በለጋ አዕምሯችን፣
የገባንን ፅፈን፤
ልክ ነው በማለት፣
ልክነትን አልፈን፤
ወራዜነት ቀጥፈን፤
እኛነትን ጥለን፣
እኔነትን ታቅፈን፤
በተናጠል ኖረን፤
አይገርምም?
ዛሬም ትክክል ነን፤
ወዶ አይተርቱ
"ሆድ ከሀገር ይሰፋል"
ለሆዱ ያደረም፣
ትውልድን ያጠፋል፤
ማንነት ለማወቅ፣
"ጠይቁ" የሚሉን፤
በኛ ሊከብሩ ነው፣
የሚነጣጥሉን፤
እነሱ
ሁሉም በፊናቸው፣
የሚሰብኩን እውነት፤
(ያው እውነት ከተባለ!)
የኔ ጥያቄ ግን፣
ምንድነው ማንነት?
እህት፣ ወንድምህ ላይ፣
መቀሰር ጣትህን?
(እንደዛ ከሆነ)
የዛሬ ስላቅህ
ነገ ተመልሶ፣
ይነካል ቤትህን፤
ሕመሜ ካስደሳ፣
ከበሮ ካስነሳ፣
ጎሽ፣ እሰይ፣ ለማለት፤
ከደጅህ ካራቀኝ፣
ክንድህ ካልጠበቀኝ፣
የቱ ጋር ነው እውነት?
ምንድነው ነው ልክነት?
የልጅነታችን፤
በሙሉ ልባችን፤
አድጎብን ማመኑ፣
ትተን መመርመሩን፤
ዛሬም ትክክል ነው፣
ሌሎች የሚነግሩን።
🖋ON
@getem
@getem
@getem
የገባንን ፅፈን፤
ልክ ነው በማለት፣
ልክነትን አልፈን፤
ወራዜነት ቀጥፈን፤
እኛነትን ጥለን፣
እኔነትን ታቅፈን፤
በተናጠል ኖረን፤
አይገርምም?
ዛሬም ትክክል ነን፤
ወዶ አይተርቱ
"ሆድ ከሀገር ይሰፋል"
ለሆዱ ያደረም፣
ትውልድን ያጠፋል፤
ማንነት ለማወቅ፣
"ጠይቁ" የሚሉን፤
በኛ ሊከብሩ ነው፣
የሚነጣጥሉን፤
እነሱ
ሁሉም በፊናቸው፣
የሚሰብኩን እውነት፤
(ያው እውነት ከተባለ!)
የኔ ጥያቄ ግን፣
ምንድነው ማንነት?
እህት፣ ወንድምህ ላይ፣
መቀሰር ጣትህን?
(እንደዛ ከሆነ)
የዛሬ ስላቅህ
ነገ ተመልሶ፣
ይነካል ቤትህን፤
ሕመሜ ካስደሳ፣
ከበሮ ካስነሳ፣
ጎሽ፣ እሰይ፣ ለማለት፤
ከደጅህ ካራቀኝ፣
ክንድህ ካልጠበቀኝ፣
የቱ ጋር ነው እውነት?
ምንድነው ነው ልክነት?
የልጅነታችን፤
በሙሉ ልባችን፤
አድጎብን ማመኑ፣
ትተን መመርመሩን፤
ዛሬም ትክክል ነው፣
ሌሎች የሚነግሩን።
🖋ON
@getem
@getem
@getem
❤28
ሀገር እንደ ጭድ ኮስኩሳኝ
ሳስታውሳት ስትረሳኝ
ኢትዬጵያ ወባ ሆናብኝ
ራሴ...ለአንገት ከብዳብኝ
ሀገር ጀርባዋን ስታሳየኝ
ስተን እንደ ሽታ
ወገን ሚባል ጠፋኝ ረግፎ በበሽታ
ሀገርማ
ጫንቃዋማ
ቆስሏል እንደ ንፍሮ
ሀገርማ ፊቷማ
ተቀባብቷል በፊልትሮ
ህዝብ ሚሉት እየሰመጠ
ጉድጓድ ደርሷል የግል ኑሮ
ሀገር እንደ ጭድ ኮስኩሳኝ
ሳስታውሳት ስትረሳኝ
እያደርኩ እየሞትኩኝ
ጥንብ አንሳ ላያነሳኝ
ሰው መሆንጥሎኝ
አውሬ ነው የሚያነሳኝ
ብቻ ጭዱ ያለቦታዋ
እኔን ማቀፍ ለምን ሻተች
ሀገር ታጥባ ወታ
በእኔ እቅፍ እየሸተተች
ለመሽተቴ አትፍረዱ
እንባዬ ነው የሚያወዛኝ
ሳቅ ባክህ አይባልም
ሀገር ሞቶበት ላለ ሀዛኝ
ሀገር ወባ ሆና
ስታንቀጠቅጠኝ በትኩሳት
መቼም ህመሜ ናት
አንዳንዴ አይነግሩትም
ህመምን ጠልተው አይጠሉትም
እያንቀጠቀጠችኝ
እያብረከረከችኝድ
በጭድ ቤቷ እየኮሰኮሰችኝ
ወባ ሆና እያመመችኝ
ትታ የማተወኝ
ትቼ የማልተዋት
ሀገር አለችኝ
By @geez_mulat
@getem
@getem
@getem
ሳስታውሳት ስትረሳኝ
ኢትዬጵያ ወባ ሆናብኝ
ራሴ...ለአንገት ከብዳብኝ
ሀገር ጀርባዋን ስታሳየኝ
ስተን እንደ ሽታ
ወገን ሚባል ጠፋኝ ረግፎ በበሽታ
