🌿🌾🌙💫🌟💫✨💐
አዬ ከራማው ሠፊ ነው
ሀድራው የበዛ ነው
ምን ይነገር ለሱ
ራህመቱ ብዙ
የፍቅርን ስብሐት
ካአንድነት ጋር አብሮ ክልኤቱ ብሎ
በፈሪሀ ሰበዝ ልዩ ወ ውበቱ
ያኖረን ባንድላይ ሠናይ ሠብ ብሎ ።
......ጎፍታኮ ዋቀዮ....
....አጃይብ ያረቢ.....
ማድመቅህን አብዛው:ውበት ጨምርልን
በፈሪሀ ብዛት ብርሃን አብዛልን
ሐድራችን ይሙላልን
ሐሴት እንድናረግ: ጨለማ እንዲጠፋ
ፍቅርን አሰልሰው አስርግ እንዳይወጣ
በረካህ ይበርክት በምድራችን ይሙላ
አሜን ይሁንልን ከራማችን ይሙላ።️✨
@ቤሊና (07/10/2018 ዓ.ም)
🌟💫ኢድ ሙባረክ🌟✨
@getem_sourcebot
@getem
@getem
አዬ ከራማው ሠፊ ነው
ሀድራው የበዛ ነው
ምን ይነገር ለሱ
ራህመቱ ብዙ
የፍቅርን ስብሐት
ካአንድነት ጋር አብሮ ክልኤቱ ብሎ
በፈሪሀ ሰበዝ ልዩ ወ ውበቱ
ያኖረን ባንድላይ ሠናይ ሠብ ብሎ ።
......ጎፍታኮ ዋቀዮ....
....አጃይብ ያረቢ.....
ማድመቅህን አብዛው:ውበት ጨምርልን
በፈሪሀ ብዛት ብርሃን አብዛልን
ሐድራችን ይሙላልን
ሐሴት እንድናረግ: ጨለማ እንዲጠፋ
ፍቅርን አሰልሰው አስርግ እንዳይወጣ
በረካህ ይበርክት በምድራችን ይሙላ
አሜን ይሁንልን ከራማችን ይሙላ።️✨
@ቤሊና (07/10/2018 ዓ.ም)
🌟💫ኢድ ሙባረክ🌟✨
@getem_sourcebot
@getem
@getem
#የፍቅር ጥግ#
ሳቅሽ ፅጌረዳ፥ያልተቀነጠበ
አይንሽ ላይ ያሸተ፥ጥርስሽ ላይ ያበበ
አፍሽ የወይን ዛፍ
ከማር የማይነጥፍ
ሽንጥሽ የወርቅ አልጋ፥አመለ ወላንሳ
ጎዝጉዘዉ ቢተኙ፥አጋም የሚያስረሳ።
ቀረሮ ደረቴ፥ አልታደለምና ከቶ ላንቺ ገላ
ዘብ አደርሽ ሆንኩኝ፥እንዳይገባ ሌላ።
ማፍቀር ማለት መቅናት ማለት ነዉ።የፍቅር ጥጉም ቅናት ነዉ። ፍቅር በቅናት ይገለፃል:ነገር ግን ቅናት ሁሉ ፍቅር አይደለም።
(የዋርካ ስር ነፍሶች)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ሳቅሽ ፅጌረዳ፥ያልተቀነጠበ
አይንሽ ላይ ያሸተ፥ጥርስሽ ላይ ያበበ
አፍሽ የወይን ዛፍ
ከማር የማይነጥፍ
ሽንጥሽ የወርቅ አልጋ፥አመለ ወላንሳ
ጎዝጉዘዉ ቢተኙ፥አጋም የሚያስረሳ።
ቀረሮ ደረቴ፥ አልታደለምና ከቶ ላንቺ ገላ
ዘብ አደርሽ ሆንኩኝ፥እንዳይገባ ሌላ።
ማፍቀር ማለት መቅናት ማለት ነዉ።የፍቅር ጥጉም ቅናት ነዉ። ፍቅር በቅናት ይገለፃል:ነገር ግን ቅናት ሁሉ ፍቅር አይደለም።
(የዋርካ ስር ነፍሶች)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
❤1
ውሻ ነኝ
=== ==
የጉዞየ ምዕራፍ የህይወቴ ቃና
በፍቅርሽ ማዕበል መንፈሤ የፀና፣
..
ካወኩሽ ጀምሮ ከጥንት እሥከ ዛሬ
ላንች የሠሠትኩት የለም ነበር ፍቅሬ።
..
ያኔ ሙሉ ነበርኩ እጄ ያለጠረ
ልቤም ደሥተኛ ነው በፍቅር የከበረ።
..
የምትፈልጊውን ሁሉን የማሣካ
ባንች ደሥታ ብቻ ውሥጤ የሚረካ።
..
እሡ ነበር ለኔ የደሥታየ ጣራ
የኔን ሥም ረሥተውት ባንች ሥም ሥጠራ።
..
እንዲህ ትይኝ ነበር...
" ከሠማይ የራቀ ከውቅያኖሥ የሠፋ
ላንተ ፍቅር አለኝ ፍፁም የማይጠፋ።
አጣህ ነጣህ ብየ አልወጣም ካንተ እቅፍ ቃሌን ባላከብር
ምላሤ ይታጠፍ። "
በሚጥም ልሣንሽ ብለሽኝ ነበረ
ይሄው ጊዜ ሺሮት ቃልሽ ተሠበረ።
..
የኔ ንብረት አልቆ ፍቅሬ ግን በርትቶ
ያንች ፍቅር ሢያረጅ ገንዘብሽ በርክቶ፣
..
ያጣ መናጢ ነው ብለሽ ተጠየፍሽኝ
ወዳላቸው ሥትሄጅ እኔን ግን ሸሸሺኝ።
..
አንች ብትሸሺኝም አልቀነሠም ፍቅሬ
እንደ ሎሌሺ ሁኝ ሥከትል አብሬ፣
..
