አልወስድሽም
///////////////
በጉልበት ፈጀሁት
ህዝበ አዳሙን ሁሉ፣
አላይም አልደርስም
አንቺ ዘንድ እስኪሉ።
ገንዘብ እንደ ቅጠል
ሚበቅል ይመስል፣
በስጦታ አንቺን
ቀን በቀን ስከልል።
ከአድማስ ወድያ
ከጀንበር ስር፣
ግዛት ቦታን ሳሰማምር፣
አበባ አንቺን የማይተኩ
ፅጌሬዶች ስደረድር።
ተራሮችን ስቀርፅልሽ፣
ያንቺን ውብ መልክ ላስይዝልሽ።
የዛፍን ቅርፅ ስቀይረው፣
ታላቅ ፍቅሬን እንዲገልፀው።
ዳመኖችን ስስልልሽ
እንድትወጂው ሳደርግልሽ፣
ከሰማይ ዳር ቀስቴን ይዤ
ደመና ላይ ሳሰፍርልሽ፣
አንቺ አላየሽ፣
ይህ ፍቅሬንም አላስተዋልሽ፣
ስጦታዬን አልተቀበልሽ፣
ግዛቴንም ከቶ አልፈለግሽ፣
እንዲሁ ብቻ ዝም ብለሽ
እኔን ጥለሽ መናኒ ሆንሽ።
ሁሉን ባደርግ ብሰጥሽም፣
አንቺን አንቺ ካደረገሽ
ከፈጣሪስ አልወስድሽም።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
///////////////
በጉልበት ፈጀሁት
ህዝበ አዳሙን ሁሉ፣
አላይም አልደርስም
አንቺ ዘንድ እስኪሉ።
ገንዘብ እንደ ቅጠል
ሚበቅል ይመስል፣
በስጦታ አንቺን
ቀን በቀን ስከልል።
ከአድማስ ወድያ
ከጀንበር ስር፣
ግዛት ቦታን ሳሰማምር፣
አበባ አንቺን የማይተኩ
ፅጌሬዶች ስደረድር።
ተራሮችን ስቀርፅልሽ፣
ያንቺን ውብ መልክ ላስይዝልሽ።
የዛፍን ቅርፅ ስቀይረው፣
ታላቅ ፍቅሬን እንዲገልፀው።
ዳመኖችን ስስልልሽ
እንድትወጂው ሳደርግልሽ፣
ከሰማይ ዳር ቀስቴን ይዤ
ደመና ላይ ሳሰፍርልሽ፣
አንቺ አላየሽ፣
ይህ ፍቅሬንም አላስተዋልሽ፣
ስጦታዬን አልተቀበልሽ፣
ግዛቴንም ከቶ አልፈለግሽ፣
እንዲሁ ብቻ ዝም ብለሽ
እኔን ጥለሽ መናኒ ሆንሽ።
ሁሉን ባደርግ ብሰጥሽም፣
አንቺን አንቺ ካደረገሽ
ከፈጣሪስ አልወስድሽም።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
❤43👍4
የነፍሴን ጫጫታ፤
የዉስጤን ግርታ፤
በቃላት ሰድሬ፤
ሐረግ አዋቅሬ፤
ሰ ር ዤ፤
ደ ል ዤ፤
ስሜቴን አርቅቄ፤
ሀሳቤን ጨምቄ፤
ጭንቀቴን ጠፍፌ፤
በወረቀት ፅፌ፤
ጨምድጄ፤
ቀድጄ፤
ክብሪቱን፤
ለኮስኩት፤
በእሳት፤
አ ነ ደ ድ ኩ ት፤
በአመድ በጭሱ፤
ህይወቴን አየሁት።
[ ዔደን ታደሰ ]
@topazionnn
@getem
@getem
የዉስጤን ግርታ፤
በቃላት ሰድሬ፤
ሐረግ አዋቅሬ፤
ሰ ር ዤ፤
ደ ል ዤ፤
ስሜቴን አርቅቄ፤
ሀሳቤን ጨምቄ፤
ጭንቀቴን ጠፍፌ፤
በወረቀት ፅፌ፤
ጨምድጄ፤
ቀድጄ፤
ክብሪቱን፤
ለኮስኩት፤
በእሳት፤
አ ነ ደ ድ ኩ ት፤
በአመድ በጭሱ፤
ህይወቴን አየሁት።
[ ዔደን ታደሰ ]
@topazionnn
@getem
@getem
❤31🔥22👍10
ቤተሰብ ሳልጦር
ፈርቼ እያደርኩ ኑሮን እንደጦር
እንኳን ለሌላው ሳልሆነ ለራሴ
ልክ እንደ ሙሴ
በምድረ በዳ
ነፍሴን ሳልሸክፍ ሳልሰናዳ
ባዲስ መቃብር ገላዬን ሳልከት
ዐይመጣም ቀኔ ነፍቶ መለከት
ብቁ መሆኔን ሳይመለከት።
መች እበቃለሁ?