ሀገርማ
ጫንቃዋማ
ቆስሏል እንደ ንፍሮ
ሀገርማ ፊቷማ
ተቀባብቷል በፊልትሮ
ህዝብ ሚሉት እየሰመጠ
ጉድጓድ ደርሷል የግል ኑሮ
ሀገር እንደ ጭድ ኮስኩሳኝ
ሳስታውሳት ስትረሳኝ
እያደርኩ እየሞትኩኝ
ጥንብ አንሳ ላያነሳኝ
ሰው መሆንጥሎኝ
አውሬ ነው የሚያነሳኝ
ብቻ ጭዱ ያለቦታዋ
እኔን ማቀፍ ለምን ሻተች
ሀገር ታጥባ ወታ
በእኔ እቅፍ እየሸተተች
ለመሽተቴ አትፍረዱ
እንባዬ ነው የሚያወዛኝ
ሳቅ ባክህ አይባልም
ሀገር ሞቶበት ላለ ሀዛኝ
ሀገር ወባ ሆና
ስታንቀጠቅጠኝ በትኩሳት
መቼም ህመሜ ናት
አንዳንዴ አይነግሩትም
ህመምን ጠልተው አይጠሉትም
እያንቀጠቀጠችኝ
እያብረከረከችኝድ
በጭድ ቤቷ እየኮሰኮሰችኝ
ወባ ሆና እያመመችኝ
ትታ የማተወኝ
ትቼ የማልተዋት
ሀገር አለችኝ
By @geez_mulat
@getem
@getem
@getem
❤39👍5🔥2
የሰካራሙ ፍልስፍና ✍️
እዚያ ሰማይ
ከማደሪያው ከመቅደሱ፣ ሱራፌል ተጋርዶ ፊቶቹን ይሰጋል
እዚህ ምድር
አንድ ሰካራም ሰው፣ ለእግዚያር ምክር ይዞ በድፍረት ያወጋል
እንደዚህ ይለዋል በሰካራም ድምጡ
በደልና መፅድቅ እንዲለዋወጡ...
እንዲህ ተናገረ...
" ሰማያት ያለኸው፣ እግዚያር ሆይ ጌታዬ
ሃሳብ ቢጤ ላንተ፣ በፊትህ ከታዬ
ምን መሰለህ እግዚያር...
በዚህኛው አለም በምንኖርባት፣
ሰዎች በተቃርኖ መርህ ይኖራሉ
ተው!...ስትል ጥሰው፣
አድርግ ያልካቸውን መቼ ያደርጋሉ?
እኔንም ተመልከት...
አትስከር ያልከውን፣ ትዛዝህን ልጥስ
ዘውትር እየጠጣው፣ ዘውትር ለምን ላልቅስ?
ስለዚህ እግዝያር
ለዚህ ተቃርኖ ዛር
አንድ መፍትሔ አለኝ...
አታድርግን ጓግተን ከምንላወሰው
ህግጋት ቀልብሰህ ብትቃረን ከሰው
እጥር ምጥን ያለች፣ ፈጥረህ ሰማይ ድግስ
አድርግን አታድርግ፣ እንዲያ ብታደርግስ?...
(ቤተ መቅደስ እንዳትመጡ
የወይን ጠጅ ሂዱ ጠጡ
ቅድስናን እንዳትኖሩ
በደል ብቻ ሂዱ ዝሩ)...
በዛች ትንሽ ድግስ
አድርግን አታድርግ፣ እንዲያ ብታደርግስ?
እኔንም ተመልከት...
እዚህኛው ዓለም ላይ፣ ሰው ተቃርኖን ተግቶ ይከውናል
እንዳትመጡ ስላልክ
ፍቃድህን ልጥስ፣ ምናልባት መቅደስህ እመጣ ይሆናል።"
"
እዚያ ሰማይ
ከማደሪያው ከመቅደሱ፣ ሱራፌል ተጋርዶ ፊቶቹን ይሰጋል
እዚህ ምድር
አንድ ሰካራም ሰው፣ ለእግዚያር ምክር ይዞ በድፍረት ያወጋል።
ፈጥረህ ትንሽ ድግስ
አድርግን አታደርግ፣ እንዲያ ብታደርግስ
¶
በደል አቅፎ እየኖረ፣ እንዲያ ያመካኛል
ሐጥያት መፅደቅ ቢሆን፣ እያለ ይመኛል።
ፈጥረህ ሰማይ ድግስ
እንዲያ ብታደርግስ።
By ሰምረ የሽዋስ
@getem
@getem
@getem
እዚያ ሰማይ
ከማደሪያው ከመቅደሱ፣ ሱራፌል ተጋርዶ ፊቶቹን ይሰጋል
እዚህ ምድር
አንድ ሰካራም ሰው፣ ለእግዚያር ምክር ይዞ በድፍረት ያወጋል
እንደዚህ ይለዋል በሰካራም ድምጡ
በደልና መፅድቅ እንዲለዋወጡ...
እንዲህ ተናገረ...
" ሰማያት ያለኸው፣ እግዚያር ሆይ ጌታዬ
ሃሳብ ቢጤ ላንተ፣ በፊትህ ከታዬ
ምን መሰለህ እግዚያር...
በዚህኛው አለም በምንኖርባት፣
ሰዎች በተቃርኖ መርህ ይኖራሉ
ተው!...ስትል ጥሰው፣
አድርግ ያልካቸውን መቼ ያደርጋሉ?
እኔንም ተመልከት...
