፥ ፍቅሬ ተነክብሩ
ይቀባኝ ጀመረ ፥ ያረሰርሰኝ
ሀገሬን ሀገሬን ፥ ሀገር አሰኘኝ
በመስተፋቅሩ ፥ አስለፈለፈኝ ።
፨
፨
፨
በሉ ፍቷትማ ፦
እነባለ እውቀት ፥ እነ በሳሰሉ
እንዳሻው ይሆናል ፥ ብላችሗል አሉ
ሰው ታልዘለለበት ፥ እንዳሻው ባገሩ
ሀገሬ ማለቱ ፥ ምንድነው ሚስጥሩ ።
፨
፨
አልያም ተርጉሟት ፦
እነ ወሬ አደር ፥ እነ ነውር ጌጡ
እንዳሻው ይጥፉል ፥ ብላቹ አቃልጡ
እኔ እንደው ብያለሁ ፥ ዐለሙ ይፍረደኝ
እንኳን በናት ምድሬ ፥ የትም እንዳሻው ነኝ ።
።
፨
፨
፨
፨
14-10-10
( እንዳሻው አለማየሁ ፦ ፦ ።)
@getem
@getem
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፦ ያዝ እንግዲህ ፦፦፦፦
የቅጠሉ ሽታ ፥ እጅግ አፍኖኛል
ይሄንን ሺፈራው ፥ ብነቅል ይሻለኛል
ተወዲህ ሲዳማ ፥ ተወዲያ ጋምጎፋ
በሞሪንጋ ሽታ ፥ ቤታችን ከረፋ ።
፨
፨
፨
አይ አባ ሀይለ ማርያም ፥ ጭቁኑ የግዜር ሰው
መንበሩ ለብልቦት ፥ ሆዴን አላወሰው
ይሻል ነበር ወንጌል ፥ እንደልማዳችን
ውርስ አስቀጥል ብለው ፥ወጡ ተልባችን ።
፨
፨
፨
ለቆረሱት ስጋ ፥ ላፈሰሱት ጠጅ
ከፋዩ አንተ ነህ ፥ በርትተህ ስራ'ጅ
ትነዳለህ አሉ ፥ ተቀምጠህ ጋቢና
ስንቱ ወጣት ቆሞ ፥ ቀርቶ በጎዳና ።
፨
፨
፨
ለማ ለማ ሲሉኝ ፥ አረሙ መስሎኛል
ለካስ ጤናዳም ነው ፥ተሩቁ ታይቶኛል
ስንቱን ጂኒ ሁላ ፥ ያስላቅቃል አሉ
አባይ እረገፈ ፥ እንደሳር ቅጠሉ ።
፨
፨
፨
ታደሰልኝ ሀይሌ ፥ ካሱም እንደ ካሳ
መርገም ቤቴ ቀርቶ ፥ በረከት ተረሳ
ጳጳስ ቄስ አልጠፋ ፥በሀገር በቤቱ
ስብሃት እያሉ ፥ምነው የማይፈቱ ።
፨
፨
፨
አቢይ አቢይ ቢሉ ፥ ያው ጦሙን ነው ብዬ
ሰውም አቢይ አለው ፥ኸረ እናንተ ሆዬ
በመንበር ቢሆኑ ፥ በመድረክ ቢቆሙ
ቁርጥ የመሰለኝ ፥ ድስትና ግጣሙ
ሲናዳነ ኖሮ ፥ ስንቱ እንከፍ ጋሬጣ
ይገዛኛል ያልኩት ፥ አባት ሆኖኝ መጣ
ልክ እንደብሉያት ፥ እንደመፃህፍት
ክፋ መጣ ብዬ ፥ ስጀምር ትንቢት
ጣድቅ ንጉስ ታየኝ ተወደ ናዝሬት ።
፨
፨
፨
እኔ እጣን አለበኝ ፥ ለፂዮን ታቦት
ልቦና ይስጥህ ብዬ ፥ የተሳልኩበት
