ተጠራጣሪ ነኝ !!
…
ብፁዕ ፃድቅ ሁሉ…
ከአላህ ጋራ ሁኖ ፥ ኮኮቦች ቢያዘንብም
ማርያም ስትፈትል ፥ አብሯት ቢሸምንም
ተጠራጣሪ ነኝ!
ሰው ሁሉ ሌባ ነው ፥ ማንንም አላምንም!
…
የሻማችን እሳት ፥ ብርሀን ሲቀማ
ለዘመናት ያህል ፥ ስላየን ጨለማ
ፃድቅ በግራ እጁ
ጨረቃን ቢሰጠን ፥ እንባችን ይደርቃል
እኔ ግን አላምንም !
ምናልባት ቀኝ እጁ ፥ ፀሀይን ይሰርቃል! !
…
በጨለማ ዘመን
ጥቂት መራራቱ
ጥቂት ደግነቱ
ብርሀን ሰርታ እንጂ ፥ መልአክ የሚመስለው
የትኛው ፍጡር ነው
ከአውራ ጣቱ ጣገብ ፥ ሌባ ጣት የሌለው ??
…
(ናትናኤል ጌቱ)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
…
ብፁዕ ፃድቅ ሁሉ…
ከአላህ ጋራ ሁኖ ፥ ኮኮቦች ቢያዘንብም
ማርያም ስትፈትል ፥ አብሯት ቢሸምንም
ተጠራጣሪ ነኝ!
ሰው ሁሉ ሌባ ነው ፥ ማንንም አላምንም!
…
የሻማችን እሳት ፥ ብርሀን ሲቀማ
ለዘመናት ያህል ፥ ስላየን ጨለማ
ፃድቅ በግራ እጁ
ጨረቃን ቢሰጠን ፥ እንባችን ይደርቃል
እኔ ግን አላምንም !
ምናልባት ቀኝ እጁ ፥ ፀሀይን ይሰርቃል! !
…
በጨለማ ዘመን
ጥቂት መራራቱ
ጥቂት ደግነቱ
ብርሀን ሰርታ እንጂ ፥ መልአክ የሚመስለው
የትኛው ፍጡር ነው
ከአውራ ጣቱ ጣገብ ፥ ሌባ ጣት የሌለው ??
…
(ናትናኤል ጌቱ)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
👍1
#ምን_ይውጠኝ_ነበር?
*
*
ዕድል የቀናኝ ለት ዐይኖችሽን ካየው
ድንገት እንኳ ላፍታ፣
የጆሮዬን ታምቡር ሊቀደው ይደርሳል
የልቤ ትርታ።
:
:
ከጨበጥሺኝ ደሞ ለስላሳው መዳፍሽ
አርፎ መዳፌ ላይ
አንቺን በነካ እጄ ሌላ ሰው መጨበጥ ያስጠላኛል ብታይ።
:
:
የገጠሙ እንደሆን ሰላምታን አስታከው ጉንጭሽና ጉንጬ፣
ከርማ እንደተፈታች እንደንቦሳይቱ አልጠግብም እሮጬ።
:
:
እንደው የገረመኝ
በድንገት ተያይተን
ሰላም ተባብለን
ጉንጭ ተገጣጥመን
እኔ ላይ ካሳደርሽ ያንን ሁሉ ስሜት
ያንን ሁሉ ነገር፣
ማርን በሚያፈልቁት በከናፍሮችሽ
ከንፈሬን ብትስሚኝ ምን ይውጠኝ ነበር?