አትስከር ያልከውን፣ ትዛዝህን ልጥስ
ዘውትር እየጠጣው፣ ዘውትር ለምን ላልቅስ?
ስለዚህ እግዝያር
ለዚህ ተቃርኖ ዛር
አንድ መፍትሔ አለኝ...
አታድርግን ጓግተን ከምንላወሰው
ህግጋት ቀልብሰህ ብትቃረን ከሰው
እጥር ምጥን ያለች፣ ፈጥረህ ሰማይ ድግስ
አድርግን አታድርግ፣ እንዲያ ብታደርግስ?...
(ቤተ መቅደስ እንዳትመጡ
የወይን ጠጅ ሂዱ ጠጡ
ቅድስናን እንዳትኖሩ
በደል ብቻ ሂዱ ዝሩ)...
በዛች ትንሽ ድግስ
አድርግን አታድርግ፣ እንዲያ ብታደርግስ?
እኔንም ተመልከት...
እዚህኛው ዓለም ላይ፣ ሰው ተቃርኖን ተግቶ ይከውናል
እንዳትመጡ ስላልክ
ፍቃድህን ልጥስ፣ ምናልባት መቅደስህ እመጣ ይሆናል።"
"
እዚያ ሰማይ
ከማደሪያው ከመቅደሱ፣ ሱራፌል ተጋርዶ ፊቶቹን ይሰጋል
እዚህ ምድር
አንድ ሰካራም ሰው፣ ለእግዚያር ምክር ይዞ በድፍረት ያወጋል።
ፈጥረህ ትንሽ ድግስ
አድርግን አታደርግ፣ እንዲያ ብታደርግስ
¶
በደል አቅፎ እየኖረ፣ እንዲያ ያመካኛል
ሐጥያት መፅደቅ ቢሆን፣ እያለ ይመኛል።
ፈጥረህ ሰማይ ድግስ
እንዲያ ብታደርግስ።
By ሰምረ የሽዋስ
@getem
@getem
@getem
❤23🔥13👍2🤩1
የቁም ፍቅር
ስደክም ብውል አዳር ብለፋም፤
አስታውሳለሁ ከውስጤ አይጠፋም፤
የዛ ቀን ግለት የዛች ቀኑ ፍም፤
ያገኘሁሽ ቀን በዛች ካፌ ፍክት ብለሽ፣
ያየሁሽ ለታ እዚያ ጥግ ላይ ስልክሽን ይዘሽ፤
'ሰው አለው' ብዬ ወንበሩን ልስብ፣
ገና ሳልለው እንዲሁ ባሳብ፤
ሳወጣ ሳወርድ ቃላት ስመርጥ፣
አይንሽን ስቃኝ ከንፈሬን ስመጥ፤
እንዲሁ ቆሜ እንዲሁ እንዳለሁ፤
ለካ ሳላውቀው እረዥም ሰአት ተገትሬያለሁ፤
አሁን ስመለስ ራሴን ሳገኘው፤
ዙሪያ ገባውን ባይኔ ብቃኘው፤
አልለማ አልሰማ አልጠፋ አልበራ፤
እንዲሁ ብቻ ግትር ብዬ እንደጅብራ፤
'እብድ ነው?' በሚል አስተያየትሽ ብትገረምሚኝ፤
አቅፌው ሄድኩኝ ያንድ ደቂቃ ፍቅሬን ሳትሰሚኝ፤
By @Lawyerly1
@getem
@getem
@getem
ስደክም ብውል አዳር ብለፋም፤
አስታውሳለሁ ከውስጤ አይጠፋም፤
የዛ ቀን ግለት የዛች ቀኑ ፍም፤
ያገኘሁሽ ቀን በዛች ካፌ ፍክት ብለሽ፣
ያየሁሽ ለታ እዚያ ጥግ ላይ ስልክሽን ይዘሽ፤
'ሰው አለው' ብዬ ወንበሩን ልስብ፣
ገና ሳልለው እንዲሁ ባሳብ፤
ሳወጣ ሳወርድ ቃላት ስመርጥ፣
አይንሽን ስቃኝ ከንፈሬን ስመጥ፤
እንዲሁ ቆሜ እንዲሁ እንዳለሁ፤
ለካ ሳላውቀው እረዥም ሰአት ተገትሬያለሁ፤
አሁን ስመለስ ራሴን ሳገኘው፤
ዙሪያ ገባውን ባይኔ ብቃኘው፤
አልለማ አልሰማ አልጠፋ አልበራ፤
እንዲሁ ብቻ ግትር ብዬ እንደጅብራ፤
'እብድ ነው?' በሚል አስተያየትሽ ብትገረምሚኝ፤
አቅፌው ሄድኩኝ ያንድ ደቂቃ ፍቅሬን ሳትሰሚኝ፤
By @Lawyerly1
@getem
@getem
@getem
❤40🔥7
ይቅር በላቸው[ፀሎት]
የሞገቱኝን ሽራፊ ቀኖች
ያስጀነኑኝን ጎዶሎ ሀብቶች...
_ _ _
ሸንበቆ ድግፍ እፍኝ ትምክህቶች
መውደቂያ ያጡ ድፍን ተምኔቶች!
ይቅር በላቸው...
የተጣደፉ ፈራጅ ከንፈሮች
ያልተማከሩ ልብና አፎች!
ያልደነገጡ ድንድን ስሜቶች
ያልተረጋጉ ሰንካላ እምነቶች!
ይቅር በላቸው!
ይበልጥም...
_ _ _
ያስመከቱኝን ውዥቅ ቀለማት
ያስፎከሩኝን ግንጥል ድምቀታት!
