ግጥም ብቻ 📘
64.3K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
የናፈቁ ነፍሶች ደስ የሚል ግጥም (poem)
😔 የናፈቁት ነፍሶች 😔

@getem
@getem
◌◌◌◌◌ በብቸኝነት ◌◌◌◌◌
ከተማው ተይዞ ሲጣል ምድረበዳ
ሰው ከራሱ በቀር ለሌላው እንግዳ
ሆኖ ሲውል ሲያድር በብቸኝነቱ
ሞተች ያላል አለም
ውስጣዊ ፍጥረቱ።

በደበበ ሰይፉ

@getem
@getem
✧✧✧ ብዙ ተባዙ

የእናትነት እጣ፣ ያባትነት ውርሱን
የፍጥረትን ምስጢር፣ የቤተሰብ ቅርሱን
የትውልድ አደራ፣ የብዙ ተባዙን፤
ለአእምሮህ ሳይሆን ባሻው ለሚከንፈው
ለልቦናሽ ሳይሆን ስርአት ለሚገድፈው
ለፈቃድህ ሳይሆን እብደት ለሚለክፈው
ለህሊናሽ ሳይሆን ዓለም ለሚያጎድፈው፤
ሰጠው ለሽፍደትህ ጦር ለማይመልሰው
ለመግነጢስ ገላሽ ጾም ለሚያስፈርሰው
ጻፈው በገበናሽ በጉያሽ ትኩሳት
በማትሟገተው የጭንህ ዲን እሳት፤
በሰጣችሁ ርስት በወጉ አንድትረቡ
በሴስ አቆራኝቶ በወሲብ ቀለቡ
ምድርን በሰው ሞላት በኪነጥበቡ።

ፋሲል ይትባረክ

@getem
@getem
🖼📸📷🖼📸📷🖼📷📷
የፎቶግራፍ አድናቂ ከሆኑ በተለያየ መልኩ ሃገርኛ ምስሎችን በየቀኑ ለእናንተ እናደርሳለን ሊንኩን ተጭነው ይቀላቀሉ
እናመሰግናለን ።
📸📷📸📷📸📷📸📷📸📷📸
@Mykeypictures
ባክህ ቶሎ አትምጣ...
--------------------------
(እዮብ ዘ ማርያም)
.
.
ጥሩ እንዳደረጉ እንደሰሩ ደህና
ብለው ይፀልያሉ ጌታ ሆይ ቶሎ ና
እኔ ግን ምስኪኑ ሀጢያተኛ ልጅህ
ይችን ፀሎት ፀለይኩ ወድቄ ከደጀህ
አምላኬ፣
ካለሁበት ሀጢያት ነብሴን ሳላወጣ
በንስሀ ፀፀት እራሴን ሳልቀጣ
ባክህ ቶሎ አትምጣ!

@getem
@getem
@lula_al_greeko
ሰውን ግን ምን ነካው
በቶራህ
በስብዕናችን ቻናል ብቻ join @Abysinia @Abysinia
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖 ግጥምን በጃዝ በነፃ

