ሎጥ ነሽ
🦘
ቅጥልጥል ፥ብግንግን ፥እርር እምር ፤
ዝምም፥ ልምም ፥እድር ፤
እፍን፥ እምቅ ፥ላጀብ ፥ብድር ፤
ለወዝ ላይላፋ ፥ለዳገቱ ስብር ፤
ተንስኢ ላስነግር ፥በዋጉ ሰው አንዲር ፤
እኛ...እ'ድር..እኔ ላብር ፥ለራስ ሳድር ፣
ላለም ደረት ንፍት፥ ለራስ አንገት ስብር
'
'
ላክል ፤
ባክል ፤
ላንስ ፤
ዳንስ ፤
አይሆን ላይሆን ፥
ላገር ስሪያ ማሰሪያ ፣
መች አምሳሏ ነበረ፥
ያከበረችው ጥያ ፣
ቀጥ ብላ ማንጋጠጥ፥
ሎጥነሽ ወይ ?ኢትዬጵያ....
'
'
ግዕዝ ሙላት 🦘
@geez_mulat
@getem
@getem
@getem
🦘
ቅጥልጥል ፥ብግንግን ፥እርር እምር ፤
ዝምም፥ ልምም ፥እድር ፤
እፍን፥ እምቅ ፥ላጀብ ፥ብድር ፤
ለወዝ ላይላፋ ፥ለዳገቱ ስብር ፤
ተንስኢ ላስነግር ፥በዋጉ ሰው አንዲር ፤
እኛ...እ'ድር..እኔ ላብር ፥ለራስ ሳድር ፣
ላለም ደረት ንፍት፥ ለራስ አንገት ስብር
'
'
ላክል ፤
ባክል ፤
ላንስ ፤
ዳንስ ፤
አይሆን ላይሆን ፥
ላገር ስሪያ ማሰሪያ ፣
መች አምሳሏ ነበረ፥
ያከበረችው ጥያ ፣
ቀጥ ብላ ማንጋጠጥ፥
ሎጥነሽ ወይ ?ኢትዬጵያ....
'
'
ግዕዝ ሙላት 🦘
@geez_mulat
@getem
@getem
@getem
👍31❤8🔥5😱3
“ስኬተኛ ማነው ?”
ብዬ ጠየቅኋቸው
ታዋቂ አመጡልኝ
ይሄ ነው መልሳቸው ።
አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …
አሳዩኝ ከበርቴ
ባለ ንብረት ፣ ነዋይ
እንደዚህ ያለውን
ቀና ብዬም አላይ።
አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …
አመጡልኝ ምሁር
ፊደል የቆጠረ
የተመራመረ
ይሄም አልሰመረ።
አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …
ጠሩ ባለ ጥበብ
በጥሁፍ በቅኔ
ያስገኘልን ረብ
(በርግጥ ጥሩ ነበር
እንደዚህ ሲታሰብ )
መልስ ግን አይደለም።
አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …
አንድ አጩ ቀጥሎ
ጽድቁን አደላድሎ
ያናናቀ ሞቱን…
የቃል ጥሩር ለብሶ
ያስታጠቀ ነፍሱን…
አገኙብኝ መልሱን !
(ሚካኤል አ)
@getem
@getem
@getem
ብዬ ጠየቅኋቸው
ታዋቂ አመጡልኝ
ይሄ ነው መልሳቸው ።
አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …
አሳዩኝ ከበርቴ
ባለ ንብረት ፣ ነዋይ
እንደዚህ ያለውን
ቀና ብዬም አላይ።
አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …
አመጡልኝ ምሁር
ፊደል የቆጠረ
የተመራመረ
ይሄም አልሰመረ።
አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …
ጠሩ ባለ ጥበብ
በጥሁፍ በቅኔ
ያስገኘልን ረብ
(በርግጥ ጥሩ ነበር
እንደዚህ ሲታሰብ )
መልስ ግን አይደለም።
አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …
አንድ አጩ ቀጥሎ
ጽድቁን አደላድሎ
ያናናቀ ሞቱን…
የቃል ጥሩር ለብሶ
ያስታጠቀ ነፍሱን…
አገኙብኝ መልሱን !
(ሚካኤል አ)
@getem
@getem
@getem
👍47❤30🤩3
ወዳንቺ እዘረጋለሁ!
ባድግ ብዬ
ባውቅ ብዬ
አንዳች ምስጢር ተረድቼ ባልፍ ብዬ!
መቃብር ቤቴን ማሞቂያ
የሙት መንደሬን ማድመቂያ
ካለፉም ወዲያ መታወቂያ…
የምትሆን
አንድ ሀተታ
አንድ እውነታ
የህይወትን ምናልባት
የመኖርን እልባት
አውቃት ነበር እንድልባት
ወዳንቺ እዘረጋለሁ!
