ግጥም ብቻ 📘
65.7K subscribers
1.54K photos
31 videos
61 files
176 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
. ተንበርክኮ መድረስ
ተጎንብሶ መንገስ
አቀርቅሮ ሹመት
አሽቀንጥሮ ድሎት
ጸሎት

እስኪበሩ ማንከስ
እስኪስቁ ማልቀስ
እስኪይዙ ማጣት
እስኪረቱ ችሎት
ጸሎት

By Rediet Aseffa

@getem
@getem
@paappii
69👍14🔥9
አታውቂም
(kerim

የተዋቡ አይኖችሽ ካልተፋብኝ እቶን
አፍሽ ካልጠራብኝ የርግማን መዓቱን
በዚህ ሁሉ መሀል
መዓዛሽን ካልማግኩት
ታድያ ምኑን ኖርኩት?
-
-
-
አለም ብትጠፋ
ካንቺ እጦት አይከፋ

አታውቂም
መኖርሽ እንደሚያኖረኝ
አታውቂም
ከሌላም አይቼሽ ደስታ እንደሚያሰክረኝ

ከኔ ደስታ ይልቅ ስለ አንቺ ደስታ
የልቤ መሻት ነው ስላንቺ አዬመታ

አላውቅም
ቅናት ይሉት ስሜት ወዴት ተሰወረ
ልቤስ ስለ እጦቱ ስለምን ታተረ?
(እንዳልኩሽ አላውቅም)


By @poem2513

@getem
@getem
@paappii
33👍20👎1🔥1😢1
ድንገት ያገኘሁት የድሮ ግጥሜ
____

ጀምበር ገባች ፥ መሸ
ያጸዳሁት ቤቴም ፥ መልሶ ቆሸሸ
አልጠፋም መብራቱ
አልተበላም 'ራቱ
አሁንም ክፍት ነው በርና መስኮቱ ።
ለቁር ተጋለጠ ፥ ጓዳዬ እንደ ውጪው
መቼ ነው የምትመጪው ?

መጽሐፍ ገለጥኩና መልሼ ዘጋሁት
ልጽፍ አሰብኩና ብዕሬን ወረወርኩት
መቆም መንጎራደድ
መቆም መንጎራደድ
መቆዘም መተከዝ ፥ በሐሳብ መሰደድ
ደርሶ ብንን ብንን
ደሞ ቁጭ ብድግ
ካንቺ ውጭ አላውቅም ምን እንደምፈልግ ።

ምኞት ነው ያለኝ ፥ ዝም ብሎ ምኞት
ወይ የማያኖር ፥ ወይ የማያስሞት

ትመጫለሽ እያልኩ በጉጉት ከምኖር
ምናለ በሞትኩኝ ለአንድ ለስድስት ወር ።

@getem
@getem
@paappii

By Hab Hd
74👍34😁26🤩7😢5
............

ትከተይኛለሽ ብዬ ስለማስብ
በሄድኩበት ሁሉ እጅ እንድሰበስብ
መዞር እፈራለሁ
ዞሬ ያጣሁሽ እንደው
ብቻዬን መሆኔስ ምን ነጻነት አለው
ትከተይኛለሽ
በአለሁበት አለሽ
ብዬ ስለማስብ
ትዝታ እንደ ገላ ይዳብሰኝና
አለሄደችም ብዬ
ልቤን አጽና..ና...ና
ጀርባዬን አምናለሁ
አንቺ ከነጠቀኝ
እውነት ምን ዋጋ አለው
ያልኖሩበት ነገ ተስፋው ምን ሊጠቅም
አለሽ ብዬ አምናለሁ
ዞሬ ግን አላቀም
በሄድኩበት ሁሉ
በሳር በገደሉ
እረኛ ያጣ በሬ በኮቴው ሲያደቀው
አንቺን ነሽ በዬ ነው በተስፈ የምስቀው
ጠረንሽ ቢጠፋኝ
ሽቶ ያኮፈሳት ላባም ሴት ፈልጌ
በሴሰኛ ስሜት ጭኗን ተፋትጌ
ሲረካ መንፈሴ
አንቺ ነሽ ብሎ ነው
የሚስቀው ጥርሴ
መቼም ለመኮነን
መዞርም አያሻም ሀጥያት በዝቷል ከፊት
የከፋኝ ጊዜ ነው የማቀው ያንቺን ፊት
ትከተይኛለሽ
ባለሁበት አለሽ
ብዬ ስለማምን
እንትን ተመኝቼ ጌታዬን ስለምን
የሷንም እላለው
ይሰማሽ እንደሆን
እንጃ ምን አውቃለሁ
መሄድ እንደቀላል
መንገዱን ሲያረዝመው
መድረስ አይናፍቅም
አለሽ ብዬ አምናለሁ
ዞሬ ግን አላቅም