ወይ እንደ ገሞራ ፥ ያሙቅህ በሳት ።
፨
፨
፨
እንዴት አድሯል አባይ ፥ያፈለገ ጣና
ገዴን ያመጣልኝ ፥ አርጎ ባለዝና
በኣባይ አናት ላይ ፥ ባህር ዳር ደመቀ
ዛሬ ያኮራኝ ገባ ፥ እንዳልተሳቀቀ ።
፨
፨
፨
ወየሁ መጣ ፍቅሬ ፥ የብዕሩ ጌታ
ፍቅር የድሬ ሰው ፥ የቶሎሳ ሽታ
ቲያስተሳስር ያድራል ፥ ሀበሻን ባንዳፍታ
ፍቅር ጠፋ ብዬ ፥ ባገር በመንደሩ
ቀለም ይዞ መጣ ፥ ፍቅሬ ተነክብሩ
ይቀባኝ ጀመረ ፥ ያረሰርሰኝ
ሀገሬን ሀገሬን ፥ ሀገር አሰኘኝ
በመስተፋቅሩ ፥ አስለፈለፈኝ ።
፨
፨
፨
በሉ ፍቷትማ ፦
እነባለ እውቀት ፥ እነ በሳሰሉ
እንዳሻው ይሆናል ፥ ብላችሗል አሉ
ሰው ታልዘለለበት ፥ እንዳሻው ባገሩ
ሀገሬ ማለቱ ፥ ምንድነው ሚስጥሩ ።
፨
፨
አልያም ተርጉሟት ፦
እነ ወሬ አደር ፥ እነ ነውር ጌጡ
እንዳሻው ይጥፉል ፥ ብላቹ አቃልጡ
እኔ እንደው ብያለሁ ፥ ዐለሙ ይፍረደኝ
እንኳን በናት ምድሬ ፥ የትም እንዳሻው ነኝ ።
።
፨
፨
፨
፨
14-10-10
( እንዳሻው አለማየሁ ፦ ፦ ።)
@getem
@getem
#ወረት_ብቻ_እንዳይሆን
፡
ወደ ገነት ስትሮጥ ፥ ቅን ነብሴን ለማፅደቅ
ቀኜን ቀን ቢጥላት ፥ ተቆርጣ ብትወድቅ፣
ወረት ብቻ እንዳይሆን ፥ ነገረ ሥራዬ
እግሬን ተሸከምኳት ፥ እኔም በተራዬ።
-----------><----------
( በርናባስ ከበደ )
@getem_sourcebot
@getem
@getem
፡
ወደ ገነት ስትሮጥ ፥ ቅን ነብሴን ለማፅደቅ
ቀኜን ቀን ቢጥላት ፥ ተቆርጣ ብትወድቅ፣
ወረት ብቻ እንዳይሆን ፥ ነገረ ሥራዬ
እግሬን ተሸከምኳት ፥ እኔም በተራዬ።
-----------><----------
( በርናባስ ከበደ )
@getem_sourcebot
@getem
@getem
✍✍ቢኒ የቅዱስ ሚካኤል ልጅ✍✍
ዶ= ዶግ አመድ አድርጎት የጅቦቹን ሴራ
ክ= ክብር አጎናፅፎ የእማማን አደራ
ተ= ተገኘቷል ሙሴያችን ፍቅር ለሀገራችን
ር= ርስት ሆኖ ሊቆየን ውሎ ከልባችን
አ= አብሮነት አዋቂ በፍቅር ማራኪ
ብ= ብርሃን ፈንጣቂ አንድነት ሰባኪ
ይ= ይሁን ብሎ አማኝ
አ= አይሰስት ቸር አዳኝ
ህ= ህያው አስተሳሰብ ብሄራዊ አርማ