ከሰማይ በታች አዲስ ነገር
ከምድር ከፍ ብሎ የሚነገር
“የከንቱ ከንቱ” የምትባል
የአላዋቂን ፈላስፋ
በአፍጢሙ የምትደፋ
ስታቅፊ ዐለም እንደሚጠቀለል
ስትገፊም ሰውነት ከላባ እንደሚቀል
ስትስሚ ኢምንት እንዲሆን ጠፈሩ
ስትነክሺም ማንነት እንደሚበተን አፈሩ…
ይቺን ምስጢር ተረድቼ ባልፍ ብዬ
የህይወት መስመሬን ማንቂያ
ውሎ አዳሬን መደበቂያ
ተስፋ ህልሜን መታረቂያ
የምትሆን
አንዲት ሁነት
አንዲት ኪነት
የመክረምን ፍልስምና
ከንቱነት ላይ ውብ አድርጋ ሸምና
ታውቀኝ ነበር እንድልባት
ወዳንቺ እዘረጋለሁ ካልተረሳሁ ምናልባት።
By Yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
ባድግ ብዬ
ባውቅ ብዬ
አንዳች ምስጢር ተረድቼ ባልፍ ብዬ!
መቃብር ቤቴን ማሞቂያ
የሙት መንደሬን ማድመቂያ
ካለፉም ወዲያ መታወቂያ…
የምትሆን
አንድ ሀተታ
አንድ እውነታ
የህይወትን ምናልባት
የመኖርን እልባት
አውቃት ነበር እንድልባት
ወዳንቺ እዘረጋለሁ!
ከሰማይ በታች አዲስ ነገር
ከምድር ከፍ ብሎ የሚነገር
“የከንቱ ከንቱ” የምትባል
የአላዋቂን ፈላስፋ
በአፍጢሙ የምትደፋ
ስታቅፊ ዐለም እንደሚጠቀለል
ስትገፊም ሰውነት ከላባ እንደሚቀል
ስትስሚ ኢምንት እንዲሆን ጠፈሩ
ስትነክሺም ማንነት እንደሚበተን አፈሩ…
ይቺን ምስጢር ተረድቼ ባልፍ ብዬ
የህይወት መስመሬን ማንቂያ
ውሎ አዳሬን መደበቂያ
ተስፋ ህልሜን መታረቂያ
የምትሆን
አንዲት ሁነት
አንዲት ኪነት
የመክረምን ፍልስምና
ከንቱነት ላይ ውብ አድርጋ ሸምና
ታውቀኝ ነበር እንድልባት
ወዳንቺ እዘረጋለሁ ካልተረሳሁ ምናልባት።
By Yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
👍31❤17
ለተለያዩ የማስታወቂያ፣ የዘፈን ክሊፕ እና ድራማዎች ስራዎች በአዲስ አበባ ውስጥ ብቻ የሚኖሩ ሰዎችን ካስት ማድረግ እንፈልጋለን። - እድሜያቸው ከ35-45 - ከ25-30 - ከ10-18 ያሉ ወንዶችን እና ሴቶችን በአስቸኳይ እንፈልጋለን። የሚከተሉትን በቴሌግራም ይላኩልን። - 1 ሙሉ ሰውነት የሚያሳይ ፎቶ - 1 ከወገብ በላይ - 1 ፈገግታ የሚያሳይ ፎቶዎችን - ስም ስልክ እና እድሜ በሚከተለው አድራሻ ይላኩልን። https://t.me/Ribki30 ስልክ የሚደወልላቸው ለስራው ሲመረጡ ብቻ ስለሆነ በትዕግስት ይጠብቁ ዘንድ እንጠይቃለን።
Telegram
Ribka Sisay
Ave Maria💛
👍19❤3
❝ ሣቅ ተከሽኖ ግጥም ተመጥኖ ❞ ታላቅ የመክፈቻ ፕሮግራም በግዮን ሆቴል !
ዘሃ ኢቨንትስ ከግዮን ሆቴል ጋር በመተባበር የሚያዘጋጀው የኪነጥበብ ምሽት ፤ 4ተኛ መድረኩን አርብ ታህሣሥ 25 - 2017 ዓ.ም ምሽት ከ10 : 30 ጀምሮ ያቀርባል ።
ጋሽ አያልነህ ሙላት ፣ ሠዓሊ እሸቱ ጥሩነህና ኮሜዲያን ደረጄ ሀይሌ የክብር እንግዶቻችን ናቸው ።
የምሽቱ ፈርጥ ልዩ የክብር እንግዳችን አርቲስት ዓለም ፀሀይ ወዳጆ ናት ።
ደራሲና ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም እና ሰለሞን ሳህለ ውብ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ።
ኮሜዲያን ናሆም በየነ መድረኩ ላይ ይደምቃል ፤ የአብጸጋ ተመስገን የተከሸነች ወግ አዘጋጅቷል ፤ ፈገግታ ባንድ ጥዑም ሙዚቃዎቹን አሰናድቷል ፣ ሒስ ፣ አጭር ፊልም ፣ ስዕልና ሌሎች ብዙ ትርዒቶች ተዘጋጅተዋል ።
