ገጠር ለምትኖረው ወንድሜ
እንደምን ነህ ክንዴ
እኔ አለሁ በደህና
ልጆች ደህና ናቸው
ጫቅሎቹ በሙላ?
~~~~~~~~~
ከብቶችሳ ክንዴ ደህና ተዋልደዋል?
ጎረቤቱ ሁላስ በደህና ከርመዋል
~~~~~~~~~
ሰብሉስ ያፈራል ማሳውስ እንዴት ነው
ዩርያውና ዳፑን በደምብ ለመደው
~~~~~~~~~
ሽምብራና ጤፉስ ጎተራ ይሞላል
ቅቤና ወተቱስ ለወዳጅ ይተርፋል
~~~~~~~~~
ድሮ እንደነበረው
አልፎ ሃጅ እንግዳስ ተቤትህ ይገባል
እግሩን ይታጠባል ቡን ይፈላለታል
ተሸቱ ተማሩ እስቲጠግብ ይበላል
~~~~~~~~~
ብቻ ኸመስገን ነው እንደሱ ተሆነ
ባሕልና ወጉ ታልተበታተነ
~~~~~~~~~
የኔን ነገር ተወው
የከተሜ ነገር ምንም ጥሩ የለው
ክፉም እንዳልለው
ቡላሌ አጥልቄአለው
ለውርጩ የሚሆን ጨርቅ ቀይሬአለው
ታዲያ ምን ያደርጋል
የሰው የመኪናው ጫጫታው ከብዶኛል
ታምቡሬ ተዛብቶ በሽታ ሁኖኛል
አካሌም ደንዝዟል
ጉልበቴ ሟሙቷል
~~~~~~~~~
ተይችና ተይች የግር ጉዞ የለም
እድሜ ለመኪና ስንዝር ይዞህ እልም
~~~~~~~~~
ነዳጅ ታገር ጠፍቶ ሰው በግሩ የሄደ ለት
በጨርቅ ታጅሎ ይቀራል ለሳምንት
አይመጣም መስሪያ ቤት
~~~~~~~~~
አይ ከተሜ ጀግናው ምኑን እንደበላው
ጣይ ነካ ታረገው ወዲያው ሽብልል ነው
~~~~~~~~~
የምግቡን ነገር ተወኝ ወንድማለም
ለመኖር ነው እንጂ ጠግቦ መብላት የለም
~~~~~~~~~
እንጀራውም ተፌስታሉ ሳስቷል
ለያውም ጀሶ የንጨት ብናኝ ይጨምሩበታል
~~~~~~~~~
አብሮ መብላት የለም ጎረቤት ተጣርቶ
ለራስ መጎድጎድ ነው ደጁነን ዘጋግቶ
~~~~~~~~~
ስማ ወንድማለም ሰው በጣም ረክሷል
እምነት የለለውን ሐይማኖት አብዝቷል
~~~~~~~~~
ኑሮው ውድ ሆነና ቲበዛ ችግሩ
ሰው መስራት አቆመ ላገሩ ለክብሩ
~~~~~~~~~
ይልቅ ለነጮቹ ተወዲያ ላሉቱ
ሰው ያከማቻሉ በብር ሚሸጡቱ
~~~~~~~~~
አሁን አሁንማ ብቻውን ሚያወራው
የቀወሰው በዝቷል
አዛኝ የለም እንጂ ሰው በቁሙ ሞቷል
~~~~~~~~~
ይገርምሃል ክንዴ
የከብት ማዋያው ሜዳው ሁሉ ጠፍቷል
ሰማይ የሚነካ ቤት ሰርተውበታል
~~~~~~~~~
ታዲያ እንዲህ ያለውን ቤት የሰሩት ሰዎች
እግዜር ቅርባቸው ነው
ሆዳቸው ት..........ል.........ቅ ነው
~~~~~~~~~
ሌላ ቤት ጭማሪ የፈለጉ እንደሁማ
ለቸሩ ፈጣሪ ወተው ይነግሩታል ተቤታቸው ማማ
እርሱም ቸር ነውና ለቅርብ የሚሰማ
~~~~~~~~~
ያሉትን በሙሉ ውሰዱ ይላቸዋል
የምድር ድካማቸውን ያከማችላቸዋል
በሕንጻ ስራቸው ያፈሰሱትን ደም ይቆጥርላቸዋል
~~~~~~~~~
እናልህ ወንድሜ
አገር አምሮበታል!
ሰው ግን ደክሞታል!
~~~~~~~~~
እናም ሁሉን ትቼ ወደ ገጠር
ልመጣ ነው እልኃለሁ
እኔ ባልከብር እንኳ አገር አከብራለሁ!!!።
~~~~~~~~~//~~~~~~~~~~
## ኤፍሬም አለም ##
@ ጎንደር አዘዞ
@getem_sourcebot
@getem
@getem
እንደምን ነህ ክንዴ
እኔ አለሁ በደህና
ልጆች ደህና ናቸው
ጫቅሎቹ በሙላ?
~~~~~~~~~
ከብቶችሳ ክንዴ ደህና ተዋልደዋል?
ጎረቤቱ ሁላስ በደህና ከርመዋል
~~~~~~~~~
ሰብሉስ ያፈራል ማሳውስ እንዴት ነው
ዩርያውና ዳፑን በደምብ ለመደው
~~~~~~~~~
ሽምብራና ጤፉስ ጎተራ ይሞላል
ቅቤና ወተቱስ ለወዳጅ ይተርፋል
~~~~~~~~~
ድሮ እንደነበረው
አልፎ ሃጅ እንግዳስ ተቤትህ ይገባል
እግሩን ይታጠባል ቡን ይፈላለታል
ተሸቱ ተማሩ እስቲጠግብ ይበላል
~~~~~~~~~
ብቻ ኸመስገን ነው እንደሱ ተሆነ
ባሕልና ወጉ ታልተበታተነ
~~~~~~~~~
የኔን ነገር ተወው
የከተሜ ነገር ምንም ጥሩ የለው
ክፉም እንዳልለው
ቡላሌ አጥልቄአለው
ለውርጩ የሚሆን ጨርቅ ቀይሬአለው
ታዲያ ምን ያደርጋል
የሰው የመኪናው ጫጫታው ከብዶኛል
ታምቡሬ ተዛብቶ በሽታ ሁኖኛል
አካሌም ደንዝዟል
ጉልበቴ ሟሙቷል
~~~~~~~~~
ተይችና ተይች የግር ጉዞ የለም
እድሜ ለመኪና ስንዝር ይዞህ እልም
~~~~~~~~~
ነዳጅ ታገር ጠፍቶ ሰው በግሩ የሄደ ለት
በጨርቅ ታጅሎ ይቀራል ለሳምንት
አይመጣም መስሪያ ቤት
~~~~~~~~~
አይ ከተሜ ጀግናው ምኑን እንደበላው
ጣይ ነካ ታረገው ወዲያው ሽብልል ነው
~~~~~~~~~
የምግቡን ነገር ተወኝ ወንድማለም
ለመኖር ነው እንጂ ጠግቦ መብላት የለም
~~~~~~~~~
እንጀራውም ተፌስታሉ ሳስቷል
ለያውም ጀሶ የንጨት ብናኝ ይጨምሩበታል
~~~~~~~~~
አብሮ መብላት የለም ጎረቤት ተጣርቶ
ለራስ መጎድጎድ ነው ደጁነን ዘጋግቶ
~~~~~~~~~
ስማ ወንድማለም ሰው በጣም ረክሷል
እምነት የለለውን ሐይማኖት አብዝቷል
~~~~~~~~~
ኑሮው ውድ ሆነና ቲበዛ ችግሩ
ሰው መስራት አቆመ ላገሩ ለክብሩ
~~~~~~~~~
ይልቅ ለነጮቹ ተወዲያ ላሉቱ
ሰው ያከማቻሉ በብር ሚሸጡቱ
~~~~~~~~~
አሁን አሁንማ ብቻውን ሚያወራው
የቀወሰው በዝቷል
አዛኝ የለም እንጂ ሰው በቁሙ ሞቷል
~~~~~~~~~
ይገርምሃል ክንዴ
የከብት ማዋያው ሜዳው ሁሉ ጠፍቷል
ሰማይ የሚነካ ቤት ሰርተውበታል
~~~~~~~~~
ታዲያ እንዲህ ያለውን ቤት የሰሩት ሰዎች
እግዜር ቅርባቸው ነው
ሆዳቸው ት..........ል.........ቅ ነው
~~~~~~~~~
ሌላ ቤት ጭማሪ የፈለጉ እንደሁማ
ለቸሩ ፈጣሪ ወተው ይነግሩታል ተቤታቸው ማማ
እርሱም ቸር ነውና ለቅርብ የሚሰማ
~~~~~~~~~
ያሉትን በሙሉ ውሰዱ ይላቸዋል
የምድር ድካማቸውን ያከማችላቸዋል
በሕንጻ ስራቸው ያፈሰሱትን ደም ይቆጥርላቸዋል
~~~~~~~~~
እናልህ ወንድሜ
አገር አምሮበታል!