ይቅር በላቸው!
አልደበቁኝም ልሽሽው ካልኩት
አላስጣሉኝም ከተሯሯጥኩት
አላወጡኝም ከሰው ትከሻ
ወይ አልሰጡኝም ዝና ሙገሳ፨
ይቅር በላቸው!
ማራቸው ያለህ ልቤ አስታኮ፧
አብረህ አስበኝ ሊልህ ነው እኮ፧፧
By @alem3_b [ዓለም]
@getem
@getem
@getem
የሞገቱኝን ሽራፊ ቀኖች
ያስጀነኑኝን ጎዶሎ ሀብቶች...
_ _ _
ሸንበቆ ድግፍ እፍኝ ትምክህቶች
መውደቂያ ያጡ ድፍን ተምኔቶች!
ይቅር በላቸው...
የተጣደፉ ፈራጅ ከንፈሮች
ያልተማከሩ ልብና አፎች!
ያልደነገጡ ድንድን ስሜቶች
ያልተረጋጉ ሰንካላ እምነቶች!
ይቅር በላቸው!
ይበልጥም...
የሞገቱኝን ሽራፊ ቀኖች!
ያስጀነኑኝን ጎዶሎ ሃብቶች!
_ _ _
ያስመከቱኝን ውዥቅ ቀለማት
ያስፎከሩኝን ግንጥል ድምቀታት!
ይቅር በላቸው!
አልደበቁኝም ልሽሽው ካልኩት
አላስጣሉኝም ከተሯሯጥኩት
አላወጡኝም ከሰው ትከሻ
ወይ አልሰጡኝም ዝና ሙገሳ፨
ይቅር በላቸው!
By @alem3_b [ዓለም]
@getem
@getem
@getem
❤47🔥11👍3😱2
ድሮ አንቺን ለማየት
ሰፈርሽ ስመጣ
አንዲት ዝርግ ድንጋይ
አየሁ ተቀምጣ ፤
ቁጭ አልኩኝ በድንገት
እንዲህ እንደ ዘበት…
ያፈቀረሸ ልቤ ፣ ሳሉ ሲነሳበት
ማስታገሻ ነበር ፣ ሰፈርሽ መገኘት።
ዛሬስ አትይኝም?
እዛው ተቀምጬ
አትመጣም ወይ? እያልሁ
አንቺ ብትቀሪ…
:
ዲግሪ ጭኖ መጣ
ሀይስኩል ተማሪ።
እዛው ትናንትና
እዛው አንቺ ሰፈር
ከጠፍጣፉ ድንጋይ
ሳልነሳ ቀንቶኝ…
:
ያምና ብላቴና
ያልፈኛል ገላምጦኝ።
አትገረሚም ወይ?
ሳልነሳ ከዛ
ቤተ መቅደስ ታዛ
ከስር የማይጠፋ
የወንጌል ሰባኪ
ቅስናውን ገድፎ
በየመሸታ ቤት
ሲያወርድ ያድራል ውስኪ።
እዛው ትናንትና
አንቺን ከማይበት
ከጠፍጣፉ ድንጋይ
ተቀምጬ እያለሁ
አንዱ አብሮ አደጌ
በመኺና ባየው-
እጆቼን ዘረጋሁ
ለናፍቆት ሰላምታ
መስታወቱን ሳበ
በእንዴት ነህ? ፈንታ
ያን ጊዜ ተከፋሁ
ውስጤን ቦረቦረኝ-
ምናል እንደ ድሮው
አቅፎ ሰላም ቢለኝ?
(ጎስቁያለሁ በቃ?🤔)
አትገረሚም ወይ?
ሰዎች አሉኝ ከንቱ
መንገድ ቀየሩብኝ
ቀፍፎ ፣ ጎርብጧቸው
ዘባተሎ ጨርቄ…
ያካሌ ቡትቱ።
(ጎስቁያለሁ ለካ !)
እዛው ቁጭ ብዬ
ተዓምር ደረሰ
ሰፈሩ ተዳሰ
ቅጥሩ ፈራረሰ
የግቢያችሁ በሩ
ይከብድ የነበረው
በአባትሽ ትከሻ…
:
የማንም ወመኔ
አጨሰበት ሺሻ።
እዛችው ከትናንት
ከግቢያችሁ ማዶ
እስክሰማ ድረስ
ቀጭን ክፉ መርዶ
:
እየጫኑ ዲግሪ፣
እየናቀኝ ውሪ፣
ሰክሮ እየሳተ…
የ’ግዜአብሔር አዳሪ
እብድ ነው እያሉኝ
እነ ቲቲ ፣ ሜሪ
እየተቃመበት
የአባትሽ ገዳም
እየተጨሰበት
የእናትሽ በዓት
ትዝታችን ሲናድ
በከተማ ልማት ፤
አንዱም ድል ሳይመታኝ
ስንቱን ዘመን ሽሬ
እልፍ ዘመን ኖሬ
ሁሉን እየረታሁ …
ሁሉን እየነሳሁ…
“አግብታለች” ቢሉኝ
በድንገት ተነሳሁ።
(ታስታውሽኝ ይሆን?)
አታውቂኝም ለካ🥹
ሚካኤል .አ
@getem
@getem
@paappii
ሰፈርሽ ስመጣ
አንዲት ዝርግ ድንጋይ
አየሁ ተቀምጣ ፤
ቁጭ አልኩኝ በድንገት
እንዲህ እንደ ዘበት…
ያፈቀረሸ ልቤ ፣ ሳሉ ሲነሳበት
ማስታገሻ ነበር ፣ ሰፈርሽ መገኘት።
ዛሬስ አትይኝም?