ለበለጠ መረጃ በ 0935697143 ይደውሉ ።
የ YouTube ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ 👍
https://youtube.com/channel/UC9ItbVvxXMLV7QIT-rCJyTg?si=Mj5GlhjsE1ZvBtjM
@getem
@getem
ዘሃ ኢቨንትስ ከግዮን ሆቴል ጋር በመተባበር የሚያዘጋጀው የኪነጥበብ ምሽት ፤ 4ተኛ መድረኩን አርብ ታህሣሥ 25 - 2017 ዓ.ም ምሽት ከ10 : 30 ጀምሮ ያቀርባል ።
ጋሽ አያልነህ ሙላት ፣ ሠዓሊ እሸቱ ጥሩነህና ኮሜዲያን ደረጄ ሀይሌ የክብር እንግዶቻችን ናቸው ።
የምሽቱ ፈርጥ ልዩ የክብር እንግዳችን አርቲስት ዓለም ፀሀይ ወዳጆ ናት ።
ደራሲና ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም እና ሰለሞን ሳህለ ውብ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ።
ኮሜዲያን ናሆም በየነ መድረኩ ላይ ይደምቃል ፤ የአብጸጋ ተመስገን የተከሸነች ወግ አዘጋጅቷል ፤ ፈገግታ ባንድ ጥዑም ሙዚቃዎቹን አሰናድቷል ፣ ሒስ ፣ አጭር ፊልም ፣ ስዕልና ሌሎች ብዙ ትርዒቶች ተዘጋጅተዋል ።
ለበለጠ መረጃ በ 0935697143 ይደውሉ ።
የ YouTube ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ 👍
https://youtube.com/channel/UC9ItbVvxXMLV7QIT-rCJyTg?si=Mj5GlhjsE1ZvBtjM
@getem
@getem
👍20🤩3❤2
አቀርቃሪ አሉኝ፣
ቀና ብሎ ማየት መራመድ ሲሸሸኝ፣
ሊያብድላት ነው አሉኝ፣
በቁሜም በሕልሜም ቅዠት ሲረብሸኝ።
ሊረታ ነው አሉኝ፣
ስንቀጠቀጥላት ስሟ ትዝ ሲለኝ፣
ትክክል ናቸው ወይ፣
እኔ ከምወስን እናንተ ንገሩኝ?
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@getem
ቀና ብሎ ማየት መራመድ ሲሸሸኝ፣
ሊያብድላት ነው አሉኝ፣
በቁሜም በሕልሜም ቅዠት ሲረብሸኝ።
ሊረታ ነው አሉኝ፣
ስንቀጠቀጥላት ስሟ ትዝ ሲለኝ፣
ትክክል ናቸው ወይ፣
እኔ ከምወስን እናንተ ንገሩኝ?
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@getem
❤31👍17🤩7👎3😁2
.............
ትብታብ አይደለም ድግምት
ደብተራ አይደለም አስማት
ንጹሕ ፍቅር ነው ምናኔ
ለሚወዱት የመሞት ጭካኔ
እንኳን አሁን፤ከገላዬም ደም ቢነጥፍ
ደምስሬም ጅማቴም
ስምክን ነው የሚጥፍ
ዘረ ደሀ አፈቀርሽ
ዘራችንን አረከሽ
ብለው ቢያጠምቁኝም
ለፍቅርህ ስለሆን
የክፉዋች ጸበል፤መድን አይሆነኝም
ይልቅ በዛብህ፤አንጀትክን ሰብስብ
ከዛሬ ይልቅ፤ነገህን አስብ
አይዞህ በዛብህ፤ይህን ቀን ቻለው
ሰብለ ወንጌልህ
ከአትሮንስ ወርጄ ተጠፍሬያለው
ግን አትሳቀቅ፤ይህም ቀን ያልፈል
የክፉ ጅራፍ፤ጽናት ይጽፉል
የሚለው ቃሏን፤ከፍቅሩ ሰምቶ
በተስፋ አባብሎ፤ልቡን አጽናንቶ
ከተማ ገብቶ ቢጠብቃትም
ወንጌሉን ካሻው አላገኛትም
የእግዜር ኑዛዜ፤የእውነት ቃሉ
የአዳም ጥፋት፤የአምላክ አምሳሉ
የሄዌን ስህተት፤ክፉይ አካሉ
አትብላ ካለው፤ከፍሬው በልቶ
ፍቅርን በደለው፤የሞት ሞት ሞቶ
ግን በበዛብህ፤ቃሉ ልዩ ነው
ከህይወት መስቀል፤አዳኙ ማነው
አዳም ከበላው፤በለስ ሲያላምጥ
ከወንጌል ይልቅ፤ልቡን ሲያስበልጥ
ፍቅርን በደለው፤የኑሮ ጣጣው