By @mad12titan

@getem
@getem
@paappii
👍4026🔥4😢2
ስርአት!
(የሞገሤ ልጅ)
አንተ የእኔ ምትክ፣
የእራሴ መታያ የአብራኬ ክፋይ፣
እንኳንም ወለድኩህ፣
የፈጠረህ ፈቅዶ ዐይኔን በዐይኔ እንዳይ።

አንተ ግን ቸኩለህ፣
መልሰህ መሄድህ ወደመጣህበት፣
ምን ሰይጣን መክሮህ ነው፣
ያረከኝ በሃዘን እንድኮረማመት።

የውልህ ልንገርህ፣
ተወልዶ ማረፉ በሰላሳኛ ቀን፣
ላንተም ኪሳራ ነው፣
ለኔም የእድሜ ልክ ስብራት ሰቀቀን።

ያንተን ጉዳት ላርዳህ፣
ለገነት ከሆነ ሞትህ በዚህ እድሜ፣
እኔም አልገባሁም፣
ካንተ በላይ ኖሬ 55 ቀን ጾሜ።

By @tafachgitm

@getem
@getem
@getem
😢33👍239👎3😱2
..........


ቀለም
ጸሀይ አይደለችም የቸረች ተፈጥሮን
ውበቷ ነው እንጂ ጨለማን ሰውሮን
በነጭና ጥቁር
በበዛበት ህይወት
ተፈጥሮን በረሳ ቀለም በናፈቀው
ጸሀይ አይደለችም
ገላሽን አቅፎ ነው ጓዳዬ የሞቀው
ቤቴ የደመቀው
ያልተጋሩት እቶን
የሚማገዱበት ልክ እንደ ዕሳት ዕራት
ሞቶ የመኖር ብስራት
በብርሀኗ ውስጥ በሚንቦገቦገው
ፍቅርን ልፈልገው
ስዳራሽ እያዩ
ሞቶ ነው እያሉ ህያዋን ሲለዩ
ለዚህ ነው የምልሽ
ቀለም
ጸሀይ አይደለችም የሰጠች ተፈጥሮን
ውበቷ ነው እንጂ ጨለማን ሰውሮን
በሳት ላልተዳሩ
ላልተፋቀሩ!
ቅሉ አይገባቸውም የቀለም አደሱ
የፍቅራቸው ምሱ ?
ዕሳት ዕራት መሆን ጸጋ መች ታደለ
ከሚነድ ወላፈን ጠብታን ያከለ
ለዕሳት ነፍስ የዘራ ስጋውን ሰውቶ
ጸሀይ አይደለችም
ውበቷ ብቻ ነው የሚታየው ጎልቶ


By @mad12titan

@getem
@getem
@getem
👍2716🔥4
በየሰፈሩ ሰፍረን
በየአጥሩ ተንጠልጠለን
አድዋን ያህል
አድባር ጥለን

ካምና ርቀን
ዛሬን ንቀን
ነገን ናፍቀን
መራመዱ እየጨነቀን
በየጥጉ ተናንቀን

ቀኑን ማሰብ እስኪያስፈራው
የታለ ባለፈረሱ?
የታለ ባለ ባንዴራው?
የታል የትውልድ አደራው?

አድዋን ያህል ትልቅ ጥለት
አድዋን ያህል ህብር ቀለም
ክብሩ ገብቶን
ፍሬው ታይቶን
ሳንደምቅበት ተያይዘን
ሳንኮራበት ታሪክ መዘን
በጊዜ ፊት እንዲህ ፈዘን

ያከበረን ያስከበረን
ኩራት ሆኖ ያዘለቀን
አድዋ ያህል ዘ ላ ለ ም ቀን
ስሙን መጥራት
ድሉን ማሰብ ተናነቀን?!