ውድ የግጥም ብቻ ወዳጆች እንሆ የሁለችንም ቤት በሆነው በብሄራዊ ቲያትር ነገ ዕለተ ረዕቡ ግንቦት ፲፭ በ 11:30 ሁላችሁንም ጋብዘናችውሃል። እንደው ጠሪ አክባሪ ነውና አደራ እንዳትቀሩብን ብለናል።
~~~ ወቸው ጉድ! ~~

ኣምሳለች
እሺ እያለች
ኣታለለች
እምቢ ብትል
ምን ታስከትል?

ልጅ ቅጣው
ለሽምጠጣው
ዘልሎ ወጣው
ኣለሁ ብሎ
ሄደ ጥሎ

ጋሽ ገመዳ
ዶፍ ኣራዳ
ያ ወራዳ
ተሽቀርቃሪ
ኣጭበርባሪ!

’ትየ ሙና
ከጋሸ ጦና
በጥሞና
ደጅ ካስጠኑ
ይኮነኑ

ኣባ ተክሌ
ኣልባሌ
ጨው ኣሞሌ
ጥምጥማቸው
ከበዳቸው

እሱን ጥሩት
ኣትቅጠሩት
ምን ትፈሩት
ባባ ዘውዱ
መጣ ጉዱ

በገመቹ
ላዩ ታቹ
ተሰላቹ
መሃል ሆዳቸው
ቡጢ በሏቸው!

ለልመና
’ትየ ሃና
የሉምና
ዘመድኩን
ያ ብኩን

ዘልዓለም
ሲፋለም
ያየ የለም
ና ኣሉት
ሊበሉት

ኣቶ ካሰው
ልጅ ጣሰው
በጣጠሰው
ኣስናቀ
ቦጨቀ

ዘበርጋ
ሳይረጋ
ተዘረጋ
ሲነጋ
ተዋጋ

ዳምጠው
ኣዳለጠው
ኣመለጠው
ኣሓዱ
ምጣዱ

ሓመልማል
ከጀማል
ስትማማል
ሙስጣፋ
ተንከራፋ

ኣቶ ያለው
ሞት ዘለለው
ምን ይሻለው
ልጅ ገለታ
እንጃለታ

ሳቢሳ
ከግሪሳ
ለቶሎሳ
ኣቶ ገቢሳ ያ ደሳሳ

ወልደሩፋኤል ያ ሳጥናኤል
በሚካኤል
ዓርፎ ይሥራ
ሰው ኣይጥራ

ጥላሁን እስኪ ኣሁን
ምን ይሁን
ባላባት
በቀረባት

እንደፎከረው
ኣከራክረው
ኣይምረው
ያጠረው
ኣበጠረው

ኣቶ ፈረደ
ተወራረደ
ተንገዳገደ
ኣቶ ረታ
መላ መታ

ኣቶ ፈለቀ
የልጅ ዘለቀ
ጥርስ ኣወለቀ
ዓለሙ
ድዳሙ

ለዓብደላ
ኣስኪጠላ
ስጡት ጠላ
ሲጠጣ
ይንጣጣ

ለቢራራ
ሳይጣራ
ስጡት ቢራ
እስኪነቃ
ይንቃቃ

ልጅ መርሻ
ከጥሻ
ምን ትሻና ውጣ
ዓይንህ ይውጣ

ኣድማሱ
ከትራሱ
መለስለሱ
ተቃቀፉ
ተናቀፉ

ይላላ
ፊት ኋላ
ሞላላ
ኋላ -ሸት
ጥላ -ሸት

’ትየ ምርጡ
ሲጠጡ
ምኑ ቅጡ
ለጠላቸው
ኣልከፍላቸው!

ዓለሚቱ
ከማሚቱ
ሲጓተቱ
ምሕረቱ
መሞቱ

ተማሪ
መሰሪ
ሰርሳሪ
ሲሰረስር
ይከስር

ሊበሉት
ሰለሉት
ደለሉት
ያ ነጋሽ
ተናካሽ

ከወርቁ
መዳረቁ
ይታረቁ
ለፀሎት
ማ’ ብሎት ብሎት

ፀሓዬ
ከታዬ
ተያዬ
ብድር
በምድር

ኣማረ
ዘመረ
ከበረ
ሲዘምር
ይደምር

ወንዳፍራሽ
ካምባፍራሽ
በኣዳራሽ
ተጣሉ
ሊባሉ

ለኣመሉ
ኣስካሉ
እያሉ
ምን መጣ
ገበጣ

ስብሓቱ
ከጫልቱ
ማንጋቱ
’ንጃለቱ
ያ ገልቱ

ልጅ ሃይሉ
ሳይከፍሉ
ሊበሉ
ብድራቸው
ስጧቸው

ልጅ መራራ
ሲንጠራራ
ተሰበራ
ወደቀ
ደቀቀ

ሰመረ
መከረ
ሰከረ
ሲሰክር
ይፎክር

ገ/ኢ. ጐርፉ።

@getem
@getem
ባክህ ቶሎ ይምጣ!
(ስምረት አበበ)

እንኳንና 40,- ሺህ አመት ቢሰጥህ
ዝንት አለም አትጸድቅም በወዝ በጥረትህ
ይልቁኑስ ይምጣ.....
ድካምህን ያገዘው
በጎልጎልታ ሞቶ ሀጢያትህን ያጠበው
ጽድቅ የለኝም ብለህ ራስህን አትኮንን
ጽድቁን ቆጥሮልሀል እሱን ያመንከው ቀን

("ባክህ ቶሎ አትምጣ" ለሚለው ግጥም የተሰጠ ምላሽ)

@getem
@getem
@poemmedia
~~~~ አባወራ ~~~~

