የናፍቆት አለንጋ ሲያናውጣት ነብሱ
ለአይኑ ቦታ ለቆ ሳይከፈት ጥርሱ
በገፋሽው ፍቅር ቂም እንደነከሰ
ሰብአዊ አካሉ ዘውትር እያነሰ
እጅና እግሩ ደረትና አንገቱ
ምላሥ ጆሮ አፍንጫ የላይ ሰውነቱ
መቃብር ያልገቡ በድን አካላቱ
ከቁም ሞት ለመዳን ለነፍስ ሲዋትቱ
ግና
ዘለላ ውሀውን
መሬት እየረጨ
ከእንባ እጢዎቹ ውስጥ
ፍቅር እያመነጨ
የማይታይ ቀለም እያርከፈከፈ
በሽፋሽፍቱ ጫፍ ስምሽን እየፃፈ
ሞቶም ሳይለይለት
ወድቆም ሳይነሳ
ጊዜ ይቅበረው ተብሎ
በሰው እንደተረሳ
ጥላቻ እና ሀዘን
ፍቅር እና ደስታን እንደተንተራሰ
አይኑ
አይኑ ብቻ ቀረ እንባ እየፈሰሰ
ምንያህል ጥላሁን
12/08/2010
@getem
@getem
ለአይኑ ቦታ ለቆ ሳይከፈት ጥርሱ
በገፋሽው ፍቅር ቂም እንደነከሰ
ሰብአዊ አካሉ ዘውትር እያነሰ
እጅና እግሩ ደረትና አንገቱ
ምላሥ ጆሮ አፍንጫ የላይ ሰውነቱ
መቃብር ያልገቡ በድን አካላቱ
ከቁም ሞት ለመዳን ለነፍስ ሲዋትቱ
ግና
ዘለላ ውሀውን
መሬት እየረጨ
ከእንባ እጢዎቹ ውስጥ
ፍቅር እያመነጨ
የማይታይ ቀለም እያርከፈከፈ
በሽፋሽፍቱ ጫፍ ስምሽን እየፃፈ
ሞቶም ሳይለይለት
ወድቆም ሳይነሳ
ጊዜ ይቅበረው ተብሎ
በሰው እንደተረሳ
ጥላቻ እና ሀዘን
ፍቅር እና ደስታን እንደተንተራሰ
አይኑ
አይኑ ብቻ ቀረ እንባ እየፈሰሰ
ምንያህል ጥላሁን
12/08/2010
@getem
@getem
◉ ኢዲሞክራት ስሞች
ግዛቸው ሸንቁጤ
በለው ድፋባቸው
ቅጣው ግፋወሰን
ደባልቄ ያዛቸው
ዳምጠው አስጨናቂ
አሸብር በላቸው
ግጨው አያርገጤ
አሰግድ ጌታቸው
እኔ እንዳስተዋለ
ሆኜ እንደተመልካች
ብዬ መደብኩዋቸው
የሰው መብት ተጋፊ ወይም ገፋፊዎች
ጭራሽ አምባገነን
ኢዲሞክራት ስሞች !!!
😊ከቶአታው
@Lula_al_greeko
@getem
@getem
ግዛቸው ሸንቁጤ
በለው ድፋባቸው
ቅጣው ግፋወሰን
ደባልቄ ያዛቸው
ዳምጠው አስጨናቂ
አሸብር በላቸው
ግጨው አያርገጤ
አሰግድ ጌታቸው
እኔ እንዳስተዋለ
ሆኜ እንደተመልካች
ብዬ መደብኩዋቸው
የሰው መብት ተጋፊ ወይም ገፋፊዎች
ጭራሽ አምባገነን
ኢዲሞክራት ስሞች !!!