ይህንን መኖር
እንደምሰፋው ጠንቅቄ አውቃለሁ።
ውጊያ ሳልገጥም ወይ ጦር ሳያምረኝ
በብርሃን ጣቶች ሳይመረምረኝ
ለምን አመጣኝ ምን ሊያስጀምረኝ?
በማያገባኝ ፍልሚያ ደክሜ
ያልቆሰልኩትን ህመም አክሜ
ድል ላላጣጥም
ሰው...
ተዋጋሁ አይልም ቀኑን ሳይገጥም።
በአንዳች አዚም ኮከብ ሳልገትር
ታምር ሳልሠራ በትንሽ በትር
ከሕይወት መዳፍ ሳላነብ እጣ
የኔውስ ነገ ባሻው ቀን ይምጣ!
ይመጣል ያሉት የታለ ታዲያ
አልጠብቀውም ከንግዲህ ወዲያ።
By Yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
ፈርቼ እያደርኩ ኑሮን እንደጦር
እንኳን ለሌላው ሳልሆነ ለራሴ
ልክ እንደ ሙሴ
በምድረ በዳ
ነፍሴን ሳልሸክፍ ሳልሰናዳ
ባዲስ መቃብር ገላዬን ሳልከት
ዐይመጣም ቀኔ ነፍቶ መለከት
ብቁ መሆኔን ሳይመለከት።
መች እበቃለሁ?
ይህንን መኖር
እንደምሰፋው ጠንቅቄ አውቃለሁ።
ውጊያ ሳልገጥም ወይ ጦር ሳያምረኝ
በብርሃን ጣቶች ሳይመረምረኝ
ለምን አመጣኝ ምን ሊያስጀምረኝ?
በማያገባኝ ፍልሚያ ደክሜ
ያልቆሰልኩትን ህመም አክሜ
ድል ላላጣጥም
ሰው...
ተዋጋሁ አይልም ቀኑን ሳይገጥም።
በአንዳች አዚም ኮከብ ሳልገትር
ታምር ሳልሠራ በትንሽ በትር
ከሕይወት መዳፍ ሳላነብ እጣ
የኔውስ ነገ ባሻው ቀን ይምጣ!