By Thomas lemma

@getem
@getem
@paappii
👍3933🔥8😢3🤩1
"ድንቄም ቆራጭ"😁😁😁
"""""""""""""""""""""
ከልብ ተሠርንቆ ልውጣ አልውጣ እያለ፤
ያስገባንው ነገር ከአቅም ካየ"ለ።
ይውጣ ምናባቱ ልብን ከበሽተ ካላረገን ደህና፤
አንቅሮ መትፋት ነው ከሚያሳጣን ጤና።

ሰውም እንደዚህ ነው፥
የልባችን እሳት የልባችን ንዳድ ለሱ ከበረደው፤
የፍቅራችን ሙቀት ቀዝቅዞ ከታየው።
ምን ሊያረግ ይቀመጥ ሊሆነን ፈተና፤
ከተመቸው ይሂድ መንገዱ ያውና።

የልባችን መሻት መሻቱ ካልሆነ፤
የመውደድ ፍላቱ ከሱው ከተነነ።
ልቡ የሸፈተን አስረን ላናስቀረው፤
መንገዱ ያውና ይሂድ ከተመቸው።

ብዬ እፎክርና ዝቼ በሃሳቤ፤
አስሮ ያስቀመጠው ይሸነፋል ልቤ።

አድሮ ልመና...ተው ፍታኝ
የቃልህ እስረኛ ነኝ🥹

ምን ላርግ ከእኔ ዘንድ አልሰራም

ጦቢያ
ቀን 21
የካቲት፦2017-አርብ

@getem
@getem
@getem
👍4416
ሀሰት በከበባት ኢ ፍትሀዊ አለም ተከሳሽ በሙሉ ወንጀለኛ አይደለም

አይገርምም ...?

የሚታዘዙለት ሳርና ንፋሱ ሀጢአት የሌለባት ንፁህ ሳለች ነፍሱ
ወንጀለኛ ተብሎ ፤

ተከሳሽ ነበረ ክርስቶስ እራሱ፡፡

By Eyob Z Mariam

@getem
@getem
@paappii
119👍34😢8
Forwarded from ሥዕል ብቻ © (Leul M.)
የካቲት ወርሀ-ገብረ-ክርስቶስ ;

ቅዳሜ የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 8:30 ሰአት በገብረ ክርስቶስ ሙዚየም 6 ኪሎ ፧ አመታዊው አለማቀፍ የገብረክርስቶስ ቀን በስነ ግጥምና ስነ ጥበብ ደምቆ ይከበራል። ገብረክርስቶስንና ድንቅ ስራዎቹን የምትወዱ ሁሉ ተጋብዛችሁዋል። ፕሮግራሙ በቀጥታ ስርጭት ይተላለፋል።


ምንጭ
አርቲስት በቀለ መኮንን

@Seiloch
👍1511
ምኞት ምትጸንሰው

ምኞት ፀንሳ ሃጥያትን ትወልዳለች፣
ፑልም ተጀምራ ቁማር ትሆናለች።
ለመዝናናት በሚል በተልካሻ ምክንያት፣
ምኞት ትሄዳለች ወደ ትልቅ ሃጥያት።
ሃጥያት ሲተነተን በብዙ መንገድ ነው፣
እንደ ሃጥያቱ ብዛት በሲኦልም ሲኬድ የራስ ክፍል አለው።
ከሃሳቤ ሳልስት ከፑሉ ሳልወጣ፣
ቁማሩን ተወው እንጂ ከፑል ቤት አትውጣ።

By G.hanun

@getem
@getem
@getem
😁36👍186😱3🔥1🤩1
በግድ የፈለቀች
ጠብ አደረኩ እምባ
"በቃ ይፍቱኝ አባ"

ይሄ ነው ሀጥያቴ
ከእግሮ ስር ያራቀኝ
ምን ልስራ
ምን ላድርግ
አዚሙ እንዲለቀኝ?

አዩኝ ትክ ብለው
ቀረቡኝ
ቀረብኩኝ
መስቀል ተሳለምኩኝ

ከዛ ግን አላውቅም
ካልቾ .. ጥፊ .. ጨምቧ
".. ያማል እኮ አባ"

"ዝምበል"
"አባ ይፍቱኝ በል"

"አዎን አባ ይፍቱኝ"
አገላብጠው መቱኝ።

"ይኸው የኔ ጎበዝ
መንፈሰ ከርታታው
አንዲህ ነው ሚፈታው"
እስቲ ዝቅ
እስቲ ዝቅ
ከዛ አንዴ ድልቅ!

