ረሳኋት
(ሚካኤል አ)
ጤዛ እኮ ነው ገጽዋ
በማለዳ ረጥቦ ፣ ቀትር የሚሰዋ።
ጉም ነው የሷ መውደድ
ጋርዳዋለች ሲሉ ፣ እኔ አለው ስራመድ።
ጣሟን ዘነጋሁት ፣ እንደ በዓል ዶሮ
ዛሬ እንኳ ብቀምሳት ፣ እኩል ነች ከሽሮ።
ጠረኗ ጠፍቶኛል ፣
አዲስ ነኝ ለራሴ
እሰይ ከስማ ቀረች ፣
ያቺ የሰው ከሴ !
ጆሮዬን አልሰጥም
ስሟን እየጠሩ ፣ ተቀምጠው ጎኔ
እዛው ጨፈርኩበት ፣ በአምና ድንኳኔ።
፡
እያየኋት ከሳች
፡
እያየኋት ጠፋች
፡
እንደ አየር ጢያራ፣
ደመናማው ሰማይ
ይብላኝ ለሷ ፣ ጠራ።
:
እያልኩኝ ደንፍቼ
ላገኘሁት ሁሉ ፣ ጉራዬን ስነፋ
“ረሳኋት “ በሚል
አንድ ከንቱ ግጥም ፣ ብቅ አለች ተጽፋ።
ኡፋ 🥹
@getem
@getem
@paappii
(ሚካኤል አ)
ጤዛ እኮ ነው ገጽዋ
በማለዳ ረጥቦ ፣ ቀትር የሚሰዋ።
ጉም ነው የሷ መውደድ
ጋርዳዋለች ሲሉ ፣ እኔ አለው ስራመድ።
ጣሟን ዘነጋሁት ፣ እንደ በዓል ዶሮ
ዛሬ እንኳ ብቀምሳት ፣ እኩል ነች ከሽሮ።
ጠረኗ ጠፍቶኛል ፣
አዲስ ነኝ ለራሴ
እሰይ ከስማ ቀረች ፣
ያቺ የሰው ከሴ !
ጆሮዬን አልሰጥም
ስሟን እየጠሩ ፣ ተቀምጠው ጎኔ
እዛው ጨፈርኩበት ፣ በአምና ድንኳኔ።
፡
እያየኋት ከሳች
፡
እያየኋት ጠፋች
፡
እንደ አየር ጢያራ፣
ደመናማው ሰማይ
ይብላኝ ለሷ ፣ ጠራ።
:
እያልኩኝ ደንፍቼ
ላገኘሁት ሁሉ ፣ ጉራዬን ስነፋ
“ረሳኋት “ በሚል
አንድ ከንቱ ግጥም ፣ ብቅ አለች ተጽፋ።
ኡፋ 🥹
@getem
@getem
@paappii
❤50😁19🔥7😢6
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እኔ ያንቺን ውበት በቋሚነት ማደንቅ፣
ብዙ ሰው አየሁኝ እውነትን ሲደብቅ፡፡
እኔስ አያስችለኝ፧
መኳል ነው ማስሸብረቅ ባለቀው ማማርሽ፣
አይቶ ዝም ሲል ግን ስንቱን ታዘብኩልሽ?!
ይቺ ጠባብ ቤቱ ትዕቢቱ ከልክላው
እንጂ የማይስልሽ፧
ዝምታ ሲያበዛ መልስ ያጣ እንዳይመስልሽ፨
//ክብሬን ክሬን ሲል ነው የማያወድስሽ//
(ወትሮም በዚ አገር
አብሰልሳይ ይቀድማል፧
ከሚያቆላጵስሽ!)
@mypoems396
@getem
@getem
@getem
እኔ ያንቺን ውበት በቋሚነት ማደንቅ፣
ብዙ ሰው አየሁኝ እውነትን ሲደብቅ፡፡
እኔስ አያስችለኝ፧
መኳል ነው ማስሸብረቅ ባለቀው ማማርሽ፣
አይቶ ዝም ሲል ግን ስንቱን ታዘብኩልሽ?!
