ሥዕል ማሳል ለምትፈልጉ በሙሉ
በ +251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ ፎቶ በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ ማዘዝ ይችላሉ!
#ሥዕል_ብቻ
@seiloch
@seiloch
በ +251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ ፎቶ በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ ማዘዝ ይችላሉ!
#ሥዕል_ብቻ
@seiloch
@seiloch
❤48👍39👎13🤩8🎉5😁2😱2
መኖር
በፍላጭ ሰከንዶች፤
በሽራፊ ሰዓት፤
በደቂቃ ቅንጣት፤
እለት እየገፉ፤
ወራት እያለፉ፤
እየጣሉ አመታት፤
በዘመን ምትሀት፤
በአንዲት የጊዜ ጋት፤
መኖር መሳብ አይደል፤
ወደሞት መጠጋት ?
By @poetkidus
@getem
@getem
@paappii
በፍላጭ ሰከንዶች፤
በሽራፊ ሰዓት፤
በደቂቃ ቅንጣት፤
እለት እየገፉ፤
ወራት እያለፉ፤
እየጣሉ አመታት፤
በዘመን ምትሀት፤
በአንዲት የጊዜ ጋት፤
መኖር መሳብ አይደል፤
ወደሞት መጠጋት ?
By @poetkidus
@getem
@getem
@paappii
❤46👍16🔥1
ፆመ እባላለሁ ፥ ፆሜን እየፈታሁ
(ሳሙኤል አለሙ)
እንቁላሉን፣ስጋውን እንዳልበላሁ
ሰው ያውቃል፤
ወተቱን ፣ እርጎውን እንዳልጠጣሁ
ሰው ያውቃል፤
ላግኘው ብየ
ልያዘው ብየ
እንዳልወጣኝ ፥ ክፉ ቃል
ሰው ያውቃል፤
አውቃለሁ አያውቁም
አያውቁም አውቃለሁ ፤
ስብሰለሰል ግዜ
ስንገበገብ ግዜ
የከንፈሬን ስሷን ቆዳ
--ልጬው እየበላሁ
ፆመ እባላለሁ ፥ ፆሜን እየፈታሁ።
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
@Getem
(ሳሙኤል አለሙ)
እንቁላሉን፣ስጋውን እንዳልበላሁ
ሰው ያውቃል፤
ወተቱን ፣ እርጎውን እንዳልጠጣሁ
ሰው ያውቃል፤
ላግኘው ብየ
ልያዘው ብየ
እንዳልወጣኝ ፥ ክፉ ቃል
ሰው ያውቃል፤
አውቃለሁ አያውቁም
አያውቁም አውቃለሁ ፤
ስብሰለሰል ግዜ
ስንገበገብ ግዜ
የከንፈሬን ስሷን ቆዳ
--ልጬው እየበላሁ
ፆመ እባላለሁ ፥ ፆሜን እየፈታሁ።
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
@Getem
🔥33👍25❤24😁12😱2🎉2😢1
ደህና ዋልሽ አልኳትኝ
የፈካውን ፊቷን በአይኖቼ እየካደምኩ
"እግዛቤር ይመስገን"
በጥፍጥ አንደበቷ በከንፈር ተማረኩ
"አንተስ እንዴት ከረምክ....ተስማማህ አየሩ"
ግርምታ እየያዛት ብመጣ በወሩ
"..ኧኧ....ይመስገን ጀሊሉ.."
"ይመስገን ጀሊሉ"
"ምነው ጠፋህሳ ከሄድክበት ግድም
እንደው ቢቻል...ቢቻል
አይደወልም አንድም"
"አፉ በይኝ አቦ....
ባይመቻችልኝ ነው መደወል መርሳቴ"
ተጠጋሁ ከፊቷ አሳረፍኩ አንጀቴን
"ይልቁንስ አንቺው
ከዛ ከሩቅ ሀገር ያመጣሁት አለ
ከተስማማሽ ላንቺ ብትለብሺው ምናለ"
"ማርያምን..?......የታለ.."