#ሄኖክ_ብርሃኑ
አስተያየት ካሎት @henokbirhanu
@getem_soursebot
@getem
@getem
*
*
ዕድል የቀናኝ ለት ዐይኖችሽን ካየው
ድንገት እንኳ ላፍታ፣
የጆሮዬን ታምቡር ሊቀደው ይደርሳል
የልቤ ትርታ።
:
:
ከጨበጥሺኝ ደሞ ለስላሳው መዳፍሽ
አርፎ መዳፌ ላይ
አንቺን በነካ እጄ ሌላ ሰው መጨበጥ ያስጠላኛል ብታይ።
:
:
የገጠሙ እንደሆን ሰላምታን አስታከው ጉንጭሽና ጉንጬ፣
ከርማ እንደተፈታች እንደንቦሳይቱ አልጠግብም እሮጬ።
:
:
እንደው የገረመኝ
በድንገት ተያይተን
ሰላም ተባብለን
ጉንጭ ተገጣጥመን
እኔ ላይ ካሳደርሽ ያንን ሁሉ ስሜት
ያንን ሁሉ ነገር፣
ማርን በሚያፈልቁት በከናፍሮችሽ
ከንፈሬን ብትስሚኝ ምን ይውጠኝ ነበር?
#ሄኖክ_ብርሃኑ
አስተያየት ካሎት @henokbirhanu
@getem_soursebot
@getem
@getem
#ሃገር_ማለት_ዳቦ...
ሃገር ማለት ዳቦ
ዳቦ ማለት ሃገር
አይኖች ተጨናብሰው በጭስ ምትጋገር
ሃገር ማለት ዳቦ
ሃገር ማለት እናት
አናስቆርስ ብለው ልጆች የሞቱላት
ሃገር ማለት ዳቦ
ሃገር ማለት እናት
እየትቆረሰች ጎረቤት ሚወስዳት
ብርሃን ታዬ(Bra Han)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ሃገር ማለት ዳቦ
ዳቦ ማለት ሃገር
አይኖች ተጨናብሰው በጭስ ምትጋገር
ሃገር ማለት ዳቦ
ሃገር ማለት እናት
አናስቆርስ ብለው ልጆች የሞቱላት
ሃገር ማለት ዳቦ
ሃገር ማለት እናት
እየትቆረሰች ጎረቤት ሚወስዳት
ብርሃን ታዬ(Bra Han)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
😍ባርኒ ተመልሷል😍
# የታለፈ_እና_ያለፈበት
፡
የነብሳችን ጥማት
የስጋችን ሐሴት፣
ፍላጎት ስሜቱ
ሙቀቱ -- ግለቱ፣
ቸብቸቦ ሙዚቃው፣ የደነስንበቱ
ቀልድና ጨዋታው፣ የፈገግንበቱ፣
ዥንጉርጉር ልብሳችን
ጥምልምል ፀጉራችን
ጥድፍድፍ ኮቴያችን
ዜማ ፉጨታችን፣
የረገጥነው መሬት፣ የእግራችን ዳና
ሲቀር ከኀላችን፣ ሰው ተጓዥ ነውና፣
፡
ከአንጀት ያሳቀን
አድሮ ቢያሳቅቀን፣
የኮረኮረን ጣት፣ ቢያስነባን መልሶ
ያበድንለት ነገር፣ ቢያሳብደን ደርሶ፣
ሁሉ አልዋጥ ቢለን
ቢያን..ገሸ..ግሸን
ዛሬ ላይ ቢያስጠላን ፣ የትላንቱ ቀለም
አልፈነው ነው እንጂ፥ አልፎበት አይደለም።
-----------------------//---------------------
( በርናባስ ከበደ )
፡
:
በነገራችን ታች ... ይህ ግጥም እርጅናና ሃሳብ ተጫጭኖኝ በ26ተኛ
አመት የልደቴ በአሌ ዋዜማ የከተብኩት መሆኑ ታሳቢ ይሁንልኝ። የዛሬ
26 አመት (ሰኔ 5፣ 1984 )ስወለድ ቀኑ ደመናማ ነበር። እናም...
ከማህፀን ስወጣ እንደ ቻይና ሞባይል ድንገት "እሪሪሪ!!" አልኩኝ።
እማዬም በእሪታዬ ውስጥ አንዳች ጥበባዊ መጠራት ተመለከተች።
''ይሄ ልጅ ልቅሶው ቤት ይመታል፣ ገጣሚ ነው ሚሆነው'' አለች።
የጠ.ሚ/ሩ እናት በሰባት አመቱ ትንቢት ተናገሩ። የኔዋ ግን በሰባት ቀኔ
ከልቅሶዬ ዜማ ሰምና ወርቅ አገኘችበት።
እናላችሁ .... ብዙም ወራት ሳልቆይ ... አፌን የፈታሁበትን ሃሌታ ቃል
ተናገርኩ። በዚህም ገጣሚነቴ እስከወድያኛው ተረጋገጠ። ቃሉም
የሚከተለው ነበረ። .....
