ግጥም ብቻ 📘
64.3K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
😂😜😜
የግንቦት ሀያ በአል አቀባበር እንዴት ነው?

በሬው
@wegoch
@wegoch
@getem
ለእዮብ ዘማርያም
እና
ስምረት


ብዙ ከዘገየህ ቀርተሀል
ብየ አለምን እንዳላይ፣
ቶሎም መጠህብኝ ፍኖስ ሳላበራ
በጨለመ ሰማይ፣

ከምታስጨንቀኝ ከምታሸብረኝ
ፋኖስን ፍለጋ ከምታራሩጠኝ

እባክህን አምላክ ከዚህ ሁላ ጣጣ
በንስሀ ፀሎት እራሴን ሳልቀጣ
ብዙም እንዳዘገይ ቶሎም እንዳትመጣ።

@getem
@getem
@lula_al_greeko
..

ከፍቶህ ተጎሳቁለህ
እያዩ እንዳላዩህ
ባላየ ዝም እሚሉህ

አልበቃ ሲላቸው.....

እንዲህ ነው እንዲህ ናት
እያሉ በኩራት
በራሳቸው ችሎት
ተከሳሽ በሌለበት
ፍርድ ከመስጠት

ምነው?.....

ያንተን ኑሮ ኖረው
በተጓዙሉህ ጉዞህ
እያንዷንዷ እርምጃህ
የዘወትር ስሜትህ
አድምጠው ተረድተው
አንተን መስለው
አንተን ሆነው
በፈረድብህ ።
...



Tedros g. Belay

@getem
@getem
...እኔ...

ላንች ያለኝ ፍቅር
እንደ ስጋ ምኞት
እንደጌታ ታምር
ሺመሽም ሲነጋም
አድሮ የሚጨምር።

(ግጥም እዎዳለው)

@getem
@getem
#በዕውቀቱ_ሥዩም

ወደ ምንም የሚያደርስው መንገድ

ቸኳይ የሚመስለው
ፈጣን የሚመስለው
በውልውል መኪና
በፋሺን መጫምያ
ወይም በባዶ እግሩ
ሸው እልም የሚለው
ይሄ ሁሉ ምሁር ይሄ ሁሉ ማይም
መንገዱን የሞላው ከታችም ከላይም
ሲመላለስ እንጂ ሲደርስ አይታይም፡፡

@getem
@getem
@lula_al_greeko
               "ውበት እና አፍንጫ"

   የሾለ አፍንጫሽ ውብ ነው የተባለው
   የውበት መለኪያ የአፍንጫ መሰልከክ
   ሆኖ እንዳይመስልሽ
   ይልቅስ ደፍጣጣው ሰልካካ እንድትባይ
      እድል ፈጠረልሽ
 
      ሰልካካ አፍንጫ
    ከደፍጣጣው አንፃር ተመዝኖ የመጣ
    የውበት መግለጫ
    መሆኑን ዘንግተሽ
    ውበት መሰልከክ ነው እያልሽ ባገሩ ትመፃደቂያለሽ

     ረስተሽው አንጂ
     ሰልካካ አፍንጫ
     ደፍጣጣ አፍንጫ
      ምንም ተነፃፅረው (አንዱ ከአንዱ በልጦ)
      ውበትን መለኪያ ማሳያ ቢሆኑ
      ሁለቱም ሲነኩ የሚወጣው ነገር አንድ አይነት መሆኑ
      
        ከ ዮሴፍ ግርማ ወርቅነህ
          @getem
          @Wegoch


  
  
አንችን የሳምኩለት
( © #እሱባለው_ኢትዮጵያዊ )

ገነት እንደገባሁ ~ ልቤ ተደስቶ
ሀጥያተኛ ሲማር ~ ሲኦልም ተከፍቶ
ክዋክብት በሀሴት~ ከሰማይ ሲረግፉ
ተራሮች ተንደው ~ ምድር ሲነጠፉ
ደራሲያን ሁሉ ~ ስላንቺ ሲፅፉ


ስደተኛ ሁሉ ~ እቤት ተመልሶ
ጤና የነሳቸው ~ ሁሉም ተፈውሶ
ስራ ፈላጊዎች ~ አግኝተው እንጀራ
እናት በልጆቿ ~ በልቧ ስትኮራ
በሰልፍ የሰለቹት
ታክሲ ጠባቂዎች ~ መኪና ሲገዙ
አበዳሪ ሀገራት~ እዳ ሲሰርዙ
መንግሥት ያሰረውን ~ በምህረት ሲፈታ
ሀሳብ አሸንፎ ~ ጥይትን ሲረታ
ጎዳና እሚተኛው~ ቪላ ተሸልሞ
ብሄርተኛው ሁሉ~ ባንድነቱ ቆሞ