"አለ ከሰነኩት...ከሻንጣዬ ግድም
ቢሆን ለደብርሽ ለባዕልሽ ግልድም"
"ደስ ይለኛል....ወላዲቷን"
ደስ ብሏታል የእውነቷን
"በል ና ቅመስ የቡና ቁርስ
አልወረደም ገና አቦሉ"
"የለም ልሂድ.....ሌላ ጊዜ
ሳይብስብኝ ይህ ቀትሩ"
"ማይሆነውን....
እዚህ መተህ አትመለስ
የባታ ነው ፀበል ቅመስ"
"ወላሂ..ይቅርብኝ ሩቅ ነው መንገዴ
ባየሆን ልዝገን ካለው ባዶ እንዳይሆን ሆዴ"
ዘገንኩት ከቁርሱ ካፌ ላይ ወረወርኩ
ያመጣሁላትን ለገላዋ አስረከብኩ
"ባታ ትስጥልኝ አለሜ...."
"አሜን....ሙሃመዴ"
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
የፈካውን ፊቷን በአይኖቼ እየካደምኩ
"እግዛቤር ይመስገን"
በጥፍጥ አንደበቷ በከንፈር ተማረኩ
"አንተስ እንዴት ከረምክ....ተስማማህ አየሩ"
ግርምታ እየያዛት ብመጣ በወሩ
"..ኧኧ....ይመስገን ጀሊሉ.."
"ይመስገን ጀሊሉ"
"ምነው ጠፋህሳ ከሄድክበት ግድም
እንደው ቢቻል...ቢቻል
አይደወልም አንድም"
"አፉ በይኝ አቦ....
ባይመቻችልኝ ነው መደወል መርሳቴ"
ተጠጋሁ ከፊቷ አሳረፍኩ አንጀቴን
"ይልቁንስ አንቺው
ከዛ ከሩቅ ሀገር ያመጣሁት አለ
ከተስማማሽ ላንቺ ብትለብሺው ምናለ"
"ማርያምን..?......የታለ.."
"አለ ከሰነኩት...ከሻንጣዬ ግድም
ቢሆን ለደብርሽ ለባዕልሽ ግልድም"
"ደስ ይለኛል....ወላዲቷን"
ደስ ብሏታል የእውነቷን
"በል ና ቅመስ የቡና ቁርስ
አልወረደም ገና አቦሉ"
"የለም ልሂድ.....ሌላ ጊዜ
ሳይብስብኝ ይህ ቀትሩ"
"ማይሆነውን....
እዚህ መተህ አትመለስ
የባታ ነው ፀበል ቅመስ"
"ወላሂ..ይቅርብኝ ሩቅ ነው መንገዴ
ባየሆን ልዝገን ካለው ባዶ እንዳይሆን ሆዴ"
ዘገንኩት ከቁርሱ ካፌ ላይ ወረወርኩ
ያመጣሁላትን ለገላዋ አስረከብኩ
"ባታ ትስጥልኝ አለሜ...."