በቃሉ አኑሮ በእውነቱ ቀጣው
ድሮም ያን ጊዜ፤በኦሪት ዘመን
ክፉ ጎልያድ፤በሀይል ሲዘምን
ጉልበቱን ነስቶ፤መሬት ያኖረ
ጠጠሩ ሳይሆን፤እምነት ነበረ
በማፍቀር እምነት፤ነፍሱን አጽንቶ
ቢጠብቃትም ከተማ ገብቶ
ወንጌሉን አጣት፤ከባዕድ ሀገር
የህመም ጥልቁን፤ለማን ይናገር
ህልሙን አለሙን፤ሁሉንም ትቶ
አቅሉን እስኪስት፤ወንበዴ እጅ ገብቶ
በፍቅር መስቀለ የተሰቀለ
ኤሎሄ አይደለም፤ሰብለ ነው ያለ
የእግዜር ማቅ ለባሽ፤አንቺ መነኩሴ ሴት
እረፍትን ፍለጋ፤ከገባሽበት ቤት
ካልጋ ያገኘሽው፤እሱ ነው ወንጌልሽ
ጣር ባሰረው ድምጸት
ሰ...ሰ..ሰብለ ብሎ የሚልሽ
እንዲ ነው ፍቅር፤እንዲ ነው ስቅለት
እንዲ ነው መሞት፤እንዲህ ነው ድህነት
ፍቅር ቢበድል፤የእውነት ልኩ
ወንጌል ያጣ ሰው፤ወንጌል ነው መልኩ
Based on ፍቅር እስከ መቃብር
by @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
ትብታብ አይደለም ድግምት
ደብተራ አይደለም አስማት
ንጹሕ ፍቅር ነው ምናኔ
ለሚወዱት የመሞት ጭካኔ
እንኳን አሁን፤ከገላዬም ደም ቢነጥፍ
ደምስሬም ጅማቴም
ስምክን ነው የሚጥፍ
ዘረ ደሀ አፈቀርሽ
ዘራችንን አረከሽ
ብለው ቢያጠምቁኝም
ለፍቅርህ ስለሆን
የክፉዋች ጸበል፤መድን አይሆነኝም
ይልቅ በዛብህ፤አንጀትክን ሰብስብ
ከዛሬ ይልቅ፤ነገህን አስብ
አይዞህ በዛብህ፤ይህን ቀን ቻለው
ሰብለ ወንጌልህ
ከአትሮንስ ወርጄ ተጠፍሬያለው
ግን አትሳቀቅ፤ይህም ቀን ያልፈል
የክፉ ጅራፍ፤ጽናት ይጽፉል
የሚለው ቃሏን፤ከፍቅሩ ሰምቶ
በተስፋ አባብሎ፤ልቡን አጽናንቶ
ከተማ ገብቶ ቢጠብቃትም
ወንጌሉን ካሻው አላገኛትም
የእግዜር ኑዛዜ፤የእውነት ቃሉ
የአዳም ጥፋት፤የአምላክ አምሳሉ
የሄዌን ስህተት፤ክፉይ አካሉ
አትብላ ካለው፤ከፍሬው በልቶ
ፍቅርን በደለው፤የሞት ሞት ሞቶ
ግን በበዛብህ፤ቃሉ ልዩ ነው
ከህይወት መስቀል፤አዳኙ ማነው
አዳም ከበላው፤በለስ ሲያላምጥ
ከወንጌል ይልቅ፤ልቡን ሲያስበልጥ
ፍቅርን በደለው፤የኑሮ ጣጣው
በቃሉ አኑሮ በእውነቱ ቀጣው
ድሮም ያን ጊዜ፤በኦሪት ዘመን
ክፉ ጎልያድ፤በሀይል ሲዘምን
ጉልበቱን ነስቶ፤መሬት ያኖረ
ጠጠሩ ሳይሆን፤እምነት ነበረ
በማፍቀር እምነት፤ነፍሱን አጽንቶ
ቢጠብቃትም ከተማ ገብቶ
ወንጌሉን አጣት፤ከባዕድ ሀገር
የህመም ጥልቁን፤ለማን ይናገር
ህልሙን አለሙን፤ሁሉንም ትቶ
አቅሉን እስኪስት፤ወንበዴ እጅ ገብቶ
በፍቅር መስቀለ የተሰቀለ
ኤሎሄ አይደለም፤ሰብለ ነው ያለ
የእግዜር ማቅ ለባሽ፤አንቺ መነኩሴ ሴት
እረፍትን ፍለጋ፤ከገባሽበት ቤት
ካልጋ ያገኘሽው፤እሱ ነው ወንጌልሽ
ጣር ባሰረው ድምጸት
ሰ...ሰ..ሰብለ ብሎ የሚልሽ
እንዲ ነው ፍቅር፤እንዲ ነው ስቅለት
እንዲ ነው መሞት፤እንዲህ ነው ድህነት
ፍቅር ቢበድል፤የእውነት ልኩ
ወንጌል ያጣ ሰው፤ወንጌል ነው መልኩ
Based on ፍቅር እስከ መቃብር
by @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍37❤31😁1
የነገዬ ምርኩዝ የትናንት መፅናኛ
የህይወቴ ትርጉም የጊዜ መዳኛ
መራመጃ መንገድ ህመምን አስረሽ
የፅልመቴ መብራት እኔን አስታዋሽ
ጣዕም ሰጭ ስኳር ህይወት ማጣፈጫ
የዛሬን ትካዜ
የዛሬን ፍዛዜ
በያልፋል ደስታ ስሜት መቀየጫ
የዋሻ ውስጥ ጮራ ፍንጣቂ ብርሀን
የህይወቴ ካርታ የመርከቤ ካፕቴን
ትርጉም አልባን እኔን ሀዘን የወረረኝ
ከጥልቅ ትካዜ ውስጥ ወዝውዞ ያነቃኝ
ተስፋ ነው ሻማዬ...