😊ከቶአታው
@Lula_al_greeko
@getem
@getem
👍1
ግጥም ብቻ 📘
◉ ኢዲሞክራት ስሞች ግዛቸው ሸንቁጤ በለው ድፋባቸው ቅጣው ግፋወሰን ደባልቄ ያዛቸው ዳምጠው አስጨናቂ አሸብር በላቸው ግጨው አያርገጤ አሰግድ ጌታቸው እኔ እንዳስተዋለ ሆኜ እንደተመልካች ብዬ መደብኩዋቸው የሰው መብት ተጋፊ ወይም ገፋፊዎች ጭራሽ አምባገነን ኢዲሞክራት ስሞች !!! 😊ከቶአታው @Lula_al_greeko…
ግጥም ብቻ 📘
፪ በጎጠኘነት አይን ያየው ተመልካች 😒ዋኖሴ የሥም ዝርዝሮቹን ከዓስተዉሎትሕ ሳይ ዕኔም አንድ ኃሳብ ብልጪ አለብኝ ቆይ:: እኒሕ ከዚሕ በላይ የደረደርካቸዉ ሥሞቹ በሙሉ አንድ ዘር ጠቋሚ በእዉነት ይመሥላሉ:: እናም አካሄዴ! ከርዕሥሕ ሳየው ኃሳብሕን በሾዴ የዚሕ ስም ባለቤት ኢ-ዲሞክራት ነው ለማለት ነዉ እንዴ? @getem @getem
የቶታአው ምልስ ለ ዋኖሴ 😊
እኔ አላልኩኝም አልወጣኝ እንደሱ
ምናለ ደርሳችሁ እሳት ባትለኩሱ
እኔ ያልኩት ስሙን
የግል መጠሪያዉን
ደሞ እኒህን ስሞች ማን ላንዱ አረጋቸው
አበሻ ጫፍ ከጫፍ ነው ሚጠራባቸው
ፈልግ ብታደርግ ከሱማሌ አታጣም አንድ አሪፍ ጌታቸው
እናም ብዙ አታዉኩዋት አትጥላችሁ ነፍሴ
በተለይ ደሞ አንተን ወንድሜ ዋኖሴ
የዋርካ ዉስጥ አምዴ ተጠሪና ዋሴ
አንተም ዘር ቆጠራ ቁልቁል ልትወርድ
እንዳትቀልብኝ በልኮ አትዋረድ
እልቅ ዝም ብለህ ያዘው ገብስ ገብሱን
ይቅርብህ በል ጣለው ተወው መተርጎሙን
ቶታአውኮትኳች
@getem
@getem
እኔ አላልኩኝም አልወጣኝ እንደሱ
ምናለ ደርሳችሁ እሳት ባትለኩሱ
እኔ ያልኩት ስሙን
የግል መጠሪያዉን
ደሞ እኒህን ስሞች ማን ላንዱ አረጋቸው
አበሻ ጫፍ ከጫፍ ነው ሚጠራባቸው
ፈልግ ብታደርግ ከሱማሌ አታጣም አንድ አሪፍ ጌታቸው
እናም ብዙ አታዉኩዋት አትጥላችሁ ነፍሴ
በተለይ ደሞ አንተን ወንድሜ ዋኖሴ
የዋርካ ዉስጥ አምዴ ተጠሪና ዋሴ
አንተም ዘር ቆጠራ ቁልቁል ልትወርድ
እንዳትቀልብኝ በልኮ አትዋረድ
እልቅ ዝም ብለህ ያዘው ገብስ ገብሱን
ይቅርብህ በል ጣለው ተወው መተርጎሙን
ቶታአውኮትኳች
@getem
@getem
("ከዛፍ የተቀመረ ዜማ")
ካ'ለም እቅፍ ወጥቶ
ካ'ለም እቅፍ ሸሽቶ
ወደ ገዳም ሲሄድ
ደክሞት ተዝለፍልፎ
ብላቴናዉ ያሬድ ካ'ንድ ዛፍ ስር አርፎ
ከዛፉ ግንድ ሥር ትል ሲሸልል ሰማ
እንዲህ በሚል ዜማ
"ዛፍ ነዉ ህይወቴ
ቅጠልዋ እራቴ
ሰባት ጊዜ ልውደቅ
ሰባቴ እንድወጣ
የኀላ ኀላ 'ራቴን አላጣ"
ይህን ስትሰማ ቅጠሊቱ ራደች
መሸሽ ባይሆንላት ሙሾን አወረደች
"ዛፉ ህይወቴ ነው
ግን ኀያል ቢመስልም
ተራራ ቢመስልም
ተራራ ቢያክልም
የማታ የማታ
ከትል አያስጥልም"
ያሬድ ይሄን ሰምቶ
ትሉ በጥረቱ ራት ሲበላ አይቶ
ተስፋውን አጸናዉ
በቅጠሏ ዕጣ ግን ተነካ ልቡናው
ከዚያም ተመልሶ
የትሉን ፉከራ