ይቺ ጠባብ ቤቱ ትዕቢቱ ከልክላው
እንጂ የማይስልሽ፧
ዝምታ ሲያበዛ መልስ ያጣ እንዳይመስልሽ፨
//ክብሬን ክሬን ሲል ነው የማያወድስሽ//
(ወትሮም በዚ አገር
አብሰልሳይ ይቀድማል፧
ከሚያቆላጵስሽ!)
@mypoems396
@getem
@getem
@getem
❤32🔥7🎉1
የመፅሐፉ ርዕስ :- የርሷ ስም
ገጣሚው / ፀሐፊው :- ዳዊት ጥዑማይ
በገበያ ላይ ውሏል
መፅሐፋን ማግኘት ለምትሹ
አዲስ አበባ ለምትገኙ
👉 + 2519 47 15 39 95
ወይንም
👉 +2519 45 52 52 49
ሐዋሳ ለምትገኙ
....... +251949002056
👉 +2519 47 15 39 95
ወይንም
👉 + 2519 49 00 20 56
@faberfortunae
በመደወል ማዘዝ ትችላላችሁ ።
( መልካም ንባብ )
ገጣሚው / ፀሐፊው :- ዳዊት ጥዑማይ
በገበያ ላይ ውሏል
መፅሐፋን ማግኘት ለምትሹ
አዲስ አበባ ለምትገኙ
👉 + 2519 47 15 39 95
ወይንም
👉 +2519 45 52 52 49
ሐዋሳ ለምትገኙ
....... +251949002056
👉 +2519 47 15 39 95
ወይንም
👉 + 2519 49 00 20 56
@faberfortunae
በመደወል ማዘዝ ትችላላችሁ ።
( መልካም ንባብ )
❤36👍5🔥1
#አምላኬ_ሆይ
.
.
.
ለጎረምሳ ገላ፣
ከቆንጆ ሴት ሌላ።
ላንበሳ ምንጋጋ ፣
የድኩላ ስጋ ።
ለልባም እመቤት፣
የጣልያን ድርብ ድስት።
ላራሽ ለገበሬ፣
ሁለት ጥንድ በሬ ።
የምትሰጥ ፈጣሪ፣
የህዝበ አዳም መሪ።
ለጠገበ ማጣት፣
ለሰነፍ ሰው ቅጣት።
ለተዋጊ ጦሩን፣
ለሚወጣ በሩን።
ለሂያጅ ሰፊ መንገድ፣
ለሚጠይቅ ዘመድ።
ላዘነ ሰው መርሻ፣
ለተራበው ጉርሻ፣
ለጠማው ማርከሻ፣
የምትሆን መጠጊያ፣
የምትችል ትከሻ።
ላም ለገዛ በረት፣
ለበደለ ምህረት፣
ላገባ በረከት።
ለእስራኤል መና፣
ለዝናብ ደመና።
ለጌቶ ብርንዶ፣
ለእንቦሳ ሰርዶ።
ለጴጥሮስ መረብ፣
ለላሜህ ልጅ መርከብ።
ለዳዊት መንግስቱን፣
ለእዮብ ትዕግስቱን።
የቸርካቸው አባት፣
የሌለህ ደም ግባት።
ጎዶሎን የምትሞላ፣
ጥብቁን የምታላላ።
እደጅህ ላይ ካረፈው፣
ሞልቶ ከተረፈው።
ለኔም ሰው አታጣም፣
ይልቅ ስጠኝና፤
ላመስግንህ በጣም !!🙏🙏🙏
✍️ ዓቢይ ( @abiye12 )
@getem
@getem
@getem
.
.
.