መ= መድሃኒቷ የሆነ ከልብ የሀገር ካስማ
ድ= ድንቅ ሰው ተገኝቷል ዛሬ ደስ ይበልሽ ኩሪልን እማማ
እናመሰግናለን ታላቁ መሪያችን ♥♥♥
ታሪካዊ ቀን 16/10/2009
ለዚች ታሪካዊ ቀን በመብቃታችን እድለኞች ነን ለሞቱት ወገኖቻችን ነፍስ ይማርልን🙏🙏🙏
ለተጎዱትም ምህረቱን ስጥልን 🙏🙏🙏
@getem
@getem
@getem
ዶ= ዶግ አመድ አድርጎት የጅቦቹን ሴራ
ክ= ክብር አጎናፅፎ የእማማን አደራ
ተ= ተገኘቷል ሙሴያችን ፍቅር ለሀገራችን
ር= ርስት ሆኖ ሊቆየን ውሎ ከልባችን
አ= አብሮነት አዋቂ በፍቅር ማራኪ
ብ= ብርሃን ፈንጣቂ አንድነት ሰባኪ
ይ= ይሁን ብሎ አማኝ
አ= አይሰስት ቸር አዳኝ
ህ= ህያው አስተሳሰብ ብሄራዊ አርማ
መ= መድሃኒቷ የሆነ ከልብ የሀገር ካስማ
ድ= ድንቅ ሰው ተገኝቷል ዛሬ ደስ ይበልሽ ኩሪልን እማማ
እናመሰግናለን ታላቁ መሪያችን ♥♥♥
ታሪካዊ ቀን 16/10/2009
ለዚች ታሪካዊ ቀን በመብቃታችን እድለኞች ነን ለሞቱት ወገኖቻችን ነፍስ ይማርልን🙏🙏🙏
ለተጎዱትም ምህረቱን ስጥልን 🙏🙏🙏
@getem
@getem
@getem
👍3
የኔ መንገድ!!!!!
ከባርነት ጫጉላ፤
ከግርድና ማጀት፤
ና ውጣ ተብየ፤
የተጠራሁበት፤
የተቀባሁበት፤
የተመረጥኩበት፤
የልቤን ከነአን፤
በነፍሴ ሰሌዳ፤ በደም ቀለም ፅፌ፤
እንደ ኢያሱ ካሌብ፤
ከነአንን ወረስኳት፤
የሞት ውሽንፍሩን፤ ባህሩን አልፌ።
ፈርኦን ሞኝ ነው፤
ተከትሎኝ ነበር፤
በግዞት ማድጋ ፤
መልሶ ሊግተኝ፤ የምሬት ሰፍነጉን፤
ተመለስ እያለ፤
እያግተለተለ፤
የፉከራ ሰልፉን፤ የትእቢት ፈረሱን።
እናም እንደዚህ ነው፤
በሰው መንገድ ቀንተው፤
በሄድኩበት ዱካ፤
እንሂድ እናስቀረው፤ ብለው የፎከሩ፤
ባህሩ ተከፍሎ፤
መልካውን ስሻገር፤
መንገዱ በላቸው፤ ውሃ ሆነው ቀሩ።
ይኸው በኔ ቀዬ፤
የሰው መንገድ ጥጉ፤
ለነሱም የሚሆን እየመሰላቸው፤
በሰው መንገድ ቀንተው፤
ከመንገድ ሊያስቀሩኝ፤
መንገድ የጀመሩ፤
እንደ ፈርኦን ጦር፤ ቀይ ባህር ዋጣቸው።
((( ጃ ኖ )))
@Balmbaras
@getem
@getem
ከባርነት ጫጉላ፤
ከግርድና ማጀት፤
ና ውጣ ተብየ፤
የተጠራሁበት፤
የተቀባሁበት፤
የተመረጥኩበት፤