"አሜን....ሙሃመዴ"
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
👍58❤22🤩6
አልከነፍኩም ስላፈቀርኩ
ተሰባበርኩ እንጂ የትም
መልስ የለሽም ለጥያቄ
ልብሽ እኔን አያካትም
ያንቺ ፍቅር አሳነሰኝ
ደጅ አስጠናኝ በዳጃፉ
ሰው እንደሆን ወሬ አያጣም
ይለቅመኛል ሁሌ ባፉ
ህመም ብቻ ውስጤ እሳቱ
አይዳፈን እየነደድኩ
መፈቀር ግን ህያው ሞት ነው
ስቃይ ብቻ ማፍቀር ልኩ
አላመንሽም ያንደበቴን
የማፍቀሬን ስር ትርጉሙን
አይወደኝም ሰርክ መልስሽ
አላወቅሽም ጥግ ህመሙን
ተፈቃሪ ምን ግድ አለው
ምን ቢፈቅር እንደሀገሩ
አፍቃሪ ነው ነገር ሚፈጅ
የሚማገድ ለወደሩ
ትገርሚያለሽ አንቺ ብቻ
አላመንሽም የኔን ፍቅር
አትወድህም ቢለኝም ሰው
ከደጃፍሽ ዛሬም አልቀር
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ተሰባበርኩ እንጂ የትም
መልስ የለሽም ለጥያቄ
ልብሽ እኔን አያካትም
ያንቺ ፍቅር አሳነሰኝ
ደጅ አስጠናኝ በዳጃፉ
ሰው እንደሆን ወሬ አያጣም
ይለቅመኛል ሁሌ ባፉ
ህመም ብቻ ውስጤ እሳቱ
አይዳፈን እየነደድኩ
መፈቀር ግን ህያው ሞት ነው
ስቃይ ብቻ ማፍቀር ልኩ
አላመንሽም ያንደበቴን
የማፍቀሬን ስር ትርጉሙን
አይወደኝም ሰርክ መልስሽ
አላወቅሽም ጥግ ህመሙን
ተፈቃሪ ምን ግድ አለው
ምን ቢፈቅር እንደሀገሩ
አፍቃሪ ነው ነገር ሚፈጅ
የሚማገድ ለወደሩ
ትገርሚያለሽ አንቺ ብቻ
አላመንሽም የኔን ፍቅር
አትወድህም ቢለኝም ሰው
ከደጃፍሽ ዛሬም አልቀር
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
👍26❤12🔥4
ቅጽርህ የእናት እቅፍ
ሸክምን የሚያራግፍ
አልተነፍስ ጸሎት አይወጣ ቃል ከአፌ
ይተናል ጭንቀቴ ስመለስ አርፌ
እመጣለሁ ደጅህ ሀሳብ አንጠልጥዬ
እገባለሁ ቅጽርህ አንገቴን ደፍቼ
መች ታዝንብኛለህ
መች ትወቅሰኛለህ በሽቅጬ ከርፍቼ
አይነድህ ድፍረቴ
አይቆጨኝ ስንፈቴ
አይበሽቅህ ስህተቴ
አይገደኝ ዝለቴ
በኦና ተግባሬ
ውድቀት አንከርፍፌ ስቆም ከነእድፌ
ምን አድርጌልህ ነው?
አክመህ ምትልከኝ በምህረት መርፌ
ከመቀመጥ በቀር
ኢምንት ታህል ድርጊት ፈጽሜ የማላውቅ
አንዲት ዘለላ እንባ
በጉንጬ ሳልሰድ እንዴት ደመቅኩ በሳቅ?
እንዴት ቻልኩ መፍገግ?
እንዴት ቻልኩ ማማር?
እሬት ህይወት ይዤ
አጣፍጥልኝ ሳልል ሳልጠይቅ የሀሴት ማር
ትዕቢት አይሉት ጥጋብ
ፍርሃት አይሉት ስጋት
ስም ያላገኘሁለት
አንዳች አሳሪ ኃይል ወርሮኝ እንደ ውጋት
አላልኩኝ እግዚኦታ አልቆምኩኝ ሰዓታት
ፈውስ አሰኝቶኝ አላደረስኩ ኪዳን
ስለረገጥኩ ብቻ
ስላረፍኩ በቤትህ ይገባኝ ነበር መዳን?
እንጃ!
ብቻ እመጣለሁ ሀሳብ አንጠልጥዬ
ደጅህ እገኛለሁ ማረኝ ቃልን ጥዬ
አርፋለሁ ካንዱ ጥግ አንገቴን ደፍቼ
መች ትቆጣኛለህ
ሰማዕቱ ጊዮርጊስ ከነእድፌ ተኝቼ
ቆይቼ
ቆይቼ
.