አንችን ተከትየ በሆንኩሽ ጠበቃ
" ውሻ ነህ እንዴ አንተ ? አትከተል በቃ! "
ብለሽ አኮራሽኝ ቆረጥሽልኝ ጥሜን
ዳግም እንዳያመኝ ፈወሥሽው ህመሜን።
..
ውለታየን ክደሽ ፍቅሬን ብትንቂ
ሠድበሽ አሥደሠትሽኝ ሚሥጥሩን ሣታውቂ።
..
ለሁሉም ንገሪ ሣትደብቂያቸው
አንችን የምከተል ውሻ ነው በያቸው።
..
አንዴ ከወደደ መልሶ እማይከዳ
ጥላቱን ነው እንጅ ወዳጅ እማይጎዳ፣
..
ቃሌን የምጠብቅ ለጌታየ ታማኝ
አንችኮ "ተኩላ" ነሽ እኔ ግን " ውሻ " ነኝ። ...............
.........አወ እኔ ውሻ ነኝ
በይ የኔን ውሻነት ላገር አሣውቂ
ያንችን ተኩላነት ግን እንዳትደብቂ።
....
ማንም በሌለበት በባህር ዳርቻ
ሥንዝናና ነበር እኔና አንች ብቻ፣
..
ጨለማው ተተካ ቀኑ ተቀየረ
ተኩላው አብሮ ሢሄድ ውሻው ብቻ ቀረ።
....................አወ እኔ ውሻ ነኝ።።።
ከገጣሚ ናትናኤል የተወሰደ ፡፡ ለቃሌ ታማኝ ነኝ
~~~~~~~~~
፡
ምንም ብንለያይ አደራ አትርሳኝ
ብለሽ መዳፍሽን በጄ ያስመታሽኝ
በስምሽ ያስማልሽኝ
የገባሁልሽ ቃል እንዳልፈረሰ ነው
ቃል አባይ አይድለሁ እስካሁን ህያው ነው
፡
በትዝታ ቅኝት በሰመመን ዜማ
ክረምት'ና በጋ ቀን ወይም ጨለማ
ሳንካ ሳይሆንብኝ መፈራረቃቸው
ወቅት…
ቦታ…
ጊዜ…
አንዳች ሳያግደኝ …
በክፉም በደጉ አስታውስሻለው
፡
ጨረቃ ስትወጣ ጨረቃን እያየሁ
በሰማይ ሰሌዳ በክዋክብት ብዛት አንቺኑ ስላለሁ
አስታውስሻለሁ
፡
ሆዴም ሆዱን ብሶት የተከፋሁ ግዜ
ብቸኝነት ወርሶኝ ሰፍሮብኝ ትካዜ
በሬን ዘጋግቼ ብቻዬን ቤቴ ውስጥ
በሀሳብ ድር ትብታብ ቆዝሜ ስቀመጥ
ደግሞ ውል ብሎኝ በሬ እንዲቆረቆር
ጉዳዬ ነው የሚል ስለኔ መቸገር
ሰው ያስፈለገኝ 'ለት . . .
ሌላከየትመቶ
BYNati
@getem
@getem
=== ==
የጉዞየ ምዕራፍ የህይወቴ ቃና
በፍቅርሽ ማዕበል መንፈሤ የፀና፣
..
ካወኩሽ ጀምሮ ከጥንት እሥከ ዛሬ
ላንች የሠሠትኩት የለም ነበር ፍቅሬ።
..
ያኔ ሙሉ ነበርኩ እጄ ያለጠረ
ልቤም ደሥተኛ ነው በፍቅር የከበረ።
..
የምትፈልጊውን ሁሉን የማሣካ
ባንች ደሥታ ብቻ ውሥጤ የሚረካ።
..
እሡ ነበር ለኔ የደሥታየ ጣራ
የኔን ሥም ረሥተውት ባንች ሥም ሥጠራ።
..
እንዲህ ትይኝ ነበር...
" ከሠማይ የራቀ ከውቅያኖሥ የሠፋ
ላንተ ፍቅር አለኝ ፍፁም የማይጠፋ።
አጣህ ነጣህ ብየ አልወጣም ካንተ እቅፍ ቃሌን ባላከብር
ምላሤ ይታጠፍ። "
በሚጥም ልሣንሽ ብለሽኝ ነበረ
ይሄው ጊዜ ሺሮት ቃልሽ ተሠበረ።
..
የኔ ንብረት አልቆ ፍቅሬ ግን በርትቶ
ያንች ፍቅር ሢያረጅ ገንዘብሽ በርክቶ፣
..
ያጣ መናጢ ነው ብለሽ ተጠየፍሽኝ
ወዳላቸው ሥትሄጅ እኔን ግን ሸሸሺኝ።
..
አንች ብትሸሺኝም አልቀነሠም ፍቅሬ
እንደ ሎሌሺ ሁኝ ሥከትል አብሬ፣
..
አንችን ተከትየ በሆንኩሽ ጠበቃ
" ውሻ ነህ እንዴ አንተ ? አትከተል በቃ! "
ብለሽ አኮራሽኝ ቆረጥሽልኝ ጥሜን
ዳግም እንዳያመኝ ፈወሥሽው ህመሜን።
..
ውለታየን ክደሽ ፍቅሬን ብትንቂ
ሠድበሽ አሥደሠትሽኝ ሚሥጥሩን ሣታውቂ።
..
ለሁሉም ንገሪ ሣትደብቂያቸው
አንችን የምከተል ውሻ ነው በያቸው።
..
አንዴ ከወደደ መልሶ እማይከዳ
ጥላቱን ነው እንጅ ወዳጅ እማይጎዳ፣
..
ቃሌን የምጠብቅ ለጌታየ ታማኝ
አንችኮ "ተኩላ" ነሽ እኔ ግን " ውሻ " ነኝ። ...............
.........አወ እኔ ውሻ ነኝ
በይ የኔን ውሻነት ላገር አሣውቂ
ያንችን ተኩላነት ግን እንዳትደብቂ።
....
