ጥበብ
//////////////////////////
የቆሰለች ጉድፍ ነብሴን፣
አውሬ የሆነች ማንነቴን።
አንቺ ቀርበሽ አላመድሻት፣
በመዳበስ ዝም አስባልሻት።
የኔ ሂሶጵ
ከጉድፌ ያነፃሽኝ፣
ዘማዊ ነህ
ብለሽ እንክዋን ያልገፋሽኝ፣
አንቺን ላጠምድ
ልሰርቅሽ ስል የሰረቅሽኝ፣
ሌባ ስሆን
ዘብ ጠባቂሽ ያደረግሽኝ፣
ከሺ እንዳልሄድኩ
ካንቺ እንዳልርቅ ያለገመድ የጠለፍሽኝ።
ቃልሽ አስማት
እጅሽ ደግሞ የአስማት በትር፣
ከነካሽኝ ተቀይሬ
ካንቺ ስር ነው እኔ ማድር።
ያንቺስ ይገርማል፣
ሰለሞንስ ያውቀው ይሆን
ይህን ጥበብ፣
በነካው ሰው
መጠበቅን ወይ መከበብ።
በታሪክስ ይኖር ይሆን
ቁርጥ አንቺን የመሰለ፣
ተቅበዝባዥን በማላመድ
ከቤቱ ስር ሰው ያዋለ።
እሷ
ያጠመደች እኔን አሳ፣
ያለመረብ በዳበሳ።
የያዘችኝ እኔን እሳት፣
ያለውሃ በእጅዋ ብልሃት።
እኔም ብሄድ ዞሬ ከስዋ፣
ይሄ ልቤ ፍቅር አይረሳ።
ማን አስተማራት ይህን ጥበብ፣
በዝምታ ዳብሳ
አገኘች የኔን ልብ፣
ማን አስተማራት?
ማን አስተማረሽ?
ማን?
@abela_black
@getem
@getem
@getem
//////////////////////////
የቆሰለች ጉድፍ ነብሴን፣
አውሬ የሆነች ማንነቴን።
አንቺ ቀርበሽ አላመድሻት፣
በመዳበስ ዝም አስባልሻት።
የኔ ሂሶጵ
ከጉድፌ ያነፃሽኝ፣
ዘማዊ ነህ
ብለሽ እንክዋን ያልገፋሽኝ፣
አንቺን ላጠምድ
ልሰርቅሽ ስል የሰረቅሽኝ፣
ሌባ ስሆን
ዘብ ጠባቂሽ ያደረግሽኝ፣
ከሺ እንዳልሄድኩ
ካንቺ እንዳልርቅ ያለገመድ የጠለፍሽኝ።
ቃልሽ አስማት
እጅሽ ደግሞ የአስማት በትር፣
ከነካሽኝ ተቀይሬ
ካንቺ ስር ነው እኔ ማድር።
ያንቺስ ይገርማል፣
ሰለሞንስ ያውቀው ይሆን
ይህን ጥበብ፣
በነካው ሰው
መጠበቅን ወይ መከበብ።
በታሪክስ ይኖር ይሆን
ቁርጥ አንቺን የመሰለ፣
ተቅበዝባዥን በማላመድ
ከቤቱ ስር ሰው ያዋለ።
እሷ
ያጠመደች እኔን አሳ፣
ያለመረብ በዳበሳ።
የያዘችኝ እኔን እሳት፣
ያለውሃ በእጅዋ ብልሃት።
እኔም ብሄድ ዞሬ ከስዋ፣
ይሄ ልቤ ፍቅር አይረሳ።
ማን አስተማራት ይህን ጥበብ፣
በዝምታ ዳብሳ
አገኘች የኔን ልብ፣
ማን አስተማራት?
ማን አስተማረሽ?
ማን?
@abela_black
@getem
@getem
@getem
❤29👍3🔥1
እኔ
ባይተዋር
የእፍታ ብናኝ
በየሄድኩበት ዕምባ ሚቀናኝ፤
በዬጥላው ስር የምሰባበር
ያለ በረሃ የማላውቅ ሀገር፤
ከቁር ከሐሩር የተወዳጀሁ
ገና ሽል ሳለሁ ኑሬ ያረጀሁ፤
ድስቴ
ምጣዴ ያልተሟሸልኝ ፤
ከማማጥ በቀር
ወልዶ መደሰት የማይኾንልኝ፤
-
እኔ
ባይተዋር
የዕጣ ፍርደኛ
ለጊዜ በደል የሌለኝ ዳኛ፤
የጊዜ ንጉስ
ያለገላጋይ የሚበድለኝ
ከማደግ በቀር ጥላት የሌለኝ፤
ልክ እንደ ብናኝ
ያነስኩ የሳሳሁ
ስበርር የምኖር እየተገፋሁ፤
ድንገት ተነስቶ ሰው የሚርበኝ
በየትከሻው ማልቀስ የሚያምረኝ፤
በየትከሻው ጎጆ የሰራሁ
ከሰው የምኖር ሰው እየፈራሁ፤
-
እኔ
ባይተዋር
የምርጫ ጌታ፤
ሀገሬ ማዶ
ከጉም ኮረብታ፤
ለብሶ የሚኖር የጭጋግ ኩታ፤
ዘሬ መከራ
አድባሬ ዋይታ
የማይሞላልኝ ሳስር ስፈታ ፤
አባቴ ለቅሶ
እናቴ ለቅሶ
ሕይወት ያቆመኝ ያለ ምሶሶ፤
ቢገልጡኝ ቁስል
ቢነኩኝ ቁስል
ቶሎ ሚደክመኝ ገና አረፍኩኝ ስል፤
-
እኔ
ባይተዋር
ፎካሪ ሽፍታ
ጫካ የማድር ድቤ ስመታ ፤
ሐዘኔን ትቼ የማልሰደድ