ፍጡራን በሙሉ
በደስታ ሲሞሉ

በረሃዉ ለምልሞ~ በአበቦች ይደምቃል
አራዊት በፊናው~ በፍቅር ይስቃል
የምመኘው ሁሉ ~ ሆኖ ይታየኛል
አንቺን የሳምኩለት ~ እንዲህ ያደርገኛል ።
______ ዛሬ |2010_______

@getem
@getem
@lula_al_greeko
🤩1
ስዕል ሙዚቃ ነው


በእርሳስ ተጭሮ ቀለም የተቀባ
ለነፍስ የቀረበ
ከሩቅ የሚያደምጡት ልብን የሚያባባ
ስዕል ሙዚቃ ነው

በነጠብጣብ ልቀት፡ስንኝ ተደርድሮ
በቡሩሽ የሚዜም፡በሀሳብ ገመድ ታስሮ
ስዕል ሙዚቃ ነው

በቀለማት ቅኝት በአርምሞ ሚደመጥ
ሲያሻው
የሚያስጨፍር ጮቤ የሚያስረግጥ

……ሰለሞን ጠቢቡ

@getem
@getem
@AmharicTreka
በትግል የተገኘ ውበት
(በላይ በቀለ ወያኔ)
.
.
ባሩድ ባሩድ የሚል ፣ የገላሽ መአዛ
ዜና ዜና ሚሸት ፣ ያንደበትሽ ለዛ
እንደ እግረኛ ጦር...
የተደረደረው ፣ የሚማርክ ጥርስሽ
እንደ ሻብያ ጦር...
የሚንቀጠቀጠው ፣ ዳሌሽ እና ጡትሽ
ስልጣን ስልጣን የሚል ...
ቢስሙት ማይሰለች ፣ የስስ ከንፈርሽ ጣ'ም
ይህ ሁሉ ውበትሽ ፣ ሚናፍቀው በጣም
በፅኑ ትግል እንጂ ፣ በተፈጥሮ አልመጣም

@getem
@getem
@lula_al_greeko
😁1
 በ አገኘሁ አሰግድ

“ ያስለቅሳል እንጂ ይህስ አያሳቅም
ግንድ ተደግፎ ዝንጀሮ ጫት ሲቅም”
(አማርኛ እንዳበጁሽ አትበጂም)

@getem
@getem
#አለማማር_ማማር
:
:
ገጣሚው በግጥሙ ገና ከምርጊቱ
ውበትን ያደንቃል
ወረቀት ብዕሩም የቆንጆን ሴት ፀዳል
እልፍ ያንፀባርቃል።
:
:
አንደኛው ገጣሚ:
:
:
ዐይኖችሽን አይተው ኮከቦች አፈሩ
ድንቄም ብርሃን ሆንን ብለው ተናገሩ።
ፀሀይዋም ጠለቀች ባለችበት ቦታ
አንቺን ብታይ ጊዜ ተደናግራ ፈርታ።
እውነት እልሻለው ምዬ በዚ ሰማይ
ጨረቃም ሻማ ናት ካንቺ አንፃር ስትታይ።
እያለ ይገጥማል እያለ ይፅፋል
ቃላትን መልምሎ ውበትን ያጎርፋል
ሰማይ ጠቀስ ግጥሙን በቀለም ይነድፋል።
:
:
ሌላኛው ገጣሚም:
:
:
ገና ከሩቅ ሳይሽ ይድናል ህመሜ
ብሞትም አይቆጨኝ ከንፈርሽን ስሜ።
ባለንጋ ጣቶችሽ የዳበስሺኝ እንደው
እንደ ቶን እሳት ነው ውስጠቴ ሚነደው።
ዳሌሽ እየኮራ ባትሽ ላይ ሲሳለቅ
እኮሰምናለው እንደመታው መብረቅ።
ወገብሽ ሲል ዘመም ጥርስሽ ሲገለጥ
ነግቶ ይመሽብኛል ምራቄን ስውጥ።
እያለ ይገጥማል እያለ ይፅፋል
መልዕቁን ዘርግቶ ቁንጅናን ይቀዝፋል
ዘንድሮስ ገጣሚው በውበት ተለክፏል።
:
:
አቤት ጊዜው ከፋ አቤት ጥበብ ከፋ
ለመልከ ጥፉ ሴት የሚገጥም ጠፋ።
ከሊቅ እስከ ደቂቅ ባንድ አሳብ ታጠረ
መልከ ጥፉነትም ግጥም ሳይሆን ቀረ።
:
:
ይህን ተመልክቶ ይህን ዐይቶ ኖሮ
ሌላም ሰው እንዲለምድ
ለመልከ ጥፉ ሴት ግጥምን በመፃፍ
እስኪ እኔው ፈር ልቅደድ።
:
:
ያ ገጣጣው ጥርስሽ የኔ ጥርስ ቢሆን
ምነኛ ታደልኩኝ
ያለምንም ችግር አጥንት እንደ ስጋ ስለሚቆርጥልኝ።
ብይ ሚያክሉትን እነዚያን ዐይኖችሽ ያየዋቸው እንደው
ምን እንዶን ባላውቅም አንድ ስሜት አለ ልቤን የሚርደው።
ከእጥረቱ የተነሳ አልያዝም ብሎሽ
ፀጉርሽ ሲፈታ
ያንን ያየው ጊዜ ከቃላት በላይ ነው የሚሰማኝ ደስታ።
የከናፍሮችሽ ትልቅ ዳቦ ማከል
በውነት ይገርመኛል
የራበኝ እንደሆን ሄደ ግመጣቸው
ብሎም ያሰኘኛል።
እያልለኩኝ ገጥማለው እያልኩኝ ፅፋለው
የመልከ ጥፉን ሴት ውበት አገዝፋለው
አለማማር ማማር እንደሆነም ነድፋለው።