የቅጠሏን ለቅሶ
ባ'ንድ ላይ ለውሶ
ዜማውን ቀመረ
ዜማው ተዘመረ
ከሰው ነፍስ ተስማማ
በሰው ድምፅ አማረ ።
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ካ'ለም እቅፍ ወጥቶ
ካ'ለም እቅፍ ሸሽቶ
ወደ ገዳም ሲሄድ
ደክሞት ተዝለፍልፎ
ብላቴናዉ ያሬድ ካ'ንድ ዛፍ ስር አርፎ
ከዛፉ ግንድ ሥር ትል ሲሸልል ሰማ
እንዲህ በሚል ዜማ
"ዛፍ ነዉ ህይወቴ
ቅጠልዋ እራቴ
ሰባት ጊዜ ልውደቅ
ሰባቴ እንድወጣ
የኀላ ኀላ 'ራቴን አላጣ"
ይህን ስትሰማ ቅጠሊቱ ራደች
መሸሽ ባይሆንላት ሙሾን አወረደች
"ዛፉ ህይወቴ ነው
ግን ኀያል ቢመስልም
ተራራ ቢመስልም
ተራራ ቢያክልም
የማታ የማታ
ከትል አያስጥልም"
ያሬድ ይሄን ሰምቶ
ትሉ በጥረቱ ራት ሲበላ አይቶ
ተስፋውን አጸናዉ
በቅጠሏ ዕጣ ግን ተነካ ልቡናው
ከዚያም ተመልሶ
የትሉን ፉከራ
የቅጠሏን ለቅሶ
ባ'ንድ ላይ ለውሶ
ዜማውን ቀመረ
ዜማው ተዘመረ
ከሰው ነፍስ ተስማማ
በሰው ድምፅ አማረ ።
@getem
@getem
@lula_al_greeko
።።።።እኔ አደለሁማ።።።።።
ባንቺስ ምን ሊፈረድ ነው እንጂ በነሱ
የወንድነት ክብሩን ረግጠው በረሱ
የተቆለፈን በር እያዩ 'ሚያንኳኩ
ሰሚ በሌለበት የሚለፈልፉ
ተራራን እንደ ኳስ ሊገፉ 'ሚለፉ
ፍቅር በልመና በገንዘብ የሚሉ
ምኑንም ሳዪዙት ልሞት ነው በሚሉ
ነው እንጂ በነሱ ባንቺስ ምን ሊፈረድ
እያሸረጋገዱ ለሆኑልሽ ገረድ
።
።
እኔ አደለውማ እንግዲ 'ደነሱ
እሺ ስትይ እሺ
እምቢ ስትይ እምቢ
ነው የልቤ መልሱ
መቻል ያውቅበታል ሁሉንም በሆዱ
ለፍልፎ እንደነሱ አይወጣም በጉዱ
በቃ እንዳጠብቂ ለቅሶ ና ልመና
ሁሌ የለም ፋሲካ አንዳዴም ነው ገና
።
።
✍ነባ
@getem
@getem
ባንቺስ ምን ሊፈረድ ነው እንጂ በነሱ
የወንድነት ክብሩን ረግጠው በረሱ
የተቆለፈን በር እያዩ 'ሚያንኳኩ
ሰሚ በሌለበት የሚለፈልፉ
ተራራን እንደ ኳስ ሊገፉ 'ሚለፉ
ፍቅር በልመና በገንዘብ የሚሉ
ምኑንም ሳዪዙት ልሞት ነው በሚሉ
ነው እንጂ በነሱ ባንቺስ ምን ሊፈረድ
እያሸረጋገዱ ለሆኑልሽ ገረድ
።
።
እኔ አደለውማ እንግዲ 'ደነሱ
እሺ ስትይ እሺ
እምቢ ስትይ እምቢ
ነው የልቤ መልሱ
መቻል ያውቅበታል ሁሉንም በሆዱ
ለፍልፎ እንደነሱ አይወጣም በጉዱ
በቃ እንዳጠብቂ ለቅሶ ና ልመና
ሁሌ የለም ፋሲካ አንዳዴም ነው ገና
።
።
✍ነባ
@getem
@getem
👍1
*ሄደች ያሉኝ ዕለት*
እግሬ እንደለመደው አይኗን ልየው ብሎ
ከሰፈርሽ ውሎ
ድንገት ብትቀሪበት ልቤ ሲጨናነቅ
የጎረቤት ጨቅላ ጠርቶ አንቺን ቢያስጠይቅ
ከሀገር ወታለች መባልሽን ሰማና
ምስልሽን አትሞ ትካዜን ተላብሶ ቀረ ከጎዳና።
አንቺ በሄድሽበት ጥላሽ ባረፈበት
አንችን ብቻ ስሎ
በድን ሰውነቱን ከኋላ አስከትሎ
ወድቋል ራሱን ጥሎ።
ኢማ...