ተስፋ ነው ሻማዬ
የትናንትን ፅልመት ዛሬን ያበራልኝ
By ዘይድ ሁሴን
ታህሳስ -27 -2017
@getem
@getem
@getem
የህይወቴ ትርጉም የጊዜ መዳኛ
መራመጃ መንገድ ህመምን አስረሽ
የፅልመቴ መብራት እኔን አስታዋሽ
ጣዕም ሰጭ ስኳር ህይወት ማጣፈጫ
የዛሬን ትካዜ
የዛሬን ፍዛዜ
በያልፋል ደስታ ስሜት መቀየጫ
የዋሻ ውስጥ ጮራ ፍንጣቂ ብርሀን
የህይወቴ ካርታ የመርከቤ ካፕቴን
ትርጉም አልባን እኔን ሀዘን የወረረኝ
ከጥልቅ ትካዜ ውስጥ ወዝውዞ ያነቃኝ
ተስፋ ነው ሻማዬ...
ተስፋ ነው ሻማዬ
የትናንትን ፅልመት ዛሬን ያበራልኝ
By ዘይድ ሁሴን
ታህሳስ -27 -2017
@getem
@getem
@getem
❤34👍30😢4🔥1
ቢሆንም
ፍቅር ይሉት ጣጣ ሲፀነስ
ሰው ከሰውነቱ ላይ ሲቀነስ
አይተናል
አይተናል የነበር ፍቅር ሲለፈፍ
በከሸፈ ፍቅር ጤንነት ሲቀሰፍ
አይተናል
ፍቅር የመርገምት ቃል እስኪመስለን
ከእጦት በላይ ንቀታቸው ያቆሰለን
አይተናል
በጫማቸው በረገጡን
ከትቢያ ላይ ባስቀመጡን
ላቀመሱን የፍቅርን ፅዋ መራር ጣዕም
ልክፍት ነውና
ይሄው እስከዛሬ እንፅፋለን ግጥም
ቢሆንም
በዬ ዘፈኑ ሆድ የባሰን
የናፍቆት ህመም የዳበሰን
አንድ ሰው ለመውደድ ዘመናት ያነሰን
ስንት አፍቃሪ አለን
የትዝታ ፈረስ ወስዶ ሚመልሰን
የማይመጣ እንደሚጠብቁ ቢታወቅም ቅሉ
በአልኮል በሲጋራ በጫትም ገረባ የተጠለሉ
ከእልፍ አእላፍ የበዙ ስንት ልቦች አሉ ?
By kerim
@poem2513
@getem
@getem
@getem
ፍቅር ይሉት ጣጣ ሲፀነስ
ሰው ከሰውነቱ ላይ ሲቀነስ
አይተናል
አይተናል የነበር ፍቅር ሲለፈፍ
በከሸፈ ፍቅር ጤንነት ሲቀሰፍ
አይተናል
ፍቅር የመርገምት ቃል እስኪመስለን
ከእጦት በላይ ንቀታቸው ያቆሰለን
አይተናል
በጫማቸው በረገጡን
ከትቢያ ላይ ባስቀመጡን
ላቀመሱን የፍቅርን ፅዋ መራር ጣዕም
ልክፍት ነውና
ይሄው እስከዛሬ እንፅፋለን ግጥም
ቢሆንም
በዬ ዘፈኑ ሆድ የባሰን
የናፍቆት ህመም የዳበሰን
አንድ ሰው ለመውደድ ዘመናት ያነሰን
ስንት አፍቃሪ አለን
የትዝታ ፈረስ ወስዶ ሚመልሰን
የማይመጣ እንደሚጠብቁ ቢታወቅም ቅሉ
በአልኮል በሲጋራ በጫትም ገረባ የተጠለሉ
ከእልፍ አእላፍ የበዙ ስንት ልቦች አሉ ?
By kerim
@poem2513
@getem
@getem
@getem
👍64❤24
ባያቸውስ ኖሮ ?
(ሚካኤል አስጨናቂ)
እርግት ያለች ወተት
ስክን ያለች ቡና …
ይሄን ችኩል ዘመን
አልዋጀችምና …
ተንገበገብኩላት
ተሳተብኝ አቅሌ
ሆንኩላት ባተሌ ።
ጥልል እንደ ጠላ
ኩልል እንደ ጠበል
ከአንገቷ ስር ገነት
ገድ ጥሎኝ ብጠለል
አ..ን..ሰ…ፈ…ሰ…ፈ…ች….ኝ
አ…ር..ገ…ፈ...ገ…ፈ…ች…ኝ
ቃላት ሳ’ተነፍስ
ጥርሶቿን ሳትገልጥ
ቅቤ ሆነ ልቤ..
ገጽዋ ላይ ሲቀልጥ ፤
ያን ጊዜ ተቃናች !
ብታጣብኝ ኩራት
ስስ ጎኔ ቢገርማት
(ዓይኖቿ ፍም እሳት)
አንገቴን ሰበርኩኝ
ፈርቼው ይሄን ፍም
ቢሆንም …
ቢሆንም …
ለዓይኖቿ አፀፋ
መስጠት ሳልፈልግም
ለንቋሳው
……………………….. ተንጋለልሁ
ለዚ’ች ሞቃት ግርግም
:
ደረቷ ላይ ፍግም !