ማንም በሌለበት በባህር ዳርቻ
ሥንዝናና ነበር እኔና አንች ብቻ፣
..
ጨለማው ተተካ ቀኑ ተቀየረ
ተኩላው አብሮ ሢሄድ ውሻው ብቻ ቀረ።
....................አወ እኔ ውሻ ነኝ።።።
ከገጣሚ ናትናኤል የተወሰደ ፡፡ ለቃሌ ታማኝ ነኝ
~~~~~~~~~
፡
ምንም ብንለያይ አደራ አትርሳኝ
ብለሽ መዳፍሽን በጄ ያስመታሽኝ
በስምሽ ያስማልሽኝ
የገባሁልሽ ቃል እንዳልፈረሰ ነው
ቃል አባይ አይድለሁ እስካሁን ህያው ነው
፡
በትዝታ ቅኝት በሰመመን ዜማ
ክረምት'ና በጋ ቀን ወይም ጨለማ
ሳንካ ሳይሆንብኝ መፈራረቃቸው
ወቅት…
ቦታ…
ጊዜ…
አንዳች ሳያግደኝ …
በክፉም በደጉ አስታውስሻለው
፡
ጨረቃ ስትወጣ ጨረቃን እያየሁ
በሰማይ ሰሌዳ በክዋክብት ብዛት አንቺኑ ስላለሁ
አስታውስሻለሁ
፡
ሆዴም ሆዱን ብሶት የተከፋሁ ግዜ
ብቸኝነት ወርሶኝ ሰፍሮብኝ ትካዜ
በሬን ዘጋግቼ ብቻዬን ቤቴ ውስጥ
በሀሳብ ድር ትብታብ ቆዝሜ ስቀመጥ
ደግሞ ውል ብሎኝ በሬ እንዲቆረቆር
ጉዳዬ ነው የሚል ስለኔ መቸገር
ሰው ያስፈለገኝ 'ለት . . .
ሌላከየትመቶ
BYNati
@getem
@getem
አንቺ ካለሽልኝ
( እሱባለው ኢትዮጵያዊ)
አንቺ ካለሽልኝ
*
*
*
ሁሉም ይኖረኛል።
የጠየኩት ሁሉ፤ ይመለስልኛል
አለቆቹ ሁሉ፤ ይታዘዙልኛል።
*
*
አንቺ ካለሽልኝ
ሁሉም ይኖረኛል
*
*
ቤታችን በደስታ ፤በሃሴት ይሞላል
ሁሉ ያሸበርቃል
ግቢያችን በፍቅር ፤ ሳይበላ ይጥግባል
አንቺ ካለሽልኝ
ሁሉም ይኖረኛል።
********
ሁሌም ኑሪልኝ
ሰኔ ፰ ፪ሺህ፲
( እሱባለው ኢትዮጵያዊ)
@getemsource
@getem
@getem
( እሱባለው ኢትዮጵያዊ)
አንቺ ካለሽልኝ
*
*
*
ሁሉም ይኖረኛል።
የጠየኩት ሁሉ፤ ይመለስልኛል
አለቆቹ ሁሉ፤ ይታዘዙልኛል።
*
*
አንቺ ካለሽልኝ
ሁሉም ይኖረኛል
*
*
ቤታችን በደስታ ፤በሃሴት ይሞላል
ሁሉ ያሸበርቃል
ግቢያችን በፍቅር ፤ ሳይበላ ይጥግባል
አንቺ ካለሽልኝ
ሁሉም ይኖረኛል።
********
ሁሌም ኑሪልኝ
ሰኔ ፰ ፪ሺህ፲
( እሱባለው ኢትዮጵያዊ)
@getemsource
@getem
@getem
#ናፍቆት
//ኑረዲን ዒሣ//
ስጋዬን ሲበላኝ በጥርሴ ነከስኩት
ቆዳዬን ሲበላኝ በጥፍሬ ፎከትኩት
እፎይ አስታገስኩት
ፀጥ ረጭ አረኩት።
የውስጥ አጥንቴ ግን ሲበላኝ ነዝንዞ
ሲነክሰኝ ጠዝጥዞ
ምንም አላረኩት
ምንም አላከኩት
ላልችል ችየ ቻልኩት።
አልፎክተው ነገር፣ ቆዳዬን መንቅሬ
አላኝከው ነገር፣ ስጋዬን ሰርስሬ
ይኸው እስከዛሬ፣
አጥንቴ እየበላኝ፣ አለሁልሽ(ህ) ፍቅሬ።
✅ያበደች የተረጋጋች ቅዳሜ
@lula_al_greeko
@getem ..
@getem
@getemsource
//ኑረዲን ዒሣ//
ስጋዬን ሲበላኝ በጥርሴ ነከስኩት
ቆዳዬን ሲበላኝ በጥፍሬ ፎከትኩት
እፎይ አስታገስኩት
ፀጥ ረጭ አረኩት።
የውስጥ አጥንቴ ግን ሲበላኝ ነዝንዞ
ሲነክሰኝ ጠዝጥዞ
ምንም አላረኩት
ምንም አላከኩት
ላልችል ችየ ቻልኩት።
አልፎክተው ነገር፣ ቆዳዬን መንቅሬ
አላኝከው ነገር፣ ስጋዬን ሰርስሬ
ይኸው እስከዛሬ፣
አጥንቴ እየበላኝ፣ አለሁልሽ(ህ) ፍቅሬ።
✅ያበደች የተረጋጋች ቅዳሜ
@lula_al_greeko
@getem ..