ሄደች ያሉኝ እለት
እንደዚህ ሆኛለው
እንዳልሞት እንዳልድን
ባንቺ ቆስያለው ባንቺው ነፍሪያለው
መሬትን ሰማይ ነው ሰማይን ምድር ነው
ብዬ ተሟግቼ እብድ ተብያለው
የቀኙን ለግራ የግራውን ለቀኝ
ጫማየን አዙሬ ተጫምቼዋለው
ሱሪየን ገልብጬ አጥልቄልሻለው...
ሀ ወደላይ አይደል..በ መስሎ ታይቶኛል
እንኳንስ ትተሺኝ..
ስትርቂ ከጎኔ ነገር ይጠመኛል
ምድር ሰማይ መስሎ እንዳልቆም አርጎኛል
እውነት ለመናገር
ካገር ወጣች ሲሉኝ እንዲህ ተሰምቶኛል።
እባክሽ ቶሎ ነይ... ጓዴ ነይ...
ኢማ ነይ።
(ስምኦን)
ለማታውቀኝ ለማውቃት ኢማንዳ።
@getem
@getem
@lula_al_greeko
እግሬ እንደለመደው አይኗን ልየው ብሎ
ከሰፈርሽ ውሎ
ድንገት ብትቀሪበት ልቤ ሲጨናነቅ
የጎረቤት ጨቅላ ጠርቶ አንቺን ቢያስጠይቅ
ከሀገር ወታለች መባልሽን ሰማና
ምስልሽን አትሞ ትካዜን ተላብሶ ቀረ ከጎዳና።
አንቺ በሄድሽበት ጥላሽ ባረፈበት
አንችን ብቻ ስሎ
በድን ሰውነቱን ከኋላ አስከትሎ
ወድቋል ራሱን ጥሎ።
ኢማ...
ሄደች ያሉኝ እለት
እንደዚህ ሆኛለው
እንዳልሞት እንዳልድን
ባንቺ ቆስያለው ባንቺው ነፍሪያለው
መሬትን ሰማይ ነው ሰማይን ምድር ነው
ብዬ ተሟግቼ እብድ ተብያለው
የቀኙን ለግራ የግራውን ለቀኝ
ጫማየን አዙሬ ተጫምቼዋለው
ሱሪየን ገልብጬ አጥልቄልሻለው...
ሀ ወደላይ አይደል..በ መስሎ ታይቶኛል
እንኳንስ ትተሺኝ..
ስትርቂ ከጎኔ ነገር ይጠመኛል
ምድር ሰማይ መስሎ እንዳልቆም አርጎኛል
እውነት ለመናገር
ካገር ወጣች ሲሉኝ እንዲህ ተሰምቶኛል።
እባክሽ ቶሎ ነይ... ጓዴ ነይ...