.
.
.
☞☞☞"ውዴ!"☜☜☜
:
:
እና .... መልካም ልደት ለኔ!!
:
እንደ ህፃናቱ እንደነ ሚጣ ልደት እናዝግ እንዴ???....
:
" አምሳ አመትህ ነው?"
:
'አ..ይ..ደ..ለ..ም!!!!'
:
"አርባ ዘጠኝ አመትህ ነው?"
:
'አ..ይ..ደ..ለ..ም!!!!''
:
'አርባ ስምንት አመትህ ነው?"
:
'አ..ይ..ደ..ለ..ም!!!!'
፡
"አርባ ሰባት አመትህ ነው?"
፡
'አ..ይ..ደ..ለ..ም!!!!'
፡
"አርባ ስድስት ኣመትህ...... ??"
፡
"ኧረ ኡ!ኡ!ኡ!! አይደለም አልኳቹ እኮ!! ልታሳብዱኝ ነው እንዴ??"
እንኳን ተወለድክልን ባርኒ
ግጥም ብቻ
@getem_sourcebot
@getem
@getem
# የታለፈ_እና_ያለፈበት
፡
የነብሳችን ጥማት
የስጋችን ሐሴት፣
ፍላጎት ስሜቱ
ሙቀቱ -- ግለቱ፣
ቸብቸቦ ሙዚቃው፣ የደነስንበቱ
ቀልድና ጨዋታው፣ የፈገግንበቱ፣
ዥንጉርጉር ልብሳችን
ጥምልምል ፀጉራችን
ጥድፍድፍ ኮቴያችን
ዜማ ፉጨታችን፣
የረገጥነው መሬት፣ የእግራችን ዳና
ሲቀር ከኀላችን፣ ሰው ተጓዥ ነውና፣
፡
ከአንጀት ያሳቀን
አድሮ ቢያሳቅቀን፣
የኮረኮረን ጣት፣ ቢያስነባን መልሶ
ያበድንለት ነገር፣ ቢያሳብደን ደርሶ፣
ሁሉ አልዋጥ ቢለን
ቢያን..ገሸ..ግሸን
ዛሬ ላይ ቢያስጠላን ፣ የትላንቱ ቀለም
አልፈነው ነው እንጂ፥ አልፎበት አይደለም።
-----------------------//---------------------
( በርናባስ ከበደ )
፡
:
በነገራችን ታች ... ይህ ግጥም እርጅናና ሃሳብ ተጫጭኖኝ በ26ተኛ
አመት የልደቴ በአሌ ዋዜማ የከተብኩት መሆኑ ታሳቢ ይሁንልኝ። የዛሬ
26 አመት (ሰኔ 5፣ 1984 )ስወለድ ቀኑ ደመናማ ነበር። እናም...
ከማህፀን ስወጣ እንደ ቻይና ሞባይል ድንገት "እሪሪሪ!!" አልኩኝ።
እማዬም በእሪታዬ ውስጥ አንዳች ጥበባዊ መጠራት ተመለከተች።
''ይሄ ልጅ ልቅሶው ቤት ይመታል፣ ገጣሚ ነው ሚሆነው'' አለች።
የጠ.ሚ/ሩ እናት በሰባት አመቱ ትንቢት ተናገሩ። የኔዋ ግን በሰባት ቀኔ
ከልቅሶዬ ዜማ ሰምና ወርቅ አገኘችበት።
እናላችሁ .... ብዙም ወራት ሳልቆይ ... አፌን የፈታሁበትን ሃሌታ ቃል
ተናገርኩ። በዚህም ገጣሚነቴ እስከወድያኛው ተረጋገጠ። ቃሉም
የሚከተለው ነበረ። .....
.
.
.
☞☞☞"ውዴ!"☜☜☜
:
:
እና .... መልካም ልደት ለኔ!!