@getem
@getem
@paappii
(ሚካኤል አስጨናቂ)
እርግት ያለች ወተት
ስክን ያለች ቡና …
ይሄን ችኩል ዘመን
አልዋጀችምና …
ተንገበገብኩላት
ተሳተብኝ አቅሌ
ሆንኩላት ባተሌ ።
ጥልል እንደ ጠላ
ኩልል እንደ ጠበል
ከአንገቷ ስር ገነት
ገድ ጥሎኝ ብጠለል
አ..ን..ሰ…ፈ…ሰ…ፈ…ች….ኝ
አ…ር..ገ…ፈ...ገ…ፈ…ች…ኝ
ቃላት ሳ’ተነፍስ
ጥርሶቿን ሳትገልጥ
ቅቤ ሆነ ልቤ..
ገጽዋ ላይ ሲቀልጥ ፤
ያን ጊዜ ተቃናች !
ብታጣብኝ ኩራት
ስስ ጎኔ ቢገርማት
(ዓይኖቿ ፍም እሳት)
አንገቴን ሰበርኩኝ
ፈርቼው ይሄን ፍም
ቢሆንም …
ቢሆንም …
ለዓይኖቿ አፀፋ
መስጠት ሳልፈልግም
ለንቋሳው
……………………….. ተንጋለልሁ
ለዚ’ች ሞቃት ግርግም
:
ደረቷ ላይ ፍግም !
@getem
@getem
@paappii
👍46❤8🤩2
መኖር መኖር መኖር!
(በእውቀቱ ስዩም)
በማይ በምሰማው
አንዳንዴ ስገረም
ህይወት ከናላማው
ስህተት ይሆን እንዴ፤ በሞት የሚታረም?
ማለት ይቃጣኛል
የዚህ ዓለም ኑሮ
ጥያቄ ወርውሮ
ምላሽ ያሳጣኛል፡፡
ደሞ አንዳንዴ ሳስብ
ስለሰው ልጅ ስራ
የሰናፍጭ ቅንጣት በምታክል ጥበብ
የሚንድ ተራራ
በጨለመ ምድር፤ ብርሃን እሚዘራ
በሰማይ ጎዳና፤ ወፍ የሚያሰማራ
ባህርን የሚያጠምድ ፤መብረቅ የሚገራ፤
ከቀለሞች መሀል ፤ ምስል የሚያነቃ
ከዝምታ መሀል፤ የሚያፈልቅ ሙዚቃ
በቃሉ በጣቱ
በቅመም ቅንጣቱ
ዘልቆ የሚያክመኝ
እንደ ሳንዱቅ ከፍቶ፤ መልሶ እሚገጥመኝ
ይህንን ሁሉ ሳይ፤ ህይወት እየጣመኝ
መኖር መኖር መኖር፤ መኖር ነው የምመኝ ፤
@getem
@getem
(በእውቀቱ ስዩም)
በማይ በምሰማው
አንዳንዴ ስገረም
ህይወት ከናላማው
ስህተት ይሆን እንዴ፤ በሞት የሚታረም?
ማለት ይቃጣኛል
የዚህ ዓለም ኑሮ
ጥያቄ ወርውሮ
ምላሽ ያሳጣኛል፡፡
ደሞ አንዳንዴ ሳስብ
ስለሰው ልጅ ስራ
የሰናፍጭ ቅንጣት በምታክል ጥበብ
የሚንድ ተራራ
በጨለመ ምድር፤ ብርሃን እሚዘራ
በሰማይ ጎዳና፤ ወፍ የሚያሰማራ
ባህርን የሚያጠምድ ፤መብረቅ የሚገራ፤
ከቀለሞች መሀል ፤ ምስል የሚያነቃ
ከዝምታ መሀል፤ የሚያፈልቅ ሙዚቃ
በቃሉ በጣቱ
በቅመም ቅንጣቱ
ዘልቆ የሚያክመኝ
እንደ ሳንዱቅ ከፍቶ፤ መልሶ እሚገጥመኝ
ይህንን ሁሉ ሳይ፤ ህይወት እየጣመኝ
መኖር መኖር መኖር፤ መኖር ነው የምመኝ ፤
@getem
@getem
❤49👍30🔥10😱2
አንተ እንባዬ ምረጥ
ልግለጥህ?
ልዋጥህ?
ላፍንህ?
ልልቀቅህ?
ላፍስስህ
ላምቅህ?
ምን ላርግህ? ምከረኝ
ምንድነህ? ንገረኝ
እህል ትሆን ጠፊ?
ወይስ ሽል ነህ ገፊ?
በጊዜ ልወቅህ...
ላቅርብ ወይ ላርቅህ...
አጫጅ ነህ አራሚ?
ተጓዥ ነህ ከራሚ?
አላፊ ነህ ቋሚ?
ምንድነህ?
ምን ላርግህ?
ላግድህ?
ላውርድህ?
ጋርጄ ልካድምህ?
አውርጄ ልካድህ?
ቢያፍኑህ ቀሪ ነህ?
ቢለቁህ ኗሪ ነህ?
እንባዬ ምን ላድርግህ?
ላስርግህ?
ልጥረግህ?
እንዳ'ይን እንዳ'ፍንጫ
ቋሚ መገለጫ
መታወቂያ መልኬ ፡ ሆነህ ትኖራለህ?