ለጎረምሳ ገላ፣
ከቆንጆ ሴት ሌላ።
ላንበሳ ምንጋጋ ፣
የድኩላ ስጋ ።
ለልባም እመቤት፣
የጣልያን ድርብ ድስት።
ላራሽ ለገበሬ፣
ሁለት ጥንድ በሬ ።
የምትሰጥ ፈጣሪ፣
የህዝበ አዳም መሪ።
ለጠገበ ማጣት፣
ለሰነፍ ሰው ቅጣት።
ለተዋጊ ጦሩን፣
ለሚወጣ በሩን።
ለሂያጅ ሰፊ መንገድ፣
ለሚጠይቅ ዘመድ።
ላዘነ ሰው መርሻ፣
ለተራበው ጉርሻ፣
ለጠማው ማርከሻ፣
የምትሆን መጠጊያ፣
የምትችል ትከሻ።
ላም ለገዛ በረት፣
ለበደለ ምህረት፣
ላገባ በረከት።
ለእስራኤል መና፣
ለዝናብ ደመና።
ለጌቶ ብርንዶ፣
ለእንቦሳ ሰርዶ።
ለጴጥሮስ መረብ፣
ለላሜህ ልጅ መርከብ።
ለዳዊት መንግስቱን፣
ለእዮብ ትዕግስቱን።
የቸርካቸው አባት፣
የሌለህ ደም ግባት።
ጎዶሎን የምትሞላ፣
ጥብቁን የምታላላ።
እደጅህ ላይ ካረፈው፣
ሞልቶ ከተረፈው።
ለኔም ሰው አታጣም፣
ይልቅ ስጠኝና፤
ላመስግንህ በጣም !!🙏🙏🙏
✍️ ዓቢይ ( @abiye12 )
@getem
@getem
@getem
❤63🔥34👍6😁1
የተፈጥሮ ልዕልት
ልብን ካስደሰተች ቆንጆ ሴት በሳቋ
ሀሴት ትርቃለች ቀጥ ሲል ማፍቀሯ
የጨከነች ለት መሸሽ ስታበዛ
ሀዘን ይመለሳል ስትቀር ቀዝቅዛ
ፀሃይቱም ብትሆን የጠዋቷ ብስራት
የንጋቷ ኮከብ የአስራ ሁለት ሰዓት
ዓለምን ብትከብ ፀዳሏን አርብባ
ከቀን መብራት ጋር እሷም ተደርባ
እንደለመደባት ባትወጣም ጨክና
ፅልመት አትፈጥርም አይደለችም ዋና
ፋኖስም ተተኪ አምፖል ተሰባሪ
አልቃሻውም ሻማ ሲለኩሱት ቀሪ
ያቺ ጨረቃ ግን ተስፋ ግራ ሲዘም
ሞት ጥላ ሲያጠላ ስትጠበብ ዓለም
ልቦና ሲሰለብ ሰዎች ሲያንቀላፉ
መናፍስተ እርኩሳን ሲያንሰፈስፉ
ምድር ስታረምም ሸፍኗት ጨለማ
ተፈጥሮ ሲነጥቃት የድምቀቷን ግርማ
የብርሃን ልዕልት አለቃ ምስለኔ
የእስትንፋስ ያህል ጨረቃ ናት ለኔ !
ዳዊት ጥዑማይ
17/11/18
ዳ ሰኒያ ዓዲ _አሕፈሮም
@getem
@getem
@getem
ልብን ካስደሰተች ቆንጆ ሴት በሳቋ
ሀሴት ትርቃለች ቀጥ ሲል ማፍቀሯ
የጨከነች ለት መሸሽ ስታበዛ
ሀዘን ይመለሳል ስትቀር ቀዝቅዛ
ፀሃይቱም ብትሆን የጠዋቷ ብስራት
የንጋቷ ኮከብ የአስራ ሁለት ሰዓት
ዓለምን ብትከብ ፀዳሏን አርብባ
ከቀን መብራት ጋር እሷም ተደርባ
እንደለመደባት ባትወጣም ጨክና
ፅልመት አትፈጥርም አይደለችም ዋና
ፋኖስም ተተኪ አምፖል ተሰባሪ
አልቃሻውም ሻማ ሲለኩሱት ቀሪ
ያቺ ጨረቃ ግን ተስፋ ግራ ሲዘም
ሞት ጥላ ሲያጠላ ስትጠበብ ዓለም
ልቦና ሲሰለብ ሰዎች ሲያንቀላፉ
መናፍስተ እርኩሳን ሲያንሰፈስፉ
ምድር ስታረምም ሸፍኗት ጨለማ
ተፈጥሮ ሲነጥቃት የድምቀቷን ግርማ
የብርሃን ልዕልት አለቃ ምስለኔ
የእስትንፋስ ያህል ጨረቃ ናት ለኔ !
ዳዊት ጥዑማይ
17/11/18
ዳ ሰኒያ ዓዲ _አሕፈሮም
@getem
@getem
@getem
❤23👍2🔥1
ጊዜው በረረ አይድል
የሮቤል አልበምን
በቅጡ ሳንሰማ
ያን ሌት ያደርነውን
ሰፈር ሳንታማ
አመቱ ሄደ አድል
ክንፍ አበጀ አይድል
ዝም ብሎ ይበራል
አሞራ የሌለው
የዚህ ትውልድ እድል
ነይ እንሂድን ዜማ
ሌሊት ስንሳሳም
በቅጡ ሳንሰማ..
ፍፁም ሳንረጋ
ጊዜው ሄደ አይድል
ሄደን ተመለስን
ሳንመለስ ከጥል
ወድቀን ከራስ ትግል
ደግሞ ሳንዋጋ
ከፍለን የደም ዋጋ
አልጋው ፀጥ ያለበት ትግላችን
በቃ ሳንረጋ
ጊዜ በረረ አድል
ፈርቶ ዝምታችን ..
ነይ እንሂድ
ነይ አንሂድ
ሄደን ለማይቆም ጊዜ
እግራችን አይልፋ
እንኳን የሰማነው
የተሳሳምነው
ከአልጋችን እየጠፋ
አንሂድ አንሂድ
አይሰክንም አየሩ
ብዙ ነው አገሩ
ልታይ ልታይ ይላል
መስታዎት ለእውሩ
ጊዜው በረረ አድል
በእኒያ ሌሊት ከፈን
በሮቤል ዘፈን
በሀይል ተቃቅፈን
የተሻሸንበት..
የተሟሸንበት
ምናለ እንኳ
ሙዚቃ እስኪያበቃ
እግዜሩ ዘመኑን
ክንፍ ቢነሳበት
መናፈቄ እንኳ
አለመናፈቄ እንኳ
ማወላወሌ እንኳ
ሳልወስን ሳላውቀው
በረረብኝ አይድል
ትዝታ ሲነፍገኝ
የዚህ ትውልድ እድል
እንጃ ተነጫነጭኩ
ናፍቀሽኝስ አይድል??
.
.
Based on idea
ሮቤል ሚደቅሳ (ነይ እንሂድ Music )
ግዕዝ ሙላት
@geez_mulat
@getem
@getem
@getem
የሮቤል አልበምን
በቅጡ ሳንሰማ
ያን ሌት ያደርነውን
ሰፈር ሳንታማ
አመቱ ሄደ አድል
ክንፍ አበጀ አይድል
ዝም ብሎ ይበራል
አሞራ የሌለው
የዚህ ትውልድ እድል
ነይ እንሂድን ዜማ
ሌሊት ስንሳሳም
በቅጡ ሳንሰማ..
ፍፁም ሳንረጋ
ጊዜው ሄደ አይድል
ሄደን ተመለስን
ሳንመለስ ከጥል
ወድቀን ከራስ ትግል
ደግሞ ሳንዋጋ
ከፍለን የደም ዋጋ
አልጋው ፀጥ ያለበት ትግላችን
በቃ ሳንረጋ
ጊዜ በረረ አድል
ፈርቶ ዝምታችን ..
ነይ እንሂድ
ነይ አንሂድ
ሄደን ለማይቆም ጊዜ
እግራችን አይልፋ
እንኳን የሰማነው
የተሳሳምነው
ከአልጋችን እየጠፋ
አንሂድ አንሂድ
አይሰክንም አየሩ
ብዙ ነው አገሩ
ልታይ ልታይ ይላል
መስታዎት ለእውሩ
ጊዜው በረረ አድል
በእኒያ ሌሊት ከፈን
በሮቤል ዘፈን
በሀይል ተቃቅፈን
የተሻሸንበት..
የተሟሸንበት
ምናለ እንኳ
ሙዚቃ እስኪያበቃ
እግዜሩ ዘመኑን
ክንፍ ቢነሳበት
መናፈቄ እንኳ
አለመናፈቄ እንኳ
ማወላወሌ እንኳ
ሳልወስን ሳላውቀው
በረረብኝ አይድል
ትዝታ ሲነፍገኝ
የዚህ ትውልድ እድል
እንጃ ተነጫነጭኩ
ናፍቀሽኝስ አይድል??
.
.
Based on idea
ሮቤል ሚደቅሳ (ነይ እንሂድ Music )
ግዕዝ ሙላት
@geez_mulat
@getem
@getem
@getem
❤26👍3😁1