@getem
@getemsource
Forwarded from SPACE COMPUTER
" አለንጋ" የግጥም መድብል
ነገ ሰኔ 10/2010 ይመረቃል።
በገጣሚና ደራሲ ትዘዘው ክንዴ
"አለንጋ" የግጥም ስብስቦች
በዕለቱ ገጣሚያን ስራቸውንና የተመረጡ ከመፅሀፉ የተወሰዱ ግጥሞችን ያቀርባሉ።
ነገ እሁድ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሄራዊ ቤተመፅሀፍት እና ቤተመዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ የጥበብ ሰዎች በተገኙበት ይመረቃል።
እናንተም ተጋብዛችዋል
መግብያ በነፃ
@lula_al_greeko
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
ነገ ሰኔ 10/2010 ይመረቃል።
በገጣሚና ደራሲ ትዘዘው ክንዴ
"አለንጋ" የግጥም ስብስቦች
በዕለቱ ገጣሚያን ስራቸውንና የተመረጡ ከመፅሀፉ የተወሰዱ ግጥሞችን ያቀርባሉ።
ነገ እሁድ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሄራዊ ቤተመፅሀፍት እና ቤተመዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ የጥበብ ሰዎች በተገኙበት ይመረቃል።
እናንተም ተጋብዛችዋል
መግብያ በነፃ
@lula_al_greeko
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
አንተ የሌለህ እለት
ሰማይ ይታረሳል
ምድር ይታመሳል
መልካም እውነት ወርዶ
ሀሠት ይፀነሳል።
አንተ የሌለህ እለት
ጨረቃ አዘቅዝቃ
ወይ ምድር ትላለች
ፀሀይ ሰማይ ጠፍታ
ምድር ትቆማለች።
አንተ የሌለህ እለት
ውቅያኖሶች ሸሽተው
ምድርን ይከድናሉ
ነፍሳቱ ነጉደው
ምድርን ይመታሉ።
አንተ እዚህ ከሌለህ
ጉልበት ይለምሻል
ፍቅር ይቆሽሻል
ልቦች ይደማሉ
ሰዎች ይከዳሉ
መሞት ይመኛሉ።
ስለዚ አንተ ሰላም
አንተ የመኖር ተስፍ
ከኛ እርቀህ አትሂድ
ከኛ ዘንድ አትጥፍ።🙏🙏
........ ((ሊዱ))
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ሰማይ ይታረሳል
ምድር ይታመሳል
መልካም እውነት ወርዶ
ሀሠት ይፀነሳል።
አንተ የሌለህ እለት
ጨረቃ አዘቅዝቃ
ወይ ምድር ትላለች
ፀሀይ ሰማይ ጠፍታ
ምድር ትቆማለች።
አንተ የሌለህ እለት
ውቅያኖሶች ሸሽተው
ምድርን ይከድናሉ
ነፍሳቱ ነጉደው
ምድርን ይመታሉ።
አንተ እዚህ ከሌለህ
ጉልበት ይለምሻል
ፍቅር ይቆሽሻል
ልቦች ይደማሉ
ሰዎች ይከዳሉ
መሞት ይመኛሉ።
ስለዚ አንተ ሰላም
አንተ የመኖር ተስፍ
ከኛ እርቀህ አትሂድ
ከኛ ዘንድ አትጥፍ።🙏🙏
........ ((ሊዱ))
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ጨ ረ ቃ ....(ከ ጌታየ )
ጨረቃ...
አንዛብ በፈተለ
ቁር ባዘለ ንጋት፣
ባዲስ ሂወት ተስፋ
በፈገግታ ውህደት፣
ወይንም!
በነፍስ እልፊያ
በእስትንፋስ ጥምርት፡፡
ጎህ ሳይቀድ ፈንጥቆ
በተራራ ቁንጮ እንደሚወጣ አደይ፣
በውድቅቱ ሌሊት
በሰማይ አድማስ ላይ፣
.........ፈንድቀሽ ስትታይ፣
በክዋከብት ዓለም
በንግሰት ዘመንሽ፣
ቀና ብሎ ለሚያይ
አይቶ ለሚያደንቅሽ፣
በግዛትሽ ዙፋን
በደስታ ሰክረሻል፣
ላስተዋለሽ ደግሞ
በውብ ሳቅሽ መሀል
ሀዘን ሰንቀሻል፣
አንቺ ውብ ጨረቃ...
"
"
ስለ አንዳች ኩርፊያሽ
እንደ ማለዳ ጉም
ፍካትሽ ተነነ፣
የተከዘው ልብሽ
ሳቅሽን ተወነ፣
ይህ...ስለምን ሆነ?
ከዋከብት አዘኑ....!
"
"
ከዋከብት አዘኑ፣
ከ'ግርሽ ስር ተደፍተው
ማቅ ለብሰው ለመኑ፣
ቁጥር ፈታ በሚል
በጎለሰው ፊትሽ
ደመናው ተጨንቋል፣
ባይኖቹ ኮረጆ
እንባውን ሰንቋል፣
ነፋስ ተቆጥቶ
እሳትን አስንቋል፡፡
፡
እናም...
በዚች የምጥ ሌሊት
ከሰማይ ሰማይ ላታርጊ፣
በአርያምሽ ፀንተሽ
ለዘላለም ላትመስጊ፣
የፍንደቃ እንቁ ሳቅሽን
በዕንባሽ ግምጃ ስትሸሽጊ፣
፡
አንቺ ውብ ጨረቃ፣
ላላወቁሽ የፍንደቃ፣
.......የቡረቃ፣
ልብ ላሉሽ ደግሞ.....
የዕንባ ዶፍ የሳግ ሲቃ፣
፡
እናም..........በቃ!
በዚች ከንቱ አለም፣
ሞትሽን የሚሞት
ቤዛ ሚሆን የለም፣
፡
የዙፋንሽ አቻ
ባልንጀራሽ ፀሃይ፣
የዕንባሽን ትንፋገን
የውስጥሽን ስቃይ፣
...እንፋሎትሽን ሳታይ፣
ከተራሮች ጀርባ
እግሯን ዘርግታለች፣
ከሞቀው ዕልፍኟ
ሰላም ትሰብካለች፣
አ
ይ
ይ
__////____________
february 13/2010
.....☞[Getaye.T]
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ጨረቃ...
አንዛብ በፈተለ
ቁር ባዘለ ንጋት፣
ባዲስ ሂወት ተስፋ
በፈገግታ ውህደት፣
ወይንም!