.
.
ቆይቼ ስነሳ
ተጋድሞ አየዋለሁ ሸክሜ እንደ ሬሳ
አልጸለየም ሳትል
አልለመነም ሳትል
አላነባም ሳትል
ይገርመኛል እኮ
ጊዮርጊስ አባቴ ጭንቀቴን ስትጥል
ይገርመኛል ቅጽርህ...
ልክ እንደ እናት እቅፍ
ደስታን 'ሚያሳቅፍ!
አባብሎ 'ሚያሳርፍ!
ሸክምን 'ሚያራግፍ!
.
.
.
እርፍ!
#ኤልዳን
@marda129
@getem
@getem
@getem
ሸክምን የሚያራግፍ
አልተነፍስ ጸሎት አይወጣ ቃል ከአፌ
ይተናል ጭንቀቴ ስመለስ አርፌ
እመጣለሁ ደጅህ ሀሳብ አንጠልጥዬ
እገባለሁ ቅጽርህ አንገቴን ደፍቼ
መች ታዝንብኛለህ
መች ትወቅሰኛለህ በሽቅጬ ከርፍቼ
አይነድህ ድፍረቴ
አይቆጨኝ ስንፈቴ
አይበሽቅህ ስህተቴ
አይገደኝ ዝለቴ
በኦና ተግባሬ
ውድቀት አንከርፍፌ ስቆም ከነእድፌ
ምን አድርጌልህ ነው?
አክመህ ምትልከኝ በምህረት መርፌ
ከመቀመጥ በቀር
ኢምንት ታህል ድርጊት ፈጽሜ የማላውቅ
አንዲት ዘለላ እንባ
በጉንጬ ሳልሰድ እንዴት ደመቅኩ በሳቅ?
እንዴት ቻልኩ መፍገግ?
እንዴት ቻልኩ ማማር?
እሬት ህይወት ይዤ
አጣፍጥልኝ ሳልል ሳልጠይቅ የሀሴት ማር
ትዕቢት አይሉት ጥጋብ
ፍርሃት አይሉት ስጋት
ስም ያላገኘሁለት
አንዳች አሳሪ ኃይል ወርሮኝ እንደ ውጋት
አላልኩኝ እግዚኦታ አልቆምኩኝ ሰዓታት
ፈውስ አሰኝቶኝ አላደረስኩ ኪዳን
ስለረገጥኩ ብቻ
ስላረፍኩ በቤትህ ይገባኝ ነበር መዳን?
እንጃ!
ብቻ እመጣለሁ ሀሳብ አንጠልጥዬ
ደጅህ እገኛለሁ ማረኝ ቃልን ጥዬ
አርፋለሁ ካንዱ ጥግ አንገቴን ደፍቼ
መች ትቆጣኛለህ
ሰማዕቱ ጊዮርጊስ ከነእድፌ ተኝቼ
ቆይቼ
ቆይቼ
.
.
.
ቆይቼ ስነሳ
ተጋድሞ አየዋለሁ ሸክሜ እንደ ሬሳ
አልጸለየም ሳትል
አልለመነም ሳትል
አላነባም ሳትል
ይገርመኛል እኮ
ጊዮርጊስ አባቴ ጭንቀቴን ስትጥል
ይገርመኛል ቅጽርህ...
ልክ እንደ እናት እቅፍ
ደስታን 'ሚያሳቅፍ!
አባብሎ 'ሚያሳርፍ!
ሸክምን 'ሚያራግፍ!
.
.
.
እርፍ!
#ኤልዳን
@marda129
@getem
@getem
@getem
❤51👍22🔥6👎3
አወቅሽኝ
አወኩሽ
.
.
.