ወንደላጤ አይደለሁ
ጮኛ ፈላጊ
አፍላ አፍቃሪ አይደለሁ
ጅንን ተውረግራጊ፤
አልፏል እንደጥላ
ቆሞቀርነቴ
በትዳር ከለላ
ተከትቷል ስጋቴ።
ቀርቷል መሳቀቄ
በራዬን ደብቄ
ሽበቴን መንጭቄ
ቦርጬን አስጨንቄ
ከእድሜ ትንቅንቄ።
በእግዜር ፊት መሃላ
ፈቅዳኛለች ሚስቴ
እጣዬን ተካፍላ
ማእድህ ማእዴ ብላ
ገብታለች ከቤቴ፤
ላትሄድ እኔን ትታ
ትዳሯን ላትፈታ
ባምር ብንገላታ
ባሸንፍ ብረታ
ብወፍር ብከሳ
ብወድቅ ብነሳ
ባስታውስ ብረሳ
ባንኳርፍ ብፈሳ።

ፋሲል ይትባረክ

@getem
@getem
👍1
ቀጥረሽኝ....
ፈላስፋ አደረግሽኝ(ርእሱ ነው)
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ላገኝህ ስትዪኝ...
በፊትሽ ለማመር ፣ በፊትሽ ልነጣ
ልብሴን አጣጥቤ ፣ ገመድ ላይ ሳሰጣ
ደመናው ኬት መጣ?
አርፍጄ እንዳላጣሽ ፣ ስፈራ ስሳቀቅ
ልብሴን በላዬ ላይ
በእግር መንገድ ላደርቅ
ስራመድ እየሮጥኩ
መንገዱ አጠረ ፣ ካልሽኝ ቦታ ደረስኩ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ሰአቱ እስኪደርስ ፤ ሰአት እየፈጀሁ
በምናብ ገፄ ላይ
ስትመጭ የምልሽን ፣ ቃል እያዘጋጀሁ
ካንቺ ጋራ ስሆን...
እንዴት እንደምሔድ ፣ አካሔድ ሳጠና
አንዴ አንገት ስሰብር ፣ አንዴ አንገት ሳቀና
አንዴ እግሬን ስጎትት፣ አንዴ እግሬን ሳነጥር
ቀፈቴን ስደብቅ ፣ ደረቴን ስወጥር
እንደድሮ ለኪ ፣ እርምጃ ስቆጥር
ጫማዬን ነደለው ፣ አገኘኝ እንቅፋት
ሰአቱ ገና ነው...
ኒስትሮ ጋ ሔድኩኝ ፣ ጫማ ለማሰፋት፡፡
ሊስትሮው...
በወስፌ መንጠቆው ፣ ጅማቱን ይጠልፋል
ቀዳዳ እያበጀ ፣ ቀዳዳ ይሰፋል
ይለኛል ጫማዬ...
"የህይወት ትንሽ ሽንቁር...
ጊዜና ግመልን ፣ እኩል ያሳልፋል፡፡
ሰአቴን አየሁት ፣
ከቀጠርሽኝ ሰአት ፣ ጥቂት ደቂቃ አልፏል፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።፣።።፣።፣
እየተጣደፍኩኝ...
ያልሽኝ ቦታ እስክደርስ
እስካገኝሽ ድረስ
ቅድም ያጠረብኝ...
እዛው በዛው ሆኖ ፣ ራቀኝ መንገዱ
መድረስ ተረት ሆነ ፣ "ሲሔዱ ሲሔዱ
ሲሔዲ ሲሔዱ
ሲሔዱ ሲሔዱ ፣ መንገዱ አያልቅም
ሳጣሽ ተፈላሰፍኩ...
መፈለግ ነው ብዬ ፣ የፍልስፍና አቅም፡፡
፡፡፡ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እፈላሰፋለሁ!
ልብሴን ስዳብሰው ፣ እላዬ ላይ ደርቋል
ሰማዩን አየሁት ፣ ደመናው ተፍቋል
መንገዱ ቅድም ላይ ፣ ልሔደው ስል ያልቃል
አሁን ላይ ስሔደው...
ስሔደው ስሔደው ፣ ስሔደው ይርቃል፡፡
ወደ ጫማዬ ሳይ ፣ አንድ እግሬ ነው ባዶ
ሊስትሮው እጅ ላይ....
ትቼው መጥቻለሁ ፣ ያልሽኝ ሰአት ሔዶ
የህይወትን ሽንቁር...
ላይጠግን ይሰፋል ፣ በወስፌ ተቀዶ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እፈላሰፋለሁ...
ቀድሜ መጥቼ ፣ በማርፈዴ ሳጣ
በጣም ከቀደመ....
እጅጉን ይሻላል ፣ አርፍዶ የመጣ፡፡
ሰው የሚሉት ፍጡር...
ነፍስ ከስጋ ጋር ፣ እኩል ሲሞግተው
ፍፁም ልሁን ሲል ነው ፣ ፍፁም የሚስተው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እፈላሰፋለሁ...
ቀድሜሽ መጥቼ ፣ አርፍጃለሁ ሳውቀው
እፈላሰፋለሁ!
ቀድመው ሲያረፍዱ ነው ፣ መንገድ የሚርቀው
እፈላሰፋለሁ!!!
የሚጠነቀቅ ነው ፣ ማይጠነቀቀው!!!