ሰው ግን ደክሞታል!
~~~~~~~~~
እናም ሁሉን ትቼ ወደ ገጠር
ልመጣ ነው እልኃለሁ
እኔ ባልከብር እንኳ አገር አከብራለሁ!!!።
~~~~~~~~~//~~~~~~~~~~
## ኤፍሬም አለም ##
@ ጎንደር አዘዞ
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ግብር ከፋይ ግጥም
(ልዑል ሀይሌ)
ጥያቄ አለኝ ላንቺ!
70 ዓመት ለመኖር 50 ዓመት መበደር
50 ለመበደር 20 ዓመት መታሰር
የተፈረደ ሰው
ባልኖረው ኑረት ውስጥ
የቱ ጥያቄ ነው
ግብር ተከፍሎበት ቶሎ ሚመለሰው?
.
ከእናት ሆድ ሲወጣ ለማይኖረው ዕድሜ
ቶሎ ለሚቀጠፍ ቶሎ ለሚሰበር
ለምን ነው ንገሪኝ ከገላው ተቆርጦ ዕትብቱ ሚቀበር?
.
ሌላም ጥያቄ አለኝ!
በፍቅር ንግድ ዓለም
ዕልፍ ትዝታዎች ገዝቶ ላተረፈ
በዋጋ ግሽበት ውስጥ
የዕምነቱን ሱቆች ከስሮ ለቆለፈ
በግብር ትመና ከሽያጩ በላይ
ግብር እንዲከፍል የተፈረደ ሰው
የቱ ጥያቄ ነው ቶሎ ሚመለሰው?
.
ሌላም ጥያቄ አለኝ!
ላንቺ ሳቅ ፈገግታ ጥርስን ሸጦ ማደር
ላንቺ ቁመት መርዘም መሰላል መበደር
አፈር እንዳይነካሽ 'ኮብልስቶን ማንጠፍ'
ስጦታ እንዳያምርሽ ፅጌረዳ መቅጠፍ
ላንቺ ሕይወት ሲባል
ሕይወቱን በመክፈል ለተፈረደ ሰው
ባልኖረው ኑረት ውስጥ
የቱ ጥያቄ ነው ቶሎ ሚመለሰው?
የቱ ጥያቄ ነው?
መወለድ ምንድነው?
መልስሽን አውቃለሁ ቋንቋ ነው ትያለሽ
ዘር መቁጠሩን ተዪ ከቋንቋ ምን አለሽ?
ይልቅ መልሺልኝ
መወለድ ምንድነው?
ማንነት ምንድነው?
መሞትስ ምንድነው?
ከነዚህ መካከል ቅድሚያ የሚመለስ
ግብር ምከፍልበት ጥያቄ የቱ ነው?
ሌላም ጥያቄ አለኝ?
እስካሁን ለፃፍኩት ለገለጥኩት ሃሳብ
በጥያቄ አንድምታ
ግብሩን ገምቺልኝ ስንት ስንኝ ልክፈል
የስንቱን ቤት ልምታ?
@getem_sourcebot
@getem
@getem
(ልዑል ሀይሌ)
ጥያቄ አለኝ ላንቺ!
70 ዓመት ለመኖር 50 ዓመት መበደር
50 ለመበደር 20 ዓመት መታሰር
የተፈረደ ሰው
ባልኖረው ኑረት ውስጥ
የቱ ጥያቄ ነው
ግብር ተከፍሎበት ቶሎ ሚመለሰው?
.
ከእናት ሆድ ሲወጣ ለማይኖረው ዕድሜ
ቶሎ ለሚቀጠፍ ቶሎ ለሚሰበር
ለምን ነው ንገሪኝ ከገላው ተቆርጦ ዕትብቱ ሚቀበር?
.
ሌላም ጥያቄ አለኝ!
በፍቅር ንግድ ዓለም
ዕልፍ ትዝታዎች ገዝቶ ላተረፈ
በዋጋ ግሽበት ውስጥ
የዕምነቱን ሱቆች ከስሮ ለቆለፈ
በግብር ትመና ከሽያጩ በላይ
ግብር እንዲከፍል የተፈረደ ሰው
የቱ ጥያቄ ነው ቶሎ ሚመለሰው?
.
ሌላም ጥያቄ አለኝ!
ላንቺ ሳቅ ፈገግታ ጥርስን ሸጦ ማደር
ላንቺ ቁመት መርዘም መሰላል መበደር
አፈር እንዳይነካሽ 'ኮብልስቶን ማንጠፍ'
ስጦታ እንዳያምርሽ ፅጌረዳ መቅጠፍ
ላንቺ ሕይወት ሲባል
ሕይወቱን በመክፈል ለተፈረደ ሰው
ባልኖረው ኑረት ውስጥ
የቱ ጥያቄ ነው ቶሎ ሚመለሰው?
የቱ ጥያቄ ነው?
መወለድ ምንድነው?
መልስሽን አውቃለሁ ቋንቋ ነው ትያለሽ
ዘር መቁጠሩን ተዪ ከቋንቋ ምን አለሽ?
ይልቅ መልሺልኝ
መወለድ ምንድነው?
ማንነት ምንድነው?
መሞትስ ምንድነው?
ከነዚህ መካከል ቅድሚያ የሚመለስ
ግብር ምከፍልበት ጥያቄ የቱ ነው?
ሌላም ጥያቄ አለኝ?
እስካሁን ለፃፍኩት ለገለጥኩት ሃሳብ
በጥያቄ አንድምታ
ግብሩን ገምቺልኝ ስንት ስንኝ ልክፈል
የስንቱን ቤት ልምታ?
@getem_sourcebot
@getem
@getem
👍2
ናፍቆትሽ ቀለም ነው
ዛሬ ባትኖሪ - ካካሌ ብትርቂ - አለሽ ከመንፈሴ
ኑሮን ምኖርብሽ - ተስፋን ማልምብሽ - የለት ተቀን ሱሴ
ቀለሜ ነሽ ለኔ - ያውም የተዋበ - ህብር ቀለም ያለው
ለአይን ማራኪ - አግራሞት ፈጣሪ - ብዙ ፍቅር ያለው
ብዙ መውደድ ያለው
ናፍቆትሽ ቀለም ነው!