ያለ በረሃ ሀገር የማልለምድ ፤
እንጀራዬ ዕውር
ወጤ ደንቆሮ
ሳለቅስ የምውል ግዋሮ ለግዋሮ፤
እኔ
ባይተዋር
የድብርት ራት
ከወዳጅ በቀር የሌለኝ ጥላት።
By Tewodros kassa
@getem
@getem
@paappii
ባይተዋር
የእፍታ ብናኝ
በየሄድኩበት ዕምባ ሚቀናኝ፤
በዬጥላው ስር የምሰባበር
ያለ በረሃ የማላውቅ ሀገር፤
ከቁር ከሐሩር የተወዳጀሁ
ገና ሽል ሳለሁ ኑሬ ያረጀሁ፤
ድስቴ
ምጣዴ ያልተሟሸልኝ ፤
ከማማጥ በቀር
ወልዶ መደሰት የማይኾንልኝ፤
-
እኔ
ባይተዋር
የዕጣ ፍርደኛ
ለጊዜ በደል የሌለኝ ዳኛ፤
የጊዜ ንጉስ
ያለገላጋይ የሚበድለኝ
ከማደግ በቀር ጥላት የሌለኝ፤
ልክ እንደ ብናኝ
ያነስኩ የሳሳሁ
ስበርር የምኖር እየተገፋሁ፤
ድንገት ተነስቶ ሰው የሚርበኝ
በየትከሻው ማልቀስ የሚያምረኝ፤
በየትከሻው ጎጆ የሰራሁ
ከሰው የምኖር ሰው እየፈራሁ፤
-
እኔ
ባይተዋር
የምርጫ ጌታ፤
ሀገሬ ማዶ
ከጉም ኮረብታ፤
ለብሶ የሚኖር የጭጋግ ኩታ፤
ዘሬ መከራ
አድባሬ ዋይታ
የማይሞላልኝ ሳስር ስፈታ ፤
አባቴ ለቅሶ
እናቴ ለቅሶ
ሕይወት ያቆመኝ ያለ ምሶሶ፤
ቢገልጡኝ ቁስል
ቢነኩኝ ቁስል
ቶሎ ሚደክመኝ ገና አረፍኩኝ ስል፤
-
እኔ
ባይተዋር
ፎካሪ ሽፍታ
ጫካ የማድር ድቤ ስመታ ፤
ሐዘኔን ትቼ የማልሰደድ
ያለ በረሃ ሀገር የማልለምድ ፤
እንጀራዬ ዕውር
ወጤ ደንቆሮ
ሳለቅስ የምውል ግዋሮ ለግዋሮ፤
እኔ
ባይተዋር
የድብርት ራት
ከወዳጅ በቀር የሌለኝ ጥላት።
By Tewodros kassa
@getem
@getem
@paappii
❤60😢16🔥9
'ደሀ አይደለሽም!'
~~~~~
ተወጣጠርሽ አሉ
ቆዳሽ እስኪጠብሽ
ተመፃደቅሽ አሉ
መልክሽ እስኪበልጥሽ፤
ደግሞም ብለሽ ብለሽ
ንቀት ጀመርሽ አሉ ትናንትን ረስተሽ፣
ዛሬን ብትጎብዢ
በሰው 'ሰው' ብትሆኚ ሰውነትን ትተሽ!
~~~~
የሆነውስ ሆኖ
ወቃሽ ተቺሽ በዝቶ
ብንጠላሽም እኛ፣
ማድረግሽ አይቀርም
በገንዘብ በሀብትሽ
እኛኑ ዘበኛ፤
እሱ አልበቃ ብሎም
በአሽሙር በሀሜት
ወጋ ቢያደርጉሽም፣
ይፈሩሻልና
ፊትለፊትሽ መጥተው
አይናገሩሽም.....
ም
ክ
ን
ያ
ቱ
ም
ደሀ አይደለሽም!!!!!!!!
By @Weyblann ያቡ
@getem
@getem
@getem
~~~~~
ተወጣጠ
ቆዳሽ እስኪጠብሽ
ተመፃደቅሽ አሉ
መልክሽ እስኪበልጥሽ፤
ደግሞም ብለሽ ብለሽ
ንቀት ጀመርሽ አሉ ትናንትን ረስተሽ፣
ዛሬን ብትጎብዢ
በሰው 'ሰው' ብትሆኚ ሰውነትን ትተሽ!
~~~~
ወቃሽ ተቺሽ በዝቶ
ብንጠላሽም እኛ፣
ማድረግሽ አይቀርም
በገንዘብ በሀብትሽ
እኛኑ ዘበኛ፤
እሱ አልበቃ ብሎም
በአሽሙር በሀሜት
ወጋ ቢያደርጉሽም፣
ይፈሩሻልና
ፊትለፊትሽ መጥተው
አይናገሩሽም.....
ም
ክ
ን
ያ
ቱ
ም
ደሀ አይደለሽም!!!!!!!!
By @Weyblann ያቡ
@getem
@getem
@getem
❤75🔥19👍12😢3😱1
ዉርደት እና ኩነት
እንደአካሄዳቸው
በመንታ መንገድ ላይ
ፍቱን ታዳኝ ናቸው...
አንዱ በጋለው ናስ
ከሰል ይደርባል...
ሌላኛል ሲደላው...
ደርቦ ሲሞቀው
ውስጥ ውስጡን ይቀልጣል
ውጪው እንደከሰል
ጠቁሮ ሳያበቃ...
ከማገዶው ገደል...
ከፍሙ ስር ያድራል
ሊነቃ ይልና....
..................
በዘብ ጣሩ ዘልቆ
ፍሙ ለገረፈው...
አንድ ጥያቄ አለው...
..........................
ማጀት ባልጠፋበት
ምቾት ሀገር ሆኖ
ከተድላው ሰመመን
በደን ስንከራተት....
እሳቱ ሳይነካኝ ፍሙ ስር ተኝቼ
ባድር ምን አለበት??...
በኢያሱ ከበደ
ታህሳስ 7, 2018 ዓ.ም
@getem
@getem
@paappii
እንደአካሄዳቸው
በመንታ መንገድ ላይ
ፍቱን ታዳኝ ናቸው...
አንዱ በጋለው ናስ
ከሰል ይደርባል...
ሌላኛል ሲደላው...
ደርቦ ሲሞቀው
ውስጥ ውስጡን ይቀልጣል
ውጪው እንደከሰል
ጠቁሮ ሳያበቃ...
ከማገዶው ገደል...
ከፍሙ ስር ያድራል
ሊነቃ ይልና....
..................
በዘብ ጣሩ ዘልቆ
ፍሙ ለገረፈው...
አንድ ጥያቄ አለው...
..........................
ማጀት ባልጠፋበት
ምቾት ሀገር ሆኖ
ከተድላው ሰመመን
በደን ስንከራተት....
እሳቱ ሳይነካኝ ፍሙ ስር ተኝቼ
ባድር ምን አለበት??...
በኢያሱ ከበደ
ታህሳስ 7, 2018 ዓ.ም
@getem
@getem
@paappii
❤27🔥5👍1🤩1
ነጠብጣብ ሀሳቦች
(በእውቀቱ ስዩም)
በዘመን አየር ፤ ጫጫታው ከብሮ
በጩኸት መሀል፤ ዜማ ተቀብሮ
ጆሮ ግንባር ላይ፥ ቤቱን ለመስራት
እንዳልፈለገ
ወደ ማጅራት
አፈገፈገ::
****
የሞሰቡን ወግ፥ ፌስታሉ ወርሶት
ለምለሙ እንጀራ ፥ ረድኤት አንሶት
ቢጎርሱት እንባ ፥ ቢውጡት ብሶት !
****
ምንገዱ ሁሉ ፥የሚያሰናክል
ቁልቁለት ሲያዝል ፥ የዳገት ያክል
ስኬት በስኒ፥ ላባችን በጋን
በወግ ለመሞት ሁሌ እየተጋን
መኖር ዘነጋን::
By Bewuketu seyum
@getem
@getem
@paappii
(በእውቀቱ ስዩም)
በዘመን አየር ፤ ጫጫታው ከብሮ
በጩኸት መሀል፤ ዜማ ተቀብሮ
ጆሮ ግንባር ላይ፥ ቤቱን ለመስራት
እንዳልፈለገ
ወደ ማጅራት
አፈገፈገ::
****
የሞሰቡን ወግ፥ ፌስታሉ ወርሶት
ለምለሙ እንጀራ ፥ ረድኤት አንሶት
ቢጎርሱት እንባ ፥ ቢውጡት ብሶት !
****
ምንገዱ ሁሉ ፥የሚያሰናክል
ቁልቁለት ሲያዝል ፥ የዳገት ያክል
ስኬት በስኒ፥ ላባችን በጋን
በወግ ለመሞት ሁሌ እየተጋን
መኖር ዘነጋን::
By Bewuketu seyum
@getem
@getem
@paappii
❤75🔥6👍5🤩4
ባልጀራዬ ላልኩት ሚስጥር ብዬ ብነግረዉ ፤
እሱም ለባልንጀራዉ አትንገር ብሎ ነገረዉ፤
ሲቀንስና ሲጨምር ለራሱ እንደተመቸዉ፤
ዞረ ዞረና ሚስጥሬ እኔ ጋር ደርሶ አረፈዉ።
[ ዔደን ታደሰ ]
@topazionnn
@getem
@getem
እሱም ለባልንጀራዉ አትንገር ብሎ ነገረዉ፤
ሲቀንስና ሲጨምር ለራሱ እንደተመቸዉ፤
ዞረ ዞረና ሚስጥሬ እኔ ጋር ደርሶ አረፈዉ።
[ ዔደን ታደሰ ]
@topazionnn
@getem
@getem
😁47👍34❤12🤩5
ናፍቆ....
ቦታ ምረጫ ትቶ ሲበላ ከኔውጋ
እረፍት አየነሳ አልተኛ እስኪነጋ
መባነን ልማዴ በሸለብታው መሀል
አምጣልኝ እያለ ናፍቆትሽ ይጮሀል
ሊያይሽ አስቦ በአካል እንድትመጪ
ቢጠራሽ ደመና ጋርዶሻል አትወጪ
ላላለቀው ፍቅር መለየት ለቀጣው
ተሸክሜ ምዞር ከልቤ አላጣው
ግር እንዳለኝ ግራው ለኔ አዘምብሎ
ከአይኔ ሲያውለው ያለፈውን ስሎ
አካላቴ ደክሞ አልታዘዝ ብሎ
የሚያረገው ጠፍቶት በትዝታ ዝሎ
ዛሬም ማዶ ያያል ፀሀይ ብትወጣ
ከተራበሽ ልቤ ይዛሽ እንድትመጣ...።
By #nimo
@getem
@getem
@getem
ቦታ ምረጫ ትቶ ሲበላ ከኔውጋ
እረፍት አየነሳ አልተኛ እስኪነጋ
መባነን ልማዴ በሸለብታው መሀል
አምጣልኝ እያለ ናፍቆትሽ ይጮሀል
ሊያይሽ አስቦ በአካል እንድትመጪ
ቢጠራሽ ደመና ጋርዶሻል አትወጪ
ላላለቀው ፍቅር መለየት ለቀጣው
ተሸክሜ ምዞር ከልቤ አላጣው
ግር እንዳለኝ ግራው ለኔ አዘምብሎ
ከአይኔ ሲያውለው ያለፈውን ስሎ
አካላቴ ደክሞ አልታዘዝ ብሎ
የሚያረገው ጠፍቶት በትዝታ ዝሎ
ዛሬም ማዶ ያያል ፀሀይ ብትወጣ
ከተራበሽ ልቤ ይዛሽ እንድትመጣ...።
By #nimo
@getem
@getem
@getem
❤48👍10🔥3😢3
የፈገግታዬ ጦር
//////////////////
በጥርሴ የገደልኩት
የጠላት ጋጋታ፣
ሶምሶምን ያስንቃል
ቢወዳደር ላፍታ።
የወንጭፍ ውርወራ
የበትር ዱላቸው፣
የቃላት የስድብ
የንቀት ጦራቸው፣
የጠለፈኝ ገመድ
የነሱ እቅዳቸው።
የወደኩኝ ለታ
ያረፈብኝ ትቢያ፣
ቀና አልኩኝ ሲባል
ጠላቴ እንደ አጥቢያ።
ከከፍታ ቆሞ
ዝቅ ብሎ ቢያየኝ፣
በሳቄ ገደልኩት
ገና ቀና እንዳልኩኝ።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
//////////////////
በጥርሴ የገደልኩት
የጠላት ጋጋታ፣
ሶምሶምን ያስንቃል
ቢወዳደር ላፍታ።
የወንጭፍ ውርወራ
የበትር ዱላቸው፣
የቃላት የስድብ
የንቀት ጦራቸው፣
የጠለፈኝ ገመድ
የነሱ እቅዳቸው።
የወደኩኝ ለታ
ያረፈብኝ ትቢያ፣
ቀና አልኩኝ ሲባል
ጠላቴ እንደ አጥቢያ።
ከከፍታ ቆሞ
ዝቅ ብሎ ቢያየኝ፣
በሳቄ ገደልኩት
ገና ቀና እንዳልኩኝ።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
❤45🔥14😁11👍5🤩1
እግዜር ስላንቺ ይፈራኛል
እክለፈለፋለሁ
የመልዓክት ስልኮች
ላንቺ ሲደውሉ
ይወስዱሻል ብዬ
እኔ ሳዋራቸው
ይኮላተፋሉ.....
ይርበተበታሉ....
የማፍቀሬን ስስት
ልኩንም ያውቃሉ
ተላኪ መልዓክት
ከወደቅሽባቸው
የህመም አልጋዎች
መጠው ቢፈልጉም
የቱ ጋር ነው የወደቅሽው
ከእኔ በቀር እንኳ
መልዓክትም አላወቁም
ደብቄሻለሁና
ከእግዜር ጋ አኩኩሉ
ሞትም እኔን ፈርቶ
እግዜሩን ይዋሻሉ
ቢዋሹም ስዋዋል
የሰማይን መሬት
ለእረፍትሽ እንዲሆን
ገነት ታንሳለች
የእቅፌን ሚዛን
የመዘንኩት እንደሆን
ጉሙን አጭጄው
ለወደቅሽበት ትራስ ለማድረግ
ደረት ላለው ልብ
ምን ይሰራል ከቶ ቁስን ማፈላለግ
.....ልክ እንደሰርግ
መልዓክት ይፈሩኛል
ሊጠሩሽ ሲመጡ ሰፈር ሲጠይቁ
የስስቴን መጠን
የማፍቀሬን መጠን
ልኩን ስለሚያውቁ
እግዜር ይፈራኛል
አንቺን በመውድ ውስጥ
እኔ እንዳልወሰድ
ታማ አልጋ ለተኛች
ፍቅረኛ ላለችው
ታስፈራለችና
ሞት የሚሏት መንገድ
ንዴቴ እጥፍ ነው
ያውቁታል ስስቴን
የመንሰፍሰፍ ጦሩ
ያልታዘዙትን ሟች
እንደሚያመጡ ሲያውቁ
መልዓክትም ፈሩ
ለምን...?
ስልኩን ሲደውሉ
አንቺን ጠራው ብለው
እኔን ስለሚጠሩ
ግዕዝ ሙላት
@GEEZ_MULAT
ስለ ሁለቱ የሞቱ ፍቅረኞች መታሰቢያ
@getem
@getem
@getem
እክለፈለፋለሁ
የመልዓክት ስልኮች
ላንቺ ሲደውሉ
ይወስዱሻል ብዬ
እኔ ሳዋራቸው
ይኮላተፋሉ.....
ይርበተበታሉ....
የማፍቀሬን ስስት
ልኩንም ያውቃሉ
ተላኪ መልዓክት
ከወደቅሽባቸው
የህመም አልጋዎች
መጠው ቢፈልጉም
የቱ ጋር ነው የወደቅሽው
ከእኔ በቀር እንኳ
መልዓክትም አላወቁም
ደብቄሻለሁና
ከእግዜር ጋ አኩኩሉ
ሞትም እኔን ፈርቶ
እግዜሩን ይዋሻሉ
ቢዋሹም ስዋዋል
የሰማይን መሬት
ለእረፍትሽ እንዲሆን
ገነት ታንሳለች
የእቅፌን ሚዛን
የመዘንኩት እንደሆን
ጉሙን አጭጄው
ለወደቅሽበት ትራስ ለማድረግ
ደረት ላለው ልብ
ምን ይሰራል ከቶ ቁስን ማፈላለግ
.....ልክ እንደሰርግ
መልዓክት ይፈሩኛል
ሊጠሩሽ ሲመጡ ሰፈር ሲጠይቁ
የስስቴን መጠን
የማፍቀሬን መጠን
ልኩን ስለሚያውቁ
እግዜር ይፈራኛል
አንቺን በመውድ ውስጥ
እኔ እንዳልወሰድ
ታማ አልጋ ለተኛች
ፍቅረኛ ላለችው
ታስፈራለችና
ሞት የሚሏት መንገድ
ንዴቴ እጥፍ ነው
ያውቁታል ስስቴን
የመንሰፍሰፍ ጦሩ
ያልታዘዙትን ሟች
እንደሚያመጡ ሲያውቁ
መልዓክትም ፈሩ
ለምን...?
ስልኩን ሲደውሉ
አንቺን ጠራው ብለው
እኔን ስለሚጠሩ
ግዕዝ ሙላት
@GEEZ_MULAT
@getem
@getem
@getem
❤32👍2👎2
በጅምር የቀረ
////////////////
ከትላንቷ ሚያርቅ
ከነገ ሚያግባባት፣
ከዝሙት አለሟ
አሽሽቶ ሚያርቃት።
ያቺ ዘማዊ ሴት
ትልቅ ግንብ ገነባች፣
ሰራችው ቆለለች
ከትላንት ራቀች፣
የሀጢያት ቡትቶን
አውልቃ እየጣለች።
ከዘመናት በኋላ
መኖርን ስትጀምር፣
ታሪኳን የሚያውቁ፣
የድንጋይዋን ክምር ይገፉባት ጀመር።
ወንጭፋቸው የእሳት
የጠጠር ግርፋት፣
የስሜት ልባቸው
ተመለሺ እያላት።
ሴትነቷ ጎልቶ
ሰውነት ተረስቶ፣
የዝሙት እጃቸው
ካብ ድንጋይ አንስቶ።
ደጋግመው ወገሯት
ደጋግመው ገፉባት ፣
የኔ ያለችው አጥር
እማይሆን ሆነባት፣
ትላንት ከሷ በራፍ
እንሙት እንዳላሏት፣
ትላንት ከሷ ገላ
አንውጣ እንዳላሏት፣
ስንት ቃል ውለታ
እንዋል እንዳላሏት።
በገንዘብ በቁጥር
የገዙትን ገላ፣
በዲናር የያዙት
የሴትነት ወዟ።
አውልቃው ብትወጣ
መኖር ልትጀምር፣
በግንቧ ፍርስራሽ
ከተቷት መቃብር።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
////////////////
ከትላንቷ ሚያርቅ
ከነገ ሚያግባባት፣
ከዝሙት አለሟ
አሽሽቶ ሚያርቃት።
ያቺ ዘማዊ ሴት
ትልቅ ግንብ ገነባች፣
ሰራችው ቆለለች
ከትላንት ራቀች፣
የሀጢያት ቡትቶን
አውልቃ እየጣለች።
ከዘመናት በኋላ
መኖርን ስትጀምር፣
ታሪኳን የሚያውቁ፣
የድንጋይዋን ክምር ይገፉባት ጀመር።
ወንጭፋቸው የእሳት
የጠጠር ግርፋት፣
የስሜት ልባቸው
ተመለሺ እያላት።
ሴትነቷ ጎልቶ
ሰውነት ተረስቶ፣
የዝሙት እጃቸው
ካብ ድንጋይ አንስቶ።
ደጋግመው ወገሯት
ደጋግመው ገፉባት ፣
የኔ ያለችው አጥር
እማይሆን ሆነባት፣
ትላንት ከሷ በራፍ
እንሙት እንዳላሏት፣
ትላንት ከሷ ገላ
አንውጣ እንዳላሏት፣
ስንት ቃል ውለታ
እንዋል እንዳላሏት።
በገንዘብ በቁጥር
የገዙትን ገላ፣
በዲናር የያዙት
የሴትነት ወዟ።
አውልቃው ብትወጣ
መኖር ልትጀምር፣
በግንቧ ፍርስራሽ
ከተቷት መቃብር።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
❤47🔥24👍8🤩2
እሳት
/////////////////
እንደ ከሰል ፍሙ
ንዳድሽ ቃጠሎ፣
ባናገርሽኝ ቁጥር
ንዴቴ አይሎ፣
ጨጓራ ኩላሊት ምን የቀረሽ አለ
ባንቺ ውስጤ ተቃጥሎ።
ከፍምም ፍም አንቺ፣
ምታንገበግቢ የምታስደስቺ ።
ሙቀትሽ ሙቅ አይደል
በጣሙን ያነዳል፣
ማንስ አንቺን ችሎ
ሁሌ ይቃጠላል።
እኔ፣
አንቺን እያፈቀርኩ
ብታፈን ብቃጠል፣
እኔ እየቀለጥኩኝ
አረኩሽ ነበልባል።
ፍቅር ይሉት እሳት
አንቺ የሱ ትኩሳት፣
ንዳድ ከቃጠሎ
አርገውት ልቤን ቤት።
ምድጃ አካሌ ውስጥ
እሳት ሆነሽ አንቺ፣
ፍቅርሽ ውሃ አድርጎ
አዛመደኝ ካንቺ።
አቃጥይ አንድጂኝ
መላ አካሌ እስኪተን፣
የዘነብኩኝ ለታ
እንዳደርግሽ ሰከን።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
/////////////////
እንደ ከሰል ፍሙ
ንዳድሽ ቃጠሎ፣
ባናገርሽኝ ቁጥር
ንዴቴ አይሎ፣
ጨጓራ ኩላሊት ምን የቀረሽ አለ
ባንቺ ውስጤ ተቃጥሎ።
ከፍምም ፍም አንቺ፣
ምታንገበግቢ የምታስደስቺ ።
ሙቀትሽ ሙቅ አይደል
በጣሙን ያነዳል፣
ማንስ አንቺን ችሎ
ሁሌ ይቃጠላል።
እኔ፣
አንቺን እያፈቀርኩ
ብታፈን ብቃጠል፣
እኔ እየቀለጥኩኝ
አረኩሽ ነበልባል።
ፍቅር ይሉት እሳት
አንቺ የሱ ትኩሳት፣
ንዳድ ከቃጠሎ
አርገውት ልቤን ቤት።
ምድጃ አካሌ ውስጥ
እሳት ሆነሽ አንቺ፣
ፍቅርሽ ውሃ አድርጎ
አዛመደኝ ካንቺ።
አቃጥይ አንድጂኝ
መላ አካሌ እስኪተን፣
የዘነብኩኝ ለታ
እንዳደርግሽ ሰከን።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
❤29🔥7👍1
ትንሽ ቦታ _
* * * * * * *
በዚህ ዓመት . . .
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሽ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ብቻ መሰደጃ . . .
ምን-አለበት…?
ለምን-አልባት ብንተውለት…?
ፍጹም መሆን ስለማንችል…
ትንሽ ባዶ እንዋዋል
በልባችን ደግ በኩል
ለአንጎላችን መላወሻ - ትንሽ ቦታ እንተውለት
“ምን-አልባት” የምንልበት…!
ልክ እንደ አምና ለዚህ ዓመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰሪያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ
ጥግ ድረስ የለም ስራ
ጥግ ድረስ የለም ፋታ
በልባችን ደግ በኩል
እንፈልግ ባዶ ቦታ
የጳጉሜ ዓይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለዋወጫ
* * * * * * * * * * * *
By ነቢይ መኮንን
@getem
@getem
@paappii
* * * * * * *
በዚህ ዓመት . . .
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሽ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ብቻ መሰደጃ . . .
ምን-አለበት…?
ለምን-አልባት ብንተውለት…?
ፍጹም መሆን ስለማንችል…
ትንሽ ባዶ እንዋዋል
በልባችን ደግ በኩል
ለአንጎላችን መላወሻ - ትንሽ ቦታ እንተውለት
“ምን-አልባት” የምንልበት…!
ልክ እንደ አምና ለዚህ ዓመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰሪያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ
ጥግ ድረስ የለም ስራ
ጥግ ድረስ የለም ፋታ
በልባችን ደግ በኩል
እንፈልግ ባዶ ቦታ
የጳጉሜ ዓይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለዋወጫ
* * * * * * * * * * * *
By ነቢይ መኮንን
@getem
@getem
@paappii
❤53👍11🔥6
ምርጫ
////////
ሺ ገዳይ ነሽ አሉ
ባንቺ የታለሉ፣
ካንቺ እየደረሱ
ስንቶች ስንቴ ማሉ።
እግዜር በእጁ ጭሯት
ተወርዋሪ ኮከብ፣
ጭራዋን አርዝማ
ምትዞር በወንዶች ልብ።
ዘብ አዳኝ በፍቅሯ
ስንቱ ከሷ ደርሶ ጠባቂ እየሆናት፣
አዲስ መጤ ነኝ ባይ
እንደቀልድ ቢመኛት፣
ዱላቸውን ቀማሽ
ሳይቀርብ ሳይጠጋት።
ውበትሽ ብርሀን
ጊዜ እንደሰማይ፣
ሆኖ ቢከተልሽ
ወንድ ሁሉ አገልጋይ።
ጭረሽ የፍቅር እሳት
አንቺ ተወርዋሪ፣
ከስንቱ ህይወት ውስጥ
ስትሰዋወሪ።
በምርጫ ተከበሽ
በዝቶ ፍላጎትሽ፣
ሳሩ ለምለም ገላሽ
ጤዛ ደግሞ ጊዜሽ።
በችኮላ ሄደው
በፍጥነት ቢበሩ፣
እኒያ አዳሞችሽ
ድንገት ተሰወሩ።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
////////
ሺ ገዳይ ነሽ አሉ
ባንቺ የታለሉ፣
ካንቺ እየደረሱ
ስንቶች ስንቴ ማሉ።
እግዜር በእጁ ጭሯት
ተወርዋሪ ኮከብ፣
ጭራዋን አርዝማ
ምትዞር በወንዶች ልብ።
ዘብ አዳኝ በፍቅሯ
ስንቱ ከሷ ደርሶ ጠባቂ እየሆናት፣
አዲስ መጤ ነኝ ባይ
እንደቀልድ ቢመኛት፣
ዱላቸውን ቀማሽ
ሳይቀርብ ሳይጠጋት።
ውበትሽ ብርሀን
ጊዜ እንደሰማይ፣
ሆኖ ቢከተልሽ
ወንድ ሁሉ አገልጋይ።
ጭረሽ የፍቅር እሳት
አንቺ ተወርዋሪ፣
ከስንቱ ህይወት ውስጥ
ስትሰዋወሪ።
በምርጫ ተከበሽ
በዝቶ ፍላጎትሽ፣
ሳሩ ለምለም ገላሽ
ጤዛ ደግሞ ጊዜሽ።
በችኮላ ሄደው
በፍጥነት ቢበሩ፣
እኒያ አዳሞችሽ
ድንገት ተሰወሩ።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
❤26👍5
ውብ የነበረች
የሸክላ ስኒ
የተሰበረች
ወድቃ ከደጄ ፤
ሳያት ከውስጧ፡ ራሴን አይቼ
ባዝን ባነሳት ፡ ጠርዟ ቢላዋ
ቆርጣኝ በደሜ፡ ሟልጮ ገላዋ
ዳግም ወደቀች፡ ከጄ አምልጣኝ
እንኳን ወደቀች ፡ እግዜር አወጣኝ።
እንኳን ሰበርኩት ፡ ስባሪ ጎኗን !
እንኳን አንስቼ ፡ ስጥል በድኗን
ተላለፈብኝ ፡ በእጄ ጥፋቷ
አባት ሆንኩለት ፡ ለየቲም ሞቷ።
አንዲት የሸክላ፡ ስኒ ተሰብራ
ወዟን አፍስሳ ፡ ላፈር ገብራ
ጣይዋ ሳይገኝ ፡ ባያት ተቀብራ
ገሏን አንስቼ ፡ ዳግም ስጥላት
ነበረች ተብሎ፡ ተለቀሰላት ፤
ትኩስ እንዲባል፡ ደረቅ አጽሟ
ምክንያት ተገኘሁ ፡ ቃኤል ወንድሟ
ከእንግዲህ ይረፍ ፡ጸጥ ይበል ደሟ።
ለየቅል አብረን ፡
አጉል ተሰብረን ፡
ገል ሆነን ኖረን ፡
ድንገት ተያይተን ፡
ለእቅፍ ጓጉተን ፡
ከወደቅንበት ፡ ለመነሳሳት ፤
እጆቻችንን ፡ ስንዘረጋጋ
በስባሪያችን ፡ ብንወጋጋ ፤
ደም አስተያይተን ፡ እንዳንላቀስ
በቁስሎቻችን ፡ እንዳንካሰስ
ከጅ እንጣጣል ፡ እንከሳከስ
እንከሳከስ ፡ እስክንልም ድረስ
በሰባራችን ፡ እስካንታወስ ፤
ቅርፅ ቅጣችን ፡ እስከሚረሳ
ሞተን ፈራርሰን ፡ እስክንነሳ
እንከሳከስ ፤
ደቃቃ ሲሆን ፡ ገላችን ብናኝ
ንፋስ አንስቶን ፡ ባየር ላይ ስንናኝ
አቧራ ሆነን ፡ እንድንገናኝ።
By Rediet Aseffa
@getem
@getem
@paappii
የሸክላ ስኒ
የተሰበረች
ወድቃ ከደጄ ፤
ሳያት ከውስጧ፡ ራሴን አይቼ
ባዝን ባነሳት ፡ ጠርዟ ቢላዋ
ቆርጣኝ በደሜ፡ ሟልጮ ገላዋ
ዳግም ወደቀች፡ ከጄ አምልጣኝ
እንኳን ወደቀች ፡ እግዜር አወጣኝ።
እንኳን ሰበርኩት ፡ ስባሪ ጎኗን !
እንኳን አንስቼ ፡ ስጥል በድኗን
ተላለፈብኝ ፡ በእጄ ጥፋቷ
አባት ሆንኩለት ፡ ለየቲም ሞቷ።
አንዲት የሸክላ፡ ስኒ ተሰብራ
ወዟን አፍስሳ ፡ ላፈር ገብራ
ጣይዋ ሳይገኝ ፡ ባያት ተቀብራ
ገሏን አንስቼ ፡ ዳግም ስጥላት
ነበረች ተብሎ፡ ተለቀሰላት ፤
ትኩስ እንዲባል፡ ደረቅ አጽሟ
ምክንያት ተገኘሁ ፡ ቃኤል ወንድሟ
ከእንግዲህ ይረፍ ፡ጸጥ ይበል ደሟ።
ለየቅል አብረን ፡
አጉል ተሰብረን ፡
ገል ሆነን ኖረን ፡
ድንገት ተያይተን ፡
ለእቅፍ ጓጉተን ፡
ከወደቅንበት ፡ ለመነሳሳት ፤
እጆቻችንን ፡ ስንዘረጋጋ
በስባሪያችን ፡ ብንወጋጋ ፤
ደም አስተያይተን ፡ እንዳንላቀስ
በቁስሎቻችን ፡ እንዳንካሰስ
ከጅ እንጣጣል ፡ እንከሳከስ
እንከሳከስ ፡ እስክንልም ድረስ
በሰባራችን ፡ እስካንታወስ ፤
ቅርፅ ቅጣችን ፡ እስከሚረሳ
ሞተን ፈራርሰን ፡ እስክንነሳ
እንከሳከስ ፤
ደቃቃ ሲሆን ፡ ገላችን ብናኝ
ንፋስ አንስቶን ፡ ባየር ላይ ስንናኝ
አቧራ ሆነን ፡ እንድንገናኝ።
By Rediet Aseffa
@getem
@getem
@paappii
❤33🔥8
አልወስድሽም
///////////////
በጉልበት ፈጀሁት
ህዝበ አዳሙን ሁሉ፣
አላይም አልደርስም
አንቺ ዘንድ እስኪሉ።
ገንዘብ እንደ ቅጠል
ሚበቅል ይመስል፣
በስጦታ አንቺን
ቀን በቀን ስከልል።
ከአድማስ ወድያ
ከጀንበር ስር፣
ግዛት ቦታን ሳሰማምር፣
አበባ አንቺን የማይተኩ
ፅጌሬዶች ስደረድር።
ተራሮችን ስቀርፅልሽ፣
ያንቺን ውብ መልክ ላስይዝልሽ።
የዛፍን ቅርፅ ስቀይረው፣
ታላቅ ፍቅሬን እንዲገልፀው።
ዳመኖችን ስስልልሽ
እንድትወጂው ሳደርግልሽ፣
ከሰማይ ዳር ቀስቴን ይዤ
ደመና ላይ ሳሰፍርልሽ፣
አንቺ አላየሽ፣
ይህ ፍቅሬንም አላስተዋልሽ፣
ስጦታዬን አልተቀበልሽ፣
ግዛቴንም ከቶ አልፈለግሽ፣
እንዲሁ ብቻ ዝም ብለሽ
እኔን ጥለሽ መናኒ ሆንሽ።
ሁሉን ባደርግ ብሰጥሽም፣
አንቺን አንቺ ካደረገሽ
ከፈጣሪስ አልወስድሽም።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
///////////////