እዛው ተቀምጬ
አትመጣም ወይ? እያልሁ
አንቺ ብትቀሪ…
:
ዲግሪ ጭኖ መጣ
ሀይስኩል ተማሪ።
እዛው ትናንትና
እዛው አንቺ ሰፈር
ከጠፍጣፉ ድንጋይ
ሳልነሳ ቀንቶኝ…
:
ያምና ብላቴና
ያልፈኛል ገላምጦኝ።
አትገረሚም ወይ?
ሳልነሳ ከዛ
ቤተ መቅደስ ታዛ
ከስር የማይጠፋ
የወንጌል ሰባኪ
ቅስናውን ገድፎ
በየመሸታ ቤት
ሲያወርድ ያድራል ውስኪ።
እዛው ትናንትና
አንቺን ከማይበት
ከጠፍጣፉ ድንጋይ
ተቀምጬ እያለሁ
አንዱ አብሮ አደጌ
በመኺና ባየው-
እጆቼን ዘረጋሁ
ለናፍቆት ሰላምታ
መስታወቱን ሳበ
በእንዴት ነህ? ፈንታ
ያን ጊዜ ተከፋሁ
ውስጤን ቦረቦረኝ-
ምናል እንደ ድሮው
አቅፎ ሰላም ቢለኝ?
(ጎስቁያለሁ በቃ?🤔)
አትገረሚም ወይ?
ሰዎች አሉኝ ከንቱ
መንገድ ቀየሩብኝ
ቀፍፎ ፣ ጎርብጧቸው
ዘባተሎ ጨርቄ…
ያካሌ ቡትቱ።
(ጎስቁያለሁ ለካ !)
እዛው ቁጭ ብዬ
ተዓምር ደረሰ
ሰፈሩ ተዳሰ
ቅጥሩ ፈራረሰ
የግቢያችሁ በሩ
ይከብድ የነበረው
በአባትሽ ትከሻ…
:
የማንም ወመኔ
አጨሰበት ሺሻ።
እዛችው ከትናንት
ከግቢያችሁ ማዶ
እስክሰማ ድረስ
ቀጭን ክፉ መርዶ
:
እየጫኑ ዲግሪ፣
እየናቀኝ ውሪ፣
ሰክሮ እየሳተ…
የ’ግዜአብሔር አዳሪ
እብድ ነው እያሉኝ
እነ ቲቲ ፣ ሜሪ
እየተቃመበት
የአባትሽ ገዳም
እየተጨሰበት
የእናትሽ በዓት
ትዝታችን ሲናድ
በከተማ ልማት ፤
አንዱም ድል ሳይመታኝ
ስንቱን ዘመን ሽሬ
እልፍ ዘመን ኖሬ
ሁሉን እየረታሁ …
ሁሉን እየነሳሁ…
“አግብታለች” ቢሉኝ
በድንገት ተነሳሁ።
(ታስታውሽኝ ይሆን?)
አታውቂኝም ለካ🥹
ሚካኤል .አ
@getem
@getem
@paappii
❤67🔥23😢19👍3
እውነትም ሰገነት!
ውሸት አልነበረም ያ ሁሉ ሙገሳ፥
ሰማይ ታህል ነበር ጨረቃ አንችን ለብሳ።
አድማስና ማማ ማጋነን ቢመስል፥
ወንዝ እንኳ ሚረጋው ሲቃኝ ባንቺ ምስል፤
እውነት? ያባይ ጅረት ሳቅሽን ይበልጣል?
የጢሱ ርግብታ? ከርጋታሽ ይሰክናል?
እስቲ ጽጌሬዳ?ይመ--ስልሻል ወይ፣
ይቅርና በበጋ እርሙንስ በጸደይ?!
ንግግርሽ ሃገር አርምሞሽ አሃጉር
አንቺ ላይ ከረመ ውበት ሲያንጎራጉር!።
ሃሳብሽ ገራገር መርኅሽ ዝምታ፣፨
.
.
.
እውነትም ሰገነት ፣ እውነትም ከፍታ!።🙌🏿
By @alem3_b [ዓለም]
@getem
@getem
@getem
ውሸት አልነበረም ያ ሁሉ ሙገሳ፥
ሰማይ ታህል ነበር ጨረቃ አንችን ለብሳ።
አድማስና ማማ ማጋነን ቢመስል፥
ወንዝ እንኳ ሚረጋው ሲቃኝ ባንቺ ምስል፤
እውነት? ያባይ ጅረት ሳቅሽን ይበልጣል?
የጢሱ ርግብታ? ከርጋታሽ ይሰክናል?
እስቲ ጽጌሬዳ?ይመ--ስልሻል ወይ፣
ይቅርና በበጋ እርሙንስ በጸደይ?!
ንግግርሽ ሃገር አርምሞሽ አሃጉር
አንቺ ላይ ከረመ ውበት ሲያንጎራጉር!።
ሃሳብሽ ገራገር መርኅሽ ዝምታ፣፨
.
.
.
እውነትም ሰገነት ፣ እውነትም ከፍታ!።🙌🏿
By @alem3_b [ዓለም]
@getem
@getem
@getem
❤48👎3🤩1
እንዳትረሺኝ ብዬሽ፤
አትርሳኝ ብለሽኝ ፤
በቃል ክር አስሬሽ፤
በቃል ክር አስረሽኝ፤
በደልሽኝ በደልኩሽ፤
በደልኩሽ በደልሽኝ ፤
ቃልሽን አከበርሽ
ቃሌን አከበርኩኝ ፤
ይሄ በደላችን...