የልቤን ከነአን፤
በነፍሴ ሰሌዳ፤ በደም ቀለም ፅፌ፤
እንደ ኢያሱ ካሌብ፤
ከነአንን ወረስኳት፤
የሞት ውሽንፍሩን፤ ባህሩን አልፌ።
ፈርኦን ሞኝ ነው፤
ተከትሎኝ ነበር፤
በግዞት ማድጋ ፤
መልሶ ሊግተኝ፤ የምሬት ሰፍነጉን፤
ተመለስ እያለ፤
እያግተለተለ፤
የፉከራ ሰልፉን፤ የትእቢት ፈረሱን።
እናም እንደዚህ ነው፤
በሰው መንገድ ቀንተው፤
በሄድኩበት ዱካ፤
እንሂድ እናስቀረው፤ ብለው የፎከሩ፤
ባህሩ ተከፍሎ፤
መልካውን ስሻገር፤
መንገዱ በላቸው፤ ውሃ ሆነው ቀሩ።
ይኸው በኔ ቀዬ፤
የሰው መንገድ ጥጉ፤
ለነሱም የሚሆን እየመሰላቸው፤
በሰው መንገድ ቀንተው፤
ከመንገድ ሊያስቀሩኝ፤
መንገድ የጀመሩ፤
እንደ ፈርኦን ጦር፤ ቀይ ባህር ዋጣቸው።
((( ጃ ኖ )))
@Balmbaras
@getem
@getem
#ከመለስ የተላከ ደብዳቤ
፡
፡
እንደው ዶክተር አብይ
ህዝቡን ምን አረከው ~ ምንድን አስነካኸው
፡
ራዕዬን ትቶ
ከኔ በላይ ላንተ ~ እንዲህ የሰገደው??
፡
ከሁሉ ከሁሉ
እኔን የገረመኝ
የሲኦሉ ጌታ ~ ሰይጣን እንኳ ባቅሙ
፡
በመደመር ወንጌል
የፍቅር ደብዳቤ
ማመልከቻ ፅፎ
ለእግዜር በመላኩ
መልአክታት ሁሉ ~ ባንተ ተገረሙ፡፡
፡
ምን ሰይጣኑ ብቻ
ሲኦልም ቃጠሎው ~ በፍቅር ቀዝቅዞ
፡
ሰላም የበዛበት
መዝናኛ ይመስላል ~ ባንተ ድርጊት ፈዞ፡፡
፡
እንደው ግን በሞቴ
ሀምሳ ሎሚ ላንዱ ~ መጫኛ ሸክም ነው
፡
የሚለውን ተረት
የሀገሬን እውነት ~ እንዴት እረሳኸው??
፡
የሚል ፅሁፍ ፅፌ
በመንፈሴ ብልክ ~ እንድተነትነው
፡
አንተ ግን ብልጥ ነህ
ክፍልፍሉን ሁላ
ደምረህ ደምረህ ~ ወደ አንድ አመጣኸው፡
፡
እና ይገርምሀል
እኔ በሰራሁት ግፍና መከራ ~ ይደሰታል ያልኩት
፡
ሰይጣንም እንደ ሰው
ሙድ እዬያዘብኝ
አያጅቦ እንዴት ነህ ~ ይለኛል ቀን ከሌት፡፡
፡<
እናም እባክህን
እዚህ እንኳ ልረፍ ~ ፍቅርህን ላክልኝ
፡
እዚያም ላሉ ጅቦች
መደመር ይበጃል ~ ብለህ ንገርልኝ፡፡
፡
# መለስ ነኝ ከሲኦል
ሚኪያስ
@getem
@getem
፡
፡
እንደው ዶክተር አብይ
ህዝቡን ምን አረከው ~ ምንድን አስነካኸው
፡
ራዕዬን ትቶ
ከኔ በላይ ላንተ ~ እንዲህ የሰገደው??
፡
ከሁሉ ከሁሉ
እኔን የገረመኝ
የሲኦሉ ጌታ ~ ሰይጣን እንኳ ባቅሙ
፡
በመደመር ወንጌል
የፍቅር ደብዳቤ
ማመልከቻ ፅፎ
ለእግዜር በመላኩ
መልአክታት ሁሉ ~ ባንተ ተገረሙ፡፡
፡
ምን ሰይጣኑ ብቻ
ሲኦልም ቃጠሎው ~ በፍቅር ቀዝቅዞ
፡
ሰላም የበዛበት
መዝናኛ ይመስላል ~ ባንተ ድርጊት ፈዞ፡፡
፡
እንደው ግን በሞቴ
ሀምሳ ሎሚ ላንዱ ~ መጫኛ ሸክም ነው
፡
የሚለውን ተረት
የሀገሬን እውነት ~ እንዴት እረሳኸው??
፡
የሚል ፅሁፍ ፅፌ
በመንፈሴ ብልክ ~ እንድተነትነው
፡
አንተ ግን ብልጥ ነህ
ክፍልፍሉን ሁላ
ደምረህ ደምረህ ~ ወደ አንድ አመጣኸው፡
፡
እና ይገርምሀል
እኔ በሰራሁት ግፍና መከራ ~ ይደሰታል ያልኩት
፡
ሰይጣንም እንደ ሰው
ሙድ እዬያዘብኝ
አያጅቦ እንዴት ነህ ~ ይለኛል ቀን ከሌት፡፡
፡<
እናም እባክህን
እዚህ እንኳ ልረፍ ~ ፍቅርህን ላክልኝ
፡
እዚያም ላሉ ጅቦች
መደመር ይበጃል ~ ብለህ ንገርልኝ፡፡
፡
# መለስ ነኝ ከሲኦል
ሚኪያስ
@getem
@getem
ትንሽ ቁረጭና!!!!!!!
አንች እናት!!!!!
ውብ እናት!!!!!!
ልስጥህ አትበይኝ፣
ውሰድ አትበይኝ፣ ርስትሽ ይቅርብኝ፣
ሰርክ ከሚያበራው፣
ከብርሃን ፈገግታሽ፣
ከሩህሩህ አንጀትሽ፣ መቼም አይበልጥብኝ።
ከብቱን ላሙን ተይው፣
አልፈልግም እኔ፣
ያንችን ጠገራ ብር፣ ወርቅ ማርትሬዛ፣
እምዬ ልንገርሽ፣
ክስካሽ ፈረንካ፣
እንጀራ ነው እንጅ፣ደግነት አይገዛ።
እናም አንች ሸጋ፣
እናም አንች እናቴ፣
የሆዴን ልንገርሽ፣
ቤትሽን የሞላው፣ ጠገራው ርስቱ፣
ጋሻ የገመሰው፣ ከብትና መሬቱ፣
ውሰድ አትበይኝ
ከቶ ምን ሊሆነኝ፣ ኮተታ ኮተቱ፣
እረ ምን ሊረባኝ፣ ምን ሊሆነኝና፣
ብሩንም እርስቱን፣
እኔ አልፈልገውም፣ ይቅርብኝ ተይና፣
ካንጀትሽ አካፍሊኝ፣ትንሽ ቁረጭና።
((( ጃ ኖ )))
ሸጋ ቀን !!!
@balmbaras
@getem
@getem
አንች እናት!!!!!
ውብ እናት!!!!!!
ልስጥህ አትበይኝ፣
ውሰድ አትበይኝ፣ ርስትሽ ይቅርብኝ፣
ሰርክ ከሚያበራው፣
ከብርሃን ፈገግታሽ፣
ከሩህሩህ አንጀትሽ፣ መቼም አይበልጥብኝ።
ከብቱን ላሙን ተይው፣
አልፈልግም እኔ፣
ያንችን ጠገራ ብር፣ ወርቅ ማርትሬዛ፣
እምዬ ልንገርሽ፣
ክስካሽ ፈረንካ፣
እንጀራ ነው እንጅ፣ደግነት አይገዛ።
እናም አንች ሸጋ፣
እናም አንች እናቴ፣
የሆዴን ልንገርሽ፣
ቤትሽን የሞላው፣ ጠገራው ርስቱ፣
ጋሻ የገመሰው፣ ከብትና መሬቱ፣
ውሰድ አትበይኝ
ከቶ ምን ሊሆነኝ፣ ኮተታ ኮተቱ፣
እረ ምን ሊረባኝ፣ ምን ሊሆነኝና፣
ብሩንም እርስቱን፣
እኔ አልፈልገውም፣ ይቅርብኝ ተይና፣
ካንጀትሽ አካፍሊኝ፣ትንሽ ቁረጭና።
((( ጃ ኖ )))
ሸጋ ቀን !!!