ወይኔ መድሃኒአለም
እጃቸው እንዴት ያማል፤
"የኔ ልጅ ይሰማል?"
በተዋጠ ልሳን
"አይሰማም አባ"
በድጋሚ ጨምቧ
የጠገበ ልጄን
ሳጠምቅ አልገኝም
እስቲ ከፍ ጨምቧ
ያንተማ አይጠፋኝም

እስቲ ከፍ ጥብስ
እስት ዝቅ ጨምቧ
"ይበቃኛል አባ!"

"ምኑ ነው ሚበቃህ?"
የኔን ትንሽ ዱላ
  ከሳር የቀለለ ፤
ንፅህና የታለ?
ድንግልና የታለ?

ከፍ ዝቅ ክልትው
ሸሸሁኝ በዳዴ ፤
አባ ይቅር በሉኝ
ተሳሳትኩኝ አንዴ
"ሰው አይደለው እንዴ?"

እሱማ ሰው ነበርክ
በእግዜር የሚፀና
ክህነቱስ ግና?
ድቁናውስ ግና?

ቀና በል  ያዝ ጧ!
አትወራጭ ፡ ድርግም!
"አይለምደኝም ዳግም"
እሱን ለግዜር በለው
ይኸው የኔ ፋንታ ፤
ከፍ ዝቅ ድርግም
"እባኮት የኔታ"

"ይቅር በሉ ይላል
ወንጌሉን አይርሱ
መመለሴን አይደል
ሚፈልገው እሱ?"
"እሱማ መተሃል
ዱላ ለወጉ ነው
ዳግም እንደማትሄድ
  .. ለማረጋገጫ ፤
"ይሄ ሁሉ እርግጫ?"

"ዝምበል"
"አባ ይፍቱኝ በል"
"እሺ ይፍቱኝ አባ"
ቀና ሳብ ጨምቧ

ከዛን ተረጋጉ
አየር ሳብ አረጉ
"ይኸውልህ ልጄ
አድገህ አይደል በእጄ
አይንህ ልቤን ወጋው
ከእሳት ሳይህ ሰጋው
ለዛ ነው የተቆጣው
እስኪ እጅህን አምጣው"

"ይኸው" ብዬ አቀበልኩ
"ለበረከት እንጂ
አይሆኑም ለመርገም፤
እንካ ዳዊት ድገም
ይበቃል የስካሁን
አንተን ሳይ ፈራለው
.. ከእቶን ከእሳት፤
ከንግዲህ አትሳሳት"

ብለው አሳለሙኝ
ዝቅ ስል አመመኝ
ለንስሃ  ያልወጣ
እምባዬ ቀደመኝ

ዱላ ያጀገነው
ልቤን ብሶት ገፋው
ስብርብር እያልኩኝ
ከእግራቸው ተደፋው

"አሳፈርኮት አባ
አሰደብኮት አባ
አስተምረው መና
አሳደገው መና
አልበሰልኩም ገና
አልበቃውም ገና
ይቅር በሉኝ አባ
አፉ በሉኝ አባ"
ብዬ ጥምጥም አልኩኝ
ጉልበታቸው ግርጌ
ጎትተው አነሱኝ
አቀፉኝ ሳብ አርገው፤
"ይሄን ልጅነት ነው
ጌታ ሚፈልገው"።

አሁን ለርሱ ስጋ
ባለበሰህ ፀጋ
ስለምትበድለው
ግፍን ስትሰበስብ ፤
እኔማ በእጄ ነህ
ለሞተልህ አስብ!።

አልቅስ እዘን እንጂ
ተስፋ ለማይቆርጠው
የምትድንበትን
ምክንያት ሲገጣጥም ፤
የጠገብክ እንደሆን
እናትህ ሆድ እንኳን
እኔን አታመልጥም!።

© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
79👍58🤩7🔥6😁6😱1
ወዬ ለኔ

ዘንድሮን ሁዳዴ
ሳልሰስት ለሆዴ
ንፍሮዉን አንፍሬ
ዳቤዉን ጋግሬ
ቢጫ ቆቤን ገዛዉ
መቋሚያም አሰራዉ
ዳሩ ምን ያደርጋል...........

ሠዉ'ነቴ አደፈ
ቃሌ ገረጀፈ
ሀሳቤ ሸፈፈ
ምን ያደርግልኛል ንፍሮ መቀቀሉ
ኑሽሮን እንብላ እስኪደርስ በአሉ።


በትዝታ ወልዴ እንደተፃፈ


@Tizita21
@getem
@getem
👍6940😢4😁2👎1
ሩህሩ ነበር ልብሽ፣
የዋህ የጨው እቃ፣
የማይከብድ ቀንበር፣
ተመቺ ለጫንቃ፤
አቃፊ ደጋፊ፣
ፈገግታ መጋቢ፣
የምሕረት ገባር፣
ከእውነት አጋቢ፤
ተናፋቂ ውበት፣
ውስጣዊ ብርሓን፣
የማይጨልም ትጋት፣
የሚደነቅ ልሳን፣
አቆራኝቶ ይዞ፣
ሰውረሽ ይዘሽው፣
የመወደድ ፅዋን እንዳይጎል ሞላሽው።

By @tafachgitm

@getem
@getem
@paappii
30👍24🔥4
ይች በሰማይ ላይ
የተሳለች ፀሐይ
በዓለም ሰልጥና መንበሯን ዘርግታ
መኖሯ ቀን ቢባል ማዘቅዘቁዋ ማታ
ለኔ ምን ሊፈይድ እኔን ምን ቸገረኝ
አትገዛኝም ፀሐይ የራሴ ዓለም አለኝ።
ፀሐይ ለዘላለም ሳቶጣም ብትቀር
የት አይቶኝ ጨለማ የት ደርሶ ከኔ በር
ባንች መምጣት መኼድ ነው ቀኔ ሚቆጠር።
በኔ ዓለም ውስጥ ያለሽ የኔ ፀሐይ አንች
ስትመጭ ይነጋል ይመሻል ስትኼጅ።

By @yonas_sileshi

@getem
@getem
@paappii
30👍26🔥3😁2
[በሠላሳ ክረምት]
.
.
ከቦኛል ፍርሀት ከቦኛል እርጅና
የጉብዝናው ወራት
በወጉ በወጉ አላለፈምና።
ያወዛውዘኛል የአዝማናት ነፋስ
መደገፊያ ምርኩዝ ከማን ብርቱ ልዋስ?
እነሳ የነበርኩ ተስፈንጥሬ እንዳነር
እራመድ የነበርኩ በግሮቼ ጀግኜ
ክንፌን ቆርጬ ጣልኩ ከፍርሀት ወግኜ።

ሳዘግም
እግሮቼ ሲርዱ
ስተኛ ጭኖቼ ሲበርዱ
የገላዬ ሙቀት ሲሸሽ ቀን ጠብቆ
ቆፈን ሲዳበለኝ እንደስም ተጣብቆ
እትቱ ዘፈኔ
ፀደይ እንዳልወጣ በጋን እንዳልገፋ
ግንባሩ ላይ ይዟል የማለፍ ወረፋ።

በሰላሳ ክረምት በሰላሳ በጋ
ገሚሱ የርግማን ጥቂቱ የፀጋ
ተብዬ ብጠየቅ “ምን አደረክበት?”
መልሴ
እንደሞላለት ሰው ዝም ብዬ ኖርኩበት።

By Yadel Tizazu

@getem
@getem
@paappii
41👍27😱3🔥2🎉1
.......