እንኳን በ'ዚህ ሕይወት
በመቃብርም ውስጥ ችሎ አያረሳሳም፤
ደግሞ እንደምታውቂው
የወዳጅ ፍቅሩ እንጅ በደሉ አይረሳም ።
By Tewodros kassa
@topazionnn
@topazionnn
አትርሳኝ ብለሽኝ ፤
በቃል ክር አስሬሽ፤
በቃል ክር አስረሽኝ፤
በደልሽኝ በደልኩሽ፤
በደልኩሽ በደልሽኝ ፤
ቃልሽን አከበርሽ
ቃሌን አከበርኩኝ ፤
ይሄ በደላችን...
እንኳን በ'ዚህ ሕይወት
በመቃብርም ውስጥ ችሎ አያረሳሳም፤
ደግሞ እንደምታውቂው
የወዳጅ ፍቅሩ እንጅ በደሉ አይረሳም ።
By Tewodros kassa
@topazionnn
@topazionnn
❤59🔥6
"ግልፅ ጠላ"
ከግልፅ ቃል ምነው ፣ ስውር ቅኔ ቀናን
ከተቀበረ አካል ፣ ትንሳኤ ሕይወት አደራን
ከቀና ጎዳና ፣ ከሀምራዊም ፈትል
ልባችን አማረው ፣ የተጠላለፈ ቅል
ምነው መመንጨሩ ፣ ምነው መጎልጎሉ
ሰውነት ነው ወይ ፣ ማይረጋው አጉሉ
ምንድነው የሆነው ፣ ምንስ ተበጀነው
ድብቁን...
ይቀናናል ማረስ ፣ ፍልሰታ አበጀነው
ምነው ተብከነከን ፣ በአሮጌ አቁማዳ
ተሯሯጥን ደርሰን ፣ ሊላትመን ከዕዳ
መፈለግ ማውጠንጠን ፣ ማወቅን አስቃዠን
መጎልጎል መመርመር ፣ መመንጨር ጎመዠን
አበሳጨንሳ ፣ ራሱ በቀጥታ
ሲጠማዘዝብን ፣ ቀኛችን በረታ
ሲጠላለፍብን ፣ ቅሉ ሲያታክት
ከዝርው ዘር ይልቅ ፣ ወደድን የክት
ሰው የሆነ ሰው ፣ ወደደ በኩሉን
ያለ አዲስ ነገር ፣ አባከነ አቅሉን
አዕምሮው ናወዘ ፣ ወረደ ትከሻው
የልቡን የልቡን ፣ በልቦናው ሲሻው
በዕውቀቱ ቅል ፣ ቁጥር ሲያማታ
አለማወቅ አውቆ ፣ በሕይወት ሲያመነታ
ግርታ ደምኖ ፣ ጭጋግን ሲፈጥር
የልቡ ሥጋ ፣ ድንጋይ ሆኖ ሲሻክር
በጭጋግ በፅልመት ፣ መኖሩ ስትመር
ያለ አዲስ ነገር ፣ አዲስ መንገድ ሲፈጥር
አጓጓዝ ያስተምራል ፣ መድረሻ ተረስቶ
መሄድ መሄድ ይላል ፣ መጨረሻውን ስቶ
በምናቡ ደክርቶ ፣ በመንገዱ ዋትቶ
አረማመድ ሲያምረው ፣ አቋቋሙን ትቶ
አሯሯጥ ይሄዳል ፣ ዛሬውን ዘንግቶ
አሁንን ለማን ፣ መዳኑ ዘግይቶ?
ዛሬን ለማን?
መኖርን ለማን?
እኮ ለማን ትቶ?
By Natnael Abebe
@getem
@getem
@getem
ከግልፅ ቃል ምነው ፣ ስውር ቅኔ ቀናን
ከተቀበረ አካል ፣ ትንሳኤ ሕይወት አደራን
ከቀና ጎዳና ፣ ከሀምራዊም ፈትል
ልባችን አማረው ፣ የተጠላለፈ ቅል
ምነው መመንጨሩ ፣ ምነው መጎልጎሉ
ሰውነት ነው ወይ ፣ ማይረጋው አጉሉ
ምንድነው የሆነው ፣ ምንስ ተበጀነው
ድብቁን...
ይቀናናል ማረስ ፣ ፍልሰታ አበጀነው
ምነው ተብከነከን ፣ በአሮጌ አቁማዳ
ተሯሯጥን ደርሰን ፣ ሊላትመን ከዕዳ
መፈለግ ማውጠንጠን ፣ ማወቅን አስቃዠን
መጎልጎል መመርመር ፣ መመንጨር ጎመዠን
አበሳጨንሳ ፣ ራሱ በቀጥታ
ሲጠማዘዝብን ፣ ቀኛችን በረታ
ሲጠላለፍብን ፣ ቅሉ ሲያታክት
ከዝርው ዘር ይልቅ ፣ ወደድን የክት
ሰው የሆነ ሰው ፣ ወደደ በኩሉን
ያለ አዲስ ነገር ፣ አባከነ አቅሉን
አዕምሮው ናወዘ ፣ ወረደ ትከሻው
የልቡን የልቡን ፣ በልቦናው ሲሻው
በዕውቀቱ ቅል ፣ ቁጥር ሲያማታ
አለማወቅ አውቆ ፣ በሕይወት ሲያመነታ
ግርታ ደምኖ ፣ ጭጋግን ሲፈጥር
የልቡ ሥጋ ፣ ድንጋይ ሆኖ ሲሻክር
በጭጋግ በፅልመት ፣ መኖሩ ስትመር
ያለ አዲስ ነገር ፣ አዲስ መንገድ ሲፈጥር
አጓጓዝ ያስተምራል ፣ መድረሻ ተረስቶ
መሄድ መሄድ ይላል ፣ መጨረሻውን ስቶ
በምናቡ ደክርቶ ፣ በመንገዱ ዋትቶ
አረማመድ ሲያምረው ፣ አቋቋሙን ትቶ
አሯሯጥ ይሄዳል ፣ ዛሬውን ዘንግቶ
አሁንን ለማን ፣ መዳኑ ዘግይቶ?