:
እንደ ህፃናቱ እንደነ ሚጣ ልደት እናዝግ እንዴ???....
:
" አምሳ አመትህ ነው?"
:
'አ..ይ..ደ..ለ..ም!!!!'
:
"አርባ ዘጠኝ አመትህ ነው?"
:
'አ..ይ..ደ..ለ..ም!!!!''
:
'አርባ ስምንት አመትህ ነው?"
:
'አ..ይ..ደ..ለ..ም!!!!'
፡
"አርባ ሰባት አመትህ ነው?"
፡
'አ..ይ..ደ..ለ..ም!!!!'
፡
"አርባ ስድስት ኣመትህ...... ??"
፡
"ኧረ ኡ!ኡ!ኡ!! አይደለም አልኳቹ እኮ!! ልታሳብዱኝ ነው እንዴ??"
እንኳን ተወለድክልን ባርኒ
ግጥም ብቻ
@getem_sourcebot
@getem
@getem
❤1👍1👎1
ቀድሞ የደረሰ ፀሎት
#በፀጋዬ ወንድወሰን
በሮች ሁሉ ሞቱ በጎችም ታረዱ
ያነሱት ፍጥረቶች ዶሮዎች ተጎዱ
ነፍስን ያጠፋ ሰዉ እርሱ ቀጠፋቸዉ
አባሮ ካሉበት ቀርጥፎ በላቸዉ ፡፡
( . . . )
#ዶሮዎች ፀለዩ
#በጎች ተማጸኑ
#በሮችም መከሩ
አያዉቁትን አምላክ አንጋጠዉ ለመኑ
የሩሀቸዉ ችግር የነፍሳቸዉ መላ
ሰዉ ነዉ ጭራቃቸዉ እነርሱን የበላ ፡፡
ስለዚህ
( . . . )
ሰዉን ጭራቅ ብለዉ በጭራቅ መስለዉ
ላ’ጥፊ ሰዎቻቸዉ
ብለዉ ተማፀኑ ሰዉን ላክባቸዉ !!!
@getem_sourcebot
@getem
@getem
#በፀጋዬ ወንድወሰን
በሮች ሁሉ ሞቱ በጎችም ታረዱ
ያነሱት ፍጥረቶች ዶሮዎች ተጎዱ
ነፍስን ያጠፋ ሰዉ እርሱ ቀጠፋቸዉ
አባሮ ካሉበት ቀርጥፎ በላቸዉ ፡፡
( . . . )
#ዶሮዎች ፀለዩ
#በጎች ተማጸኑ
#በሮችም መከሩ
አያዉቁትን አምላክ አንጋጠዉ ለመኑ
የሩሀቸዉ ችግር የነፍሳቸዉ መላ
ሰዉ ነዉ ጭራቃቸዉ እነርሱን የበላ ፡፡
ስለዚህ
( . . . )
ሰዉን ጭራቅ ብለዉ በጭራቅ መስለዉ
ላ’ጥፊ ሰዎቻቸዉ
ብለዉ ተማፀኑ ሰዉን ላክባቸዉ !!!