ወይስ ላ'ንዴ ወርደህ፡ በዚያው ትቀራለህ?
አንተ እንባዬ ምረጥ
ላብስህ?
ላልብስህ?
ወይስ እንዳላየ፡
ከኔ የወጣ ሁሉ፡
የኔ አይደለም ብዬ
ልተውህ እንባዬ?
ወይስ ልገላገል?
እውነቱን ልናገር?
እንዲህ ነህ እንዲያ ነህ
እያልኩኝ ከማበል
አላውቅህም ልበል?
By #red-8
@getem
@getem
@paappii
ልግለጥህ?
ልዋጥህ?
ላፍንህ?
ልልቀቅህ?
ላፍስስህ
ላምቅህ?
ምን ላርግህ? ምከረኝ
ምንድነህ? ንገረኝ
እህል ትሆን ጠፊ?
ወይስ ሽል ነህ ገፊ?
በጊዜ ልወቅህ...
ላቅርብ ወይ ላርቅህ...
አጫጅ ነህ አራሚ?
ተጓዥ ነህ ከራሚ?
አላፊ ነህ ቋሚ?
ምንድነህ?
ምን ላርግህ?
ላግድህ?
ላውርድህ?
ጋርጄ ልካድምህ?
አውርጄ ልካድህ?
ቢያፍኑህ ቀሪ ነህ?
ቢለቁህ ኗሪ ነህ?
እንባዬ ምን ላድርግህ?
ላስርግህ?
ልጥረግህ?
እንዳ'ይን እንዳ'ፍንጫ
ቋሚ መገለጫ
መታወቂያ መልኬ ፡ ሆነህ ትኖራለህ?
ወይስ ላ'ንዴ ወርደህ፡ በዚያው ትቀራለህ?
አንተ እንባዬ ምረጥ
ላብስህ?
ላልብስህ?
ወይስ እንዳላየ፡
ከኔ የወጣ ሁሉ፡
የኔ አይደለም ብዬ
ልተውህ እንባዬ?
ወይስ ልገላገል?
እውነቱን ልናገር?
እንዲህ ነህ እንዲያ ነህ
እያልኩኝ ከማበል
አላውቅህም ልበል?
By #red-8
@getem
@getem
@paappii
❤50👍38🔥8
አንቺን ያየ ምድር አንቺን ያየ ሰማይ
ስንት ዐመት ቀጠለ በስፍር ዕድሜው ላይ?
።።።።።።።።
በጠለቅሽበት ጥግ
መውጣት ስላቅ ሆነ ፀሐይ ቀረች አፍራ
እኔም ደስታ እንዳለው
ማልቀስ ይከብደኛል በሳቅሽበት ስፍራ።
የት ቆሜ እንባ ላፍስስ የት ልበል እዬዬ
በሳቅሽ የፈካ
አይታዘበኝም ዛፍ ቅጠሉ እያዬ?
ምድር እንዳይንቀኝ
በወንዙ በሀይቁ ቀልዬ እንዳልገኝ
በነፋሱ ትዝብት እንዳላንስ ወድቄ
ለፍጥረት እይታ በሳቅ አሸብርቄ
እስቃለሁ ለጉድ እንከተከታለሁ
እንጂማ
ሳቅሽ ዳር ብፈለግ የእውነት የታለሁ?
እና የኔ ኪዳን
መቼ ልትወጪ አሰብሽ?
እንዳያፍር ምድር እንዳያፍር ሰማይ
እግዜሩም አልሠራም ጠልቆ ሚቀር ፀሐይ!
አባባይ ሆንኩልሽ የእሹሩሩ ካድሬ
ጨለማውን በሳቅ ሳባብል አድሬ
እንቅልፍ ቢወስደው ከዛለ መዳፌ
እንባ እየናፈቁ መሳቅ ሆነ ትርፌ።
እንደሰው ሲደክመው ሌቱ ሲያንቀላፋ
አማጥኩኝ ለለቅሶ እህህህ አልኩኝ ለሳጌ
ሁሌ ምገኘው ግን ከፈገግታሽ ግርጌ።
የሳቅሽን ዘቢብ
ምን መልአክ ቀመሰው ምን አማልክት አየው
የፈገግታ ጭረት ፊቴ ማይለየው?
አንቺ…
ሕይወት ክንብል አለ ቆመ ተዘቅዝቆ
ዘላለም ይሠ
By yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
ስንት ዐመት ቀጠለ በስፍር ዕድሜው ላይ?
።።።።።።።።
በጠለቅሽበት ጥግ
መውጣት ስላቅ ሆነ ፀሐይ ቀረች አፍራ
እኔም ደስታ እንዳለው
ማልቀስ ይከብደኛል በሳቅሽበት ስፍራ።
የት ቆሜ እንባ ላፍስስ የት ልበል እዬዬ
በሳቅሽ የፈካ
አይታዘበኝም ዛፍ ቅጠሉ እያዬ?
ምድር እንዳይንቀኝ
በወንዙ በሀይቁ ቀልዬ እንዳልገኝ
በነፋሱ ትዝብት እንዳላንስ ወድቄ
ለፍጥረት እይታ በሳቅ አሸብርቄ
እስቃለሁ ለጉድ እንከተከታለሁ
እንጂማ
ሳቅሽ ዳር ብፈለግ የእውነት የታለሁ?