ይመጣል ያሉት የታለ ታዲያ
አልጠብቀውም ከንግዲህ ወዲያ።
By Yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
❤36👍3🔥2🎉1
~ቅፅበት~
ሩቅ ይመስላል እንጂ ጣሪያው ገመገሙ፤
የመሞት ሰመመን ቅርብ ነው ህመሙ፤
ስንዘር አትሄድም ከመኖር ለመውጣት፤
አንድ ክንድ አይርቅም መሞትን ለማምጣት፤
መኖር | አለመኖር
አለመኖር | መኖር
አሁን እያየሁት እየሳቀ ፊቱ፤
አሁን ዳመነና አለፈች ህይወቱ፤
አይቻታለሁኝ ትላንትና ወዲያ ገበያ ወጥታለች፤
ነፍስ ሩህ የላትም ዛሬ ግን ሞታለች፤
አሁን በቀደም'ለት ዘይሬው ነበረ፤
መገን የዱንያ ሰው ትላንት ተቀበረ፤
መኖር | አለመኖር
አለመኖር | መኖር
አቤት መልኳ ሲምር ስታሳሳ ብታይ፤
አሁን አፈር ለብሳ ሬሳ ሆነች ብካይ፤
ያ ጀግና ደንዳና ፈረጣማ ወጣቱ፤
ሞት ልግጠምህ ሲለው መች ቻለ ጉልበቱ፤
ሞሳ ህፃን ነበር ተስፋ የታጨቀ፤
የታዘዘም አይቀርም ህልሙን ተነጠቀ፤
መኖር | አለመኖር
አለመኖር | መኖር
አሁን ይሄን ስፅፍ በህይወት መኖሬ ባያጠያይቅም፣
አሁን ስታነቡት መኖሬን አላውቅም፤
ድንገት መጥቶ ጥርቅም!
By @Lawyerpoetry
@getem
@getem
@getem
ሩቅ ይመስላል እንጂ ጣሪያው ገመገሙ፤
የመሞት ሰመመን ቅርብ ነው ህመሙ፤
ስንዘር አትሄድም ከመኖር ለመውጣት፤
አንድ ክንድ አይርቅም መሞትን ለማምጣት፤
መኖር | አለመኖር
አለመኖር | መኖር
አሁን እያየሁት እየሳቀ ፊቱ፤
አሁን ዳመነና አለፈች ህይወቱ፤
አይቻታለሁኝ ትላንትና ወዲያ ገበያ ወጥታለች፤
ነፍስ ሩህ የላትም ዛሬ ግን ሞታለች፤
አሁን በቀደም'ለት ዘይሬው ነበረ፤
መገን የዱንያ ሰው ትላንት ተቀበረ፤
መኖር | አለመኖር
አለመኖር | መኖር
አቤት መልኳ ሲምር ስታሳሳ ብታይ፤
አሁን አፈር ለብሳ ሬሳ ሆነች ብካይ፤
ያ ጀግና ደንዳና ፈረጣማ ወጣቱ፤
ሞት ልግጠምህ ሲለው መች ቻለ ጉልበቱ፤
ሞሳ ህፃን ነበር ተስፋ የታጨቀ፤
የታዘዘም አይቀርም ህልሙን ተነጠቀ፤
መኖር | አለመኖር
አለመኖር | መኖር
አሁን ይሄን ስፅፍ በህይወት መኖሬ ባያጠያይቅም፣
አሁን ስታነቡት መኖሬን አላውቅም፤
ድንገት መጥቶ ጥርቅም!
By @Lawyerpoetry
@getem
@getem
@getem
❤52🔥10🤩3👍1😱1😢1
ስዕሉን አይለኩት
///////////////////
መመዘኛው መልኬ
ሚዛኑን ባይደፋም
የቁንጅናን መስፈርት
ከቶ ባላሟላም
የውስጤ ውብነት