ኢማ ነይ።
(ስምኦን)
ለማታውቀኝ ለማውቃት ኢማንዳ።
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ናፍቆት መሞቴ ነው
ጠፋሽብኝ ብዬ
የኢንተርኔት ፍቅሬ
እንዴት ነሽ ፋፊዬ
እዚህ ዋርካ ቻት ላይ
ያኔ እንዳነበብኩሽ
ወዲያዉ ነው የያዘኝ
አደገኛው ፍቅርሽ
ያ መስተፋቅርሽ
የላክሽዉ በጽሁፍ
በፍቅር የሚያስር
ደርሶ ሚያንከረፍፍ
ልቤን ድንገት ወግቶ
ቢይዘው ቀስፎ
አደባባይ ጣለኝ
ምንይሉኝን ገፎ
መቼም ይህንን ስል
ተቃዋሚ አላጣም
የዋርካ ወንድ ሁሉ
ይወድሻል በጣም
ግና የሁሎቹም
አንድነት ቢደመር
የኔ ለብቻው ነው
አይቀርብም ዉድድር
እናም አንቺ ፋፊ
እኔ ወድሽ አይደል
በናትሽ አትጥፊ
✍ የግጥም ሳይበር ኔት
@getem
@getem
ጠፋሽብኝ ብዬ
የኢንተርኔት ፍቅሬ
እንዴት ነሽ ፋፊዬ
እዚህ ዋርካ ቻት ላይ
ያኔ እንዳነበብኩሽ
ወዲያዉ ነው የያዘኝ
አደገኛው ፍቅርሽ
ያ መስተፋቅርሽ
የላክሽዉ በጽሁፍ
በፍቅር የሚያስር
ደርሶ ሚያንከረፍፍ
ልቤን ድንገት ወግቶ
ቢይዘው ቀስፎ
አደባባይ ጣለኝ
ምንይሉኝን ገፎ
መቼም ይህንን ስል
ተቃዋሚ አላጣም
የዋርካ ወንድ ሁሉ
ይወድሻል በጣም
ግና የሁሎቹም
አንድነት ቢደመር
የኔ ለብቻው ነው
አይቀርብም ዉድድር
እናም አንቺ ፋፊ
እኔ ወድሽ አይደል
በናትሽ አትጥፊ
✍ የግጥም ሳይበር ኔት
@getem
@getem
✧✧✧ ብዙ ተባዙ ☺
የእናትነት እጣ፣ ያባትነት ውርሱን
የፍጥረትን ምስጢር፣ የቤተሰብ ቅርሱን
የትውልድ አደራ፣ የብዙ ተባዙን፤
ለአእምሮህ ሳይሆን ባሻው ለሚከንፈው
ለልቦናሽ ሳይሆን ስርአት ለሚገድፈው
ለፈቃድህ ሳይሆን እብደት ለሚለክፈው
ለህሊናሽ ሳይሆን ዓለም ለሚያጎድፈው፤
ሰጠው ለሽፍደትህ ጦር ለማይመልሰው
ለመግነጢስ ገላሽ ጾም ለሚያስፈርሰው
ጻፈው በገበናሽ በጉያሽ ትኩሳት
በማትሟገተው የጭንህ ዲን እሳት፤
በሰጣችሁ ርስት በወጉ አንድትረቡ
በሴስ አቆራኝቶ በወሲብ ቀለቡ
ምድርን በሰው ሞላት በኪነጥበቡ።
✍ ፋሲል ይትባረክ ✍
@getem
@getem
የእናትነት እጣ፣ ያባትነት ውርሱን
የፍጥረትን ምስጢር፣ የቤተሰብ ቅርሱን
የትውልድ አደራ፣ የብዙ ተባዙን፤
ለአእምሮህ ሳይሆን ባሻው ለሚከንፈው
ለልቦናሽ ሳይሆን ስርአት ለሚገድፈው
ለፈቃድህ ሳይሆን እብደት ለሚለክፈው
ለህሊናሽ ሳይሆን ዓለም ለሚያጎድፈው፤
ሰጠው ለሽፍደትህ ጦር ለማይመልሰው
ለመግነጢስ ገላሽ ጾም ለሚያስፈርሰው
ጻፈው በገበናሽ በጉያሽ ትኩሳት
በማትሟገተው የጭንህ ዲን እሳት፤
በሰጣችሁ ርስት በወጉ አንድትረቡ
በሴስ አቆራኝቶ በወሲብ ቀለቡ
ምድርን በሰው ሞላት በኪነጥበቡ።
✍ ፋሲል ይትባረክ ✍
@getem
@getem
🖼📸📷🖼📸📷🖼📷📷
የፎቶግራፍ አድናቂ ከሆኑ በተለያየ መልኩ ሃገርኛ ምስሎችን በየቀኑ ለእናንተ እናደርሳለን ሊንኩን ተጭነው ይቀላቀሉ
እናመሰግናለን ።
📸📷📸📷📸📷📸📷📸📷📸
@Mykeypictures
የፎቶግራፍ አድናቂ ከሆኑ በተለያየ መልኩ ሃገርኛ ምስሎችን በየቀኑ ለእናንተ እናደርሳለን ሊንኩን ተጭነው ይቀላቀሉ
እናመሰግናለን ።
📸📷📸📷📸📷📸📷📸📷📸
@Mykeypictures
~~~ ወቸው ጉድ! ~~
ኣምሳለች
እሺ እያለች
ኣታለለች
እምቢ ብትል
ምን ታስከትል?
ልጅ ቅጣው
ለሽምጠጣው
ዘልሎ ወጣው
ኣለሁ ብሎ
ሄደ ጥሎ
ጋሽ ገመዳ
ዶፍ ኣራዳ
ያ ወራዳ
ተሽቀርቃሪ
ኣጭበርባሪ!
