ግጥም ብቻ 📘
65.7K subscribers
1.54K photos
31 videos
61 files
176 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
ወደግራ ወድቆ
ፍቅራችን ዳመራው
የትዝታሽ ጭሱን  ናፍቆት ሰማይ ጠራው

እሄዳለሁ ብዬ ሶዶ ወይ ጉራጌ
አንቺ የሌለሽበት
መስቀል እንዴት ላክብር እንደምን አድርጌ


By @Absari_seven

@getem
@getem
53😁15👎2🎉2
ወራቱ ቀኑ ጠዋቱ ምሽቱ ፤
እንደከርሞው ነው እንደትናንቱ ፤

ጣዕሙም ጠረኑም አልተቀየረም ፤
ለእኔ አዲስ ዓመት አዲስ አይደለም ፤

ያው ነው አበባው ያው ነው ዘፈኑ
ያው ነው ደመራው ያው ነው እጣኑ ፤

አልተቀየረም እጣና ዕድሌ
አልዳነም ጎኔ አልሻረም ቁስሌ ፤

ዛሬም እንዳምናው . . .

ጭጋግ አጥልቷል ፍዝ ነው ቀኔ ፤
በአበባ ብቻ የሚሻር ዘመን አላውቅም እኔ።

By Tewodros kassa

@getem
@getem
@paappii
47🔥12😢10😱5👍1🎉1
ቢታነፅ ቢወቀር!
(በእውቀቱ ስዩም)

እኔም አንድ ሰሞን
ልክ እንደ ሰለሞን
"ሁሉም ከንቱ ከንቱ ንፋስን መከተል
ላይጥሉ መታገል: ላይከብሩ መባተል"
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ: እፈላሰፍ ነበር!

ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጓሮ በር በኩል: ሰለሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ንፋስ አሳድጄ እንደ ቆቅ አጠመድሁ
ከፀሀይዋ በታች: ግልገል ፀሀይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ: ብርሀን አበደርሁ

ማቅ የነበረው ጨርቅ: ሸማ ሆኖ ቆየኝ
"ከንቱ የነበረው: "አንቱ" ሆኖ ታየኝ!

ለካስ...

ጠቢብ ቢያስተምረው
መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ: ቢታነፅ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም: ካልወደደ በቀር!

@getem
@getem
@paappii
71🔥21👍6🎉1
በህይወት መንገድ ላይ
በኑሮ ትሩፋት
ማስተዋል ከሌለ
በጥልቀት በስፋት
በእብዶች መንደር ውስጥ
ጤነኞች ከሌሉ
ጤነኞች ለእብዶች
እብዶች ይሆናሉ።

@getem
@getem
@paappii
85👍9🔥7🤩4
‎የሴትነት እጣ ክፍልሽ
‎ ምን ቢደብቅ ማፍቀርሽን
‎አይንሽ አጋልጦሻል
‎ አላምነውም ምግባርሽን

‎የወንድነት ወጌን
‎ ምን ባስቀድም አንደበቴን
‎መጠራጠር ሰርክ ልማድሽ
‎ አላመንሽም እኔነቴን

‎ እወድሻለሁ

‎ ብትሸሸጊው ያንቺን ስሜት
‎  አይንሽ ሁሉን ይነግረኛል
‎  አትደብቂኝ....ወደሽኛል


‎ዮኒ
‎     ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
👍2726
ስወደው ነው የጠላሁት
ሳፈቅረዉ ነው የሸሸሁት

የጠላሁትን እሹሩሩ የተካንኩበት
እንደጦረኛ ገፊዬን ማቅረቡ’ን ሳዉቅበት

በል…….
ወደድኩሽ ባልክበት አፍህ ጠላሁ በል
ናፈቀሺኝ ያለአንደበትህ - ላይ ታበል

እሾህን በእሾህ
ፍቅርን በመጥላት
እየወደዱ በመገፋፋት
እናስቀጥለዉ

ሰይጣኔን ሰይጣንን መስለህ ግፈፈዉ
አይነ ጥላዬን ናና እንሸዉደዉ።


ትዝታ ወልዴ✍️

@getem
@getem
@Tizita21
54👍9👎4🔥2🤩1
ቃል ከአፋቸው ሳይወጣ
ፍቅር ተሰናብቶ መለያየት መጣ
ቻው እንኳን ሳይሉኝ
ሁሉም አገለሉኝ

እኔ ብቻ ሆነ እኔን የወደደው
እሱስ ተራው ደርሶ መች ይሆን ሚሄደው

By @Absari_seven

@getem
@getem
45🤩9🔥5
የአንተም ልብ ድንጋይ
የኔም ልብ ድንጋይ ...
(ለዚያ ነው መሰለኝ )
በተጋጨን ቁጥር በፍቅር የምንጋይ።

By meron ghetnet

@getem
@getem
@paappii
65🔥20🤩17👍7
ራሱ’ንደማይጠጣ - የውሃ ማሰሮ፣
መሆን ላልተቻለው - ክው ያለ ጉሮሮ፤
አስመሳይ ደጋጎች - ውሃ ሰጡት’ና፣
የሞት ሞቱን ሲኖር - ችግሩ እንደጠና፤
ጉሮሮ ማሰሮ - ተመሳስሎባቸው፣
ያጠጡትን ቀድተው - መውሰድ ላቃታቸው፤
ረሃብ አንጎራጉሮ - ለለመደው ውሃ፣
ሰጥቶ ተቀባዮች አስቀየመልሃ!

(የሞገሴ ልጅ)
@eyadermoges

@getem
@getem
@getem
23👍16🔥4
ላውሊያ ንጉስ ለጠቋሪት ደጋሽ
ዚያራ: ላይ ካድመሽ
ህልሜን ግራ አጋባሽ
የፅልመት እጆቼን ለኑሮሽ: ከነዳሽ
በኔ ጉሜ: ይዘሽ ተፋሽው ልብሽን
ካድመሽ: አገባሽው የልደት: ቀንሽን
ድቤው ስራ አልፈታ: ከህልሜ አለው ጋንታ
ላንቺ ኑሮ ሰቶ እኔን እሚያፋታ::
  
                                            by አለምሰገድ ወልዴ

@getem
@getem
@getem
27👍4
ዛሬ ሌላ ሰው ነኝ።

ያኔ ትንሽ ሆኜ-
በእድሜዬ ለጋ - በበሓሪ ችኩል፣
አፍንጫ አሽትቻለሁ፣
ቀድሞኝ ከበሰለው - ለመታየት እኩል።

ልጅነትን ሳልፈው-
ሌላን ማየት ትቼ - ራሴን ዐየሁ እና፣
ገደብ ሰራሁለት፣
ጉጉቴ ልክ አልፎ -ስጎድል እንዳይቀና።

ልልሽ የፈለግሁት-
አንቺ ላታስቢኝ አትበይ “ረስተኸኛል”፣
የሰርግሽን ፎቶ-
ከልቤ ሳደንቀው እራሴም ገርሞኛል።
ምክንያት፣...
ያኔ ወጣትነት - ኩራት የኮፈሰኝ፣
ትእቢት ላንዳፍታ - ወስዶ የመለሰኝ፤
እልህ እየጋተ - ምላጭ የሚያስውጠኝ፣
“ዛሬ ብቻ” ባይ ኅዝብ - አስሶ እሚመርጠኝ፤
ዛሬ...
አንቺ የኖርሽውን - ዘመን የኖርኩ እኔ፣
እራሴን ያስተማርኩ - በሕይወት ጠመኔ፤
አንቺ “ፈልጉኝ” ባይ - እኔ ራሴን መሪ፣
አንቺ ላይሽ ፋኖስ - እኔ ውስጤ በሪ፤
ከመንገድሽ እሩቅ - መንገዴ ወስዶኛል፣
ሺህ ግዜ አግብተሽ - ሺህ ግዜ ብትፈቺ ምን ያናድደኛል?

በርቺ 😐
@eyadermoges

@getem
@getem
@getem
34👍21😁4🔥2
የማመንታት ፍቅር
ልሂድ ወይስ ልቅር

(ያለበት)

ጓዝሽን ጠቅልለሽ በስንብትሽ እለት
ደግሞ ተመልሶ
ከበቃኸኝ በኃላ ካልበላሁ ማለት

(ምን ይሉታል አሁን)

ተፍተሺኝ አንቅረሽ
ጥላቻን አፍቅረሽ
ባፍንጫሽ ወጥቼ
ለፍቺያችን ድግስ የወይን ጠጅ ጠጥቼ

(ችርስ ተባብለን)

ወይ መተሽ አትመጪ ወይ ቀርተሽ አትቀሪ
ድንገት ትገኛለሽ ለፍቅር ከፊቴ ስትደነቀሪ

By @Absari_seven

@getem
@getem
38👍11🔥4
‎ቆርጦልኝ ነበረ ነግሬሽ የልቤን ወድሻለሁ ብዬ
‎የምትወጂኝ መስሎኝ ስጠብቅሽ ቀረሁ ካደርኩበት ውዬ
‎ነካክተሽ ነካክሽ ልቤን አደረግሽው የፍቅርሽ ምርኮኛ
‎የማትወጂኝ ከሆን ለምን ቀሰቀስሽው ይቅር እንደተኛ

‎አይቀርም አንድ ቀን ያፈቀረሽ ልቤ የጎኑን ማግኘቱ
‎ህይወት ይቀጥላል ምን ልቤ ቢደክም አንቺን በማጣቱ
‎አገኘሽኝ እንጂ ሆኜ ያንቺ ወዳጅ
‎ከፍቅርሽ አለም ውስጥ
‎ሳላውቀው ገብቼ እንደ ባህር ሰርጓጅ

‎ግን ...

‎ያሳሰበኝ ፍቅር
‎ካንቺ ስር ያዋለኝ እንዲህ እንደከረረ
‎ሌላ ሲያይሽ ጊዜ ቀንቼ ነበረ
‎አፈቀርኩሽ ያልኩት
‎የኔ ያልኩትን ሰው በሌላ ሲታቀፍ
‎እንዴት ብዬ ልለፍ

‎የመነጠቅ መንፈስ
‎ውስጤን እንገብግቦት አላመጣሁሽም
‎እውነቱን ስነግርሽ
‎ቀንቼ ነው እንጂ አላፈቀርኩሽም

‎አልልሽም ይህን ቃሌን ድፍረት የለኝ የምልበት
‎ያጠፋዋልና የወንድነት ልኩን ይህን ያልኩሽ እለት

‎እንደገባኝ ቢሆን ከዚህ ሁሉ ነገር
‎ቅናት መንፈስ እንጂ አልነበረም ማፍቀር



‎ ዮርዳኖስ @JorDanos7

@getem
@getem
@getem
👍3735🤩6🔥5
መተላለፍ
------------------------------

“ሰው ሀገር ነው" ቢሉኝ ሀገሬ ነህ ብዬ፣
አንተ ስር ተገኘሁ ነገሬን ጣጥዬ፡፡
ለወሬ 'ማይመች የቸገረ ነገር፣
አንተ እኔን ታቅፈህ ትመኛለህ ሀገር።

By ሜሮን ጌትነት

@getem
@getem
@paappii

''ሌላ አዉነት የለኝም'' ሚለዉን የሜሮን ጌትነት ግጥም ገዝታቹ እያነበባቹ
86😁9👍5
ምን ይሻለዋል
--------------------

ሂድልኝ ሂጂልኝ
ብለን ተለያይተን

ከማነቀው ህይወት
አንቺም እኔም ገብተን

ይሄንን ልቤን ግን
ቆይ ምን ይሻለዋል

አንቺን ሲያስብ ጊዜ
እንባ ይቀድመዋል

@getem
@getem
@paappii
68😢13🔥8
    ግጥም ነው ምትመስዪው!
  ---------------------------------------
            

ከፊደል ማሳ ላይ ቃላት ለሚቃርም
ካገኘም ከትቦ እያደር ሚያርም÷
በአርኬው መባቻ  በመድፋት አባዜ
ከሃሳብ ባህር ላይ ሰጥሞ በትካዜ÷
በብዕሩ እንባ ስንኞች ሲቋጥር
ቤቱን በመዘንጋት ቤት ለመምታት ሚጥር÷
እቴ አትሞኚ ከቁብ ለማይቆጥርሽ
በፍቅር አጊጠሽ አምሮብሽ ቢያይሽ÷
በቃላት ስደራ የተሽቀረቀረ
በታሪክ ፍሰቱ ጎልቶ የዳበረ÷
ግጥም ነው ምትመስዪው
መምቻና መድፊያው ፍፃሜው ያማረ::
                     

By @Abuugida

@getem
@getem
@getem
36👍4😁1
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
--------------------------

አንቺ ስትስቂ
ከሰማይ ላይ ወፎች፣
እስከ ምድር ሰዎች፣
የገነት በር ደጆች፣
የቅዱሳን ፊቶች፣
አምረው ያበራሉ፤
ደስታን ያገኛሉ።

ትልቁ ጎልያድ
በሳቅሽ ተማሎ፣
ብላቴነው ዳዊት
ጠጠሮቹን ጥሎ፣
ያንቺን ሳቅ ነበረ
ተቃቅፈው ሚሰሙት፣
ፈገግታሽን ነበር
ሚያስቡት ሚያልሙት።

አንቺ ስትስቂ
ፀሃይ ከጨርቃ፣
ብርሃን ከጨለማ፣
ሰማይ ከምድር ጋ፣
ወፎች ከአረዊቶች፣
ክረምት ሳይቀር በጋ፣
አንድ አምሳል ነበሩ፣
በሳቅሽ ግዞት ውስጥ
አንድ ላይ ሚኖሩ።

ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ጎልያድ አቅራራ
ዳዊት ላይ ደነፋ፣
አባቶች ተከፍተው
መቋሚያ አነሱ፣
እንድትስቂላቸዉ
ፆም ፀሎት ሊያደርሱ።

ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ሰማይ አለቀሰ፣
ፀሃይ ተናደደች፣
ነፍሳትን አቃጥላ
ጨለማን ሰደደች።

እኔም ስጠባበቅ
በምኞት በተስፋ፣
ሳቅሽን ናፍቄ
ሳቅሽን ተርቤ
ግዜ ይዞኝ ጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ


@getem
@getem
@paappii
111😁6🔥5👎1
ፍቅር አለኝ ለአንተ!
-----------------------------

አደመጥሁኝ ቅኔ መልሴ መልሼ፣
ሙዚቃውን ሰማሁ ዓለሙን አስሼ።
ዜማ ሰለለብኝ ሥዕል ደበዘዘ ግጥም አነከሰ፤
ባሳይህ... ብኖረው... የልቤ አልደረሰ።
(አንደ ምን ልግለጸው?)
ጥበብ ያሳነሰው .
ቋንቋ ያኮሰሰው .
ፍቅር አለኝ ለአንተ፣
በፍጥረት ዘመን ልክ እየተጎተተ
አስከ ዓለም ፍጻሜ ደግሞ 'ሚዘረጋ፣
ብኖርም ባንኖርም
ምጽአት የሚጠብቅ በነፍስም በሥጋ።
ፍቅር አለኝ ላንተ
ምድር የሚሞላ፣
ከእግዜር የሚያስታርቅ ከእግዜር የሚያጣላ።

By Meron Ghetnet

@getem
@getem
@getem
62
ልጅ እያለሁ –··· ጨረቃ....
(በሌሊቱ ሰማይ ደምቃ ...)
ቁልቁል ዓይኔን እያየችኝ ፤
(እያልኩ –··· “ተከተለችኝ ”)
መስሎኝ የወደደችኝ...
(ሽቅብ... ሽቅብ.... እያየኋት)
ስራመድ አቅንቼ አንገቴን ፤
መች አየሁት እንቅፋቴን ?!
(ሲነቅልብኝ አውራ ጣቴን...)
ሲጥለኝ ከመሬት ጠልፎ ፤
ሲከነብለኝ አደናቅፎ ....!
(“ወደደችኝ” ካልኩት ይብስ...)
እዛው መሬት ላይ ወድቄ ፤
(ጨረቃ ከሰማይ ወርዳ...)
እስክታነሳኝ መጠበቄ ፤
ትልቁ –··· አለማወቄ ።
💧
ያኔ ታዲያ....
“አይዞህ ልጄን !
እኔን!” እያለች ፤
አንስታኝ እያባበለች ....
(በክንዶቿ ደግፋ )
አቧራዬን አራግፋ ...
ቁስሌን በጨረቅ ያሰረች ፤
እናቴ “ግጥም” ነበረች ።
💧
“ግጥም” ነበረች እናቴ ....
(አባባይ ለልጅነቴ....)
ዘቢብ ጠብታ — ለመሪር ቀኔ
ክፍተቴን መዝጊያ —  ክዳኔ ።
(ታዲያ ያኔ.....!)
ህመሜ ሲቀሰቅሰኝ...
(ጨረቃም ስትታወሰኝ....)
“እኔን ልጄን!” — መባል ሽቼ ፤
(“አመመኝ እናቴ” እያልኳት...)
እግሮቿ ላይ — ተደፍቼ....
ሲቃዬን በጨርቅ አፍኜ
(ፊቴን በቀሚሷ ሸፍኜ)
“ስቅስቅ” ያልኩት...
(“እሪ” ያልኩት...)
ልብሷ ላይ እስካሁን አለ...
እንደ ጥልፍ አምሮ –··· ተጥሎ ፤
(ዕምባዬ —··· “አበባ”  መስሎ ።)
____

የካቲት 8 — 2016 ዓም
By @Bekalushumye


@getem
@getem
@getem
74👍6🔥2😱1
አይ አንቺ ጨረቃ
.
.
.
ስንቱን ሰዉ ታዘብሽዉ?

ስንቱን አደመጥሽዉ?

የከፋዉ እንደሆን

ላንቺ የሚያወጋዉ

በልቡ ያለዉን

ሚስጥራቱን ሁሉ.....

የሚዘረግፈዉ

እስቲ ልጠይቅሽ?

ምን ቢያይብሽ ነዉ?

   ✍️ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
66🎉8👎3👍2
ምስጋና
-------------------------

ባንቺ ተማምኜ እምነቴን ጥዬብሽ
አምኜሽ ቆይቼ ቃሌን ጠብቄልሽ፣
ዛሬ ትመጣለች ግድ የለም ወይ ነገ
ፀሃዩ ፍቅራችን ስል መች ገና አደገ፣
እልፍ አላፍ አመታት ጥሎኝ እያለፈ
መንፈቅ በመንፈቅ ላይ ሄዶ እየከነፈ፣
በዋሊት ትዝታ በሀሳብ እየኖርኩኝ
ስቀመጥ ስነሳ አንቺን እያሰብኩኝ፣
ያዘዙኝን ሳደርግ ያሉኝን ስሰራ
ስንቱን አለፍኳቸው ስንቱንስ መከራ፣

ቢሆንም

እንደው ብቅ ብለሽ ካጣሽኝ ከሌለዉ
ጆሮሽን አትስጪ ቸግሮታል ለሚለዉ
የመኖሬ ተስፉ አንቺ ነበርሽና፣
ዘግይተሽ ብትመጪም ይድረስሽ ምስጋና።

@getem
@getem
@paappii
55👍13😢6🔥4