ፊቴ ላይ ባይኖርም
ከነገሮች በፊት
እኔ ባልፈጠርኩት መልክ ብመዘንም
አለባበስ ጌጤ
ለእይታ ባይስቡም
ጎደለብኝ ብዬ
እራሴን አልጠላም
አለም ሸቀጥ አርጎት
መልኮች ቢመለኩም
በአካል ሙላት ጉድለት
ንግዱን ቢነግድም
የሰውነት ሚዛን
አይን ብቻ አይደለም
ሰውነት ለገባው
ማጣት ነው ማግኘት ነው
ብዙ ትርጉም አለው
እስኪ እናስበው
በብሩህ ሸራ ላይ
የሰአሊው ስዕል
ለእይታ ቀርቦ
በብዙ ሰው መሃል
ቢያዩት ጥበቡን
የሳለውን ስዕል
ከውዳሴ አንስቶ
በትችት ቢጥሉት
እነዚ ቃላቶች
ሰዓሊውን እንጂ ስዕሉን አይለኩት
@abela_black
@getem
@getem
@getem
///////////////////
መመዘኛው መልኬ
ሚዛኑን ባይደፋም
የቁንጅናን መስፈርት
ከቶ ባላሟላም
የውስጤ ውብነት
ፊቴ ላይ ባይኖርም
ከነገሮች በፊት
እኔ ባልፈጠርኩት መልክ ብመዘንም
አለባበስ ጌጤ
ለእይታ ባይስቡም
ጎደለብኝ ብዬ
እራሴን አልጠላም
አለም ሸቀጥ አርጎት
መልኮች ቢመለኩም
በአካል ሙላት ጉድለት
ንግዱን ቢነግድም
የሰውነት ሚዛን
አይን ብቻ አይደለም
ሰውነት ለገባው
ማጣት ነው ማግኘት ነው
ብዙ ትርጉም አለው
እስኪ እናስበው
በብሩህ ሸራ ላይ
የሰአሊው ስዕል
ለእይታ ቀርቦ
በብዙ ሰው መሃል
ቢያዩት ጥበቡን
የሳለውን ስዕል
ከውዳሴ አንስቶ
በትችት ቢጥሉት
እነዚ ቃላቶች
ሰዓሊውን እንጂ ስዕሉን አይለኩት
@abela_black
@getem
@getem
@getem
❤43🔥9
ርእስ አጣን....
ዘማች ፈልገን ~ ቀምረን ደርሰን
ሆሄ ፊደላት ~ ቃላት አስሰን
እያሰባጠርን ~ እየፈጣጠርን
በስንኝ በአንጓ ~ አጥር እያጠርን......
ሀሳቡን ጨምቀን ~ ቀርቦ ወረቀት
በደማቅ ፅሁፍ ~ አስፍረንበት
ብዙ ተጨንቀን ~ እንዴትም ብለን
'በጎ' ን አንስተን ~ መጥፎውን ጥለን.....
ቤቱን መተነው ~ ፍሰቱ አምሮልን
ሁሉ መልክ ይዞ ~ ሁሉ ሰምሮልን.....
ግን፤
በእውቀት መጀነን ~ ጥበብ አሳጣን
ለግጥማችንም ~ ርእስ አጣን
By @Weyblann
@getem
@getem
@getem
ዘማች ፈልገን ~ ቀምረን ደርሰን
ሆሄ ፊደላት ~ ቃላት አስሰን
እያሰባጠርን ~ እየፈጣጠርን
በስንኝ በአንጓ ~ አጥር እያጠርን......
ሀሳቡን ጨምቀን ~ ቀርቦ ወረቀት
በደማቅ ፅሁፍ ~ አስፍረንበት
ብዙ ተጨንቀን ~ እንዴትም ብለን
'በጎ' ን አንስተን ~ መጥፎውን ጥለን.....
ቤቱን መተነው ~ ፍሰቱ አምሮልን
ሁሉ መልክ ይዞ ~ ሁሉ ሰምሮልን.....