#ሄኖክ_ብርሃኑ
ለአስተያየቶ @Henokbirhanu

@getem
@getem
በ‘ኩለ ሌት ካፊያ
።።።።።።።።።።።።

መንፈስ በሚረብሽ
ልብን በሚንጠው፣ የኩለ ሌት ካፊያ
ማንም አይናፍቅም
ከደመና ጋራ የፀሐይን ልፊያ።
ነፍስን በሚቀማ
ጉልበትን በሚያርድ፣ የጨለማ መብረቅ
ማንም አይጠብቅም
የረጠበ ነፍሱ፣ ከርጥበቱ እንዲደርቅ።

አለሁ እኔ ግና
ከፈሰሰው ዝናም፣
አንዳች ስውር ምስጢር፣ ከዘንጉ እየማተርሁ
የፀሐይንና የደመናን ርቀት በሀሳቤ እየመተርሁ።
አለሁ አኔ ግና
የመብረቅን ግለት
የነፍሴን እርጥበት
እንደ ልብስ አድራቂ፣ በግምት ስመዝን
ከጣራዬ እኩል
ነፍሴ ላይ በሚፈስ
በናፍቆትሽ ካፊያ፣ ለራሴ ሳላዝን።

ነፍሴን እንዲያረጥብ
ከፀሐይ ከልሎ
ከመብረቅ አስጥሎ
በመንፈሴ ሽንቁር፣ ልቤ ላይ ሲያካፋ
እኔ ደመና አለሁ
ከናፍቆት ፀሐይሽ፣ በሀሳቤ ስላፋ።
ላባራሽ ስለፋ!!!

#yadel

@getem
@getem
@getem
መልከኛ እውነት

ጉች ጉች ያሉ
ስኒ የመሠሉ
ጡቶቿ!!!.....እያሉ
አላፊና አግዳሚ ሊያዩሽ ይወዳሉ
አንቺም ተሽቀርቅረሽ
አውቀሽ አስጮልቀሽ
ለአይን ገበያ ታወጫቸዋለሽ
ታዲያ
ወጪና ወራጁ
እየነካሽ በእጁ
በቀን በቀን ታሽተሽ አይተው በጎመጁ
ጉቹ ይቀርና ጥልጥል ይሆናሉ
ከደረትሽ ወርደው ሆድሽ ይተኛሉ
እርቃን ቢወጡ እንኳን ተመልካች ያጣሉ
እናም ታዲያ ቆንጆ!
ውበት ጤዛነቱን
ስጋም ባዳነቱን
አይተው ቢታዘቡ
ሀበሾችም አሉ......ቁንጅናን ገደቡ
ለሰው ቅን ያሠበ...መልካም ሰው ነው ውቡ።
"አብርሀም ተክሉ"