ዛሬን ለማን?
መኖርን ለማን?
እኮ ለማን ትቶ?
By Natnael Abebe
@getem
@getem
@getem
❤14
ሂድ!
አትጠራጠሩ እውነት ነው ነገሩ
አትደናበሩ ተስማምቷል አገሩ
ተረት ተተርቶ በምግባር ተፈትቶ መፅሐፍም ተፅፏል
ወደፊት ነውንጂ ወደኋላ ያየ ባምላክ ይቀፀፋል!
By @Lawyerly1
@getem
@getem
@getem
አትጠራጠሩ እውነት ነው ነገሩ
አትደናበሩ ተስማምቷል አገሩ
ተረት ተተርቶ በምግባር ተፈትቶ መፅሐፍም ተፅፏል
ወደፊት ነውንጂ ወደኋላ ያየ ባምላክ ይቀፀፋል!
By @Lawyerly1
@getem
@getem
@getem
❤19🔥2
#ደብዝዞ_መወደድ
በልክ መሸፈን በልክ መገኘት፡
በልክ ጮሌነት በልክ መሞኘት፤
አቤት ስትችይበት!
በልክ ማወደስ በልክ መፎገር፡
መስመር ያልዘለለ ጨዋታና ነገር፤
በ ል ክ መቀበል በልክ መሸኘት፡
እ ኩ ል ሕብርና እኩል ብቸኝነት፤
አቤት ስትችይበት!
ኑሮና ቀለምሽ ወይነ~ደጋ መንደር፣
ለሰው አታሳዪ ካንድ ስምሽ በቀር።
ሳይሽቀረቀሩ ሳይሉ ወጣ ወረድ፣
ይገርማል ግን እኮ ደብዝዞ መወደድ!
አልተገኘሽም ስታሽካኪበት በየ በዓሉ
እንዲህም ሆነሽ~ታምሪያለሽ አሉ!
እቴ..
ሳትሽቀረቀሪ ሳትይ ክርትት ሰደድ፣
ማነው ያስተማረሽ?
ደብዝዞ
መወደድ!
አቤት ስትችይበት!
@myPoems396
@getem
@getem
@getem
በልክ መሸፈን በልክ መገኘት፡
በልክ ጮሌነት በልክ መሞኘት፤
አቤት ስትችይበት!
በልክ ማወደስ በልክ መፎገር፡
መስመር ያልዘለለ ጨዋታና ነገር፤
በ ል ክ መቀበል በልክ መሸኘት፡
እ ኩ ል ሕብርና እኩል ብቸኝነት፤
አቤት ስትችይበት!
ኑሮና ቀለምሽ ወይነ~ደጋ መንደር፣
ለሰው አታሳዪ ካንድ ስምሽ በቀር።
ሳይሽቀረቀሩ ሳይሉ ወጣ ወረድ፣
ይገርማል ግን እኮ ደብዝዞ መወደድ!
አልተገኘሽም ስታሽካኪበት በየ በዓሉ
እንዲህም ሆነሽ~ታምሪያለሽ አሉ!
እቴ..
ሳትሽቀረቀሪ ሳትይ ክርትት ሰደድ፣
ማነው ያስተማረሽ?
ደብዝዞ
መወደድ!
አቤት ስትችይበት!
@myPoems396
@getem
@getem
@getem
❤10🤩3🔥1
🦋ማያዬ🦋
በጨቅላ ቡረቃ
ፈንድቄ ምውለው፤
ስላንቺ ሳስብ ነው
ፈገግ የምለው፤
እፀ በለስ ወይን
የምሽት አዝመራ፤
የመለኮት እቅፍ
የፍቅር ደመራ፤
የጠዋት መዝሙሬ
ማለዳ ብስራቴ፤
ተጠግኗል ባንቺ
ደዌ ስብራቴ፤
ሀኪሜ ወዳጅሽ
ናፍቆሻል በጠና፤
ነይ መጥተሽ ደባብሽው
ይፈወሳልና፤
ብሌኔ ማያዬ
ስስት ቁንጅናዬ፤
ድብቋ ጀነቴ
ግልጧ መፅናኛዬ፤
ለውለታሽ ምላሽ
አሰናዳው ማጀት፤
ዝግጁ ነኝ ሁሌም
ካንቺ ጋር ለማርጀት፤
ፊደል ግምጃው ጠርቶኝ
ለክብሩ እጁን ስሜ፤
የሚመጥንሽን
አሰሳ ታድሜ፤
ድርሻዬን ዘግኜ
ድርሻሽን ለቅሜ፤
ይኼን ነው የምልሽ
እቺ ናት አቅሜ፤
የነፍስ ወይራ ነሽ
እጣን እና ከርቤ፤
ከፃፍኩልሽ በላይ
ይወድሻል ልቤ።
By @Abstruse12
@getem
@getem
@paappii
በጨቅላ ቡረቃ
ፈንድቄ ምውለው፤
ስላንቺ ሳስብ ነው
ፈገግ የምለው፤
እፀ በለስ ወይን
የምሽት አዝመራ፤
የመለኮት እቅፍ
የፍቅር ደመራ፤
የጠዋት መዝሙሬ
ማለዳ ብስራቴ፤
ተጠግኗል ባንቺ
ደዌ ስብራቴ፤
ሀኪሜ ወዳጅሽ
ናፍቆሻል በጠና፤
ነይ መጥተሽ ደባብሽው
ይፈወሳልና፤
ብሌኔ ማያዬ
ስስት ቁንጅናዬ፤
ድብቋ ጀነቴ
ግልጧ መፅናኛዬ፤
ለውለታሽ ምላሽ
አሰናዳው ማጀት፤
ዝግጁ ነኝ ሁሌም
ካንቺ ጋር ለማርጀት፤
ፊደል ግምጃው ጠርቶኝ
ለክብሩ እጁን ስሜ፤
የሚመጥንሽን
አሰሳ ታድሜ፤
ድርሻዬን ዘግኜ
ድርሻሽን ለቅሜ፤
ይኼን ነው የምልሽ
እቺ ናት አቅሜ፤
የነፍስ ወይራ ነሽ
እጣን እና ከርቤ፤
ከፃፍኩልሽ በላይ
ይወድሻል ልቤ።
By @Abstruse12
@getem
@getem
@paappii
❤5🔥1
እግዜር የኔው ይቆይ አስቀድማቸው..