ግን፤
በእውቀት መጀነን ~ ጥበብ አሳጣን
ለግጥማችንም ~ ርእስ አጣን
By @Weyblann
@getem
@getem
@getem
❤39👍7🔥4
ተወለድ በልቤ
/////////////////
በእስራኤል መንደር
ሕዝብ ሁሉ ሲቆጠር፣
ክርስቶስን አቅፋ ዬሴፍ ወሰሎሜ
ሄዱ ከድንግል ጋር።
ፈጣሪ አለማት
ከሀጢያት መዝገብ ላይ
ስሜን ሊፍቅልኝ፣
እንደተወለደ፣
እኔን መፃፊያ ላይ
እሱ ተፃፈልኝ።
ግና ምንያረጋል፣
አመፀኛው ልቤ
ሄሮድስን ይመስል፣
ያሳድደው ጀመር
ፈጣሪ ነው ሳይል።
ክርስቶስ ሲያንኳኳ
ሲጠራኝ በስሜ፣
የማርያምን ብቅል
እየፈጨሁ መልሴ፣
አንድ አንዴም ጨክኖ
ስስታሙ ልቤ፣
ለአምላክ ቦታ ጠፍቶት
ይህ ነብሴን አስርቤ።
ልቤን ቢለምነኝ
እግዜር ይስጥልኝ አልኩ፣
ሰጪው እንዳይገባ
ስንቴ ተከላከልኩ፣
በልደቱ እለት፣
ባይገባኝም እንኳን እንዳላሸበሸብኩ፣
ነግቶ መሸ ሲባል
በሀጢያት ፍቅር ወደኩ።
ተወለድክ ይሉኛል
አዎን አምኛለው፣
የኔን መወለድ ግን እጠራጠራለው፣
ተወለድ ልቤ ውስጥ
ያንስሀል አውቃለው፣
ትሁቱ አምላኬ
ሰው ንቀህ ማተወው፣
ሳልከፍትልህ ግባ
ላይህ እወዳለው፣
ጥቂት እንኳን ሳልኖር
ሞቼ መምጣቴ ነው።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
/////////////////
በእስራኤል መንደር
ሕዝብ ሁሉ ሲቆጠር፣
ክርስቶስን አቅፋ ዬሴፍ ወሰሎሜ
ሄዱ ከድንግል ጋር።
ፈጣሪ አለማት
ከሀጢያት መዝገብ ላይ
ስሜን ሊፍቅልኝ፣
እንደተወለደ፣
እኔን መፃፊያ ላይ
እሱ ተፃፈልኝ።
ግና ምንያረጋል፣
አመፀኛው ልቤ
ሄሮድስን ይመስል፣
ያሳድደው ጀመር
ፈጣሪ ነው ሳይል።
ክርስቶስ ሲያንኳኳ
ሲጠራኝ በስሜ፣
የማርያምን ብቅል
እየፈጨሁ መልሴ፣
አንድ አንዴም ጨክኖ
ስስታሙ ልቤ፣
ለአምላክ ቦታ ጠፍቶት
ይህ ነብሴን አስርቤ።
ልቤን ቢለምነኝ
እግዜር ይስጥልኝ አልኩ፣
ሰጪው እንዳይገባ
ስንቴ ተከላከልኩ፣
በልደቱ እለት፣
ባይገባኝም እንኳን እንዳላሸበሸብኩ፣
ነግቶ መሸ ሲባል
በሀጢያት ፍቅር ወደኩ።
ተወለድክ ይሉኛል
አዎን አምኛለው፣
የኔን መወለድ ግን እጠራጠራለው፣
ተወለድ ልቤ ውስጥ
ያንስሀል አውቃለው፣
ትሁቱ አምላኬ
ሰው ንቀህ ማተወው፣
ሳልከፍትልህ ግባ
ላይህ እወዳለው፣
ጥቂት እንኳን ሳልኖር
ሞቼ መምጣቴ ነው።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
❤52
የኤል ነገር ድንቁ
ስራው እንግዳ ነው ፡ ለሀሳብ መርቀቁ
እሳት ሆኖ ሳለ
በከብቶች እስትፋንስ ፡ በፍጡር መሞቁ
ለነፍሳችን መዳን ፡ እኛን ደጅ ጠና
ሰው ዝንጉ ነውና
እንደ ሰው ተማረ ፡ እንደ ሰው አጠና
ከሃሊ ነውና
ማዕበል አቆመ ፡ ውሃው ታዞ ፀና
እንደ በኒ አደም በጥቂቱ አደገ
እንደ አምላክነቱ . .
ከሞት ሰው አስነሳ ህይወቱን ታደገ
ለአንድ ምስኪን በጉ ከሰማይ ወረደ
ሊያስጠጋን ከክብሩ በእኛው ተዋረደ
ሰማይን አስፍቶ
ምድርን ያዋቀረ ለፍቅር ዝቅ አለ !
ሁሉን የሚችለው
እንደማይችል ሁሉ ወዶ ተሰቀለ
የኤልሻዳይ መዳፍ በችንካር ቆሰለ !