’ትየ ሙና
ከጋሸ ጦና
በጥሞና
ደጅ ካስጠኑ
ይኮነኑ
ኣባ ተክሌ
ኣልባሌ
ጨው ኣሞሌ
ጥምጥማቸው
ከበዳቸው
እሱን ጥሩት
ኣትቅጠሩት
ምን ትፈሩት
ባባ ዘውዱ
መጣ ጉዱ
በገመቹ
ላዩ ታቹ
ተሰላቹ
መሃል ሆዳቸው
ቡጢ በሏቸው!
ለልመና
’ትየ ሃና
የሉምና
ዘመድኩን
ያ ብኩን
ዘልዓለም
ሲፋለም
ያየ የለም
ና ኣሉት
ሊበሉት
ኣቶ ካሰው
ልጅ ጣሰው
በጣጠሰው
ኣስናቀ
ቦጨቀ
ዘበርጋ
ሳይረጋ
ተዘረጋ
ሲነጋ
ተዋጋ
ዳምጠው
ኣዳለጠው
ኣመለጠው
ኣሓዱ
ምጣዱ
ሓመልማል
ከጀማል
ስትማማል
ሙስጣፋ
ተንከራፋ
ኣቶ ያለው
ሞት ዘለለው
ምን ይሻለው
ልጅ ገለታ
እንጃለታ
ሳቢሳ
ከግሪሳ
ለቶሎሳ
ኣቶ ገቢሳ ያ ደሳሳ
ወልደሩፋኤል ያ ሳጥናኤል
በሚካኤል
ዓርፎ ይሥራ
ሰው ኣይጥራ
ጥላሁን እስኪ ኣሁን
ምን ይሁን
ባላባት
በቀረባት
እንደፎከረው
ኣከራክረው
ኣይምረው
ያጠረው
ኣበጠረው
ኣቶ ፈረደ
ተወራረደ
ተንገዳገደ
ኣቶ ረታ
መላ መታ
ኣቶ ፈለቀ
የልጅ ዘለቀ
ጥርስ ኣወለቀ
ዓለሙ
ድዳሙ
ለዓብደላ
ኣስኪጠላ
ስጡት ጠላ
ሲጠጣ
ይንጣጣ
ለቢራራ
ሳይጣራ
ስጡት ቢራ
እስኪነቃ
ይንቃቃ
ልጅ መርሻ
ከጥሻ
ምን ትሻና ውጣ
ዓይንህ ይውጣ
ኣድማሱ
ከትራሱ
መለስለሱ
ተቃቀፉ
ተናቀፉ
ይላላ
ፊት ኋላ
ሞላላ
ኋላ -ሸት
ጥላ -ሸት
’ትየ ምርጡ
ሲጠጡ
ምኑ ቅጡ
ለጠላቸው
ኣልከፍላቸው!
ዓለሚቱ
ከማሚቱ
ሲጓተቱ
ምሕረቱ
መሞቱ
ተማሪ
መሰሪ
ሰርሳሪ
ሲሰረስር
ይከስር
ሊበሉት
ሰለሉት
ደለሉት
ያ ነጋሽ
ተናካሽ
ከወርቁ
መዳረቁ
ይታረቁ
ለፀሎት
ማ’ ብሎት ብሎት
ፀሓዬ
ከታዬ
ተያዬ
ብድር
በምድር
ኣማረ
ዘመረ
ከበረ
ሲዘምር
ይደምር
ወንዳፍራሽ
ካምባፍራሽ
በኣዳራሽ
ተጣሉ
ሊባሉ
ለኣመሉ
ኣስካሉ
እያሉ
ምን መጣ
ገበጣ
ስብሓቱ
ከጫልቱ
ማንጋቱ
’ንጃለቱ
ያ ገልቱ
ልጅ ሃይሉ
ሳይከፍሉ
ሊበሉ
ብድራቸው
ስጧቸው
ልጅ መራራ
ሲንጠራራ
ተሰበራ
ወደቀ
ደቀቀ
ሰመረ
መከረ
ሰከረ
ሲሰክር
ይፎክር
✍ ገ/ኢ. ጐርፉ። ✍
@getem
@getem
ኣምሳለች
እሺ እያለች
ኣታለለች
እምቢ ብትል
ምን ታስከትል?