.
.
መቼም እስከኖሩ
ሰው እንደ ፊቱ
መከራው ልዬ ነው
መቼም እስካሉ
እንደ አይን መጠኑ
ሰው ዕዳው ብዙ ነው
የኔ ስቃይ ባያንስ
ባይበልጥም አቋሙ
የኔው ስኬት ይቆይ
ሌሎቹ ይቅደሙ
በየ ቤተስኪያኑ
የሚፈሱ ዕንባዎች
ተራ ሲጠብቁ
ያለቀሱት ብዙ
አመታት በተስፋ
እየጠባበቁ
አስቀድማቸው
ለምን..?
ዕንባቸው ደርቋል
ከአይናቸው
ተስፋ ስላጣ
ፊታቸው
የኔው ይደርሳል
ተራዬ ይቆየኝ
አድርግላቸው
ችግር የለውም
እኔኑ ባታዬኝ
ልቤ ስለሚያዝን
ለመከረኛ ሰው
አልፎልኝ ካልደረስኩ
ይለፍብኝ በማልቅሰው
' በማለቅሰው ዕንባ
በተስፋዬ ካፊያ
ሰውን ካላኖርኩት
ምን ያደርጋል ጥድፊያ
እግዜር...የኔው ይቆይ
እናቶች ይቅደሙ
አባቶች ይቅደሙ
በልጅ ፊት አንሰው
ባለማኖር ውስጥ
ስለሚታመሙ
አባት አንሶ አይታይ
ግርማው አይጠውልግ
በልመናው ቃል
ተራው አስቀድመው
እንዲያደገድግ
ተራዬ ደርሶኝ
ስኬቴ ሁሉ ለሰው ካልደረሰ
ለሰው ኗሪው ይቅደም
መጨረሻ ልሁን
ዕንባን ካላበሰ
@geez_mulat
ይነበብ
ይህ ግጥም ፍፁም ከልቤ ያለውን ሀሳብ ያለምንም የቃላት ምርጫ የፃፍኩት ስራዬ ነው እስከ ሂዎት መጨረሻዬ የምወደው ስራዬ ነው መታወሻ ይሁነኝ
@getem
@getem
@getem
.
.
መቼም እስከኖሩ
ሰው እንደ ፊቱ
መከራው ልዬ ነው
መቼም እስካሉ
እንደ አይን መጠኑ
ሰው ዕዳው ብዙ ነው
የኔ ስቃይ ባያንስ
ባይበልጥም አቋሙ
የኔው ስኬት ይቆይ
ሌሎቹ ይቅደሙ
በየ ቤተስኪያኑ
የሚፈሱ ዕንባዎች
ተራ ሲጠብቁ
ያለቀሱት ብዙ
አመታት በተስፋ
እየጠባበቁ
አስቀድማቸው
ለምን..?
ዕንባቸው ደርቋል
ከአይናቸው
ተስፋ ስላጣ
ፊታቸው
የኔው ይደርሳል
ተራዬ ይቆየኝ
አድርግላቸው
ችግር የለውም
እኔኑ ባታዬኝ
ልቤ ስለሚያዝን
ለመከረኛ ሰው
አልፎልኝ ካልደረስኩ
ይለፍብኝ በማልቅሰው
' በማለቅሰው ዕንባ
በተስፋዬ ካፊያ
ሰውን ካላኖርኩት
ምን ያደርጋል ጥድፊያ
እግዜር...የኔው ይቆይ
እናቶች ይቅደሙ
አባቶች ይቅደሙ
በልጅ ፊት አንሰው
ባለማኖር ውስጥ
ስለሚታመሙ
አባት አንሶ አይታይ
ግርማው አይጠውልግ
በልመናው ቃል
ተራው አስቀድመው
እንዲያደገድግ
ተራዬ ደርሶኝ
ስኬቴ ሁሉ ለሰው ካልደረሰ
ለሰው ኗሪው ይቅደም
መጨረሻ ልሁን
ዕንባን ካላበሰ
@geez_mulat
ይነበብ
@getem
@getem
@getem
❤10👍3🔥1