@getem
@getem
@lula_al_greeko
ስወድሽ ውደጂኝ
(Dakstar)


ውዴ.....
እኔ አንቺን መውደዴ
መጥፎ እድል አይደለም ችግር የሚያመጣ
ወንጀልም አይደለም በህግ የሚያስቀጣ
ሀጢያትም አይደለም አንገት የሚያስደፋ
ሰማይ ቤት አትቆምም ነብሴ ተጠይቃ-ትዕዛዝ ተላልፋ
ታድያ አንቺን መውደዴ ምን ላይ ነው ጥፋቱ?

ወደድኩሽ ማለቴስ ምንድነዉ ክፋቱ?
ጠልተሺኝ እንዳይሆን ቁርጡን እንዳላውቀው
እንደምትወጂኝ ነው ውስጥሽ 'ሚያሳብቀው።
ታድያ እየተዋደድን አንድ ሆኖ ውስጣችን
ለምን እንራራቅ እንሁን ለብቻችን

ስለዚህ ውድዬ.......
ባንቺ ጨርቅ ሳልጥል ወይ ሳታሳብጂኝ
በፍፁም ተማምነን ሳልከዳሽ ሳትከጂኝ
-- ሳልጎዳሽ ሳትጎጂኝ
መራራቁን ትተሽ ስወድሽ ውደጂኝ

@Dakstar5🎭
@getem
@getem
ሀገሬ ነው

ሀገሬ ነው ይላል ሀገሩን ድሮ
አባቱ የሰጠውን ጥሎታል ዘንድሮ
ታድያ ለምንድነው ሀገሬ ነው የሚለው
ሀገር ሳይኖረው ሀገሬ ነው ያለው
እቴም ስልጣኔ ወጉ ያላማረ
የራሱን ሳያቅ የሰው እየተማረ
እቴም እድገት አምጪ
ለራሷ ሳትሆን ለሰው ተንጫጪ
ሀገሬ ነው ይላል የሰው አድማቂ
የራሱን ክዶ የሰው ናፋቂ


DaDa Coffee


@getem
@getem
//ቶሎ አትምጣ//
በማሪያማዊት

የትኛው ፅድቄ ነው የቱ መልካም ስራ
እባክ ቶሎ ና ብሎ የሚያስጠራ
ግብሬ ካላማረ ስራዬ ከከፋ
የስም አመኔታ በውስጤ ቢሰፋ
ትዛስህን ከጣስኩ በአደባባይ ቆሜ
ውስጥህን ከሰበርኩ ክፋትን ሰንቄ
ልቦና እንድትሰጠኝ ጥፋቴን አውቄ
ልፀልይ ወዳንተ ተፀጽቼ በእንባ
እባክህ አትምጣ ንሰሀ እስክገባ

ማርያማዊት
(እዬብ ዘ ማርያምን ደግፌ ነው)

@getem
@getem
@lula_al_greeko
---እንቆቅልሽ ---


አንድ ሰው ተራበ
እጆቹን ታጠበ
መዓድ አቀረበ
የገበታው ዓይነት መዓዛው ቢያውድም
ለተራበ ስጋው ያቀረበው ሁሉ ምን በቂ ቢሆንም
ዕትኡ በሰላም እስኪባል አልበላም

እንቆቅልሽ
ሌላውም ተርቦ
እጆቹን ተጣጥቦ
ማዕዱን አቅርቦ
ካማረ ገበታው ካረደው ፍሪዳ ከጠላ ከጠጁ
ሊጠጣ ሊበላ ቢዘረጋም እጁ
ፍላጎት ግን ከዳው
በድኑን አስቀምጦ መንፈሱ ግዜ አጣ ሐሳብ
አነጎድው