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ሰላም የግጥም ብቻ ወዳጆች (@getem)
መሶብ ባህላዊ የሙዚቃ ባንድ በብሔራዊ ቲያትር ጋር በመተባበር ፣ ፯ ኛውን ዙር "አንዲር የሙዚቃ ትርኢት " ዛሬ ዕለተ ማክሰኞ ከቀኑ 11:30 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር እንደሚቀርብ የባንዱ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ እንዲሁም በባንዱ ውስጥ የዋሽንት ችሎታ ባለቤት የሆነው አርቲስት ጣሰው ወንድሙ ሹክ ብሎናል።
በዕለቱ በባንዱ የተቀነባበሩ አዳዲስ ሙዚቀዎች፣ በ ፰ ሴት ድምፃውያን የሚቀርቡ ዜማዎች እንዲሁም ልዩ የዳንስ ትርኢት እንደሚቀርብ ሰምተናል።
በነገራችን ላይ የሙዚቀ ትርኢቱን ለመታደም መግቢያው በነፃ መሆንንም ለማወቅ ችለናል።
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
@Getem
መሶብ ባህላዊ የሙዚቃ ባንድ በብሔራዊ ቲያትር ጋር በመተባበር ፣ ፯ ኛውን ዙር "አንዲር የሙዚቃ ትርኢት " ዛሬ ዕለተ ማክሰኞ ከቀኑ 11:30 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር እንደሚቀርብ የባንዱ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ እንዲሁም በባንዱ ውስጥ የዋሽንት ችሎታ ባለቤት የሆነው አርቲስት ጣሰው ወንድሙ ሹክ ብሎናል።
በዕለቱ በባንዱ የተቀነባበሩ አዳዲስ ሙዚቀዎች፣ በ ፰ ሴት ድምፃውያን የሚቀርቡ ዜማዎች እንዲሁም ልዩ የዳንስ ትርኢት እንደሚቀርብ ሰምተናል።
በነገራችን ላይ የሙዚቀ ትርኢቱን ለመታደም መግቢያው በነፃ መሆንንም ለማወቅ ችለናል።
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
@Getem
Forwarded from MarkdownBot
ሳያነብት እንዳያልፉ
// የስስታሙ ነጋዴ ታሪክ //
➖➖➖➖➖➖➖➖
በአንድ ወቅት አንድ ፈጣሪ በሰጠው ጸጋ አመስግኖ የማያውቅ
ስስታም ነጋዴ ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን..........ሙሉ መረጃ ለማግኘት እናለመማር ብቻ ይህንን ሠማያዊ ፅሁፍ ይንኩት👈
// የስስታሙ ነጋዴ ታሪክ //
➖➖➖➖➖➖➖➖
በአንድ ወቅት አንድ ፈጣሪ በሰጠው ጸጋ አመስግኖ የማያውቅ
ስስታም ነጋዴ ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን..........ሙሉ መረጃ ለማግኘት እናለመማር ብቻ ይህንን ሠማያዊ ፅሁፍ ይንኩት👈
#ወንድ ልጅ ሲጣላ#
ሰኞ
እርም የና'ቴን ስጋ፥ካ'ንቺ ገላ ብገኝ
ስምሽን ብጠራ፥ምርቅ ሆኖ ይነቀኝ፤
ማክሰኞ
ፍቅርሽ እንደ ቅጠል ፥ከላዬ ረገፈ
አይኔ ወፍራም ዳሌ፥ክንዴ ሽንጥ አቀፈ
ጣቴ እንደ ብርቱካን፥ቆንጆ ልጦ በላ
አዱኛዬ አበበ፥ ማር ከደጀ ፈላ፤
ዕረቡ
አይጭኑት ባ'ህያ፥አያስሩት በገመድ
እንዴት ያደርጉታል፥የዚያችን ልጅ መዉደድ፤
ሃሙስ
አመፀኛዉ ልቤ፥ዛሬ አንቺን ተመኘ
እግሬ በማለዳ ፥እደጅሽ ተገኘ፤
ዓርብ
ሆድሽ ከቶ አይጨክን፥ልብሽ በኔ ዓይፅና
ካ'ንቺ ተነጥዬ፥ሰዉ አልሆንምና፤
ቅዳሜ
እንደ ቀትር ፍትፍት፥አብዝቼ ልጉረስሽ
አልጠገብኩምና፥ደግሜ ብስምሽ
ስጭኝ ከንፈርሽን፥የሰዉ ስጋ ልብላ