የማዕዘን ድንጋይ
የነቢያት ትንቢት መርስኤ-መከራ
ስትወለድ ጊዜ የፈራንው ፈራ
by @sidrak_the_poet
@getem
@getem
@getem
ስራው እንግዳ ነው ፡ ለሀሳብ መርቀቁ
እሳት ሆኖ ሳለ
በከብቶች እስትፋንስ ፡ በፍጡር መሞቁ
ለነፍሳችን መዳን ፡ እኛን ደጅ ጠና
ሰው ዝንጉ ነውና
እንደ ሰው ተማረ ፡ እንደ ሰው አጠና
ከሃሊ ነውና
ማዕበል አቆመ ፡ ውሃው ታዞ ፀና
እንደ በኒ አደም በጥቂቱ አደገ
እንደ አምላክነቱ . .
ከሞት ሰው አስነሳ ህይወቱን ታደገ
ለአንድ ምስኪን በጉ ከሰማይ ወረደ
ሊያስጠጋን ከክብሩ በእኛው ተዋረደ
ሰማይን አስፍቶ
ምድርን ያዋቀረ ለፍቅር ዝቅ አለ !
ሁሉን የሚችለው
እንደማይችል ሁሉ ወዶ ተሰቀለ
የኤልሻዳይ መዳፍ በችንካር ቆሰለ !
የማዕዘን ድንጋይ
የነቢያት ትንቢት መርስኤ-መከራ
ስትወለድ ጊዜ የፈራንው ፈራ
by @sidrak_the_poet
@getem
@getem
@getem
❤39🔥6🤩2👍1
ሞተ
/////
መድረሻው ይሆናል
ያሉት ቦታ ሁሉ፣
አካለው አካለው
እኔን ሲፈልጉ።
ዱር አንበሳ አልቀረ
አዞ ሆድ ውስጥ አዩኝ፣
በሰማይ በምድር
ባህር ውስጥ ፈለጉኝ፣
ፈለጉኝ ፈለጉኝ
ግንስ አላገኙኝ፣
ሰማይ ቤት ይሆናል
ሞቶ ይሆናል አሉኝ።
እንዴት ያገኙኛል
ሰማይ ቢቧጥጡ ፣
ምድርን ቆፍረው
አካሏን ቢያወጡ፣
ውቅያኖስ ወይ ባህር
ቢወርዱ ከስምጡ።
የተረሳ አካል
ከቦታው የታጣ፣
ካንቺ ልብ ገብቼ
በየት በኩል ልውጣ፣
እንዴት ይገምቱ
ማንስ አውቆት ይምጣ።
ባንቺ ተሸፍኜ
እንዴትስ ያግኙኝ፣
ውስጥሽ ተሰውሬ
ሞተ እኮ ተባልኩኝ።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
/////
መድረሻው ይሆናል
ያሉት ቦታ ሁሉ፣
አካለው አካለው
እኔን ሲፈልጉ።
ዱር አንበሳ አልቀረ
አዞ ሆድ ውስጥ አዩኝ፣
በሰማይ በምድር
ባህር ውስጥ ፈለጉኝ፣
ፈለጉኝ ፈለጉኝ
ግንስ አላገኙኝ፣
ሰማይ ቤት ይሆናል
ሞቶ ይሆናል አሉኝ።
እንዴት ያገኙኛል
ሰማይ ቢቧጥጡ ፣
ምድርን ቆፍረው
አካሏን ቢያወጡ፣
ውቅያኖስ ወይ ባህር
ቢወርዱ ከስምጡ።
የተረሳ አካል
ከቦታው የታጣ፣
ካንቺ ልብ ገብቼ
በየት በኩል ልውጣ፣
እንዴት ይገምቱ
ማንስ አውቆት ይምጣ።
ባንቺ ተሸፍኜ
እንዴትስ ያግኙኝ፣
ውስጥሽ ተሰውሬ
ሞተ እኮ ተባልኩኝ።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
❤34👍3👎2😱1