@getem
@getem
ተለቀቀ ሲሉኝ ፣ ኔትወርኩ ነው ብዬ
ተለቀቀ ሲሉኝ ፣ መብራቱ ነው ብዬ
ተለቀቀ ሲሉኝ ፣ ውሀውን ነው ብዬ
ተለቀቀ ሲሉኝ ፣ ባጀቱ ነው ብዬ
ተለቀቀ ሲሉኝ ፣ ስልጣኑ ነው ብዬ
ለካስ አንዱ ኖሯል ፣ ታላቁ ሰውዬ።

በመለቀቁ ደስስ

።።። አላህና መድሐኒዓለም ተባብረው ያጎሳቁሏችሁ።።።

በላይ በቀለ ወያ

@getem
@getem
©

ህልሜ ከ'ኔ ሸሽቶ
በአንቺ እንቅልፍ ውስጥ
ማድባት ከጀመረ፣
(እመኚኝ ልንገርሽ)
የስጋዬ ሳይሆን
የነፍሴ ቁልፍ ነው
ካንቺ ዘንድ የኖረ፣

(ምክንያቱም)
ህልሜ ነው መኖሬ
በሌሊት አለም ውስጥ
አንቺን የሚያሳየኝ፣
ከስጋዬ አልፎ
ነፍሴን ሚጎበኘኝ...
(ለዚህ ነው)
...///...
ሻሸመኔ

@getem
@getem
👍1
መዋደድ መፋቀር፣ ከንቱነት ነው ብላ
ጨዋ-ነኝ ባይዋ ሴት፣ ቀረች በነጠላ፡፡

(ሲታዛዚን ;P )

@getem
@getem
*ያችን ልጅ ንገርዋት*
(ሠለሞን ሣህለ)

እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
ልከ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በሉዋት

አወ እንዳገሬ ነዉ…
እንደ ምንጩ ጣእም እንደ አፈሩ ሽታ
ልጎንጭሽ የምላት…
ልዳብስሽ የምላት ጠዋትና ማታ
ለብሻት የምኖር…
እንደ ቀዩ ጃኖ እንደ ነጩ ኩታ
ጋቢዋ ነኝ እኔ…

ጠላት የተኮሰዉ ንፋስ እንዳይነካት
ሁለት ግዜ ዙሬ…
ወገቡዋ ላይ ያደርኩ የማርያም መቀነት

እንደ አገር አርጅታ…
እንደ አገር አዉግታ ደግሞ ተበሳጭታ
እድሜዉ ይሁን ንዴት ጸጉርዋን አሸብታ
አፋፉ ላይ ቁማ…ብቻዋን ቆዝማ
ድንገት ብታገኝዋት…

እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
ልክ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በልዋት
ንገሩልኝ ዘመድ ንገሩልኝ ወገን
እኔ በሱዋ ፍቅር እንዴት እንደምሆን

እንደተዋለበት ጤናዉን እንዳጣ
በጠላ አስተናግር በጥብጦ እንደጠጣ
ያስለፈልፈኛል ጩህ ጩህ ያሰኘኛል
የቀኑ ሳይበቃዉ ሌሊት ያስዞረኛል

ጎርፉን እጠጣለሁ አፈር እቅማለሁ
ጎርፉን እየጠጣሁ….ሃገሬን እላለሁ
ጨለጥኩዋት እላለሁ
አፈሩን እየቃምኩ….ሃገሬን እላለሁ
በላሁዋት እላለሁ
ጸጉሬን እነጫለሁ ልብሴን እቀዳለሁ
እንዳይሆን እንዳይሆን እንዳይሆን ሁኛለሁ ፤

እናም ያች የኔ…
የምጠብቃት ሴት የመጣች እንደሆን
መስከረምን አልፋ…
ጥቅምትን ተሸግራ ህዳሩ ሲታጠን

ገላየ ቆሽሾ አካላቴ ዝሎ
ገጼ ተጎሳቅሎ
ድንገት አልፋኝ ብትሄድ…
ፍቅሬ ተዘንግትዋት…
ማንነቴ ጠፍትዋት…

እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
እንዳገሩ ነበር የሚወድሽ በልዋት፡፡

@getem
@getem
@lula_al_greekO
እኔ እንዳልጠራ
(ለእዮብ ዘማርያም ለስምረት እና ለመጨረሻው ገጣሚ)

አልልህም ነገር ቶሎ ና፡ ቶሎ ና
አልሠራሁምና አንዲት ነገር ደህና
ቅርም አልልህም
ወዜና ጥረቴ ሁሉም ቢደመርም
የልፋቴ ዋጋ ደሞዝ ቢታሠብም
ዕዳዬን አይከፍልም
ግና ግን ጌታዬ ይቺ ነዳይ ነፍሴ ስጋ የበደላት
ካንተ ፍቅር በቀር የለም የሚክሣት
የፈተናው ገመድ ግዜ ያከረረው
ዘመን ያደለበው
አንተ ስትመጣልን ብጣሽ ነው ሚሆነው