በነፍስ እልፊያ
በእስትንፋስ ጥምርት፡፡
ጎህ ሳይቀድ ፈንጥቆ
በተራራ ቁንጮ እንደሚወጣ አደይ፣
በውድቅቱ ሌሊት
በሰማይ አድማስ ላይ፣
.........ፈንድቀሽ ስትታይ፣
በክዋከብት ዓለም
በንግሰት ዘመንሽ፣
ቀና ብሎ ለሚያይ
አይቶ ለሚያደንቅሽ፣
በግዛትሽ ዙፋን
በደስታ ሰክረሻል፣
ላስተዋለሽ ደግሞ
በውብ ሳቅሽ መሀል
ሀዘን ሰንቀሻል፣
አንቺ ውብ ጨረቃ...
"
"
ስለ አንዳች ኩርፊያሽ
እንደ ማለዳ ጉም
ፍካትሽ ተነነ፣
የተከዘው ልብሽ
ሳቅሽን ተወነ፣
ይህ...ስለምን ሆነ?
ከዋከብት አዘኑ....!
"
"
ከዋከብት አዘኑ፣
ከ'ግርሽ ስር ተደፍተው
ማቅ ለብሰው ለመኑ፣
ቁጥር ፈታ በሚል
በጎለሰው ፊትሽ
ደመናው ተጨንቋል፣
ባይኖቹ ኮረጆ
እንባውን ሰንቋል፣
ነፋስ ተቆጥቶ
እሳትን አስንቋል፡፡
፡
እናም...
በዚች የምጥ ሌሊት
ከሰማይ ሰማይ ላታርጊ፣
በአርያምሽ ፀንተሽ
ለዘላለም ላትመስጊ፣
የፍንደቃ እንቁ ሳቅሽን
በዕንባሽ ግምጃ ስትሸሽጊ፣
፡
አንቺ ውብ ጨረቃ፣
ላላወቁሽ የፍንደቃ፣
.......የቡረቃ፣
ልብ ላሉሽ ደግሞ.....
የዕንባ ዶፍ የሳግ ሲቃ፣
፡
እናም..........በቃ!
በዚች ከንቱ አለም፣
ሞትሽን የሚሞት
ቤዛ ሚሆን የለም፣
፡
የዙፋንሽ አቻ
ባልንጀራሽ ፀሃይ፣
የዕንባሽን ትንፋገን
የውስጥሽን ስቃይ፣
...እንፋሎትሽን ሳታይ፣
ከተራሮች ጀርባ
እግሯን ዘርግታለች፣
ከሞቀው ዕልፍኟ
ሰላም ትሰብካለች፣
አ
ይ
ይ
__////____________
february 13/2010
.....☞[Getaye.T]
@getem_sourcebot
@getem
@getem
አለቀ! !!!!
በሮቹ ልግመኛ፤ ገበሬው ደንቆሮ ፤
አይናገርም ወይ፤ ዘር አለቀ ብሎ! !!!!!!!!
በየበራበሩ ፤
ዘር እየበተነ ፤
ና ግባ ና ውጣ ሲል እየሰማሁት ፤
ሸረኛው ገበሬ ፤
የጠመደበትን ስፍራውን አጣሁት ።
ይህን ቆፍጣና ልጅ ፤
ደንዳናውን መሬት ፤
እያለሰለሰ በመላ በዘዴ ፤
አዲሱን ገበሬ ፤
ዘር ዘር አርገህ ዝራ ፤
ብሎ ማደናገር ሼም አይደለም እንዴ? ??
(( ጃ ኖ )))
@balmbaras
@getem
@getem
በሮቹ ልግመኛ፤ ገበሬው ደንቆሮ ፤
አይናገርም ወይ፤ ዘር አለቀ ብሎ! !!!!!!!!
በየበራበሩ ፤
ዘር እየበተነ ፤
ና ግባ ና ውጣ ሲል እየሰማሁት ፤
ሸረኛው ገበሬ ፤
የጠመደበትን ስፍራውን አጣሁት ።
ይህን ቆፍጣና ልጅ ፤
ደንዳናውን መሬት ፤
እያለሰለሰ በመላ በዘዴ ፤
አዲሱን ገበሬ ፤
ዘር ዘር አርገህ ዝራ ፤
ብሎ ማደናገር ሼም አይደለም እንዴ? ??
(( ጃ ኖ )))
@balmbaras
@getem
@getem
"ሞሪንጋ! !!!!
የፈረንጅ ሞሪንጋ ፤
ስንት አይነት በሽታ ሰርክ እየፈወሰ ፤
የኛ ሃገር ሺፈራው ፤
በየበራበሩ ብዙ ሰው ጨረሰ ።
(( ጃ ኖ ))
@balmbaras
@getem
@getem
የፈረንጅ ሞሪንጋ ፤
ስንት አይነት በሽታ ሰርክ እየፈወሰ ፤
የኛ ሃገር ሺፈራው ፤
በየበራበሩ ብዙ ሰው ጨረሰ ።
(( ጃ ኖ ))
@balmbaras
@getem
@getem
የቀበሮ ፀሎት
(ታገል ሰይፉ)
------
እባክህ አምላኬ- ብትሬን ቀባና
እኔም ልወዝወዘው-የሙሴን ጎዳና
ያላንዳች ፍርሃት-ያለምንም ችግር
ባህሩን ከፍዬ- ህዝቤን እንዳሻግር፡፡
*
አቤት የኔ ጌታ ይህም አያረካም
በቃልህ ታምኜ -ከሆንኩልህ መልካም
ለእኔም ፍቀድልኝ-ያብራምን ምልክት
ከምድር አሸዋ-ዘሬ እንዲበረክት፡፡
*
አቤቱ ምን ልሁን-ይህም አልጠቀመኝ
እስቲ እንደ ዮናስ-ህዝብ ፊት አቁመኝ
*
ትንቢቴን ሰምቶልኝ-ሀገር ይተራመስ
ሰው እህል ይጡም-ከብቱም ሳር አይቅመስ፡፡
ይህም አያረካም-ይልቅ እንደዳዊት
አንተን በሚፈራ-ብዙ ሺህ ሠራዊት
ዙፋኔ ተከቦ-በደስታ እንዳመልክህ
የዚህን ሰው ኮከብ -አውጣልኝ እባክህ
*
አደራህን ታዲያ- ጭንቅ አትወድም ነፍሴ
ልመናዬን ሰምተህ-ካደረግከኝ ሙሴ
መከራውን ማረኝ-ያርባ ዓመት ስደቱን
በሲና በረሃ-መራብ መጠማቱን፡፡
*
ነቢዩ ዮናስን -አርገህም ስትፈጥረኝ
የባህሩን ፍዳ- ያሳውን ሆድ ማረኝ፡፡
*
አብረሃምን ሆኜም-በደስታ ሳመልክህ
ልጅህን እረደው-አትበለኝ እባክህ፡፡
***
የዲዊትም ኮከብ-በኔ ላይ ሲወጣ
እባክህ አምላኬ -ጎልያድ አይምጣ፡፡
@getem_sourcebot
@getem
@getem
(ታገል ሰይፉ)
------
እባክህ አምላኬ- ብትሬን ቀባና
እኔም ልወዝወዘው-የሙሴን ጎዳና
ያላንዳች ፍርሃት-ያለምንም ችግር
ባህሩን ከፍዬ- ህዝቤን እንዳሻግር፡፡
*
አቤት የኔ ጌታ ይህም አያረካም
በቃልህ ታምኜ -ከሆንኩልህ መልካም
ለእኔም ፍቀድልኝ-ያብራምን ምልክት
ከምድር አሸዋ-ዘሬ እንዲበረክት፡፡
*
አቤቱ ምን ልሁን-ይህም አልጠቀመኝ
እስቲ እንደ ዮናስ-ህዝብ ፊት አቁመኝ
*
ትንቢቴን ሰምቶልኝ-ሀገር ይተራመስ
ሰው እህል ይጡም-ከብቱም ሳር አይቅመስ፡፡
ይህም አያረካም-ይልቅ እንደዳዊት
አንተን በሚፈራ-ብዙ ሺህ ሠራዊት
ዙፋኔ ተከቦ-በደስታ እንዳመልክህ
የዚህን ሰው ኮከብ -አውጣልኝ እባክህ
*
አደራህን ታዲያ- ጭንቅ አትወድም ነፍሴ
ልመናዬን ሰምተህ-ካደረግከኝ ሙሴ
መከራውን ማረኝ-ያርባ ዓመት ስደቱን
በሲና በረሃ-መራብ መጠማቱን፡፡
*
ነቢዩ ዮናስን -አርገህም ስትፈጥረኝ
የባህሩን ፍዳ- ያሳውን ሆድ ማረኝ፡፡
*
አብረሃምን ሆኜም-በደስታ ሳመልክህ
ልጅህን እረደው-አትበለኝ እባክህ፡፡
***
የዲዊትም ኮከብ-በኔ ላይ ሲወጣ
እባክህ አምላኬ -ጎልያድ አይምጣ፡፡
@getem_sourcebot
@getem
@getem
👍1
አዝራር እና ንጋት
(ተገጠመ በዳንኤል ስዩም)
፡
፡
ሸሚዝ እወዳለሁ
በተለይ በተለይ አንቺ ከለበሽው
በተለይ በተለይ
እኔም እንዳይጨንቀኝ
አንቺም እንዳይጨንቅሽ
አንድ ሁለቱን አዝራር ፣ ፈተሽ ከለቀቅሽው
ጠይም እወዳለሁ
በተለይ በተለይ ፣ አንቺ እንደጠየምሸው
............
ይህ በእንዲህ እነዳለ...
እነሆ በቀደም ፣ ሸሚዝ ለብሰሽልኝ
ሁለት አዝራር ከፍተሽ ፣ ስሬ ወድቀሽልኝ
በፍቅራችን መሐል
እኔም እንደዘበት
ሁለት አዝራር ብከፍት ፣ ውበትን ፍለጋ
ብርሐን ሞላው ፊቴን...
ጠይም ደረትሽ ላይ ፣ ሁለት ፀሐይ ነጋ ።
@getemsource
@getem
@getem
(ተገጠመ በዳንኤል ስዩም)
፡
፡
ሸሚዝ እወዳለሁ
በተለይ በተለይ አንቺ ከለበሽው
በተለይ በተለይ
እኔም እንዳይጨንቀኝ
አንቺም እንዳይጨንቅሽ
አንድ ሁለቱን አዝራር ፣ ፈተሽ ከለቀቅሽው
ጠይም እወዳለሁ
በተለይ በተለይ ፣ አንቺ እንደጠየምሸው
............
ይህ በእንዲህ እነዳለ...
እነሆ በቀደም ፣ ሸሚዝ ለብሰሽልኝ
ሁለት አዝራር ከፍተሽ ፣ ስሬ ወድቀሽልኝ
በፍቅራችን መሐል
እኔም እንደዘበት
ሁለት አዝራር ብከፍት ፣ ውበትን ፍለጋ
ብርሐን ሞላው ፊቴን...
ጠይም ደረትሽ ላይ ፣ ሁለት ፀሐይ ነጋ ።
@getemsource
@getem
@getem
ምስክር ነበረኝ(ፈራጅ ዳኛ ባገኝ)
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ለጉዳቴ መጠን ፍትህ የሚከፍለኝ
ስለውነት የሚፈርድ ፈራጅ ዳኛ ባገኝ
ክሴንማ አስረጂ ምስክር ነበረኝ
፡
አንደኛ ምስክር ትሁነኝ ጨረቃ
ደምቃ ምትታየው እኛ ስንስቅ ስቃ
ስንት ያወራንባት ስንት የመከርንባት
ላትከጂኝ ላልከዳሽ የተማማልንባት
.