የሄዱትን ሁሉ
የገፋንን ሁሉ
ስቀን ሸኘናቸው
ስመን ጠቆምናቸው
በተዘጋ ጎጆ
በእንባ እየተራጨን
ከመገፋት ጽዋ
በቀል ተጎነጨን
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
መልከጥፋ መልካም
ብጉራም ቀፋፊ
ጎባጣ አንገት ደፊ
ነን ብለን አመንን
ውበትን ለመንን
የሄዱትን ሁሉ
የገፋንን ሁሉ
ስቀን ሸኛናቸው
በእናባ ጸለይናቸው
ፍቅርን ተሳልን
በበቀል ቆሰልን
ሳሚ ያጣ ከንፈር
አቃፊ ያጣ ገላ
የወደድነው ሁላ
ጸጸት አስጎነጨን
ስቆ ለእንባ እያጨን
አሸሸ መዳፋን
ነፈገን እቅፋን
ጸደቁብን በቃል
ውበት ልብ ይበቃል
ብለው ልብን ሸሹ
ገፍተው አቆሸሹ
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
መልከጥፋ መልካም
ብጉራምም ቀፋፊ
ጎባጣ አንገት ደፊ
ጉለት ሆንን ያምላካቸው
ያምላካችን
በመልካችን
ለወደድነው አነስን
ለአፈቀርነው እረከስን
ተጎነጨን መገፋትን
መተፋትን
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን


By @mad12titan

@getem
@getem
@getem
👍3011🔥9👎1
| በዚህ አለም፥ በዚህ ህይወት ፍቅር እስካ'ለ -
ለህልም፥ ለመሻት፥ ለምኞት ሁሌ መንገድ አለ።
ለእያንዳንዱ ድቅድቅ ለሊትም ብሩህ እለት አለ።

እውነቱን ስነግርሽ፦ ፈተና ነበረ በየዕለቱ፣
ሰኞ ተሰብሬ - ተነሳሁ በነጋታው በጠዋቱ።

ማክሰኞ በተስፋ እያለምኹ ዋልኹና
ረቡዕ ከሰርኹ - የእጄ ስራ ቀረ መና።

ሐሙስ ቆምኩኝ፥ ፍቅርሽን ጥበቃ
ለአማልክቱ ምስጋና ይግባቸውና -
አርብ ላይ ደረስኹ መንገዴ ነውና!

ቅዳሜን ነደድኹ ጨስኹ -
ፍቅሬን አንቺን እየጠበቅኹ፥
ሰንበትን ከመቅደሱ ቀረኹ!

ውዴ

የፍቅርሽን መንገድ እጓዛለኹ! እጓዛለኹ!
ሰንበት ሰንበት ሲሆን ቆሜ ጠብቃለኹ!

በመጠበቅም ቆሞ፥
|
በመፈለግም ሄዶ፥
|
እኔ አፈቅርሻለኹ!


•°•°•°•°•°•°••°°••°•°•°°•°•°•°•°•°•°•°•°•°•°•
በዚህ ምድር፥ በዚህ ህይወት ፍቅር እስካለ
የሚረታኝ፥ የሚያቆመኝ፥ የሚይዘኝ ማን አለ?

በዚህ አለም በዚህ ህይወት ፍቅር እስካ'አለ
ለህልም ለመሻት ለምኞት ሁሌ መንገድ አለ
ለእያንዳንዱ ድቅድቅ ለሊት ብሩህ እለት አለ

•°•°•°••°•°•°•°•°°••°•°•°•°•°•°•°•°°•°•°

By ናኹ

@getem
@getem
@paappii
👍3028
ቃለኛ ናት ለእግዜር ወጉ
ልባም ትጉህ
ኪዳን አዛይ ልበ ብርቱ
ዳር እስከ ዳር ከአስረቱ
ንቃ አተኛም ለሰዓቱ

ወተቲቱ!

ለ ሶስት ለስድስቱ
ለዘጠኝ ሰዓቱ
ቁሞ ጠላይ ለእግዜር
ነጣላ አንጋቢቱ
ተንበርካኪ ካፈር ከስነ ስዕሉ
አሜን ቃለ ከንፈር ለመረቃት ሁሉ
ጦም ኣዳሪ አትወላውል
አታውቀውም የላት ስልቱ
ወድቃ ማትገዛ ለነገረ ከንቱ

ወተቲቱ!