ልጅ ቅጣው
ለሽምጠጣው
ዘልሎ ወጣው
ኣለሁ ብሎ
ሄደ ጥሎ
ጋሽ ገመዳ
ዶፍ ኣራዳ
ያ ወራዳ
ተሽቀርቃሪ
ኣጭበርባሪ!
’ትየ ሙና
ከጋሸ ጦና
በጥሞና
ደጅ ካስጠኑ
ይኮነኑ
ኣባ ተክሌ
ኣልባሌ
ጨው ኣሞሌ
ጥምጥማቸው
ከበዳቸው
እሱን ጥሩት
ኣትቅጠሩት
ምን ትፈሩት
ባባ ዘውዱ
መጣ ጉዱ
በገመቹ
ላዩ ታቹ
ተሰላቹ
መሃል ሆዳቸው
ቡጢ በሏቸው!
ለልመና
’ትየ ሃና
የሉምና
ዘመድኩን
ያ ብኩን
ዘልዓለም
ሲፋለም
ያየ የለም
ና ኣሉት
ሊበሉት
ኣቶ ካሰው
ልጅ ጣሰው
በጣጠሰው
ኣስናቀ
ቦጨቀ
ዘበርጋ
ሳይረጋ
ተዘረጋ
ሲነጋ
ተዋጋ
ዳምጠው
ኣዳለጠው
ኣመለጠው
ኣሓዱ
ምጣዱ
ሓመልማል
ከጀማል
ስትማማል
ሙስጣፋ
ተንከራፋ
ኣቶ ያለው
ሞት ዘለለው
ምን ይሻለው
ልጅ ገለታ
እንጃለታ
ሳቢሳ
ከግሪሳ
ለቶሎሳ
ኣቶ ገቢሳ ያ ደሳሳ
ወልደሩፋኤል ያ ሳጥናኤል
በሚካኤል
ዓርፎ ይሥራ
ሰው ኣይጥራ
ጥላሁን እስኪ ኣሁን
ምን ይሁን
ባላባት
በቀረባት
እንደፎከረው
ኣከራክረው
ኣይምረው
ያጠረው
ኣበጠረው
ኣቶ ፈረደ
ተወራረደ
ተንገዳገደ
ኣቶ ረታ
መላ መታ
ኣቶ ፈለቀ
የልጅ ዘለቀ
ጥርስ ኣወለቀ
ዓለሙ
ድዳሙ
ለዓብደላ
ኣስኪጠላ
ስጡት ጠላ
ሲጠጣ
ይንጣጣ
ለቢራራ
ሳይጣራ
ስጡት ቢራ
እስኪነቃ
ይንቃቃ
ልጅ መርሻ
ከጥሻ
ምን ትሻና ውጣ
ዓይንህ ይውጣ
ኣድማሱ
ከትራሱ
መለስለሱ
ተቃቀፉ
ተናቀፉ
ይላላ
ፊት ኋላ
ሞላላ
ኋላ -ሸት
ጥላ -ሸት
’ትየ ምርጡ
ሲጠጡ
ምኑ ቅጡ
ለጠላቸው
ኣልከፍላቸው!
ዓለሚቱ
ከማሚቱ
ሲጓተቱ
ምሕረቱ
መሞቱ
ተማሪ
መሰሪ
ሰርሳሪ
ሲሰረስር
ይከስር
ሊበሉት
ሰለሉት
ደለሉት
ያ ነጋሽ
ተናካሽ
ከወርቁ
መዳረቁ
ይታረቁ
ለፀሎት
ማ’ ብሎት ብሎት
ፀሓዬ
ከታዬ
ተያዬ
ብድር
በምድር
ኣማረ
ዘመረ
ከበረ
ሲዘምር
ይደምር
ወንዳፍራሽ
ካምባፍራሽ
በኣዳራሽ
ተጣሉ
ሊባሉ
ለኣመሉ
ኣስካሉ
እያሉ
ምን መጣ
ገበጣ
ስብሓቱ
ከጫልቱ
ማንጋቱ
’ንጃለቱ
ያ ገልቱ
ልጅ ሃይሉ
ሳይከፍሉ
ሊበሉ
ብድራቸው
ስጧቸው
ልጅ መራራ
ሲንጠራራ
ተሰበራ
ወደቀ
ደቀቀ
ሰመረ
መከረ
ሰከረ
ሲሰክር
ይፎክር
✍ ገ/ኢ. ጐርፉ። ✍
@getem
@getem