እና የኔ ኪዳን
መቼ ልትወጪ አሰብሽ?
እንዳያፍር ምድር እንዳያፍር ሰማይ
እግዜሩም አልሠራም ጠልቆ ሚቀር ፀሐይ!
አባባይ ሆንኩልሽ የእሹሩሩ ካድሬ
ጨለማውን በሳቅ ሳባብል አድሬ
እንቅልፍ ቢወስደው ከዛለ መዳፌ
እንባ እየናፈቁ መሳቅ ሆነ ትርፌ።
እንደሰው ሲደክመው ሌቱ ሲያንቀላፋ
አማጥኩኝ ለለቅሶ እህህህ አልኩኝ ለሳጌ
ሁሌ ምገኘው ግን ከፈገግታሽ ግርጌ።
የሳቅሽን ዘቢብ
ምን መልአክ ቀመሰው ምን አማልክት አየው
የፈገግታ ጭረት ፊቴ ማይለየው?
አንቺ…
ሕይወት ክንብል አለ ቆመ ተዘቅዝቆ
ዘላለም ይሠ
ራል አንድ ቀን ተስቆ?
ዙሪያዬን ሳቅ ከቦኝ እምን ላይ ልደገፍ
እንባዬ ያምረዋል እዚም እዛም መርገፍ።
ያሰኘኛል ዋይታ
ዕድሜዬን ማዋዛት በሀዘን ማለዘብ
ግን ትልቅ ሀጢአት ነው
ከቁርባን ፊት ቀርቦ ቁርባኑን መታዘብ።
ሜሮን ነበር ሳቅሽ ሀዳስ የሳቅ ጠበል
ፅድቅ ነበር ለሰው
ያንድ ቀን ደስታሽ ስር ዳስ ሠርቶ መጠለል።
መቼ ልትወጪ አሰብሽ?
መቼ ልትመጪ አሰብሽ?
በፍጥረት ልብ ላይ ጎጆውን ቀልሶ
ሳቅሽ አንጀት በላ እንዳራራይ ለቅሶ።
አበባው ይስቃል
ቅጠሉ ይስቃል
እሾሁ ይስቃል ድንጋዩ ይስቃል
አፈሩ፣ እሳቱ ነፋሱ ይስቃል
አንዴም ሳያነባ ሰው እንዴት ይፀድቃል?
ሳቅሽ ወንጌል ሆነ ምጻት መፋረጃ
ውስጤ እንባ ደርድሬ
ለብይን ብጠራ አቋቋሜን እንጃ!
አቤት አቤት አቤት
ከአምላክ ከፍጡር ከማነው ወገኑ
ሺህ ኩነኔ መሃል ሳቅሽ መጀገኑ!
አንቺ የሳቅ ኪዳን
ሩቅ ነሽ ለህመም ቅርብ ነሽ ለመዳን
እኔ ግን ተመኘሁ
በፈገግታሽ በኩል እንባዬን ልነካ
አንቺ…
ማልቀስ በመፈለግ ሳቅ ይረክሳል ለካ።
አንድ ቀን ስቃልኝ
ስፍር ዕድሜዬ ላይ ዕድሜ መርቃልኝ
የሰማይ የምድሩን መሳቅ አስለምዳው
ልክ እንዳመጣጧ ብትጠልቅ ወዲያው
ሕይወት ድፍት አለ ቆመ ተዘቅዝቆ
ዘላለም ይሠራል አንድ ቀን ተስቆ?By yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
👍43❤30🤩4🔥3
ድንኳን አይጥሉለት፣
ጥየቃ አያውቀው፣
ሰአቱን መጠበቅ ቀን ማወቅ አይለቀው፤
ሁሌ አብሮ አይኖር፣
ሁሌ መጪ እንግዳ፣
ሁሌ ምቾት ነሺ የሰባት ቀን እዳ፤
ሁሌ ተባበይ ባይ፣
በመጣ በታየ፣
ሁሌ የመድሎ ልጅ በጾታ የለየ፤
ሁሌ ፊት አደብዛዥ፣
የዙር አመል ከላሽ፣
ሁሌ ተጠባቂ ሁሌ መቶ ረባሽ፤
የልምላሜ መልክ፣
ከመባረክ ጓዳ፣
የሔዋን እጣ ነው ክቡር የሤት እዳ።
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@paappii
ጥየቃ አያውቀው፣
ሰአቱን መጠበቅ ቀን ማወቅ አይለቀው፤
ሁሌ አብሮ አይኖር፣
ሁሌ መጪ እንግዳ፣
ሁሌ ምቾት ነሺ የሰባት ቀን እዳ፤
ሁሌ ተባበይ ባይ፣
በመጣ በታየ፣
ሁሌ የመድሎ ልጅ በጾታ የለየ፤
ሁሌ ፊት አደብዛዥ፣
የዙር አመል ከላሽ፣
ሁሌ ተጠባቂ ሁሌ መቶ ረባሽ፤
የልምላሜ መልክ፣
ከመባረክ ጓዳ፣
የሔዋን እጣ ነው ክቡር የሤት እዳ።
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@paappii
❤32👍16🤩5🔥3