@balmbaras
@getem
@getem
👍1
ሞሪንጋ!!!!
የፈረንጅ ሞሪንጋ ፤
ስንት አይነት በሽታ ፤ ሰርክ እየፈወሰ ፤
የኛ አገር ሽፈራው ፤
በጠራራ ጸሃይ እልፍ ሰው ጨረሰ ።
ብለን ተቀኝተን ፤
ነግረን ሳናበቃ ፤ በጉባኤ ፊት ፤
ያገሬ ገበሮች ፤
ይህንን ሺፈራው ፤
በዶማ ቆፍረው፤ መንግለው ጣሉት ።
(( ጃ ኖ ))
@Balmbaras
@getem
@getem
የፈረንጅ ሞሪንጋ ፤
ስንት አይነት በሽታ ፤ ሰርክ እየፈወሰ ፤
የኛ አገር ሽፈራው ፤
በጠራራ ጸሃይ እልፍ ሰው ጨረሰ ።
ብለን ተቀኝተን ፤
ነግረን ሳናበቃ ፤ በጉባኤ ፊት ፤
ያገሬ ገበሮች ፤
ይህንን ሺፈራው ፤
በዶማ ቆፍረው፤ መንግለው ጣሉት ።
(( ጃ ኖ ))
@Balmbaras
@getem
@getem
አቤቱ . . .
(አሌክስ አብርሃም)
ካገር ማድጋችን ውስጥ
የጥላቻ እርሾ …የቂም ቡኮ ይፍሰስ
ኑሮ የደቆሰው ደሳሳ ጎጇችን በባርኮት ይታደስ
እንደ አደይ ድምቀት ፈገግታችን ይፍካ
የተራቆተ ኪስ ይሙላ በፍራንካ
የታመሙ ነፍሳት … በገፍ ይፈወሱ
የጤና አንፋሳት በምድራችን ፊት ላይ ዘላለም ይንፈሱ
የኑሮ እርካታ ይወረድ እንደመና
የተጨቆነ ነብስ ይፈታ ይዝናና
ከኑሮ ማሳችን የፍራት አዝመራ
በነፃነት ማጭድ ከስሩ የጋጠጥ ፍራት እኛን ይፍራ !
የህፃናቶች ሳቅ በደጃችን ይድመቅ
ያዋቂወች እረፍት በሰላም ይመረቅ
ከእስረኞች አንጓ ካቴናቸው ይውለቅ
የመለያየት ግንብ በፍቅር መብረቅህ ተንኮታኩቶ ይውደቅ !!
ጎዳናዎቻችን ሞት ሞት አይሽተቱ
ወጣቶች አሻግረው ነገን ይመልከቱ
ቤታችን ይጎዝጎዝ ተስፋ እንደቄጤማ
ለተራብን እህል ውሃ ለተጠማ
በሰ. . .ፊው ይከፈት የመሪዎች ጆሮ
ህዝብ ድምፁ ይሰማ ያመፃን መቃብር
የአፈናን ትቢያ በፅናት ቆፍሮ !
ብሶት ሰለቸና
ምሬቱ መረረና
በማያልቅ ውቂያኖስ የማያልቅ ዋና
መዳከር ይብቃና
የፈጣሪ እጆች በባርኮት ይዘርጉ
እንደኖህ መርከብ ደጅ...
የክፋት ቀዳዶች በጣቱ ይዘጉ!!