አጥንቴ ይለምልም፥ሰይፌ ዝሆን ይቅላ፤
እሁድ
አንገትሽን ስዳብስ፥አፌ ከከንፈርሽ ሲገጥም
ያይንሽን ጮራ ተከትዬ፥አየሁ ስትስሚኝ አዲስ አለም።
(መሪጌታ)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
ሰኞ
እርም የና'ቴን ስጋ፥ካ'ንቺ ገላ ብገኝ
ስምሽን ብጠራ፥ምርቅ ሆኖ ይነቀኝ፤
ማክሰኞ
ፍቅርሽ እንደ ቅጠል ፥ከላዬ ረገፈ
አይኔ ወፍራም ዳሌ፥ክንዴ ሽንጥ አቀፈ
ጣቴ እንደ ብርቱካን፥ቆንጆ ልጦ በላ
አዱኛዬ አበበ፥ ማር ከደጀ ፈላ፤
ዕረቡ
አይጭኑት ባ'ህያ፥አያስሩት በገመድ
እንዴት ያደርጉታል፥የዚያችን ልጅ መዉደድ፤
ሃሙስ
አመፀኛዉ ልቤ፥ዛሬ አንቺን ተመኘ
እግሬ በማለዳ ፥እደጅሽ ተገኘ፤
ዓርብ
ሆድሽ ከቶ አይጨክን፥ልብሽ በኔ ዓይፅና
ካ'ንቺ ተነጥዬ፥ሰዉ አልሆንምና፤
ቅዳሜ
እንደ ቀትር ፍትፍት፥አብዝቼ ልጉረስሽ
አልጠገብኩምና፥ደግሜ ብስምሽ
ስጭኝ ከንፈርሽን፥የሰዉ ስጋ ልብላ
አጥንቴ ይለምልም፥ሰይፌ ዝሆን ይቅላ፤
እሁድ
አንገትሽን ስዳብስ፥አፌ ከከንፈርሽ ሲገጥም
ያይንሽን ጮራ ተከትዬ፥አየሁ ስትስሚኝ አዲስ አለም።
(መሪጌታ)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
👍1
"እኛ ስንዋደድ"
አናት ስላት እናት
ሁሌ እምናፍቃት
ደስታ ስላት ደስታ
ማትጠፋ ላንዳፍታ
እሳት ስላት እሳት
ደፍረዉ የማይነኳት
ፍቅር ስላት ፍቅር
ስለሷስ ብዘምር
ስለ ክብሯ ለመናገር
ላልጨርስ አልጀምር......
.
.
.
.
.
......ብቻ አለች አንድ ሀገር
ከህዝቦቿ ጀርባ ካድማሷ ባሻገር
(የ ሙሉ ልጅ እንድሪስ)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
አናት ስላት እናት
ሁሌ እምናፍቃት
ደስታ ስላት ደስታ
ማትጠፋ ላንዳፍታ
እሳት ስላት እሳት
ደፍረዉ የማይነኳት
ፍቅር ስላት ፍቅር
ስለሷስ ብዘምር
ስለ ክብሯ ለመናገር
ላልጨርስ አልጀምር......
.
.
.
.
.
......ብቻ አለች አንድ ሀገር
ከህዝቦቿ ጀርባ ካድማሷ ባሻገር
(የ ሙሉ ልጅ እንድሪስ)
@getem_sourcebot
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)
ሎተሪ ሻጭ እኔ...
እድል እድል እያልሁ ፣ እድሌ ቢያመልጥም
በጄ ያለን እድል
በማግኘት ምኞት ውስጥ ፣ ላለ ሰው ብሸጥም
እንደ ቆራጭ ልቦች
ተስፋ እየገመድኩኝ ፣ እድሌን አልቆርጥም፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ሎተሪ ነሽ አንቺ...
ከልብ ለቆረጠሽ ፣ ተስፋ ለሰነቀ
አገኛለሁ ብሎ
እድል ለሚሞክር ፣ እድል እየፋቀ፡፡
።።።
@getem_sourcebot
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ሎተሪ ሻጭ እኔ...
እድል እድል እያልሁ ፣ እድሌ ቢያመልጥም
በጄ ያለን እድል
በማግኘት ምኞት ውስጥ ፣ ላለ ሰው ብሸጥም
እንደ ቆራጭ ልቦች
ተስፋ እየገመድኩኝ ፣ እድሌን አልቆርጥም፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ሎተሪ ነሽ አንቺ...
ከልብ ለቆረጠሽ ፣ ተስፋ ለሰነቀ
አገኛለሁ ብሎ
እድል ለሚሞክር ፣ እድል እየፋቀ፡፡
።።።
@getem_sourcebot
@getem
@getem
@lula_al_greeko
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM