ግጥም ብቻ 📘
63.6K subscribers
1.57K photos
31 videos
61 files
180 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
~  ~  ~  ~  ~  ~  ~  ~  ~  ~  ~  ~ ~  ~
°
ብሸፍተም ሰው ስገድል..
ስትጠራኝ ሳትሸነግል..
ቀስቴን ጥዬ ተሸነፍኩኝ
አንተን ሳይህ 'ረገፍኩኝ፨

ድንገት ራደ ሰዉነቴ፣
ተፈታልኝ ሰንሰለቴ፨
°
ለካ እንዲ ነህ ሰው ስትለውጥ
ለካ እንዲ ነህ ሰው ስትጠራ፣
ጨካኙን ልብ ደግ ያልሰራ፣
ታኖራለህ ስታራራ፨፨
°
ለካ እንዲ ነህ ስታንኳኳ፣
ጻዲቅ ሆነ ገዳዩ እንኳ፨!

By @alem3_b[ዓለም]
@getem
@getem
@getem
59🔥12👍7😢6
አገር ንቆ..ሰው አይጸድቅም!

@myPoems396
@getem
@getem
@getem
15🔥4
ደህና......

እንዴት አደርክ?
    (ደህና!)

እንዴት ዋልክ?
   (ደህና!)

እንዴት አመሸክ?
   ( ደህና!)፤

ደህና ሚለው ቃሌን
    ከጅምሩ አውቀው
በሁሌ ሰላምታ
     ጠየቁኝ አጥብቀው፤
ህ!
ሰላምታው ቢበዛ
  አንድም ላይሰጥ ተስፋ
(አሁን ግን ደህና ነህ?)
    የሚል እንዴት ይጥፋ!???

@Weyblann
@getem
@getem
36😢20👍10
"ግልፅ ጠላ"

ከግልፅ ቃል ምነው ፣ ስውር ቅኔ ቀናን
ከተቀበረ አካል ፣ ትንሳኤ ሕይወት አደራን
ከቀና ጎዳና ፣ ከሀምራዊም ፈትል
ልባችን አማረው ፣ የተጠላለፈ ቅል
ምነው መመንጨሩ ፣ ምነው መጎልጎሉ
ሰውነት ነው ወይ ፣ ማይረጋው አጉሉ
ምንድነው የሆነው ፣ ምንስ ተበጀነው
ድብቁን...
ይቀናናል ማረስ ፣ ፍልሰታ አበጀነው
ምነው ተብከነከን ፣ በአሮጌ አቁማዳ
ተሯሯጥን ደርሰን ፣ ሊላትመን ከዕዳ

መፈለግ ማውጠንጠን ፣ ማወቅን አስቃዠን
መጎልጎል መመርመር ፣ መመንጨር ጎመዠን
አበሳጨንሳ ፣ ራሱ በቀጥታ
ሲጠማዘዝብን ፣ ቀኛችን በረታ
ሲጠላለፍብን ፣ ቅሉ ሲያታክት
ከዝርው ዘር ይልቅ ፣ ወደድን የክት

ሰው የሆነ ሰው ፣ ወደደ በኩሉን
ያለ አዲስ ነገር ፣ አባከነ አቅሉን
አዕምሮው ናወዘ ፣ ወረደ ትከሻው
የልቡን የልቡን ፣ በልቦናው ሲሻው
በዕውቀቱ ቅል ፣ ቁጥር ሲያማታ
አለማወቅ አውቆ ፣ በሕይወት ሲያመነታ
ግርታ ደምኖ ፣ ጭጋግን ሲፈጥር
የልቡ ሥጋ ፣ ድንጋይ ሆኖ ሲሻክር
በጭጋግ በፅልመት ፣ መኖሩ ስትመር
ያለ አዲስ ነገር ፣ አዲስ መንገድ ሲፈጥር
አጓጓዝ ያስተምራል ፣ መድረሻ ተረስቶ
መሄድ መሄድ ይላል ፣ መጨረሻውን ስቶ
በምናቡ ደክርቶ ፣ በመንገዱ ዋትቶ
አረማመድ ሲያምረው ፣ አቋቋሙን ትቶ
አሯሯጥ ይሄዳል ፣ ዛሬውን ዘንግቶ
አሁንን ለማን ፣ መዳኑ ዘግይቶ?
ዛሬን ለማን?
መኖርን ለማን?
እኮ ለማን ትቶ?

By Natnael Abebe

@getem
@getem
@getem
26👍1
ሂድ!

አትጠራጠሩ እውነት ነው ነገሩ
አትደናበሩ ተስማምቷል አገሩ

ተረት ተተርቶ በምግባር ተፈትቶ መፅሐፍም ተፅፏል
ወደፊት ነውንጂ ወደኋላ ያየ ባምላክ ይቀፀፋል!

By @Lawyerly1

@getem
@getem
@getem
25🔥5
#ደብዝዞ_መወደድ

በልክ መሸፈን በልክ መገኘት፡
በልክ ጮሌነት  በልክ   መሞኘት፤
አቤት ስትችይበት!

በልክ ማወደስ  በልክ  መፎገር፡
መስመር  ያልዘለለ  ጨዋታና ነገር፤

በ ል ክ መቀበል በልክ መሸኘት፡
እ ኩ ል ሕብርና እኩል ብቸኝነት፤
አቤት ስትችይበት!
ኑሮና ቀለምሽ ወይነ~ደጋ መንደር፣
ለሰው አታሳዪ ካንድ ስምሽ በቀር።

ሳይሽቀረቀሩ ሳይሉ ወጣ ወረድ፣
ይገርማል ግን እኮ ደብዝዞ መወደድ!
አልተገኘሽም ስታሽካኪበት በየ በዓሉ
እንዲህም ሆነሽ~ታምሪያለሽ አሉ!
እቴ..

ሳትሽቀረቀሪ ሳትይ ክርትት ሰደድ፣
ማነው ያስተማረሽ?
                             ደብዝዞ     
                                     መወደድ!

አቤት ስትችይበት!

@myPoems396
@getem
@getem
@getem
28🤩6🔥3👍1
🦋ማያዬ🦋

በጨቅላ ቡረቃ
‎ፈንድቄ ምውለው፤
‎ስላንቺ ሳስብ ነው
‎ፈገግ የምለው፤

‎እፀ በለስ ወይን
‎የምሽት አዝመራ፤
‎የመለኮት እቅፍ
‎የፍቅር ደመራ፤

‎የጠዋት መዝሙሬ
‎ማለዳ ብስራቴ፤
‎ተጠግኗል ባንቺ
‎ደዌ ስብራቴ፤

‎ሀኪሜ ወዳጅሽ
‎ናፍቆሻል በጠና፤
‎ነይ መጥተሽ ደባብሽው
‎ይፈወሳልና፤

‎ብሌኔ ማያዬ
‎ስስት ቁንጅናዬ፤
‎ድብቋ ጀነቴ
‎ግልጧ መፅናኛዬ፤

‎ለውለታሽ ምላሽ
‎አሰናዳው ማጀት፤
‎ዝግጁ ነኝ ሁሌም
‎ካንቺ ጋር ለማርጀት፤

‎ፊደል ግምጃው ጠርቶኝ
‎ለክብሩ እጁን ስሜ፤
‎የሚመጥንሽን
‎አሰሳ ታድሜ፤

‎ድርሻዬን ዘግኜ
‎ድርሻሽን ለቅሜ፤
‎ይኼን ነው የምልሽ
‎እቺ ናት አቅሜ፤

‎የነፍስ ወይራ ነሽ
‎እጣን እና ከርቤ፤
‎ከፃፍኩልሽ በላይ
‎ይወድሻል ልቤ።

By @Abstruse12

@getem
@getem
@paappii
21👍3🔥1
እግዜር የኔው ይቆይ አስቀድማቸው..
.
.
መቼም እስከኖሩ
ሰው እንደ ፊቱ
መከራው ልዬ ነው
መቼም እስካሉ
እንደ አይን መጠኑ
ሰው ዕዳው ብዙ ነው

የኔ ስቃይ ባያንስ
ባይበልጥም አቋሙ
የኔው ስኬት ይቆይ
ሌሎቹ ይቅደሙ

በየ ቤተስኪያኑ
የሚፈሱ ዕንባዎች
ተራ ሲጠብቁ
ያለቀሱት ብዙ
አመታት በተስፋ
እየጠባበቁ

አስቀድማቸው
ለምን..?
ዕንባቸው ደርቋል
ከአይናቸው
ተስፋ ስላጣ
ፊታቸው

የኔው ይደርሳል
ተራዬ ይቆየኝ
አድርግላቸው
ችግር የለውም
እኔኑ ባታዬኝ

ልቤ ስለሚያዝን
ለመከረኛ ሰው
አልፎልኝ ካልደረስኩ
ይለፍብኝ በማልቅሰው

' በማለቅሰው ዕንባ
በተስፋዬ ካፊያ
ሰውን ካላኖርኩት
ምን ያደርጋል ጥድፊያ

እግዜር...የኔው ይቆይ
እናቶች ይቅደሙ
አባቶች ይቅደሙ
በልጅ ፊት አንሰው
ባለማኖር ውስጥ
ስለሚታመሙ

አባት አንሶ አይታይ
ግርማው አይጠውልግ
በልመናው ቃል
ተራው አስቀድመው
እንዲያደገድግ

ተራዬ ደርሶኝ
ስኬቴ ሁሉ ለሰው ካልደረሰ
ለሰው ኗሪው ይቅደም
መጨረሻ ልሁን
ዕንባን ካላበሰ

@geez_mulat

ይነበብ

ይህ ግጥም ፍፁም ከልቤ ያለውን ሀሳብ ያለምንም የቃላት ምርጫ የፃፍኩት ስራዬ ነው እስከ ሂዎት መጨረሻዬ የምወደው ስራዬ ነው  መታወሻ ይሁነኝ

@getem
@getem
@getem
57👍8😢5🔥3
ወጣቶች ነበርን
በእውቀቱ ስዩም
-----------------------------

ጊዜ ሲራመድ ኮቴው ድምጥ አልባ
ከየት ተነስቶ ወደ የት ገባ
ከየት ተነስቶ ወዴት ደረሰ
ጠጉር መንጥሮ፣ ፊት እያረሰ፤

ወጣቶች ነበርን
ቅጽር የሰራን ፤ አምባ የሰበርን
ኮካ ኮላውን ባሲድ በርዘን
ብንጎነጨው፤ የማይመርዘን፤
በራዱን ያጋልን፣ ሙት ልብ ያስነሳን
ግራዋ በልተን ፤ ሎሚ ያገሳን፤

ተስፋችን ብዙ፤ እድሚያችን ለጋ
ስንሰማራ፣ ትርጉም ፍለጋ

ገላችን አይፈዝ፣ ጭቃ ቢለሰን
የማናስቀይም፤ ቡትቶ ለብሰን
ገጻችን ብሩህ፤ ልባችን ሽፍታ
ስንመነጠቅ፤ ወደ ከፍታ
የስኬት ገነት፣ ደጃፏን ከፍታ
ምትቀበለን ፣ እየመሰለን
ከቁመታችን በላይ፣ የዘለልን፤

ወጣቶች ነበርን
ዛሬ እንደዋዛ
ዘንድሮን ምሰን፤ ታችአምናን ቀበርን፤

@getem
@getem
@paappii
41👍14😢9🔥3
34👍7🔥4👎2🎉1
ጠበቅሁሽ እኔማ፣ እዚያው ስፍራ ቆሜ፣
              በአክሱም ቁመና፣ በላሊበላ እድሜ።
                እግሮቼን ተክዬ፣ ቀኔን አስረዝሜ፣
               በሄድሽበት መንገድ፣ ልቤ እየነጎደ፣
               ስንት ነገር መጣ? ስንት ነገር ሄደ?
               ስንት ጊዜስ ነጋ? ስንቴ ጎህ ቀደደ?
               ስንት ጊዜ ዘነበ? ስንት ጊዜ አባራ?
             ትመጫለሽ ብዬ፣ በቆምኩበት ስፍራ።

       ስንቴ አድማሱን ማተርኩ፣ ስንትና ስንት አመት፣
             አንገቴን አስግጌ፣ በራስ ዳሽን ቁመት።
              በአክሱም ቁመና፣ በላሊበላ እድሜ፣
              በቀጠርሽኝ ስፍራ፣ ስጠብቅሽ ቆሜ፣
             ስንት ሳቅ አለፈ? ስንትና ስንት እምባ?
             ስንቴ ክረምት ሆነ? ስንቴ ፀደይ ጠባ?
                 ስንቱ ተገናኘ? ስንቱ ሰው ተጋባ?
            ሽል ስንቴ ልጅ ሆነ? ስንትስ ጊዜ አረጀ?
              ስንት ኮት ጨረሰ? ስንት እንጀራ ፈጀ?
        ስንት አይነት ሞት አየሁ? ስንት አይነት ፍፃሜ?
              በአክሱም ቁመና፣ በላሊበላ እድሜ፣
             በቆምኩበት ስፍራ፣ ስጠብቅሽ ቆሜ።

             ስንት ዉበት አለፈ? ስንት ዉበት ነጎደ?
          ስንት ትውልድ መጣ? ስንት ትውልድ ሄደ?
         ስንት እውነት ከፍ አለ? ስንት እውነት ወረደ?
             ስንት አለም ተሻረ? ስንት አለም ነገሰ?
ስንት ሀገር ፈረሰ? ስንት ሀገር ተሰራ? ስንት ሀገር ፈረሰ?
       ስንት ሺህ አመት ሸኘሁ? ስንት ሺህ ተቀበልኩ?
            እዚያች ስፍራ ቆሜ፣ አንቺን እየጠበኩ።

                እግሬን አስረዝሜ ቆየሁ፣ ቆየሁና፣
              በላሊበላ እድሜ፣ በአክሱም ቁመና፣
                ሳትመጪ ወደ እኔ፣ ሳላገኝሽ ገና፣
             ብዙ ነገር መጥቶ፣ ብዙ ነገር ያልፋል፣
               የራስ ዳሽን ራስ፣ አንገቱን ይደፋል፣
           አክሱምም ተንዶ፣ እንደ ጨው ይረግፋል፣
             ላሊበላም ወርዶ፣ ቁልቁል ይነጠፋል፣
                 ሰማይና ምድር፣ ያልፋሉ ታያለሽ፣
           እኔ ግን እዚያው ነኝ፣ አንቺ እስክትመለሽ።

By Elias shitawun

@getem
@getem
@paappii
59👍6😢6🤩3
🌿 MEET & MINGLE 🤝
One minute. Many connections.

Are you an artist, creative, cultural practitioner, organisation, or donor looking to connect, discover new opportunities, and explore potential collaborations?

Join us for an evening of quick introductions, meaningful conversations, and new connections with fellow members of the creative ecosystem.

⏱️ 1 minute to introduce your work
(For those interested)
🤝 Connect with new people
🔎 Discover new ideas and opportunities
🥂 Have fun and mingle

📅 29 July 2026
🕠 5:30 PM
📍 Creative Hub Ethiopia,
Old Post office, Piassa, Addis Ababa

🎟️ Registration: https://scan.page/5lJGCr

Come ready to share what you're working on, what you're looking for, and what you can bring to the table.
One minute. Many connections.
See you there!

#MeetAndMingle #CreativeEthiopia #Networking #CreativeCommunity #Collaboration #EUNIC #AddisAbaba

@getem
@getem
7👍2