እንቆቅልሽ
አንድም ከዚ አለ
ተርቦ የዋለ
ምን ርሃብ ቢሰማው ቢጨማደድ ፊቱ
ምን  ቢጮህም ወስፋቱ
እጁን አይታጠብ
ማዕዱን አያቀርብ
ጥግ ይዞ ተቀምጧል
በደከሙ  ዓይኖቹ ህዝቡን ያማትራል

እንቆቅልሽ
አማኝ ነብሱን ብሎ
ሐብታሙ ሲጨነቅ
ድሃው ግን በማጣት
ሶስት ሰወች ተራቡ  ዓለም እንደዚ ናት
እንቆቅልሽ ህይወት እንቆቅልሽ ዓለም
ከጥያቄ በቀር ምን ጊዜም መልስ የለም!!!!!!!

(((ሳሚ ዘ-ሖኅተ)))

@getem
@getem
(((በላይ በቀለ ወያ )))
በአዲስ የ ግጥም መድብል


"እልፍ " ላሉት እልፍ
እልል ላሉት ክንፍ
በምታድል ሀገር
ከባሻገር ወዲያ ፣ አለና ባሻገር
ድልድይ ሆኖ ያልፋል
ሌሎችን አሻግሮ ፣ ራሱ 'ማይሻገር ።

እነሆ በቅርቡ መጣሁ ብሎ ልኮብናል ገጣሚው
@getem
@getem
ብርድ የሰራው ወበቅ

ያው እንደምታውቂው
ዝናቡን ጠብቆ ጠፋብን መብራቱ
ነይ እስቲ እቀፊኝ
ብርድና ጨለማ እኔ አልወድም እቱ።

ብሎ አቀፋትና
ግላዊ እሳቱን ከጭኗ ለኮሰ
ደረቱ ላይ ቀልጣ
ከደረቷ በታች ፀሐይ ተፀነሰ።

የለኮሰው እሳት
በብርድ አመካኝቶ በፀሐይ ቀጠለ
ነደዱ እንደ እቶን ፍቅር ተቃጠለ።

በአንድ ፀሐይ ቀን
ሆዷን አሳየችው ታዘበ እንደገፋ
በቅፅበት በረደው
እሳታዊ አቅሙ ተሰለበ ጠፋ።
ቀስስ እያለ ራቃት
ብዙ ተከትላው ተጋባባት ብርዱ
ሁለት በረዶዎች
ጨለማ ላይ ጭረው ፀሐይ ልጅ ወለዱ።

ጨቅላ ሙቀት አዝሎ ጡቷ ስር ይስቃል
ማን ያውቃል
ለፍቅር ወግ ሳይደርስ
አባቴን ያለቀን በታሪክ ይጠልቃል
ካባቱ አስተያይቶ
ያፍላነቱን ሙቀት በለጋው ይንቃል
አሁን ግን ለጊዜው
በረዶ ታቅፎት በምቾት ይስቃል።
ፈገገገገግ
ወገገገገግ
ቦገገገገግ
ጨለማ የወለደው የብርሐን ሐረግ።

(ታምራት ሚሊዎን)

@getem
@getem
@lula_al_greeko
1👍1
#ቡና_አማረኝ_ብትይ ...

ደክሞኝ ቢሆን እንኳን
መች እኔ ሰንፋለሁ
ብቻ አንቺ ከቆላሽ
ለመውቀጡ አለሁ

ኢዛና
@getem
@getem
@lula_al_greeko
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
ግንቦት ፲፭ በብሄራዊ ቲያትር የተሳካ ምሽት አሳለፍን "ንባብ ለሂወት" በሚል መሪ ቃል ፕሮግራሙን በነፃ ላዘጋቹልን ለብሄራዊ ቤተመፅሃፍትና ቤተመዛግብት ኤጀንሲ ምስጋናችን የላቀ ነው። 🙏🙏🙏
Tsegaye Gebre-Medhin - "Abren Zim Inebel/አብረን ዝም እንበል"
~ አብረን ዝምም እንበለ ~

ጸጋዬ ገ/መድህን

@getem
@getem
~~~ ጠላቴን ስመርቅ  ~~~~

በስልጣን ከፍ ከፍ
በዝና ከፍ ከፍ
በሀብትም ከፍ ከፍ
ወደላይ ከፍ ከፍ
ከፍ ከፍ.... ከፍ ከፍ
ከዛ የወደቅህ ዕለት አጥንትህ እንዳይተርፍ::

ገጣሚ ታገል ሰይፉ

@getem
@getem