በጉልበት ፈጀሁት
ህዝበ አዳሙን ሁሉ፣
አላይም አልደርስም
አንቺ ዘንድ እስኪሉ።
ገንዘብ እንደ ቅጠል
ሚበቅል ይመስል፣
በስጦታ አንቺን
ቀን በቀን ስከልል።
ከአድማስ ወድያ
ከጀንበር ስር፣
ግዛት ቦታን ሳሰማምር፣
አበባ አንቺን የማይተኩ
ፅጌሬዶች ስደረድር።
ተራሮችን ስቀርፅልሽ፣
ያንቺን ውብ መልክ ላስይዝልሽ።
የዛፍን ቅርፅ ስቀይረው፣
ታላቅ ፍቅሬን እንዲገልፀው።
ዳመኖችን ስስልልሽ
እንድትወጂው ሳደርግልሽ፣
ከሰማይ ዳር ቀስቴን ይዤ
ደመና ላይ ሳሰፍርልሽ፣
አንቺ አላየሽ፣
ይህ ፍቅሬንም አላስተዋልሽ፣
ስጦታዬን አልተቀበልሽ፣
ግዛቴንም ከቶ አልፈለግሽ፣
እንዲሁ ብቻ ዝም ብለሽ
እኔን ጥለሽ መናኒ ሆንሽ።
ሁሉን ባደርግ ብሰጥሽም፣
አንቺን አንቺ ካደረገሽ
ከፈጣሪስ አልወስድሽም።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
❤41👍4
የነፍሴን ጫጫታ፤
የዉስጤን ግርታ፤
በቃላት ሰድሬ፤
ሐረግ አዋቅሬ፤
ሰ ር ዤ፤
ደ ል ዤ፤
ስሜቴን አርቅቄ፤
ሀሳቤን ጨምቄ፤
ጭንቀቴን ጠፍፌ፤
በወረቀት ፅፌ፤
ጨምድጄ፤
ቀድጄ፤
ክብሪቱን፤
ለኮስኩት፤
በእሳት፤
አ ነ ደ ድ ኩ ት፤
በአመድ በጭሱ፤
ህይወቴን አየሁት።
[ ዔደን ታደሰ ]
@topazionnn
@getem
@getem
የዉስጤን ግርታ፤
በቃላት ሰድሬ፤
ሐረግ አዋቅሬ፤
ሰ ር ዤ፤
ደ ል ዤ፤
ስሜቴን አርቅቄ፤
ሀሳቤን ጨምቄ፤
ጭንቀቴን ጠፍፌ፤
በወረቀት ፅፌ፤
ጨምድጄ፤
ቀድጄ፤
ክብሪቱን፤
ለኮስኩት፤
በእሳት፤
አ ነ ደ ድ ኩ ት፤
በአመድ በጭሱ፤
ህይወቴን አየሁት።
[ ዔደን ታደሰ ]
@topazionnn
@getem
@getem
❤27🔥21👍8
ቤተሰብ ሳልጦር
ፈርቼ እያደርኩ ኑሮን እንደጦር
እንኳን ለሌላው ሳልሆነ ለራሴ
ልክ እንደ ሙሴ
በምድረ በዳ
ነፍሴን ሳልሸክፍ ሳልሰናዳ
ባዲስ መቃብር ገላዬን ሳልከት
ዐይመጣም ቀኔ ነፍቶ መለከት
ብቁ መሆኔን ሳይመለከት።
መች እበቃለሁ?
ይህንን መኖር
እንደምሰፋው ጠንቅቄ አውቃለሁ።
ውጊያ ሳልገጥም ወይ ጦር ሳያምረኝ
በብርሃን ጣቶች ሳይመረምረኝ
ለምን አመጣኝ ምን ሊያስጀምረኝ?
በማያገባኝ ፍልሚያ ደክሜ
ያልቆሰልኩትን ህመም አክሜ
ድል ላላጣጥም
ሰው...
ተዋጋሁ አይልም ቀኑን ሳይገጥም።
በአንዳች አዚም ኮከብ ሳልገትር
ታምር ሳልሠራ በትንሽ በትር
ከሕይወት መዳፍ ሳላነብ እጣ
የኔውስ ነገ ባሻው ቀን ይምጣ!
ይመጣል ያሉት የታለ ታዲያ
አልጠብቀውም ከንግዲህ ወዲያ።
By Yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
ፈርቼ እያደርኩ ኑሮን እንደጦር
እንኳን ለሌላው ሳልሆነ ለራሴ
ልክ እንደ ሙሴ
በምድረ በዳ
ነፍሴን ሳልሸክፍ ሳልሰናዳ
ባዲስ መቃብር ገላዬን ሳልከት
ዐይመጣም ቀኔ ነፍቶ መለከት
ብቁ መሆኔን ሳይመለከት።
መች እበቃለሁ?
ይህንን መኖር
እንደምሰፋው ጠንቅቄ አውቃለሁ።
ውጊያ ሳልገጥም ወይ ጦር ሳያምረኝ
በብርሃን ጣቶች ሳይመረምረኝ
ለምን አመጣኝ ምን ሊያስጀምረኝ?
በማያገባኝ ፍልሚያ ደክሜ
ያልቆሰልኩትን ህመም አክሜ
ድል ላላጣጥም
ሰው...
ተዋጋሁ አይልም ቀኑን ሳይገጥም።
በአንዳች አዚም ኮከብ ሳልገትር
ታምር ሳልሠራ በትንሽ በትር
ከሕይወት መዳፍ ሳላነብ እጣ
የኔውስ ነገ ባሻው ቀን ይምጣ!
ይመጣል ያሉት የታለ ታዲያ
አልጠብቀውም ከንግዲህ ወዲያ።
By Yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
❤26👍3🔥2🎉1