ተዋወቅን
በፍቅር ነጠቅን
ጨረቃን ዳሰስናት ኮኮቦችን ቆጠርን
ቅዳሴ እና አዛንን
አስቀደስን አፈጠርን
አወኩሽ
ወደድኩሽ
ከልብ ተመኘሁሽ
ለነብሴ ፈለኩሽ
አጌጥን በፍቅራችን አስቀናን ላገሩ
ኮራን በመንደሩ
ወጣቶች ተያይተው
"ሲያምሩ...ሲያምሩ" እየተባባሉ
ወደድሽኝ
ወደድኩሽ
.
.
.
ተዋደድን
በፍቅር አበድን
ነጎድን...ነጎድን...ነጎድን
ከአፍ ባልወጣ ቃል
መፋቀራችንን ሀገር ምድሩ ያውቃል
መገረም መደነቅ ለኛ ምንም ነው
ተፋቅረን አየነው
ደላኝ ባንቺ ፍቅር
ደላሽ በኔ ፍቅር
እኔ ለንቺ
አንቺ ለኔ ካለን ሁሉም ነገር ይቅር
አፈቀርሽኝ
አፈቀርኩሽ
.
.
.
ተፋቀርን
የዛሬን ትዝታ ለነገ ወቀርን።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
አወኩሽ
.
.
.
ተዋወቅን
በፍቅር ነጠቅን
ጨረቃን ዳሰስናት ኮኮቦችን ቆጠርን
ቅዳሴ እና አዛንን
አስቀደስን አፈጠርን
አወኩሽ
ወደድኩሽ
ከልብ ተመኘሁሽ
ለነብሴ ፈለኩሽ
አጌጥን በፍቅራችን አስቀናን ላገሩ
ኮራን በመንደሩ
ወጣቶች ተያይተው
"ሲያምሩ...ሲያምሩ" እየተባባሉ
ወደድሽኝ
ወደድኩሽ
.
.
.
ተዋደድን
በፍቅር አበድን
ነጎድን...ነጎድን...ነጎድን
ከአፍ ባልወጣ ቃል
መፋቀራችንን ሀገር ምድሩ ያውቃል
መገረም መደነቅ ለኛ ምንም ነው
ተፋቅረን አየነው
ደላኝ ባንቺ ፍቅር
ደላሽ በኔ ፍቅር
እኔ ለንቺ
አንቺ ለኔ ካለን ሁሉም ነገር ይቅር
አፈቀርሽኝ
አፈቀርኩሽ
.
.
.
ተፋቀርን
የዛሬን ትዝታ ለነገ ወቀርን።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤51👍30👎4😁1
ተዘነጋሽ አይደል ገፍተው አናናቁሽ
ከሳምንታት በፊት ንግሥቴ እንዳላሉሽ
የኔማ ሽሮዬ ብለው እንዳልተቀኙ
ጥለውሽ ነጎዱ ሚሽቱን ሲያገኙ
.
እኔን የኔ አበባ
እኔን የኔ እመቤት
50 ቀን ቀርቶሻል ልትገቢ ዳግም ቤት
.
እኔ የኔ አበባ
እኔን የኔ ንግስት
ሰው ብቻ አይደለም
ማግጧል ያም ብረት ድስት
.
ሁሉም ከድተውሻል
ሁሉም ትተውሻል
ትንሽ ብቻ ታገሽ 50 ቀን ቀርቶሻል
.
ያኔ ቀኑ ሲደርስ በእየንብርክካቸው
ማሪኝ ማሪኝ ሽሮ አይቀር ማለታቸው
.
እኔን የኔ አበባ
እኔን የኔ እመቤት
50 ቀን ቀርቶሻል ልትገቢ ዳግም ቤት
አለፈልን ብለው ቢያናንቁሽም
አትፍረጂባቸው!