ዮኒ
      ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
👍198🔥1
ከዳመናው መሀል ይፈልቃል ኃያል ጢስ
ድል ለሀገሬ ሊሰጥ
በፈረሱ ይነጉዳል የአራዳው ጊዮርጊስ
ይዘምታል በሰማይ አማኝ ህዝቡን ከልሎ
የአምላክ ውብ ምድር
ቅድስት ኢትዮጵያ አትደፈር ብሎ

ይጎርፋል ሰው
ጦር ጋሻውን በእጁ አንጠልጥሎ
ምንሽር አልቤኑን በጀርባው ላይ አዝሎ
በባዶ እግሩ ጋሬጣውን ረቶ
እንዴትስ ይቀራል
ከንጉሱ ከንፈር የማርያም ስም ወጥቶ

ልክ እንደ ጦር እቃ ታቦት ተሸክሞ
ልክ እንደ አዘቦት ቀን በጾም ተሸልሞ
ቅንጣት እህል ሳይጎርስ በእምነቱ ቁሞ
ቅዳሴውን ሳይሽር በሰዓቱ ተገኝቶ
‹‹አሀዱ›› ሲል በህብረት አንድነት ገንብቶ
የዋለ ገበሬ የዋለ ሰራዊት
ድል አፍሶ ቢመለስ ይደንቃል ወይ ጥቂት?
(አይደንቅም)

አቡነ ማቲዎስ እምነትን አግዝፈው
ለሰራዊት ሲባል
‹‹ጾም ይሻር›› የሚል ትእዛዝ ተላልፈው
ከንጉስ ተሟግተው
በመስቀል አሳልመው
ባርከው ተዋጊውን ቢልኩ ወደ ውጊያ
ሰው በእህል ሳይሆን
በእምነት እንደሚረታ
ምስክር ትሆን ዘንድ አሸነፈች ጦቢያ

እኔ ግን
የድል ታሪክ ይዤ
ቆሚያለሁ ፈዝዤ
ተኝቻለሁ ደንዝዤ
አልስራ ጀብድ አልፈጽም ገድል
እንዴት ያቅተኛል
መዘከር እንኳን የአባቶቼን ድል?
ቢገባኝ ኖሮ የነጻነት ክብር
የካቲት ጊዮርጊስ
ስዕለት ባስገባሁ ለመቆሜ ተአምር

በባዶ እግር ሄዶ ጫማ ያለበሰኝ
ከአራቱም አቅጣጫ
ለአንድ አላማ ዘምቶ ሀገር ያወረሰኝ
በዘር ጎጠኝነት
ተከፋፍዬ ቢያይ በእንባው በወቀሰኝ
‹‹ ከአንድነት እርካብ ቁልቁል ተፈጥፍጠህ
በቁንጽል ማንነት ራስክን ለውጠህ
የምትኖር ሁላ አድዋን አስታውሰህ
ሁን እንደ ጥንቱ ፍቅርን ተንተርሰህ
አሻፈረኝ ካልክ ግን
‹‹ማርያምን!›› እፋረድኃለው በሰማይ
በሀገሬ ጀርባ ላይ ፈልተኃል እንደ ተባይ ››
ብሎ ባወጀብኝ
ሽልብታዬን አይቶ
እብደቴን ታዝቦ ከሞቴ ባነቃኝ
ጾም ጸሎትን ትቼ
አርብ ሮብን ረስቼ
ቅዳሴ ሰዓታት
ማህሌት ኪዳንን እኒህን ዘንግቼ
ለሆዴ አድሬ ስኖር እንደ አሳማ
ይደንቃል ወይ እውነት
ተረግጬ ብቀር ልክ እንደ ቄጤማ?
ተንኜ ብቀር ልክ እንደ ጤዛ?
ተሸንፌ ብታይ ወድቄ እንደ ዋዛ?
(አይደንቅም)

ዋ ለእኔ!
ዋ እኔ!
ርግብ ጋር ዘምቼ
ለቀረሁኝ ሞቼ

#ኤልዳን
@marda129

@getem
@getem
@getem
21👍17🔥2
ላረፈድሽው


እኔማ ጠባቂሽ
ማርፈድሽን አላይም መምጣትሽን ብቻ
ድረሽልኝ እንጅ
በዘመኔ ማብቂያ በዕድሜዬ መባቻ

ፀጉሬ ቢሸበባብት ስጋዬ ቢጃጅም
ይበስል እንደሁ እንጅ
መንፈስ አያረጅም
ነይ ፍቅሬ ወጣት ነው ልቤም እቶን እሳት
የተገላቢጦሽ ቢያደርገውም ቅሉን
የዘመን መሳሳት
ከመቅረት ይሻላል ከመጣሽ ቢረፍድም
ፅልመት ካልገፈፈ ወትሮም ጎህ አይቀድም

By @poem2513

@getem
@getem
@getem
36👍20😢3🔥2