አሁንማ ባየሽ ስትሄጂ ከፍቷታል
መሳቅ አቁማለች እንደኔው አርጓታል
በመቅረትሽ ዜና እንደኔው አዝናለች
ዳኛ ይገኝ እንጂ...ዳኛ ይገኝ እንጂ ትመሰክራለች
፡
ሁለተኛ ደሞ ያቺን ካፌ አድርጊያት
በልጅነት ጊዜ ስንቱን ያየንባት
ገብትን ለመዝናናት ሳንቲም ስለሚያጥረን
ለሁለት የምንጠጣው አንድ ምሪንዳ አዘን
አነዛም ጊዜያት በፍቅር ተባርከው
ብንደፋው አያልቅም እንኳን ጠጥተነው
.
እናም ያቺም ካፌ ፍቅራችን አይታለች
እንደ ስኳር ጣፍጧት ቃላችን ሰምታለች
ዳኛ ይገኝ እንጂ...ዳኛ ይገኝ እንጂ ትመሰክራለች
፡
ያቺን የውሃ ምንጭ የተራጨንባት
የፍቅራችን ጠበል የተጠመቅንባት
ይህንን አይታለች ሶስተኛ ትሁነን
ቀለበት ሰርተናል ዘንባባውን ቀጥፈን
ቃል ኪዳን ገብተናል ወፎቹን አድመን
.
እናማልሽ ውዴ ይህን ታስታውሳለች
ዳኛ ይገኝ እንጂ...ዳኛ ይገኝ እንጂ ትመሰክራለች
፡
ዘርዝር ካልሽኝ ደሞ እንኪ በየተራ
ለሁለት ያጠገበን ያ ኩርማን አንጀራ
ጉንፋን ስለያዘኝ የተሳልሺው ሻማ
እንቅልፍ እንቢ ሲልሽ የማዜመው ዜማ
ያ ጥርጊያ ያ መንገድ ያ የዋርካ ዛፉ
አቦ አታስለፍልፊኝ ዳኛ በለለበት ትዝብት ነው ትርፉ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
፡፡፡፡፡፡፡መኖር ደጉ(ዳዊት)
@getem
@getem
@lula_al_greeko
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ለጉዳቴ መጠን ፍትህ የሚከፍለኝ
ስለውነት የሚፈርድ ፈራጅ ዳኛ ባገኝ
ክሴንማ አስረጂ ምስክር ነበረኝ
፡
አንደኛ ምስክር ትሁነኝ ጨረቃ
ደምቃ ምትታየው እኛ ስንስቅ ስቃ
ስንት ያወራንባት ስንት የመከርንባት
ላትከጂኝ ላልከዳሽ የተማማልንባት
.
አሁንማ ባየሽ ስትሄጂ ከፍቷታል
መሳቅ አቁማለች እንደኔው አርጓታል
በመቅረትሽ ዜና እንደኔው አዝናለች
ዳኛ ይገኝ እንጂ...ዳኛ ይገኝ እንጂ ትመሰክራለች
፡
ሁለተኛ ደሞ ያቺን ካፌ አድርጊያት
በልጅነት ጊዜ ስንቱን ያየንባት
ገብትን ለመዝናናት ሳንቲም ስለሚያጥረን
ለሁለት የምንጠጣው አንድ ምሪንዳ አዘን
አነዛም ጊዜያት በፍቅር ተባርከው
ብንደፋው አያልቅም እንኳን ጠጥተነው
.
እናም ያቺም ካፌ ፍቅራችን አይታለች
እንደ ስኳር ጣፍጧት ቃላችን ሰምታለች
ዳኛ ይገኝ እንጂ...ዳኛ ይገኝ እንጂ ትመሰክራለች
፡
ያቺን የውሃ ምንጭ የተራጨንባት
የፍቅራችን ጠበል የተጠመቅንባት
ይህንን አይታለች ሶስተኛ ትሁነን
ቀለበት ሰርተናል ዘንባባውን ቀጥፈን
ቃል ኪዳን ገብተናል ወፎቹን አድመን
.
እናማልሽ ውዴ ይህን ታስታውሳለች
ዳኛ ይገኝ እንጂ...ዳኛ ይገኝ እንጂ ትመሰክራለች
፡
ዘርዝር ካልሽኝ ደሞ እንኪ በየተራ
ለሁለት ያጠገበን ያ ኩርማን አንጀራ
ጉንፋን ስለያዘኝ የተሳልሺው ሻማ
እንቅልፍ እንቢ ሲልሽ የማዜመው ዜማ
ያ ጥርጊያ ያ መንገድ ያ የዋርካ ዛፉ
አቦ አታስለፍልፊኝ ዳኛ በለለበት ትዝብት ነው ትርፉ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
፡፡፡፡፡፡፡መኖር ደጉ(ዳዊት)
@getem
@getem
@lula_al_greeko
እግሮቼን ያፀናል!!!!!!
ከዘመናት በፊት አለም ሳትፈጠር፤
ከናንተ ወገብ ላይ፤
እትብቴ እንዲሰራ፤
በሰማዩ ጌታ፤ ተፅፎልኝ ነበር።
እሰየው ተመስገን፤
ይኸው ደግሞ ዛሬ፤
አደራ ልጆቼን ፤
የሚለው ምህላችሁ፤
ያ ምርቃታችሁ፤መች ተለይኝና፤
በህይወት ባህር ፊት፤
የእናቴ ምርቃት፤
የአባቴ ቡራኬ፤ ሆኖኝ ለእግሬ ዳና፤
ተሻገር እያለኝ፤
እለፈው እያለ፤
እግሮቼን ያፀናል፤ ዛሬም እንደገና።
(( ጃ ኖ ))
የናንተ ቀን አንድ ቀን ብቻ አይደለም ዘላለም ነው!!!!!
@balmbaras
@getem
@getem
ከዘመናት በፊት አለም ሳትፈጠር፤
ከናንተ ወገብ ላይ፤
እትብቴ እንዲሰራ፤
በሰማዩ ጌታ፤ ተፅፎልኝ ነበር።
እሰየው ተመስገን፤
ይኸው ደግሞ ዛሬ፤
አደራ ልጆቼን ፤
የሚለው ምህላችሁ፤
ያ ምርቃታችሁ፤መች ተለይኝና፤
በህይወት ባህር ፊት፤
የእናቴ ምርቃት፤
የአባቴ ቡራኬ፤ ሆኖኝ ለእግሬ ዳና፤
ተሻገር እያለኝ፤
እለፈው እያለ፤
እግሮቼን ያፀናል፤ ዛሬም እንደገና።
(( ጃ ኖ ))
የናንተ ቀን አንድ ቀን ብቻ አይደለም ዘላለም ነው!!!!!
@balmbaras
@getem
@getem
# ግራ_የገባው_ቀኝ
፡
ንጋት እስከሚሆን ከንጋት ጀምሮ
ዘራሰብ ሲፋጠን ሲጓዝ ወደ ድሮ፣
ባለው ነፃ ፈቃድ በተሰጠው ስልጣን
ለመልኣክ ተስሎ ገብሮ ለሰይጣን፣
ትላንት ያጣሁትን ነገ አገኘው ብሎ
ቀናትን ሲሻገር በድር ተንጠልጥሎ፤
፡
ያረዘመው ተስፋው በመታገስ ቅባት
ከሆዱ አላልፍ ሲል እንዳንገት ክራባት፣
ለማቆየት ብቻ፣
ለማሠንበት ብቻ፣
ላም ያለች በሰማይ
ወተቷን ላታሳይ፣
አልፎ ሃጅ ዳመና ሰማዩን ሲዞረው
አካፍቶ ዞር ሊል ዘንቦ ላያሽረው፣
፡
እረፍት የነፈጉት
ባይተዋር ያረጉት ምስጢራት ሲፈቱ
ደሞ ሌላ ትንግርት ሲደቀን እፊቱ፣
ግራ ዘፈን አዝማች
መርዶ እና ምስራች
በሁለት በኩል ጠምዶት
መሳቅ ማልቀስ ከብዶት፣
፡
ህልሙ በቀን ሦስቴ ሲኮስስ ሲጎላ
ቅርፁን ሲለዋውጥ እንደ ጀምበር ጥላ፣
ከውሃ እና ከእሳት ጎዳናው ሲዋቀር
መኖርም መሞትም ሳይቻለው ሲቀር፣
ምስጋና እና ምሬት ከከንፈር ላይ ሸሹ
'ምንም አይልም' ሆነ ሰው ሁሉ ምላሹ።
----------------------//-----------------------
(ከ በርናባስ ከበደ )
@getem_sourcebot
@getem
@getem
፡
ንጋት እስከሚሆን ከንጋት ጀምሮ
ዘራሰብ ሲፋጠን ሲጓዝ ወደ ድሮ፣
ባለው ነፃ ፈቃድ በተሰጠው ስልጣን
ለመልኣክ ተስሎ ገብሮ ለሰይጣን፣
ትላንት ያጣሁትን ነገ አገኘው ብሎ
ቀናትን ሲሻገር በድር ተንጠልጥሎ፤
፡
ያረዘመው ተስፋው በመታገስ ቅባት
ከሆዱ አላልፍ ሲል እንዳንገት ክራባት፣
ለማቆየት ብቻ፣
ለማሠንበት ብቻ፣
ላም ያለች በሰማይ
ወተቷን ላታሳይ፣
አልፎ ሃጅ ዳመና ሰማዩን ሲዞረው
አካፍቶ ዞር ሊል ዘንቦ ላያሽረው፣
፡
እረፍት የነፈጉት
ባይተዋር ያረጉት ምስጢራት ሲፈቱ
ደሞ ሌላ ትንግርት ሲደቀን እፊቱ፣
ግራ ዘፈን አዝማች
መርዶ እና ምስራች
በሁለት በኩል ጠምዶት
መሳቅ ማልቀስ ከብዶት፣
፡
ህልሙ በቀን ሦስቴ ሲኮስስ ሲጎላ
ቅርፁን ሲለዋውጥ እንደ ጀምበር ጥላ፣
ከውሃ እና ከእሳት ጎዳናው ሲዋቀር
መኖርም መሞትም ሳይቻለው ሲቀር፣
ምስጋና እና ምሬት ከከንፈር ላይ ሸሹ
'ምንም አይልም' ሆነ ሰው ሁሉ ምላሹ።
----------------------//-----------------------
(ከ በርናባስ ከበደ )
@getem_sourcebot
@getem
@getem
📙ውድ የዚህ ቻነል ተከታዮች እንዴት ናችሁ? እንደሚታወቀው ቻነሎቻችን እስከዛሬ ድረስ በተቻላቸው መጠን የተመረጡ:
✅ግጥሞችን (@getem)እና
✅ወጎችን (@wegoch) ፣ሲያቀርቡላችሁ ቆይተዋል የህ እንዳለ ሆኖ በቀርብ ቀን ደሞ አድማሳቸውን ሰፋ አድርገው የተወደዱና የተመረጡ ግጥሞችን እና ወጎችን ከ ሚኪ pictures (@mykeypictures) ጋር በመተባበር በከፍተኛ ጥራት በፎቶ ይዘዉላችሁ ሊቀርቡ ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል።
ከግጥም ብቻ እና ወግ ብቻ
(@lula_al_greeko)
Mykey ምስሎች
(@mykey21)
✅ግጥሞችን (@getem)እና
✅ወጎችን (@wegoch) ፣ሲያቀርቡላችሁ ቆይተዋል የህ እንዳለ ሆኖ በቀርብ ቀን ደሞ አድማሳቸውን ሰፋ አድርገው የተወደዱና የተመረጡ ግጥሞችን እና ወጎችን ከ ሚኪ pictures (@mykeypictures) ጋር በመተባበር በከፍተኛ ጥራት በፎቶ ይዘዉላችሁ ሊቀርቡ ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል።
ከግጥም ብቻ እና ወግ ብቻ
(@lula_al_greeko)
Mykey ምስሎች
(@mykey21)
❤1