ጥግንግን እድገቶች ውሽልሽል ፍስሃ
ተጠራርጎ ይሂድ እንደክረምት ውሃ
እንዳዲስ ውለደን አዲስ ጀምበር ይውጣ
ጥላቻ ያልፀነሰ አዲስ ትውልድ ይምጣ
ለሁሉም የሚታይ ብልፅግና ይዝነብ
አንዱ ሃሴት ሲያደርግ በተከፉ ዓይኖቹ ሌላው አይታዘብ
እንደጥጋብ ማእድ ምድራችን አትግፋን
ስደት ያቀጨጨን ዘፀአት ያፋፋን
ከፋን
ከምር ከፋን !!
እስከመቸ ድረስ
በልተን …ራብተኞች
ከፍለን ባለ እዳ
በራሳችን ምድር
መኖር እንደባዳ
ተዋልደን መካኖች
ተባዝተን ብቸኞች
ተከናንበን …..እርቃን ?
በቃን
ከምር በቃን !!\
@getem
@getem
@getem
(አሌክስ አብርሃም)
ካገር ማድጋችን ውስጥ
የጥላቻ እርሾ …የቂም ቡኮ ይፍሰስ
ኑሮ የደቆሰው ደሳሳ ጎጇችን በባርኮት ይታደስ
እንደ አደይ ድምቀት ፈገግታችን ይፍካ
የተራቆተ ኪስ ይሙላ በፍራንካ
የታመሙ ነፍሳት … በገፍ ይፈወሱ
የጤና አንፋሳት በምድራችን ፊት ላይ ዘላለም ይንፈሱ
የኑሮ እርካታ ይወረድ እንደመና
የተጨቆነ ነብስ ይፈታ ይዝናና
ከኑሮ ማሳችን የፍራት አዝመራ
በነፃነት ማጭድ ከስሩ የጋጠጥ ፍራት እኛን ይፍራ !
የህፃናቶች ሳቅ በደጃችን ይድመቅ
ያዋቂወች እረፍት በሰላም ይመረቅ
ከእስረኞች አንጓ ካቴናቸው ይውለቅ
የመለያየት ግንብ በፍቅር መብረቅህ ተንኮታኩቶ ይውደቅ !!
ጎዳናዎቻችን ሞት ሞት አይሽተቱ
ወጣቶች አሻግረው ነገን ይመልከቱ
ቤታችን ይጎዝጎዝ ተስፋ እንደቄጤማ
ለተራብን እህል ውሃ ለተጠማ
በሰ. . .ፊው ይከፈት የመሪዎች ጆሮ
ህዝብ ድምፁ ይሰማ ያመፃን መቃብር
የአፈናን ትቢያ በፅናት ቆፍሮ !
ብሶት ሰለቸና
ምሬቱ መረረና
በማያልቅ ውቂያኖስ የማያልቅ ዋና
መዳከር ይብቃና
የፈጣሪ እጆች በባርኮት ይዘርጉ
እንደኖህ መርከብ ደጅ...
የክፋት ቀዳዶች በጣቱ ይዘጉ!!
ጥግንግን እድገቶች ውሽልሽል ፍስሃ
ተጠራርጎ ይሂድ እንደክረምት ውሃ
እንዳዲስ ውለደን አዲስ ጀምበር ይውጣ
ጥላቻ ያልፀነሰ አዲስ ትውልድ ይምጣ
ለሁሉም የሚታይ ብልፅግና ይዝነብ
አንዱ ሃሴት ሲያደርግ በተከፉ ዓይኖቹ ሌላው አይታዘብ
እንደጥጋብ ማእድ ምድራችን አትግፋን
ስደት ያቀጨጨን ዘፀአት ያፋፋን
ከፋን
ከምር ከፋን !!
እስከመቸ ድረስ
በልተን …ራብተኞች
ከፍለን ባለ እዳ
በራሳችን ምድር
መኖር እንደባዳ
ተዋልደን መካኖች
ተባዝተን ብቸኞች
ተከናንበን …..እርቃን ?
በቃን
ከምር በቃን !!\
@getem
@getem
@getem