ያን ግዜ ነው መፍራት
ስጋ ከነፍስ ጋር በአንድ እንዳልተሠፋ
አላቅም ይላታል ጥግ እየተጋፋ

አንተም ትመጣና
እርቃን የቀረችው ቅንጣቢ ነፍሴን
ገላልጣ ብታየው ሀፍረቴን ሀጥአቴን
ክርፋቴ ገፋፍቶህ ጥለህ ትሄዳለህ
ለፀዓዳ ቤቴ አትመጥንም ብለህ

ባትመጣ ደሞ
ይህቺ ምስኪን ነፍሴ አለም የበደላት
ዝንት አለም ልትኖር ነው ስጋዬ ሲገዛት
ስጋዬ ሲወቅጣት

የቱ ነው ሚሻለው
የቱ ነው ሚበጀው?

ብትመጣ
በህግ ያልተገዛ ባንተ ያልታመነ
ነፍሴ ተኮነነ
ብትቀር
ዘመን የጠበቀ ዘመን የዋለለ
ይመጣል እያለ
ሁልግዜ ሊኖር ነው ነፍስ እያቃጠለ

ወዳጄ
መምጣትህ ቅጣት ነው
መቅረትህም ሞት ነው
እኛ ማለት ላንተ በደረቱ ሚድህ እንፉቅቅ ልጅ ነንና
ውስጡ ያልበሰለ ጉልበቱ ያልጠና
መምጣትህም መልካም መቅረትህም ደህና
ፍቃድህ ነንና፡፡

ግና ግን ጌታዬ የሀጥአቴን ጭቃ በእንባ ሳላጠራ
እኔ እንዳልጠራ፡፡

አንተ እንደፈለክ


@getem
@getem
@inluvwidart
--የሴት ልጅ ያሉኛል አዎ የሴት ልጅ ነኝ--

አዎ የሴት ልጅ ነኝ የውዲቷ እናቴ
ከግማሽ አካልዋ ተቆርጦዋል እትብቴ

አዎ የሴት ልጅ ነኝ የኔ አንድ ውዲቷ
ጡት የምታጠባ በታጠፈ አንጀቷ

ያንስብኛል እንዴ የሴት ልጅ ለመባል
የአንድ ቀን ጭነቅዋ ምጧ አኮ ያበቃል

እንዴት አልጠራ አልባል የሴት ልጂ
ውርደት አኮ አያደለም ክብር ቢሆን እንጂ

እንደሻማ ቀልታ ብርሀን ለሆነች
የሷን ኑሮ ትታ ለኔ እየኖረች
እኔን ለማቃናት እሷ አየጎበጠች

ለራሷ ታርዛ እኔን ያለበዘች
እርጥቡ ደረቁ ለ፡ሁሉ ሲነድባት
ዋጥ አድርጋ ችላ ሰው እንድሆንላት

ለዚህ ያበቃችኝ እንድዉል ከሰው ተራ
ክብር ማንነቴ ናት በስሟ ልጠራ


ምንጭ: የግጥም አምባ
@getem
@getem
✧✧✧ ብዙ ተባዙ

የእናትነት እጣ፣ ያባትነት ውርሱን
የፍጥረትን ምስጢር፣ የቤተሰብ ቅርሱን
የትውልድ አደራ፣ የብዙ ተባዙን፤
ለአእምሮህ ሳይሆን ባሻው ለሚከንፈው
ለልቦናሽ ሳይሆን ስርአት ለሚገድፈው
ለፈቃድህ ሳይሆን እብደት ለሚለክፈው
ለህሊናሽ ሳይሆን ዓለም ለሚያጎድፈው፤
ሰጠው ለሽፍደትህ ጦር ለማይመልሰው
ለመግነጢስ ገላሽ ጾም ለሚያስፈርሰው
ጻፈው በገበናሽ በጉያሽ ትኩሳት
በማትሟገተው የጭንህ ዲን እሳት፤
በሰጣችሁ ርስት በወጉ አንድትረቡ
በሴስ አቆራኝቶ በወሲብ ቀለቡ
ምድርን በሰው ሞላት በኪነጥበቡ።

ፋሲል ይትባረክ

@getem
@getem
@getem