#አሹ2010
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ዛሬ ባትኖሪ - ካካሌ ብትርቂ - አለሽ ከመንፈሴ
ኑሮን ምኖርብሽ - ተስፋን ማልምብሽ - የለት ተቀን ሱሴ
ቀለሜ ነሽ ለኔ - ያውም የተዋበ - ህብር ቀለም ያለው
ለአይን ማራኪ - አግራሞት ፈጣሪ - ብዙ ፍቅር ያለው
ብዙ መውደድ ያለው
ናፍቆትሽ ቀለም ነው!
#አሹ2010
@getem_sourcebot
@getem
@getem
የፍቅር ከፍታ
…
አፍቅራኝ ስታምነኝ
የዋህነቴ ላይ ፥ ነፍስሽ ተንጠልጥላ
ስጦታ እንዲሆነኝ
ከህልሞችሽ ቆርሰሽ ፥ ሰጠሺኝ ጃንጥላ !
…
ወዲያው ዝናብ ጣለ
ይረሰርስ ጀመር ፥ የሰፈሬው ግዛት
ሰፈርተኛው ሮጠ
ከዝናብ ሊጠለል ፥ ጃንጥላ ለመግዛት
…
አየሽው አይደለ?
ከጅል ሲያስቆጥረኝ ፥ የፍቅርሽ ከፍታው
በልብሴ አስጠለልኩት
ውድ ጃንጥላሽን ፥ ዝናብ እንዳይመታው !!
…
( ናትናኤል ጌቱ )
@getem_sourcebot
@getem
@getem
…
አፍቅራኝ ስታምነኝ
የዋህነቴ ላይ ፥ ነፍስሽ ተንጠልጥላ
ስጦታ እንዲሆነኝ
ከህልሞችሽ ቆርሰሽ ፥ ሰጠሺኝ ጃንጥላ !
…
ወዲያው ዝናብ ጣለ
ይረሰርስ ጀመር ፥ የሰፈሬው ግዛት
ሰፈርተኛው ሮጠ
ከዝናብ ሊጠለል ፥ ጃንጥላ ለመግዛት
…
አየሽው አይደለ?
ከጅል ሲያስቆጥረኝ ፥ የፍቅርሽ ከፍታው
በልብሴ አስጠለልኩት
ውድ ጃንጥላሽን ፥ ዝናብ እንዳይመታው !!
…
( ናትናኤል ጌቱ )
@getem_sourcebot
@getem
@getem
625 ቁጥር 1(ልዑል ሀይሌ)
.
የእባቡን ጉድ-ጓድ
እንድትለኪበት ክንዴን ስዘረጋ
የእሳቱን ምድጃ
እንድታነሺበት እጆቼን ሳስጠጋ
.
ፀሐይ ጋርጄልሽ ራሴን ባጠቆርሁኝ
ዝናብ አስጠልዬሽ ውሃውን ባቆርሁኝ
.
ሰውነቴን ሁሉ ስላንቺ እያሳደርሁ
ጥለሺኝ ስትሄጂ
ከራሴ ገላ ላይ ያንቺን ገላ ቆጠርሁ
ያንቺን ሀሳብ ቆጠርሁ
.
እንዴት ነው? ሸሽተሽኝ የሄድሽበት ሃገር
ያስተዳድራል ወይ እምነት ሸጦ ማደር
.
እንዲያው ልጠይቅሽ
እምነትን መነገድ ያከስራል ያተርፋል?
ክንድን ቆርጦ መውሰድ ያከስራል ያተርፋል?
ልብ አድምቶ መሄድ ያከስራል ያተርፋል?
የኔማ ህመም ነው
ከጊዜ ጋር መጥቶ ከጊዜ ጋር ያልፋል
.
ያንቺ ግን ጨነቀኝ
ህልሞቼን ነጥቀሺኝ እንደምን ልተኛ
ቅዠቴን ነጥቀሺኝ እንደምን ልተኛ
ሸክሜ ቀለለ ምን ሰርቼ ልብላ
ሃሳቤን ወስደሽው የማስበው ጠፋ
ጭንቀቴን ሰርቀሽኝ
አለመጨነቄ እያስጨነቀኝ ነው በነጋ በጠባ
.
በነጋ በጠባ..
እጆቼን ዘርግቼ ፊትሽን አጥባለሁ
እንጀራ ዳቦውን እየጠቀለልኩኝ
አፌን እያጎረስኩ ቁርስ አበላሻለሁ
ጠግቤ እየዋልኩኝ
ያጠገብኩሽ መስሎኝ
ተመስገን እስክትዪ እጠብቅሻለሁ
.
እንዴት ነው ክደሽኝ የሄድሽበት ሃገር
ያስተዳድራል ወይ ወዳጅ ሸጦ ማደር?
.
ያስተዳድራል ወይ
(ይቀጥላል...)
07-10-10
@getem_source
@getem
@getem
.
የእባቡን ጉድ-ጓድ
እንድትለኪበት ክንዴን ስዘረጋ
የእሳቱን ምድጃ
እንድታነሺበት እጆቼን ሳስጠጋ
.
ፀሐይ ጋርጄልሽ ራሴን ባጠቆርሁኝ
ዝናብ አስጠልዬሽ ውሃውን ባቆርሁኝ
.
ሰውነቴን ሁሉ ስላንቺ እያሳደርሁ
ጥለሺኝ ስትሄጂ
ከራሴ ገላ ላይ ያንቺን ገላ ቆጠርሁ
ያንቺን ሀሳብ ቆጠርሁ
.
እንዴት ነው? ሸሽተሽኝ የሄድሽበት ሃገር
ያስተዳድራል ወይ እምነት ሸጦ ማደር
.
እንዲያው ልጠይቅሽ
እምነትን መነገድ ያከስራል ያተርፋል?
ክንድን ቆርጦ መውሰድ ያከስራል ያተርፋል?
ልብ አድምቶ መሄድ ያከስራል ያተርፋል?
የኔማ ህመም ነው
ከጊዜ ጋር መጥቶ ከጊዜ ጋር ያልፋል
.
ያንቺ ግን ጨነቀኝ
ህልሞቼን ነጥቀሺኝ እንደምን ልተኛ
ቅዠቴን ነጥቀሺኝ እንደምን ልተኛ
ሸክሜ ቀለለ ምን ሰርቼ ልብላ
ሃሳቤን ወስደሽው የማስበው ጠፋ
ጭንቀቴን ሰርቀሽኝ
አለመጨነቄ እያስጨነቀኝ ነው በነጋ በጠባ
.
በነጋ በጠባ..
እጆቼን ዘርግቼ ፊትሽን አጥባለሁ
እንጀራ ዳቦውን እየጠቀለልኩኝ
አፌን እያጎረስኩ ቁርስ አበላሻለሁ
ጠግቤ እየዋልኩኝ
ያጠገብኩሽ መስሎኝ
ተመስገን እስክትዪ እጠብቅሻለሁ
.
እንዴት ነው ክደሽኝ የሄድሽበት ሃገር
ያስተዳድራል ወይ ወዳጅ ሸጦ ማደር?
.
ያስተዳድራል ወይ
(ይቀጥላል...)
07-10-10
@getem_source
@getem
@getem
❤1
*አንቺን ላለማሰብ*
የኔታ ፍቄ(ግጥም እና ፍቅር)
፡
አንቺን ላለማሰብ እኔማ በኔ ቤት፣
ከውስጤ አውጥቼ አብዝቼ ለመርሳት፣
፡
ሲጋራውን ለኮስኩ ጢሱ እንዲጋርደኝ፣
ምስልሽን ከዓይኔ ወዲያ እንዲወስድልኝ፣
፡
ደግሜ ደግሜ ልረሳሽ ባጤሰው፣
ከንፈርሽ ናፈቀኝ ከንፈሬን ሲነካው፣
፡
እሱን ወዲያ ትቼ መጠጡንም ብጋት፣
አንቺን ላለማሰብ አንቺኑ ለመርሳት፣
፡
እያንገዳገደ ደጅሽ ይወስደኛል፣
ልረሳሽ ስደክም ትዝታሽ በልጦኛል፣
፡
ፀሀይንም ሳያት አስታውስሻለሁ፣
ትዝ ይልሽ እንደሆን ውበቷን ካንቺ ጋር አመሳስያለሁ፣
፡
ጨረቃንም ሳያት እነኚያ ምሽቶች ይከሰቱብኛል፣
ከባዶነት ነጥቀው ካለፈው ምናኔ ወስደው ይከቱኛል፣
አንቺን ላለማሰብ ለኔ አንቺኑ ማሰብ እጅግ ይቀለኛል፣
፡
ያላረኩት የለም ከውስጤ ላወጣሽ፣
ግና፣
ልረሳሽ ያልኩለት የባሰ ወደድኩሽ፣
፡
አንቺን ለመርሳት ስል አንቺን እያለምኩኝ፣
ትዝታን ለመቅበር ብዙ ብዙ ጣርኩኝ፣
፡
የሄድንበት መንድ እኔና አንቺ አብረን፣
ያወራኛል ደርሶ ይጠይቃል አንቺን፣
፡
ከፀሀዯ ንዳድ የተከለልንበት፣
ያ የሾላ ዛፍም አነሳሽ በድንገት፣
፡
አንቺን ላለማሰብ ማሰብ ባላቆምም፣
ትዝታሽ አስሮኛል የትም አላመልጥም፣
፡
ብራመድ ጎዳናው፣
ብቀመጥም ጥላው፣
፡
ማለዳ ንጋቱ፣
ድጋሜም ምሽቱ፣
ያንቺ ወዳጅ ናቸው አንቺን ሚተርቱ፣
፡
ይገርምሻል ውዴ እኔኮ እንዲ ነኝ፣
አንቺን ላለማሰብ አንቺን እያሰብኩኝ፣
ለመርሳት ፈልጌ ሁሌ እያስታወስኩኝ፣
ትዝታን አግብቼ የተሰቃየሁኝ፣
፡
እኔኮ እንዲ ነኝ፣
አንቺን ካለማሰብ መሞት የሚቀለኝ፣
ምንድነው ግን ቅኔው ፍቺና ንገሪኝ፣
አንቺን ለመርሳት ስል አንቺን ሚያሳስበኝ፣
፡
ለሄድሽው መውደዴ
ናፍቀሽኛል
ሚያዚያ 24/08/10 ረቡዕ ማለዳ 12:40...
@getem
@getem
@yeneta
የኔታ ፍቄ(ግጥም እና ፍቅር)
፡
አንቺን ላለማሰብ እኔማ በኔ ቤት፣
ከውስጤ አውጥቼ አብዝቼ ለመርሳት፣
፡
ሲጋራውን ለኮስኩ ጢሱ እንዲጋርደኝ፣
ምስልሽን ከዓይኔ ወዲያ እንዲወስድልኝ፣
፡
ደግሜ ደግሜ ልረሳሽ ባጤሰው፣
ከንፈርሽ ናፈቀኝ ከንፈሬን ሲነካው፣
፡
እሱን ወዲያ ትቼ መጠጡንም ብጋት፣
አንቺን ላለማሰብ አንቺኑ ለመርሳት፣
፡
እያንገዳገደ ደጅሽ ይወስደኛል፣
ልረሳሽ ስደክም ትዝታሽ በልጦኛል፣
፡
ፀሀይንም ሳያት አስታውስሻለሁ፣
ትዝ ይልሽ እንደሆን ውበቷን ካንቺ ጋር አመሳስያለሁ፣
፡
ጨረቃንም ሳያት እነኚያ ምሽቶች ይከሰቱብኛል፣
ከባዶነት ነጥቀው ካለፈው ምናኔ ወስደው ይከቱኛል፣
አንቺን ላለማሰብ ለኔ አንቺኑ ማሰብ እጅግ ይቀለኛል፣
፡
ያላረኩት የለም ከውስጤ ላወጣሽ፣
ግና፣
ልረሳሽ ያልኩለት የባሰ ወደድኩሽ፣
፡
አንቺን ለመርሳት ስል አንቺን እያለምኩኝ፣
ትዝታን ለመቅበር ብዙ ብዙ ጣርኩኝ፣
፡
የሄድንበት መንድ እኔና አንቺ አብረን፣
ያወራኛል ደርሶ ይጠይቃል አንቺን፣
፡
ከፀሀዯ ንዳድ የተከለልንበት፣
ያ የሾላ ዛፍም አነሳሽ በድንገት፣
፡
አንቺን ላለማሰብ ማሰብ ባላቆምም፣
ትዝታሽ አስሮኛል የትም አላመልጥም፣
፡
ብራመድ ጎዳናው፣
ብቀመጥም ጥላው፣
፡
ማለዳ ንጋቱ፣
ድጋሜም ምሽቱ፣
ያንቺ ወዳጅ ናቸው አንቺን ሚተርቱ፣
፡
ይገርምሻል ውዴ እኔኮ እንዲ ነኝ፣
አንቺን ላለማሰብ አንቺን እያሰብኩኝ፣
ለመርሳት ፈልጌ ሁሌ እያስታወስኩኝ፣
ትዝታን አግብቼ የተሰቃየሁኝ፣
፡
እኔኮ እንዲ ነኝ፣
አንቺን ካለማሰብ መሞት የሚቀለኝ፣
ምንድነው ግን ቅኔው ፍቺና ንገሪኝ፣
አንቺን ለመርሳት ስል አንቺን ሚያሳስበኝ፣
፡
ለሄድሽው መውደዴ
ናፍቀሽኛል
ሚያዚያ 24/08/10 ረቡዕ ማለዳ 12:40...
@getem
@getem
@yeneta
👏የካፊያ ምች👏
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
✍ ተፈሪ ዓለሙ(1974)
ሳልላክ ተልካ እንሂድ አለቺኝ
ካላጣችው ሰዓት ከቤት አስወጣችኝ
ጥርቅም እቅፍ አድርጋ በካፊያ ሳመቺኝ
የእድሜ ልክ ልክፍቱን ያኔ አስለከፈችኝ
መብረቅ እየጮኸ ዝናብ እያካፋ
የእኔ ልብ በሷ የሷ በእኔ ጠፋ
የሰማዩ ባህር ቁልቁል ተንዶብን
ውሃ ጠማኝ ውሃ እዘነበብን
ጠፍቼ ስመለስ ከእቅፏ ስወጣ
በርዶኝ አተኮሰኝ እቤቴ ስመጣ
እያደር አደረ ከርሞ ከረመብኝ
የዘመን ህመሜን ያን እለት ታመምኩኝ
አሁን አሁን ታዲያ!
ደመናው ሲጠቁር ነጎድጓድ ሲያጓራ
ነፋስ ሲያጉረመርም ክረምቱን ሲጠራ
ግንቦት ማለቂያ ላይ ይነሳል ህመሜ
ሲያቀብጠኝ በዝናብ በካፊያ ተስሜ
..........................ምች ተሳልሜ
@getem
@getem
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
✍ ተፈሪ ዓለሙ(1974)
ሳልላክ ተልካ እንሂድ አለቺኝ
ካላጣችው ሰዓት ከቤት አስወጣችኝ
ጥርቅም እቅፍ አድርጋ በካፊያ ሳመቺኝ
የእድሜ ልክ ልክፍቱን ያኔ አስለከፈችኝ
መብረቅ እየጮኸ ዝናብ እያካፋ
የእኔ ልብ በሷ የሷ በእኔ ጠፋ
የሰማዩ ባህር ቁልቁል ተንዶብን
ውሃ ጠማኝ ውሃ እዘነበብን
ጠፍቼ ስመለስ ከእቅፏ ስወጣ
በርዶኝ አተኮሰኝ እቤቴ ስመጣ
እያደር አደረ ከርሞ ከረመብኝ
የዘመን ህመሜን ያን እለት ታመምኩኝ
አሁን አሁን ታዲያ!
ደመናው ሲጠቁር ነጎድጓድ ሲያጓራ
ነፋስ ሲያጉረመርም ክረምቱን ሲጠራ
ግንቦት ማለቂያ ላይ ይነሳል ህመሜ
ሲያቀብጠኝ በዝናብ በካፊያ ተስሜ
..........................ምች ተሳልሜ
@getem
@getem
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ካልፈለግሽ_ክብርሽን
:
:
ሰማዩ ዳምኖ ብርድ ብርድ ሲለኝ
መተሽ አሟሙቂኝ ያላንቺስ ማን አለኝ።
:
:
ፀሀይ ከሆነ ግን ካጠገቤ አትምጪ
ግዬ ገማግልሽ እዚያው ተቀመጪ።
:
:
ለምን ብለሽ ካልሺኝ ትንሽ ከጋልኩኝ
እራሴን ማሸነፍ ስለሚያቅተኝ
እኔን ብለሽ መተሽ አጉል ከምቶኚ
ያልጠበቅሺው ገጥሞሽ በኔ ከምታዝኚ
ፀሀይ የሆነ ቀን ቅሪብኝ ባክሽን
እምቢ ካልሽ ደሞ
ነይ ምነ ችግር አለው ካልፈለግሽ ክብርሽን።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
አስተያየት ካሎት @henokbirhanu
@getem
@getem
:
:
ሰማዩ ዳምኖ ብርድ ብርድ ሲለኝ
መተሽ አሟሙቂኝ ያላንቺስ ማን አለኝ።
:
:
ፀሀይ ከሆነ ግን ካጠገቤ አትምጪ
ግዬ ገማግልሽ እዚያው ተቀመጪ።
:
:
ለምን ብለሽ ካልሺኝ ትንሽ ከጋልኩኝ
እራሴን ማሸነፍ ስለሚያቅተኝ
እኔን ብለሽ መተሽ አጉል ከምቶኚ
ያልጠበቅሺው ገጥሞሽ በኔ ከምታዝኚ
ፀሀይ የሆነ ቀን ቅሪብኝ ባክሽን
እምቢ ካልሽ ደሞ
ነይ ምነ ችግር አለው ካልፈለግሽ ክብርሽን።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
አስተያየት ካሎት @henokbirhanu
@getem
@getem
🌿🌾🌙💫🌟💫✨💐
አዬ ከራማው ሠፊ ነው
ሀድራው የበዛ ነው
ምን ይነገር ለሱ
ራህመቱ ብዙ
የፍቅርን ስብሐት
ካአንድነት ጋር አብሮ ክልኤቱ ብሎ
በፈሪሀ ሰበዝ ልዩ ወ ውበቱ
ያኖረን ባንድላይ ሠናይ ሠብ ብሎ ።
......ጎፍታኮ ዋቀዮ....
....አጃይብ ያረቢ.....
ማድመቅህን አብዛው:ውበት ጨምርልን
በፈሪሀ ብዛት ብርሃን አብዛልን
ሐድራችን ይሙላልን
ሐሴት እንድናረግ: ጨለማ እንዲጠፋ
ፍቅርን አሰልሰው አስርግ እንዳይወጣ
በረካህ ይበርክት በምድራችን ይሙላ
አሜን ይሁንልን ከራማችን ይሙላ።️✨
@ቤሊና (07/10/2018 ዓ.ም)
🌟💫ኢድ ሙባረክ🌟✨
@getem_sourcebot
@getem
@getem
አዬ ከራማው ሠፊ ነው
ሀድራው የበዛ ነው
ምን ይነገር ለሱ
ራህመቱ ብዙ
የፍቅርን ስብሐት
ካአንድነት ጋር አብሮ ክልኤቱ ብሎ
በፈሪሀ ሰበዝ ልዩ ወ ውበቱ
ያኖረን ባንድላይ ሠናይ ሠብ ብሎ ።
......ጎፍታኮ ዋቀዮ....
....አጃይብ ያረቢ.....
ማድመቅህን አብዛው:ውበት ጨምርልን
በፈሪሀ ብዛት ብርሃን አብዛልን
ሐድራችን ይሙላልን
ሐሴት እንድናረግ: ጨለማ እንዲጠፋ
ፍቅርን አሰልሰው አስርግ እንዳይወጣ
በረካህ ይበርክት በምድራችን ይሙላ
አሜን ይሁንልን ከራማችን ይሙላ።️✨
@ቤሊና (07/10/2018 ዓ.ም)
🌟💫ኢድ ሙባረክ🌟✨
@getem_sourcebot
@getem
@getem
#የፍቅር ጥግ#
ሳቅሽ ፅጌረዳ፥ያልተቀነጠበ
አይንሽ ላይ ያሸተ፥ጥርስሽ ላይ ያበበ
አፍሽ የወይን ዛፍ
ከማር የማይነጥፍ
ሽንጥሽ የወርቅ አልጋ፥አመለ ወላንሳ
ጎዝጉዘዉ ቢተኙ፥አጋም የሚያስረሳ።
ቀረሮ ደረቴ፥ አልታደለምና ከቶ ላንቺ ገላ
ዘብ አደርሽ ሆንኩኝ፥እንዳይገባ ሌላ።
ማፍቀር ማለት መቅናት ማለት ነዉ።የፍቅር ጥጉም ቅናት ነዉ። ፍቅር በቅናት ይገለፃል:ነገር ግን ቅናት ሁሉ ፍቅር አይደለም።
(የዋርካ ስር ነፍሶች)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ሳቅሽ ፅጌረዳ፥ያልተቀነጠበ
አይንሽ ላይ ያሸተ፥ጥርስሽ ላይ ያበበ
አፍሽ የወይን ዛፍ
ከማር የማይነጥፍ
ሽንጥሽ የወርቅ አልጋ፥አመለ ወላንሳ
ጎዝጉዘዉ ቢተኙ፥አጋም የሚያስረሳ።
ቀረሮ ደረቴ፥ አልታደለምና ከቶ ላንቺ ገላ
ዘብ አደርሽ ሆንኩኝ፥እንዳይገባ ሌላ።
ማፍቀር ማለት መቅናት ማለት ነዉ።የፍቅር ጥጉም ቅናት ነዉ። ፍቅር በቅናት ይገለፃል:ነገር ግን ቅናት ሁሉ ፍቅር አይደለም።
(የዋርካ ስር ነፍሶች)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
❤1
ውሻ ነኝ
=== ==
የጉዞየ ምዕራፍ የህይወቴ ቃና
በፍቅርሽ ማዕበል መንፈሤ የፀና፣
..
ካወኩሽ ጀምሮ ከጥንት እሥከ ዛሬ
ላንች የሠሠትኩት የለም ነበር ፍቅሬ።
..
ያኔ ሙሉ ነበርኩ እጄ ያለጠረ
ልቤም ደሥተኛ ነው በፍቅር የከበረ።
..
የምትፈልጊውን ሁሉን የማሣካ
ባንች ደሥታ ብቻ ውሥጤ የሚረካ።
..
እሡ ነበር ለኔ የደሥታየ ጣራ
የኔን ሥም ረሥተውት ባንች ሥም ሥጠራ።
..
እንዲህ ትይኝ ነበር...
" ከሠማይ የራቀ ከውቅያኖሥ የሠፋ
ላንተ ፍቅር አለኝ ፍፁም የማይጠፋ።
አጣህ ነጣህ ብየ አልወጣም ካንተ እቅፍ ቃሌን ባላከብር
ምላሤ ይታጠፍ። "
በሚጥም ልሣንሽ ብለሽኝ ነበረ
ይሄው ጊዜ ሺሮት ቃልሽ ተሠበረ።
..
የኔ ንብረት አልቆ ፍቅሬ ግን በርትቶ
ያንች ፍቅር ሢያረጅ ገንዘብሽ በርክቶ፣
..
ያጣ መናጢ ነው ብለሽ ተጠየፍሽኝ
ወዳላቸው ሥትሄጅ እኔን ግን ሸሸሺኝ።
..
አንች ብትሸሺኝም አልቀነሠም ፍቅሬ
እንደ ሎሌሺ ሁኝ ሥከትል አብሬ፣
..
አንችን ተከትየ በሆንኩሽ ጠበቃ
" ውሻ ነህ እንዴ አንተ ? አትከተል በቃ! "
ብለሽ አኮራሽኝ ቆረጥሽልኝ ጥሜን
ዳግም እንዳያመኝ ፈወሥሽው ህመሜን።
..
ውለታየን ክደሽ ፍቅሬን ብትንቂ
ሠድበሽ አሥደሠትሽኝ ሚሥጥሩን ሣታውቂ።
..
ለሁሉም ንገሪ ሣትደብቂያቸው
አንችን የምከተል ውሻ ነው በያቸው።
..
አንዴ ከወደደ መልሶ እማይከዳ
ጥላቱን ነው እንጅ ወዳጅ እማይጎዳ፣
..
ቃሌን የምጠብቅ ለጌታየ ታማኝ
አንችኮ "ተኩላ" ነሽ እኔ ግን " ውሻ " ነኝ። ...............
.........አወ እኔ ውሻ ነኝ
በይ የኔን ውሻነት ላገር አሣውቂ
ያንችን ተኩላነት ግን እንዳትደብቂ።
....
ማንም በሌለበት በባህር ዳርቻ
ሥንዝናና ነበር እኔና አንች ብቻ፣
..
ጨለማው ተተካ ቀኑ ተቀየረ
ተኩላው አብሮ ሢሄድ ውሻው ብቻ ቀረ።
....................አወ እኔ ውሻ ነኝ።።።
ከገጣሚ ናትናኤል የተወሰደ ፡፡ ለቃሌ ታማኝ ነኝ
~~~~~~~~~
፡
ምንም ብንለያይ አደራ አትርሳኝ
ብለሽ መዳፍሽን በጄ ያስመታሽኝ
በስምሽ ያስማልሽኝ
የገባሁልሽ ቃል እንዳልፈረሰ ነው
ቃል አባይ አይድለሁ እስካሁን ህያው ነው
፡
በትዝታ ቅኝት በሰመመን ዜማ
ክረምት'ና በጋ ቀን ወይም ጨለማ
ሳንካ ሳይሆንብኝ መፈራረቃቸው
ወቅት…
ቦታ…
ጊዜ…
አንዳች ሳያግደኝ …
በክፉም በደጉ አስታውስሻለው
፡
ጨረቃ ስትወጣ ጨረቃን እያየሁ
በሰማይ ሰሌዳ በክዋክብት ብዛት አንቺኑ ስላለሁ
አስታውስሻለሁ
፡
ሆዴም ሆዱን ብሶት የተከፋሁ ግዜ
ብቸኝነት ወርሶኝ ሰፍሮብኝ ትካዜ
በሬን ዘጋግቼ ብቻዬን ቤቴ ውስጥ
በሀሳብ ድር ትብታብ ቆዝሜ ስቀመጥ
ደግሞ ውል ብሎኝ በሬ እንዲቆረቆር
ጉዳዬ ነው የሚል ስለኔ መቸገር
ሰው ያስፈለገኝ 'ለት . . .
ሌላከየትመቶ
BYNati
@getem
@getem
=== ==
የጉዞየ ምዕራፍ የህይወቴ ቃና
በፍቅርሽ ማዕበል መንፈሤ የፀና፣
..
ካወኩሽ ጀምሮ ከጥንት እሥከ ዛሬ
ላንች የሠሠትኩት የለም ነበር ፍቅሬ።
..
ያኔ ሙሉ ነበርኩ እጄ ያለጠረ
ልቤም ደሥተኛ ነው በፍቅር የከበረ።
..
የምትፈልጊውን ሁሉን የማሣካ
ባንች ደሥታ ብቻ ውሥጤ የሚረካ።
..
እሡ ነበር ለኔ የደሥታየ ጣራ
የኔን ሥም ረሥተውት ባንች ሥም ሥጠራ።
..
እንዲህ ትይኝ ነበር...
" ከሠማይ የራቀ ከውቅያኖሥ የሠፋ
ላንተ ፍቅር አለኝ ፍፁም የማይጠፋ።
አጣህ ነጣህ ብየ አልወጣም ካንተ እቅፍ ቃሌን ባላከብር
ምላሤ ይታጠፍ። "
በሚጥም ልሣንሽ ብለሽኝ ነበረ
ይሄው ጊዜ ሺሮት ቃልሽ ተሠበረ።
..
የኔ ንብረት አልቆ ፍቅሬ ግን በርትቶ
ያንች ፍቅር ሢያረጅ ገንዘብሽ በርክቶ፣
..
ያጣ መናጢ ነው ብለሽ ተጠየፍሽኝ
ወዳላቸው ሥትሄጅ እኔን ግን ሸሸሺኝ።
..
አንች ብትሸሺኝም አልቀነሠም ፍቅሬ
እንደ ሎሌሺ ሁኝ ሥከትል አብሬ፣
..
አንችን ተከትየ በሆንኩሽ ጠበቃ
" ውሻ ነህ እንዴ አንተ ? አትከተል በቃ! "
ብለሽ አኮራሽኝ ቆረጥሽልኝ ጥሜን
ዳግም እንዳያመኝ ፈወሥሽው ህመሜን።
..
ውለታየን ክደሽ ፍቅሬን ብትንቂ
ሠድበሽ አሥደሠትሽኝ ሚሥጥሩን ሣታውቂ።
..
ለሁሉም ንገሪ ሣትደብቂያቸው
አንችን የምከተል ውሻ ነው በያቸው።
..
አንዴ ከወደደ መልሶ እማይከዳ
ጥላቱን ነው እንጅ ወዳጅ እማይጎዳ፣
..
ቃሌን የምጠብቅ ለጌታየ ታማኝ
አንችኮ "ተኩላ" ነሽ እኔ ግን " ውሻ " ነኝ። ...............
.........አወ እኔ ውሻ ነኝ
በይ የኔን ውሻነት ላገር አሣውቂ
ያንችን ተኩላነት ግን እንዳትደብቂ።
....
ማንም በሌለበት በባህር ዳርቻ
ሥንዝናና ነበር እኔና አንች ብቻ፣
..
ጨለማው ተተካ ቀኑ ተቀየረ
ተኩላው አብሮ ሢሄድ ውሻው ብቻ ቀረ።
....................አወ እኔ ውሻ ነኝ።።።
ከገጣሚ ናትናኤል የተወሰደ ፡፡ ለቃሌ ታማኝ ነኝ
~~~~~~~~~
፡
ምንም ብንለያይ አደራ አትርሳኝ
ብለሽ መዳፍሽን በጄ ያስመታሽኝ
በስምሽ ያስማልሽኝ
የገባሁልሽ ቃል እንዳልፈረሰ ነው
ቃል አባይ አይድለሁ እስካሁን ህያው ነው
፡
በትዝታ ቅኝት በሰመመን ዜማ
ክረምት'ና በጋ ቀን ወይም ጨለማ
ሳንካ ሳይሆንብኝ መፈራረቃቸው
ወቅት…
ቦታ…
ጊዜ…
አንዳች ሳያግደኝ …
በክፉም በደጉ አስታውስሻለው
፡
ጨረቃ ስትወጣ ጨረቃን እያየሁ
በሰማይ ሰሌዳ በክዋክብት ብዛት አንቺኑ ስላለሁ
አስታውስሻለሁ
፡
ሆዴም ሆዱን ብሶት የተከፋሁ ግዜ
ብቸኝነት ወርሶኝ ሰፍሮብኝ ትካዜ
በሬን ዘጋግቼ ብቻዬን ቤቴ ውስጥ
በሀሳብ ድር ትብታብ ቆዝሜ ስቀመጥ
ደግሞ ውል ብሎኝ በሬ እንዲቆረቆር
ጉዳዬ ነው የሚል ስለኔ መቸገር
ሰው ያስፈለገኝ 'ለት . . .
ሌላከየትመቶ
BYNati
@getem
@getem
አንቺ ካለሽልኝ
( እሱባለው ኢትዮጵያዊ)
አንቺ ካለሽልኝ
*
*
*
ሁሉም ይኖረኛል።
የጠየኩት ሁሉ፤ ይመለስልኛል
አለቆቹ ሁሉ፤ ይታዘዙልኛል።
*
*
አንቺ ካለሽልኝ
ሁሉም ይኖረኛል
*
*
ቤታችን በደስታ ፤በሃሴት ይሞላል
ሁሉ ያሸበርቃል
ግቢያችን በፍቅር ፤ ሳይበላ ይጥግባል
አንቺ ካለሽልኝ
ሁሉም ይኖረኛል።
********
ሁሌም ኑሪልኝ
ሰኔ ፰ ፪ሺህ፲
( እሱባለው ኢትዮጵያዊ)
@getemsource
@getem
@getem
( እሱባለው ኢትዮጵያዊ)
አንቺ ካለሽልኝ
*
*
*
ሁሉም ይኖረኛል።
የጠየኩት ሁሉ፤ ይመለስልኛል
አለቆቹ ሁሉ፤ ይታዘዙልኛል።
*
*
አንቺ ካለሽልኝ
ሁሉም ይኖረኛል
*
*
ቤታችን በደስታ ፤በሃሴት ይሞላል
ሁሉ ያሸበርቃል
ግቢያችን በፍቅር ፤ ሳይበላ ይጥግባል
አንቺ ካለሽልኝ
ሁሉም ይኖረኛል።
********
ሁሌም ኑሪልኝ
ሰኔ ፰ ፪ሺህ፲
( እሱባለው ኢትዮጵያዊ)
@getemsource
@getem
@getem
#ናፍቆት
//ኑረዲን ዒሣ//
ስጋዬን ሲበላኝ በጥርሴ ነከስኩት
ቆዳዬን ሲበላኝ በጥፍሬ ፎከትኩት
እፎይ አስታገስኩት
ፀጥ ረጭ አረኩት።
የውስጥ አጥንቴ ግን ሲበላኝ ነዝንዞ
ሲነክሰኝ ጠዝጥዞ
ምንም አላረኩት
ምንም አላከኩት
ላልችል ችየ ቻልኩት።
አልፎክተው ነገር፣ ቆዳዬን መንቅሬ
አላኝከው ነገር፣ ስጋዬን ሰርስሬ
ይኸው እስከዛሬ፣
አጥንቴ እየበላኝ፣ አለሁልሽ(ህ) ፍቅሬ።
✅ያበደች የተረጋጋች ቅዳሜ
@lula_al_greeko
@getem ..
@getem
@getemsource
//ኑረዲን ዒሣ//
ስጋዬን ሲበላኝ በጥርሴ ነከስኩት
ቆዳዬን ሲበላኝ በጥፍሬ ፎከትኩት
እፎይ አስታገስኩት
ፀጥ ረጭ አረኩት።
የውስጥ አጥንቴ ግን ሲበላኝ ነዝንዞ
ሲነክሰኝ ጠዝጥዞ
ምንም አላረኩት
ምንም አላከኩት
ላልችል ችየ ቻልኩት።
አልፎክተው ነገር፣ ቆዳዬን መንቅሬ
አላኝከው ነገር፣ ስጋዬን ሰርስሬ
ይኸው እስከዛሬ፣
አጥንቴ እየበላኝ፣ አለሁልሽ(ህ) ፍቅሬ።
✅ያበደች የተረጋጋች ቅዳሜ
@lula_al_greeko
@getem ..
@getem
@getemsource
Forwarded from SPACE COMPUTER
" አለንጋ" የግጥም መድብል
ነገ ሰኔ 10/2010 ይመረቃል።
በገጣሚና ደራሲ ትዘዘው ክንዴ
"አለንጋ" የግጥም ስብስቦች
በዕለቱ ገጣሚያን ስራቸውንና የተመረጡ ከመፅሀፉ የተወሰዱ ግጥሞችን ያቀርባሉ።
ነገ እሁድ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሄራዊ ቤተመፅሀፍት እና ቤተመዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ የጥበብ ሰዎች በተገኙበት ይመረቃል።
እናንተም ተጋብዛችዋል
መግብያ በነፃ
@lula_al_greeko
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
ነገ ሰኔ 10/2010 ይመረቃል።
በገጣሚና ደራሲ ትዘዘው ክንዴ
"አለንጋ" የግጥም ስብስቦች
በዕለቱ ገጣሚያን ስራቸውንና የተመረጡ ከመፅሀፉ የተወሰዱ ግጥሞችን ያቀርባሉ።
ነገ እሁድ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሄራዊ ቤተመፅሀፍት እና ቤተመዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ የጥበብ ሰዎች በተገኙበት ይመረቃል።
እናንተም ተጋብዛችዋል
መግብያ በነፃ
@lula_al_greeko
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
አንተ የሌለህ እለት
ሰማይ ይታረሳል
ምድር ይታመሳል
መልካም እውነት ወርዶ
ሀሠት ይፀነሳል።
አንተ የሌለህ እለት
ጨረቃ አዘቅዝቃ
ወይ ምድር ትላለች
ፀሀይ ሰማይ ጠፍታ
ምድር ትቆማለች።
አንተ የሌለህ እለት
ውቅያኖሶች ሸሽተው
ምድርን ይከድናሉ
ነፍሳቱ ነጉደው
ምድርን ይመታሉ።
አንተ እዚህ ከሌለህ
ጉልበት ይለምሻል
ፍቅር ይቆሽሻል
ልቦች ይደማሉ
ሰዎች ይከዳሉ
መሞት ይመኛሉ።
ስለዚ አንተ ሰላም
አንተ የመኖር ተስፍ
ከኛ እርቀህ አትሂድ
ከኛ ዘንድ አትጥፍ።🙏🙏
........ ((ሊዱ))
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ሰማይ ይታረሳል
ምድር ይታመሳል
መልካም እውነት ወርዶ
ሀሠት ይፀነሳል።
አንተ የሌለህ እለት
ጨረቃ አዘቅዝቃ
ወይ ምድር ትላለች
ፀሀይ ሰማይ ጠፍታ
ምድር ትቆማለች።
አንተ የሌለህ እለት
ውቅያኖሶች ሸሽተው
ምድርን ይከድናሉ
ነፍሳቱ ነጉደው
ምድርን ይመታሉ።
አንተ እዚህ ከሌለህ
ጉልበት ይለምሻል
ፍቅር ይቆሽሻል
ልቦች ይደማሉ
ሰዎች ይከዳሉ
መሞት ይመኛሉ።
ስለዚ አንተ ሰላም
አንተ የመኖር ተስፍ
ከኛ እርቀህ አትሂድ
ከኛ ዘንድ አትጥፍ።🙏🙏
........ ((ሊዱ))
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ጨ ረ ቃ ....(ከ ጌታየ )
ጨረቃ...
አንዛብ በፈተለ
ቁር ባዘለ ንጋት፣
ባዲስ ሂወት ተስፋ
በፈገግታ ውህደት፣
ወይንም!
በነፍስ እልፊያ
በእስትንፋስ ጥምርት፡፡
ጎህ ሳይቀድ ፈንጥቆ
በተራራ ቁንጮ እንደሚወጣ አደይ፣
በውድቅቱ ሌሊት
በሰማይ አድማስ ላይ፣
.........ፈንድቀሽ ስትታይ፣
በክዋከብት ዓለም
በንግሰት ዘመንሽ፣
ቀና ብሎ ለሚያይ
አይቶ ለሚያደንቅሽ፣
በግዛትሽ ዙፋን
በደስታ ሰክረሻል፣
ላስተዋለሽ ደግሞ
በውብ ሳቅሽ መሀል
ሀዘን ሰንቀሻል፣
አንቺ ውብ ጨረቃ...
"
"
ስለ አንዳች ኩርፊያሽ
እንደ ማለዳ ጉም
ፍካትሽ ተነነ፣
የተከዘው ልብሽ
ሳቅሽን ተወነ፣
ይህ...ስለምን ሆነ?
ከዋከብት አዘኑ....!
"
"
ከዋከብት አዘኑ፣
ከ'ግርሽ ስር ተደፍተው
ማቅ ለብሰው ለመኑ፣
ቁጥር ፈታ በሚል
በጎለሰው ፊትሽ
ደመናው ተጨንቋል፣
ባይኖቹ ኮረጆ
እንባውን ሰንቋል፣
ነፋስ ተቆጥቶ
እሳትን አስንቋል፡፡
፡
እናም...
በዚች የምጥ ሌሊት
ከሰማይ ሰማይ ላታርጊ፣
በአርያምሽ ፀንተሽ
ለዘላለም ላትመስጊ፣
የፍንደቃ እንቁ ሳቅሽን
በዕንባሽ ግምጃ ስትሸሽጊ፣
፡
አንቺ ውብ ጨረቃ፣
ላላወቁሽ የፍንደቃ፣
.......የቡረቃ፣
ልብ ላሉሽ ደግሞ.....
የዕንባ ዶፍ የሳግ ሲቃ፣
፡
እናም..........በቃ!
በዚች ከንቱ አለም፣
ሞትሽን የሚሞት
ቤዛ ሚሆን የለም፣
፡
የዙፋንሽ አቻ
ባልንጀራሽ ፀሃይ፣
የዕንባሽን ትንፋገን
የውስጥሽን ስቃይ፣
...እንፋሎትሽን ሳታይ፣
ከተራሮች ጀርባ
እግሯን ዘርግታለች፣
ከሞቀው ዕልፍኟ
ሰላም ትሰብካለች፣
አ
ይ
ይ
__////____________
february 13/2010
.....☞[Getaye.T]
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ጨረቃ...
አንዛብ በፈተለ
ቁር ባዘለ ንጋት፣
ባዲስ ሂወት ተስፋ
በፈገግታ ውህደት፣
ወይንም!
በነፍስ እልፊያ
በእስትንፋስ ጥምርት፡፡
ጎህ ሳይቀድ ፈንጥቆ
በተራራ ቁንጮ እንደሚወጣ አደይ፣
በውድቅቱ ሌሊት
በሰማይ አድማስ ላይ፣
.........ፈንድቀሽ ስትታይ፣
በክዋከብት ዓለም
በንግሰት ዘመንሽ፣
ቀና ብሎ ለሚያይ
አይቶ ለሚያደንቅሽ፣
በግዛትሽ ዙፋን
በደስታ ሰክረሻል፣
ላስተዋለሽ ደግሞ
በውብ ሳቅሽ መሀል
ሀዘን ሰንቀሻል፣
አንቺ ውብ ጨረቃ...
"
"
ስለ አንዳች ኩርፊያሽ
እንደ ማለዳ ጉም
ፍካትሽ ተነነ፣
የተከዘው ልብሽ
ሳቅሽን ተወነ፣
ይህ...ስለምን ሆነ?
ከዋከብት አዘኑ....!
"
"
ከዋከብት አዘኑ፣
ከ'ግርሽ ስር ተደፍተው
ማቅ ለብሰው ለመኑ፣
ቁጥር ፈታ በሚል
በጎለሰው ፊትሽ
ደመናው ተጨንቋል፣
ባይኖቹ ኮረጆ
እንባውን ሰንቋል፣
ነፋስ ተቆጥቶ
እሳትን አስንቋል፡፡
፡
እናም...
በዚች የምጥ ሌሊት
ከሰማይ ሰማይ ላታርጊ፣
በአርያምሽ ፀንተሽ
ለዘላለም ላትመስጊ፣
የፍንደቃ እንቁ ሳቅሽን
በዕንባሽ ግምጃ ስትሸሽጊ፣
፡
አንቺ ውብ ጨረቃ፣
ላላወቁሽ የፍንደቃ፣
.......የቡረቃ፣
ልብ ላሉሽ ደግሞ.....
የዕንባ ዶፍ የሳግ ሲቃ፣
፡
እናም..........በቃ!
በዚች ከንቱ አለም፣
ሞትሽን የሚሞት
ቤዛ ሚሆን የለም፣
፡
የዙፋንሽ አቻ
ባልንጀራሽ ፀሃይ፣
የዕንባሽን ትንፋገን
የውስጥሽን ስቃይ፣
...እንፋሎትሽን ሳታይ፣
ከተራሮች ጀርባ
እግሯን ዘርግታለች፣
ከሞቀው ዕልፍኟ
ሰላም ትሰብካለች፣
አ
ይ
ይ
__////____________
february 13/2010
.....☞[Getaye.T]
@getem_sourcebot
@getem
@getem