የድሃ ብረት ድስት መቼም አይለቅሽም
#ስሜታዊ_ሆነው_ነው
[ ጥሩቤል ]
@ebuh_bhr
@getem
@getem
@getem
ከሳምንታት በፊት ንግሥቴ እንዳላሉሽ
የኔማ ሽሮዬ ብለው እንዳልተቀኙ
ጥለውሽ ነጎዱ ሚሽቱን ሲያገኙ
.
እኔን የኔ አበባ
እኔን የኔ እመቤት
50 ቀን ቀርቶሻል ልትገቢ ዳግም ቤት
.
እኔ የኔ አበባ
እኔን የኔ ንግስት
ሰው ብቻ አይደለም
ማግጧል ያም ብረት ድስት
.
ሁሉም ከድተውሻል
ሁሉም ትተውሻል
ትንሽ ብቻ ታገሽ 50 ቀን ቀርቶሻል
.
ያኔ ቀኑ ሲደርስ በእየንብርክካቸው
ማሪኝ ማሪኝ ሽሮ አይቀር ማለታቸው
.
እኔን የኔ አበባ
እኔን የኔ እመቤት
50 ቀን ቀርቶሻል ልትገቢ ዳግም ቤት
አለፈልን ብለው ቢያናንቁሽም
አትፍረጂባቸው!
የድሃ ብረት ድስት መቼም አይለቅሽም
#ስሜታዊ_ሆነው_ነው
[ ጥሩቤል ]
@ebuh_bhr
@getem
@getem
@getem
👍60😁39❤20🔥7🤩2👎1
, ( ግዛትሽ ነኝ )
እንደ ሀይቅ ጠልቄ ከሃገር የሰፋሁ
አለሜን ስፈልግ ከአለም የጠፋሁ
በልብሽ መቅደስ ውስጥ አብሬ የተሰፋሁ
ሰፊ ግዛትሽ ነኝ
ወሰን ያልወጣልኝ ለክብሬ ዘብ ያጣሁ
ወሰንሽን ደፍረው ግዛትሽን ሳይወርሱት
በዳው መሬትሽን መንጥረው ሳያርሱት
ነይና ግዛትሽን አንቺው ዘብ ሁኝለት
መረቡን አስፊ እና ወሰን አብጂለት
ዳግምም አታገኝው ብትባክኝ በስለት
ችላ ያልሽው ግዛት ገዥ ሰው ያገኘ ዕለት
ውቢቷን ቀለሜን ውዲቷን ህይዎቴን
አለሜን ስፈልግ አለሜን ማጣቴን
ላንቺ እንዲህ መሆኔን አንቺ ግን አታውቂም
አንቺ ግን አንቺ ግን አንቺ ግን አታውቂም
እውነት እልሽ አለሁ ያለ እኔም አትደምቂም
By Habtish
@getem
@getem
@getem
እንደ ሀይቅ ጠልቄ ከሃገር የሰፋሁ
አለሜን ስፈልግ ከአለም የጠፋሁ
በልብሽ መቅደስ ውስጥ አብሬ የተሰፋሁ
ሰፊ ግዛትሽ ነኝ
ወሰን ያልወጣልኝ ለክብሬ ዘብ ያጣሁ
ወሰንሽን ደፍረው ግዛትሽን ሳይወርሱት
በዳው መሬትሽን መንጥረው ሳያርሱት
ነይና ግዛትሽን አንቺው ዘብ ሁኝለት
መረቡን አስፊ እና ወሰን አብጂለት
ዳግምም አታገኝው ብትባክኝ በስለት
ችላ ያልሽው ግዛት ገዥ ሰው ያገኘ ዕለት
ውቢቷን ቀለሜን ውዲቷን ህይዎቴን
አለሜን ስፈልግ አለሜን ማጣቴን
ላንቺ እንዲህ መሆኔን አንቺ ግን አታውቂም
አንቺ ግን አንቺ ግን አንቺ ግን አታውቂም
እውነት እልሽ አለሁ ያለ እኔም አትደምቂም
By Habtish
@getem
@getem
@getem
❤28👍18